#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ያዕቆብ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን?
² ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤
³ ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም።
⁴ አመንዝሮች ሆይ፥ ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።
⁵ ወይስ መጽሐፍ፦ በእኛ ዘንድ ያሳደረው መንፈስ በቅንዓት ይመኛል ያለው በከንቱ እንደ ተናገረ ይመስላችኋልን?
⁶ ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል።
⁷ እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤
⁸ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።
⁹ ተጨነቁና እዘኑ አልቅሱም፤ ሳቃችሁ ወደ ኀዘን ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ።
¹⁰ በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ ከፍ ከፍም ያደርጋችኋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ያዕቆብ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉ? በብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህ ከምቾቶቻችሁ አይደሉምን?
² ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱም ትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተ አይሆንም፤
³ ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም።
⁴ አመንዝሮች ሆይ፥ ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።
⁵ ወይስ መጽሐፍ፦ በእኛ ዘንድ ያሳደረው መንፈስ በቅንዓት ይመኛል ያለው በከንቱ እንደ ተናገረ ይመስላችኋልን?
⁶ ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል።
⁷ እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤
⁸ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ።
⁹ ተጨነቁና እዘኑ አልቅሱም፤ ሳቃችሁ ወደ ኀዘን ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ።
¹⁰ በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ ከፍ ከፍም ያደርጋችኋል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍2
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ከፍርሃት ነፃ ወጥተናል- መለየት የለም (8:31-39)
ኩነኔ የማይኖርብን ከእግዚአብሔር ጽድቅ ስለምንካፈል እና ሕግ ሊኮንነን ስለማይችል ነው፡፡ ሥጋን አሸንፈን ለእግዚአብሔር እንድንኖር የእግዚአብሔር መንፈስ ስላለን ዕዳ የለብንም፡፡ ተስፋ መቁረጥም የለም፡፡ ምክንያቱም የተባረከ ተስፋችን በሆነው በክርስቶስ መመለስ የእግዚአብሔርን ክብር እንካፈላለንና፡፡ የእግዚአብሔርን ፍቅር ስለምንለማመድ መለየት የለም:- «ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል?» (ሮሜ 8:35)።
የዚህ ምእራፍ የመጨረሻ ክፍል አጽንኦት የአማኞችን ዋስትና በተመለከተ ነው:: በክርስቶስ ፍቅር ስለተጠበቅን ትናንትን፣ ዛሬንና ነገን ልንፈራ አይገባንም፡፡ በአማኝና በጌታ መካከል መለያየት አለመኖሩን ለማስረዳት ጳውሎስ አምስት ሙግቶችን አቅርቧል::
ሀ) እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው (8:31)
እግዚአብሔር አብ ከእኛ ጋር መሆኑን ለመግልጽ ልጁን ልኳል (8:32):: ወልድም ከእኛ ጋር ነው (8:34)፣ መንፈስ ቅዱስም ከእኛው ጋር ነው (8:26)፡፡ እግዚአብሔር ሁሉ ነገር ለበጎ እንደሚሆንልን አድርጓል (8:28)። በማንነቱና በአቅርቦቱ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንደ ያዕቆብ እናለቅሳለን፣ «ልጅ አልባ አስቀራችሁኝ» (ዘፍጥ. 42:36)፣ ነገር ግን ሁሉ ነገር ለበጎ ይሆንልናል:: መቋጫው ግልጽ ነው:- «እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ፣ ማን ይቃወመናል?»
አማኝ በእያንዳንዱ ቀን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንደሆነ በመረዳት መኖር አለበት፡፡ ከእርሱ መልካም ነገርን ለመቀበል የግድ በፈተና ቢያልፉም አፍቃሪ አባታቸው የሚበጀውን ስለሚመኝላቸው፣ መፍራት አያስፈልጋቸውም፡፡ «ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም» (ኤር. 29:11)::
ለ) ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአል (8:32)
እዚህ ላይ ሙግቱ ከአነስተኛ ወደ ታላቅ ነው:: ኃጢአተኞች ሳለን እግዚአብሔር ምርጡን ከሰጠን፣ አሁንማ ልጆቹ ስንሆን የሚያስፈልገንን ሁሉ አይሰጠንምን? ኢየሱስም መሥጋትና መፍራት ሞኝነት መሆኑን ለሕዝቡ ለማስረዳት ሲሞክር ይህን ሙግት ተጠቅሟል፡፡ እግዚአብሔር ለወፎችና ለበጎች እንዲሁም ለሜዳ አበባ ግድ ይለዋል:: ለእኛማ በእርግጥ የበለጠ ያስብልናል፡፡ እግዚአብሔር የእርሱ ከሆኑት ጋር ያለው ተዛምዶ ሕግን የተመረኮዘ ሳይሆን፣ በቀራንዮ ጸጋው ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ እግዚአብሔር የራሱ ለሆኑት ሁሉ ሁሉን በነፃ ይሰጣል፡፡
ሐ) እግዚአብሔር አጽድቆናል (8:33)
ይህም በክርስቶስ ውስጥ ጻድቅ አድርጎ ቆጥሮናል ማለት ነው፡፡ ሰይጣን ሊከሰን ይወድዳል (ራእይ 12:10፤ ዘካ. 3፡1-7)፣ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ጻድቅ ሆነን እንቆማለን፡፡ እኛ በክርስቶስ የተመረጥን፣ በክርስቶስ ተቀባይነትን ያገኘን የእግዚአብሔር ምርጦች ነን፡፡ እርሱ ራሱ ስላጸደቀን እግዚአብሔር እኛን አይከስሰንም፡፡ እርሱ የሚከስሰን ከሆነ የሰጠን ደኅንነት ዋጋ ቢስ ነው፡፡ እኛ አሁንም በኃጢአታችን አለን ማለት ነው፡፡
የጽድቅን ትርጉም መረዳት ለልባችን ሰላምን ያመጣል:: እግዚአብሔር አንድን ያመነ ኃጢአተኛ ጻድቅ ብሎ ሲጠራው ዐዋጁ መቼም ቢሆን አይለወጥም፡፡ የክርስትና ልምምዳችን ከቀን ወደ ቀን ሊቀያየር ይችላል፣ ጽድቃችን ግን አይለወጥም:: እኛ ራሳችንን እንከስ ይሆናል፣ ሰዎችም ሊከስሱን ይችላሉ፤ እግዚአብሔር ግን ወደ ፍርድ ወንበር ወስዶ ፈጽሞ አይከሰንም፡፡ ኢየሱስ የኃጢአትን ዋጋ ስለ ከፈለ፣ እኛ ተጠብቀናል::
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 88-90
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከፍርሃት ነፃ ወጥተናል- መለየት የለም (8:31-39)
ኩነኔ የማይኖርብን ከእግዚአብሔር ጽድቅ ስለምንካፈል እና ሕግ ሊኮንነን ስለማይችል ነው፡፡ ሥጋን አሸንፈን ለእግዚአብሔር እንድንኖር የእግዚአብሔር መንፈስ ስላለን ዕዳ የለብንም፡፡ ተስፋ መቁረጥም የለም፡፡ ምክንያቱም የተባረከ ተስፋችን በሆነው በክርስቶስ መመለስ የእግዚአብሔርን ክብር እንካፈላለንና፡፡ የእግዚአብሔርን ፍቅር ስለምንለማመድ መለየት የለም:- «ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል?» (ሮሜ 8:35)።
የዚህ ምእራፍ የመጨረሻ ክፍል አጽንኦት የአማኞችን ዋስትና በተመለከተ ነው:: በክርስቶስ ፍቅር ስለተጠበቅን ትናንትን፣ ዛሬንና ነገን ልንፈራ አይገባንም፡፡ በአማኝና በጌታ መካከል መለያየት አለመኖሩን ለማስረዳት ጳውሎስ አምስት ሙግቶችን አቅርቧል::
ሀ) እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው (8:31)
እግዚአብሔር አብ ከእኛ ጋር መሆኑን ለመግልጽ ልጁን ልኳል (8:32):: ወልድም ከእኛ ጋር ነው (8:34)፣ መንፈስ ቅዱስም ከእኛው ጋር ነው (8:26)፡፡ እግዚአብሔር ሁሉ ነገር ለበጎ እንደሚሆንልን አድርጓል (8:28)። በማንነቱና በአቅርቦቱ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንደ ያዕቆብ እናለቅሳለን፣ «ልጅ አልባ አስቀራችሁኝ» (ዘፍጥ. 42:36)፣ ነገር ግን ሁሉ ነገር ለበጎ ይሆንልናል:: መቋጫው ግልጽ ነው:- «እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ፣ ማን ይቃወመናል?»
አማኝ በእያንዳንዱ ቀን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንደሆነ በመረዳት መኖር አለበት፡፡ ከእርሱ መልካም ነገርን ለመቀበል የግድ በፈተና ቢያልፉም አፍቃሪ አባታቸው የሚበጀውን ስለሚመኝላቸው፣ መፍራት አያስፈልጋቸውም፡፡ «ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም» (ኤር. 29:11)::
ለ) ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአል (8:32)
እዚህ ላይ ሙግቱ ከአነስተኛ ወደ ታላቅ ነው:: ኃጢአተኞች ሳለን እግዚአብሔር ምርጡን ከሰጠን፣ አሁንማ ልጆቹ ስንሆን የሚያስፈልገንን ሁሉ አይሰጠንምን? ኢየሱስም መሥጋትና መፍራት ሞኝነት መሆኑን ለሕዝቡ ለማስረዳት ሲሞክር ይህን ሙግት ተጠቅሟል፡፡ እግዚአብሔር ለወፎችና ለበጎች እንዲሁም ለሜዳ አበባ ግድ ይለዋል:: ለእኛማ በእርግጥ የበለጠ ያስብልናል፡፡ እግዚአብሔር የእርሱ ከሆኑት ጋር ያለው ተዛምዶ ሕግን የተመረኮዘ ሳይሆን፣ በቀራንዮ ጸጋው ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ እግዚአብሔር የራሱ ለሆኑት ሁሉ ሁሉን በነፃ ይሰጣል፡፡
ሐ) እግዚአብሔር አጽድቆናል (8:33)
ይህም በክርስቶስ ውስጥ ጻድቅ አድርጎ ቆጥሮናል ማለት ነው፡፡ ሰይጣን ሊከሰን ይወድዳል (ራእይ 12:10፤ ዘካ. 3፡1-7)፣ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ጻድቅ ሆነን እንቆማለን፡፡ እኛ በክርስቶስ የተመረጥን፣ በክርስቶስ ተቀባይነትን ያገኘን የእግዚአብሔር ምርጦች ነን፡፡ እርሱ ራሱ ስላጸደቀን እግዚአብሔር እኛን አይከስሰንም፡፡ እርሱ የሚከስሰን ከሆነ የሰጠን ደኅንነት ዋጋ ቢስ ነው፡፡ እኛ አሁንም በኃጢአታችን አለን ማለት ነው፡፡
የጽድቅን ትርጉም መረዳት ለልባችን ሰላምን ያመጣል:: እግዚአብሔር አንድን ያመነ ኃጢአተኛ ጻድቅ ብሎ ሲጠራው ዐዋጁ መቼም ቢሆን አይለወጥም፡፡ የክርስትና ልምምዳችን ከቀን ወደ ቀን ሊቀያየር ይችላል፣ ጽድቃችን ግን አይለወጥም:: እኛ ራሳችንን እንከስ ይሆናል፣ ሰዎችም ሊከስሱን ይችላሉ፤ እግዚአብሔር ግን ወደ ፍርድ ወንበር ወስዶ ፈጽሞ አይከሰንም፡፡ ኢየሱስ የኃጢአትን ዋጋ ስለ ከፈለ፣ እኛ ተጠብቀናል::
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 88-90
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ቃዴስ
ቃዴስ፤ ቅዱስ ማለት ነው። ከከነዓን በስተደቡብ ያለ ምድረ በዳ ስፍራ፤ መዝ. 29፥8። ቃዴስ በርኔ ተብሎም ይጠራል፤ ዘኍ. 32፥8 :: እስራኤላውያን ከግብጽ አገር ወደ ከነዓን ሲጓዙ በቃዴስ ሰፈሩ። ዐሥራ ሁለቱ ሰላዮች ከከነዓን ከተመለሱ በኋላ፥ ሕዝቡ እግዚአብሔር ወደ አገራቸው ሊያደርሳቸው እንደሚችል የተነገራቸውን ስለተጠራጠሩ እስከ ሠላሳ ሰባት ዓመት ድረስ በቃዴስ እንዲቀመጡ ተፈረደባቸው፤ ዘዳ. 1፥46። የሙሴ እኅት ማርያም በቃዴስ ሞተች። ሙሴም በዚህ ቦታ ድንጋዩን በመምታት እግዚአብሔርን አሳዘነው፤ ዘኍ. 20፥1-13።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 93
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ቃዴስ
ቃዴስ፤ ቅዱስ ማለት ነው። ከከነዓን በስተደቡብ ያለ ምድረ በዳ ስፍራ፤ መዝ. 29፥8። ቃዴስ በርኔ ተብሎም ይጠራል፤ ዘኍ. 32፥8 :: እስራኤላውያን ከግብጽ አገር ወደ ከነዓን ሲጓዙ በቃዴስ ሰፈሩ። ዐሥራ ሁለቱ ሰላዮች ከከነዓን ከተመለሱ በኋላ፥ ሕዝቡ እግዚአብሔር ወደ አገራቸው ሊያደርሳቸው እንደሚችል የተነገራቸውን ስለተጠራጠሩ እስከ ሠላሳ ሰባት ዓመት ድረስ በቃዴስ እንዲቀመጡ ተፈረደባቸው፤ ዘዳ. 1፥46። የሙሴ እኅት ማርያም በቃዴስ ሞተች። ሙሴም በዚህ ቦታ ድንጋዩን በመምታት እግዚአብሔርን አሳዘነው፤ ዘኍ. 20፥1-13።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 93
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤”
2ኛ ቆሮ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤”
2ኛ ቆሮ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
Zondervan Illustrated Bible Dictionary ( PDFDrive.com ).pdf
45.8 MB
📔Title፦ Zondervan Illustrated Bible Dictionary
👤Author፦ J.D Douglas and Merrill C.Tenney
🖋Revised By:- Moises Silva
📃Page፦ 3,263
💾Size፦45.8MB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👤Author፦ J.D Douglas and Merrill C.Tenney
🖋Revised By:- Moises Silva
📃Page፦ 3,263
💾Size፦45.8MB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ራሱ ሊያደርግ ያለውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ይህን ተናገረ።”
ዮሐንስ 6፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ራሱ ሊያደርግ ያለውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ይህን ተናገረ።”
ዮሐንስ 6፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
#እራሳችንን_እንመርምር
ብዙ ጊዜ ወደፊት ምን ይሆን ይሆን? እሺ፣ እንደዚያ ባይሆንስ እያልን ነገሮችን በስሌት እያወጣን እና እያወረድን የምንከርም ስንቶቻችን ነን? ወደፊት ስለሚሆነው ነገር ሁሉ ማወቅ ለእኛ ተሰጥቶናል? ታዲያ እኛ ምን እናድርግ?
“ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው፤ የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው።”
ዘዳግም 29፥29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ብዙ ጊዜ ወደፊት ምን ይሆን ይሆን? እሺ፣ እንደዚያ ባይሆንስ እያልን ነገሮችን በስሌት እያወጣን እና እያወረድን የምንከርም ስንቶቻችን ነን? ወደፊት ስለሚሆነው ነገር ሁሉ ማወቅ ለእኛ ተሰጥቶናል? ታዲያ እኛ ምን እናድርግ?
“ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው፤ የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው።”
ዘዳግም 29፥29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርስ ከወደደን ወተትና ማር ወደምታፈስሰው ወደዚች ምድር ያገባናል እርስዋንም ይሰጠናል።”
ዘኍልቁ 14፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርስ ከወደደን ወተትና ማር ወደምታፈስሰው ወደዚች ምድር ያገባናል እርስዋንም ይሰጠናል።”
ዘኍልቁ 14፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍1
#መጻሕፍትን_እንመርምር
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ ስለጌታችን እና ስለመድኃኒታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚናገር የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ይናገራሉ። ስለሆነም በብሉይ ኪዳን ያለውን በዝርዝር ከመመልከታችን በፊት እስቲ አንዳንድ ስለኢየሱስ የተነገሩትን ትንቢቶች እንመልከት።
1. መሲሕ የሚወለደው ከሴት ነው።
(ዘፍጥረት 3:15፤ ማቴዎስ 1:20፤ ገላትያ 4-4)
2. መሲሕ የሚወለደው በቤተልሔም ነው። (ሚክያስ 5: 2፤ ማቴዎስ 2: 1፤ ሉቃስ 2: 4-6)
3. መሲሕ ከድንግል ይወለዳል።
(ኢሳይያስ 7:14ማቴዎስ 1: 22-23፤ ሉቃስ 1: 26-31)
4. መሲሕ የሚመጣው ከአብርሃም ዘር ነው።
ዘፍጥረት 12፥3፤ ዘፍጥረት 22:18፤ ማቴዎስ 1፥1፤ ሮሜ 9፥5
5. መሲሕ ከይስሐቅ ዘር ይሆናል።
ዘፍጥረት 17፥19፤ ዘፍጥረት 21፥12፤ ሉቃስ 3፥34
6. መሲሕ የያዕቆብ ዘር ይሆናል።
(ዘኍልቍ 24፥17፤ ማቴዎስ 1፥ 2)
7. መሲሑ የመጣው ከይሁዳ ነገድ ነው።
(ዘፍጥረት 49፥10፤ ሉቃስ 3፥33፤ ዕብራውያን 7፥14
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ https://am.eferrit.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ ስለጌታችን እና ስለመድኃኒታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚናገር የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ይናገራሉ። ስለሆነም በብሉይ ኪዳን ያለውን በዝርዝር ከመመልከታችን በፊት እስቲ አንዳንድ ስለኢየሱስ የተነገሩትን ትንቢቶች እንመልከት።
1. መሲሕ የሚወለደው ከሴት ነው።
(ዘፍጥረት 3:15፤ ማቴዎስ 1:20፤ ገላትያ 4-4)
2. መሲሕ የሚወለደው በቤተልሔም ነው። (ሚክያስ 5: 2፤ ማቴዎስ 2: 1፤ ሉቃስ 2: 4-6)
3. መሲሕ ከድንግል ይወለዳል።
(ኢሳይያስ 7:14ማቴዎስ 1: 22-23፤ ሉቃስ 1: 26-31)
4. መሲሕ የሚመጣው ከአብርሃም ዘር ነው።
ዘፍጥረት 12፥3፤ ዘፍጥረት 22:18፤ ማቴዎስ 1፥1፤ ሮሜ 9፥5
5. መሲሕ ከይስሐቅ ዘር ይሆናል።
ዘፍጥረት 17፥19፤ ዘፍጥረት 21፥12፤ ሉቃስ 3፥34
6. መሲሕ የያዕቆብ ዘር ይሆናል።
(ዘኍልቍ 24፥17፤ ማቴዎስ 1፥ 2)
7. መሲሑ የመጣው ከይሁዳ ነገድ ነው።
(ዘፍጥረት 49፥10፤ ሉቃስ 3፥33፤ ዕብራውያን 7፥14
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ https://am.eferrit.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2
እንደ ግሪጎሪያን ካላንደር መሠረት የጌታችንን እና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ለምታከብሩ፣ እንኳን አደረሳችሁ! ዛሬ ማታ የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ይዘን እንጠብቃችኋለን። መልካም በዓል!
“እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።”
ማቴዎስ 1፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
“እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።”
ማቴዎስ 1፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ።”
ሐዋርያት 13፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ።”
ሐዋርያት 13፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1
የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትክክለኛው የልደት በዓል ቀን የቱ ነው?
Anonymous Quiz
8%
ሀ. ዲሴንበር 25 (ዛሬ ፈረንጆች እያከበሩ ያሉት)
26%
ለ. ጃንዋሪ 7 (ታህሳስ 28/29)
6%
ሐ. ጃንዋሪ 6
60%
መ. ቀኑ በትክክል አይታወቅም
👍2
🪔የንጉሡ የኢየሱስ ልደት (ማቴ. 1፡18-2፡23)
የክርስቶስን ልደት የሚገልጹ ወንጌላት ሁለት ብቻ ናቸው። ከእነዚህ ሁለቱ መካከል፥ ሉቃስ ስለ ክርስቶስ ልደት ሰፊ ምርምር ኣካሂዷል። ሉቃስ የክርስቶስን ልደት ከማርያም እይታ አንጻር ሲመለከት፥ ማቴዎስ ግን ከዮሴፍ እይታ አንጻር ይመለከታል።
የክርስቶስ ልደት የሆነው ዮሴፍና ማርያም ተጫጭተው ባሉበት ወቅት ነበር። እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ፥ የአይሁድ መተጫጨት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች ስለ ነበሩ፥ መቋረጥ የሚችሉት በፍች ነበር። በሚተጫጩበት ወቅት ማርያም «በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች» (ማቴ. 1፡18)።
ማርያም ስለሆነው ነገር ለዮሴፍ ገልጻለት ይሆናል። ስለዚህ የተጠቀሰ ነገር የለም። ነገር ግን ዮሴፍ በሆነ መንገድ ደርሶበታል። ነገር ግን ዮሴፍ የዋህ ሰው ስለ ነበር፥ ከሌላ ወንድ ለማርገዟ በይፋ ሊወቅሳት አልፈለገም። ስለሆነም ለእርሷ ሳይነግራት በስውር ሊተዋት አሰበ። እግዚአብሔር ግን ማርያም በትክክል ከመንፈስ ቅዱስ እንደፀነሰች ለዮሴፍ ለመንገር መልአኩን ላከ። ማርያም ከሌላ ሰው ጋር አላመነዘረችም ነበር። ምንም እንኳ ማርያም በማርግዟ ቢቀልዱባትም፥ ዮሴፍ እግዚአብሔርን ታዝዞ ማርያምን ወሰዳት።
እግዚአብሔር በዚህ መሢሑን ወደ ዓለም በመላኩ ሂደት ማርያምን ብቻ ሳይሆን ዮሴፍንም አክብሯል። እንደ ባልና የቤት ራስ ሁሉ፥ እግዚአብሔር ዮሴፍ ለልጁ ስም እንዲያወጣ መብት ሰጠው። ለክርስቶስ ስም በማውጣቱ፥ ዮሴፍ ሕጋዊ ኣባትነቱን እያረጋገጠ ነበር።
እግዚአብሔር ዮሴፍ ልጁን «ኢያሱ» (ዕብራዊ ስም) ወይም «ኢየሱስ» (ግሪካዊ ስም) ብሎ እንዲጠራ ነገረው። የሁለቱም ስሞች ፍች «እግዚእብሔር ደኅንነት ነው» የሚል ነው። ይህም የመሢሑ ቀዳሚ ተግባር ድል ነሺ ንጉሥ መሆን ሳይሆን፥ አዳኝ እንደሆነ የሚያመለክት ነው። ክርስቶስ «ሕዝቡን ከኃጢአታቸው የሚያድን» መንፈሳዊ አዳኝ እንጂ ፖለቲካዊ ነፃ አውጪ እንዳልሆነ ማቴዎስ ገልጾአል።
ማቴዎስ፥ የድንግሊቱ መውለድና የክርስቶስ ልደት ዝርዝር ጉዳዮች ሁሉ፥ በእግዚአብሔር በጥንቃቄ እንደታቀዱና በብሉይ ኪዳን እንደተተነበዩ አስረድቷል። ማርያም በሚያስደንቅ መንገድ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ስለ ወለደች፥ ኢየሱስ ሰውም አምላክም ሆኗል። ይህም እርሱ ብቻ «አማኑኤል» ማለትም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆኖኣል (ኢሳ. 7፡14)። በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር የክብር ደመናውን በሰዎች መካከል ያኖረ ሲሆን፥ አሁን ግን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በሰዎች መካከል አድሯል። ክርስቶስ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት፥ ለደቀ መዛሙርቱ አሁንም አማኑኤል እንደሚሆን፥ ማለትም እስከ መጨረሻው አብሯቸው እንደሚሆን ገልጾአል (ማቴ. 28፡18-20) ማቴዎስ ክርስቶስ የብሉይ ኪዳንን ትንቢት በመፈጸም በቤተልሔም እንደ ተወለደ ተናግሯል።
ለአይሁዶች እግዚአብሔር ለአሕዛብም ዕቅድ እንዳለው ማቴዎስ አመልክቷል። እንዲሁም መጀመሪያ ክርስቶስን ያከበሩትና ያመለኩት ሰብዓ ሰገል መሆናቸውን ገልጾአል። ማቴዎስ እነዚህ ሰብዓ ሰገል ከየት እንደ መጡ ወይም ስንት እንደሆኑ አልጠቀሰም። በክርስትና ትውፊት ሦስት ሰዎች እንደሆኑ የሚታመነው ካበረከቱት ስጦታ በመነሣት ነው። ለእነዚህ ሰዎች የተሰጠው የግሪክ ስያሜ «ማጂ» (magi) የሚል ነው። ማጂ የልዩ ሃይማኖታዊ ሰዎች ቡድን ሲሆን፥ ብዙ ምሑራን ከፋርስ ወይም ከሳውዲ ዓረቢያ እንደ መጡ ያምናሉ። እነዚህ ሰዎች በከዋክብት ጥናት ይካኑ እንጂ፥ ስለ እግዚአብሔርም በቂ ግንዛቤ የነበራቸው ይመስላል። ያዩት አዲስ ኮከብ ለአይሁዶች ልዩ ንጉሥ እንደ ተወለደ የሚያመለክት መሆኑን የተረዱ ይመስላል። ለመስገድ መፈለጋቸው ደግሞ ይህ ንጉሥ ከተራ ንጉሥ በላይ መሆኑን እንደ ተገነዘቡ ያሳያል። የአይሁዶች መዲና ወደሆነችው ኢየሩሳሌም እስኪደርሱ ድረስ ለብዙ ወራት ኮከቡን ተከትለው ተጓዙ። ንጉሡ በቤተ መንግሥት ይወለዳል ብለው ስለ ገመቱ፥ ወደ ንጉሥ ሄሮድስ ሄደው ኣዲስ ስለ ተወለደው ንጉሥ ጠየቁ።
ቀደም ሲል ዙፋኔን ይነጥቁብኛል በሚል ስጋት ከቤተሰቡ አባላት መካከል ብዙ ሰዎችን የፈጀው ንጉሥ ሄሮድስ፥ ይህን ሲሰማ ደነገጠ። በመጀመሪያ፥ የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎችን ሰብስቦ ጠየቃቸው። እነዚህ ሰዎች በብሉይ ኪዳን እንደተነገረው መሢሑ ከኢየሩሳሌም ሰባት ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ በምትገኘው በቤተልሔም እንደሚወለድ ያውቁ ነበር። ሄሮድስ ያለበትን ስፍራ አይተው እንዲነግሩት በማዘዝ ሰብዓ ሰገልን ወደ ቤተልሔም ላካቸው። ምንም እንኳ ሄሮድስ ሕጻኑን ንጉሥ ለማክበር እንደፈለገ ቢነግራቸውም፥ እውነተኛ ፍላጎቱ ግን ሕጻኑን መግደል ነበር። ኮከቡ እንደገና ለሰብዓ ሰገል ተገልጦ፥ ኢየሱስ ወደነበረበት ወደ ቤተልሔም መራቸው።
ማቴዎስን ከሉቃስ ትረካ ጋር በማነጻጸር እንደምንገነዘበው፥ ኢየሱስ ከተወለደ የተወሰነ ጊዜ አልፎ ነበር። በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ከተወለደበት ግርግም ወደ ቤት ተዛውሮ ነበር። ይህም የዘመድ ቤት ወይም እነዮሴፍ የተከራዩት ቤት ሳይሆን አይቀርም። ኢየሱስ ከተወለደ ምን ያህል ጊዜ እንዳለፈ አናውቅም። ሄሮድስ ከሰብዓ ሰገል ኮከቡ መጀመሪያ የታየበትን ጊዜ ተረድቶ እስከ ሁለት ዓመት የሆናቸውን ሕጻናት ሁሉ ስለ ገደለ፥ ኢየሱስ ከተወለደ ሁለት ዓመታት ሳይሞላው ኣይቀርም ተብሎ ይገመታል። ሰብዓ ሰገል ስጦታዎችን በመስጠትና እንደ አምላክ በማምለክ ክርስቶስን አክብረውታል።
እግዚአብሔርም ለሰብዓ ሰገል ያዩትን ለሄሮድስ ሳይናገሩ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ አድርጓል። በዚህ ታሪክ ማቴዎስ እግዚአብሔር የአይሁዶች ብቻ አምላክ እንዳልሆነና አሕዛብም የዕቅዱ አካል መሆናቸውን አመልክቷል። ክርስቶስ መሢሕ እንደሆነ በመጀመሪያ ከተገነዘቡት ሰዎች አንዳንዶቹ አሕዛብ ነበሩ። ዓለም ስለ እነርሱ ምንም ዐይነት አመለካከት ቢኖረውም ወንጌሉን ብዙውን ጊዜ እናውቃለን ከሚሉት የተሰወረው እውነት ልባቸውን ለከፈቱት ተገልጧል።
ከመሢሑ ታሪክ በስተጀርባ መንፈሳዊ ውጊያ አለ፡፡ ሰይጣን መሢሑን ለማጥፋት ፈልጎ ነበር። ይህንንም ያደረገው በዓለም ላይ ያለውን ኃይሉን እንደሚሽርበት ስለ ተገነዘበ ነበር። እግዚአብሔር ግን ልጁ ዕቅዶቹን ፈጽሞ፥ በመስቀል ላይ እንዲሞት ወስኖ ነበር። ስለዚህ ሰይጣን ኢየሱስን ለመግደል በሄሮድስ ልብ ውስጥ ያሴር እንደነበረ እግዚአብሔር በመገንዘብ፥ ዮሴፍ በመጀመሪያ ወደ ግብፅ ይዞት እንዲወርድ ከዚያም ወደ ናዝሬት ይዞት እንዲመለስ አዘዘው። ከዚያም ሄሮድስ ወደ ቤተልሔም ተጉዞ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ የሆናቸውን ሕጻናት ሁሉ አስገደለ። ይህም ሰብዓ ሰገል ኢየሱስን ለማየት የመጡት ቢያንስ ከኣንድ ዓመት ተኩል እስከ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ ሳይሆን አይቀርም ወደሚል ድምዳሚ ይመራናል። በክርስቶስ ልደት ዙሪያ በተከናወኑት በእነዚህ ክስተቶች ሁሉ፥ የእግዚአብሔር እጅ እንደ ነበረበት ማቴዎስ ያውቅ ነበር። የሕጻናቱ መገደል፥ የክርስቶስ ከግብፅና በኋላም ከናዝሬት መምጣት፥ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ተተንብዮአል።
ምንጭ:- ethiopiansite-com
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ አይ ኤም ከታተመውና የዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የክርስቶስን ልደት የሚገልጹ ወንጌላት ሁለት ብቻ ናቸው። ከእነዚህ ሁለቱ መካከል፥ ሉቃስ ስለ ክርስቶስ ልደት ሰፊ ምርምር ኣካሂዷል። ሉቃስ የክርስቶስን ልደት ከማርያም እይታ አንጻር ሲመለከት፥ ማቴዎስ ግን ከዮሴፍ እይታ አንጻር ይመለከታል።
የክርስቶስ ልደት የሆነው ዮሴፍና ማርያም ተጫጭተው ባሉበት ወቅት ነበር። እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ፥ የአይሁድ መተጫጨት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች ስለ ነበሩ፥ መቋረጥ የሚችሉት በፍች ነበር። በሚተጫጩበት ወቅት ማርያም «በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች» (ማቴ. 1፡18)።
ማርያም ስለሆነው ነገር ለዮሴፍ ገልጻለት ይሆናል። ስለዚህ የተጠቀሰ ነገር የለም። ነገር ግን ዮሴፍ በሆነ መንገድ ደርሶበታል። ነገር ግን ዮሴፍ የዋህ ሰው ስለ ነበር፥ ከሌላ ወንድ ለማርገዟ በይፋ ሊወቅሳት አልፈለገም። ስለሆነም ለእርሷ ሳይነግራት በስውር ሊተዋት አሰበ። እግዚአብሔር ግን ማርያም በትክክል ከመንፈስ ቅዱስ እንደፀነሰች ለዮሴፍ ለመንገር መልአኩን ላከ። ማርያም ከሌላ ሰው ጋር አላመነዘረችም ነበር። ምንም እንኳ ማርያም በማርግዟ ቢቀልዱባትም፥ ዮሴፍ እግዚአብሔርን ታዝዞ ማርያምን ወሰዳት።
እግዚአብሔር በዚህ መሢሑን ወደ ዓለም በመላኩ ሂደት ማርያምን ብቻ ሳይሆን ዮሴፍንም አክብሯል። እንደ ባልና የቤት ራስ ሁሉ፥ እግዚአብሔር ዮሴፍ ለልጁ ስም እንዲያወጣ መብት ሰጠው። ለክርስቶስ ስም በማውጣቱ፥ ዮሴፍ ሕጋዊ ኣባትነቱን እያረጋገጠ ነበር።
እግዚአብሔር ዮሴፍ ልጁን «ኢያሱ» (ዕብራዊ ስም) ወይም «ኢየሱስ» (ግሪካዊ ስም) ብሎ እንዲጠራ ነገረው። የሁለቱም ስሞች ፍች «እግዚእብሔር ደኅንነት ነው» የሚል ነው። ይህም የመሢሑ ቀዳሚ ተግባር ድል ነሺ ንጉሥ መሆን ሳይሆን፥ አዳኝ እንደሆነ የሚያመለክት ነው። ክርስቶስ «ሕዝቡን ከኃጢአታቸው የሚያድን» መንፈሳዊ አዳኝ እንጂ ፖለቲካዊ ነፃ አውጪ እንዳልሆነ ማቴዎስ ገልጾአል።
ማቴዎስ፥ የድንግሊቱ መውለድና የክርስቶስ ልደት ዝርዝር ጉዳዮች ሁሉ፥ በእግዚአብሔር በጥንቃቄ እንደታቀዱና በብሉይ ኪዳን እንደተተነበዩ አስረድቷል። ማርያም በሚያስደንቅ መንገድ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ስለ ወለደች፥ ኢየሱስ ሰውም አምላክም ሆኗል። ይህም እርሱ ብቻ «አማኑኤል» ማለትም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆኖኣል (ኢሳ. 7፡14)። በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር የክብር ደመናውን በሰዎች መካከል ያኖረ ሲሆን፥ አሁን ግን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በሰዎች መካከል አድሯል። ክርስቶስ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት፥ ለደቀ መዛሙርቱ አሁንም አማኑኤል እንደሚሆን፥ ማለትም እስከ መጨረሻው አብሯቸው እንደሚሆን ገልጾአል (ማቴ. 28፡18-20) ማቴዎስ ክርስቶስ የብሉይ ኪዳንን ትንቢት በመፈጸም በቤተልሔም እንደ ተወለደ ተናግሯል።
ለአይሁዶች እግዚአብሔር ለአሕዛብም ዕቅድ እንዳለው ማቴዎስ አመልክቷል። እንዲሁም መጀመሪያ ክርስቶስን ያከበሩትና ያመለኩት ሰብዓ ሰገል መሆናቸውን ገልጾአል። ማቴዎስ እነዚህ ሰብዓ ሰገል ከየት እንደ መጡ ወይም ስንት እንደሆኑ አልጠቀሰም። በክርስትና ትውፊት ሦስት ሰዎች እንደሆኑ የሚታመነው ካበረከቱት ስጦታ በመነሣት ነው። ለእነዚህ ሰዎች የተሰጠው የግሪክ ስያሜ «ማጂ» (magi) የሚል ነው። ማጂ የልዩ ሃይማኖታዊ ሰዎች ቡድን ሲሆን፥ ብዙ ምሑራን ከፋርስ ወይም ከሳውዲ ዓረቢያ እንደ መጡ ያምናሉ። እነዚህ ሰዎች በከዋክብት ጥናት ይካኑ እንጂ፥ ስለ እግዚአብሔርም በቂ ግንዛቤ የነበራቸው ይመስላል። ያዩት አዲስ ኮከብ ለአይሁዶች ልዩ ንጉሥ እንደ ተወለደ የሚያመለክት መሆኑን የተረዱ ይመስላል። ለመስገድ መፈለጋቸው ደግሞ ይህ ንጉሥ ከተራ ንጉሥ በላይ መሆኑን እንደ ተገነዘቡ ያሳያል። የአይሁዶች መዲና ወደሆነችው ኢየሩሳሌም እስኪደርሱ ድረስ ለብዙ ወራት ኮከቡን ተከትለው ተጓዙ። ንጉሡ በቤተ መንግሥት ይወለዳል ብለው ስለ ገመቱ፥ ወደ ንጉሥ ሄሮድስ ሄደው ኣዲስ ስለ ተወለደው ንጉሥ ጠየቁ።
ቀደም ሲል ዙፋኔን ይነጥቁብኛል በሚል ስጋት ከቤተሰቡ አባላት መካከል ብዙ ሰዎችን የፈጀው ንጉሥ ሄሮድስ፥ ይህን ሲሰማ ደነገጠ። በመጀመሪያ፥ የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎችን ሰብስቦ ጠየቃቸው። እነዚህ ሰዎች በብሉይ ኪዳን እንደተነገረው መሢሑ ከኢየሩሳሌም ሰባት ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ በምትገኘው በቤተልሔም እንደሚወለድ ያውቁ ነበር። ሄሮድስ ያለበትን ስፍራ አይተው እንዲነግሩት በማዘዝ ሰብዓ ሰገልን ወደ ቤተልሔም ላካቸው። ምንም እንኳ ሄሮድስ ሕጻኑን ንጉሥ ለማክበር እንደፈለገ ቢነግራቸውም፥ እውነተኛ ፍላጎቱ ግን ሕጻኑን መግደል ነበር። ኮከቡ እንደገና ለሰብዓ ሰገል ተገልጦ፥ ኢየሱስ ወደነበረበት ወደ ቤተልሔም መራቸው።
ማቴዎስን ከሉቃስ ትረካ ጋር በማነጻጸር እንደምንገነዘበው፥ ኢየሱስ ከተወለደ የተወሰነ ጊዜ አልፎ ነበር። በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ከተወለደበት ግርግም ወደ ቤት ተዛውሮ ነበር። ይህም የዘመድ ቤት ወይም እነዮሴፍ የተከራዩት ቤት ሳይሆን አይቀርም። ኢየሱስ ከተወለደ ምን ያህል ጊዜ እንዳለፈ አናውቅም። ሄሮድስ ከሰብዓ ሰገል ኮከቡ መጀመሪያ የታየበትን ጊዜ ተረድቶ እስከ ሁለት ዓመት የሆናቸውን ሕጻናት ሁሉ ስለ ገደለ፥ ኢየሱስ ከተወለደ ሁለት ዓመታት ሳይሞላው ኣይቀርም ተብሎ ይገመታል። ሰብዓ ሰገል ስጦታዎችን በመስጠትና እንደ አምላክ በማምለክ ክርስቶስን አክብረውታል።
እግዚአብሔርም ለሰብዓ ሰገል ያዩትን ለሄሮድስ ሳይናገሩ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ አድርጓል። በዚህ ታሪክ ማቴዎስ እግዚአብሔር የአይሁዶች ብቻ አምላክ እንዳልሆነና አሕዛብም የዕቅዱ አካል መሆናቸውን አመልክቷል። ክርስቶስ መሢሕ እንደሆነ በመጀመሪያ ከተገነዘቡት ሰዎች አንዳንዶቹ አሕዛብ ነበሩ። ዓለም ስለ እነርሱ ምንም ዐይነት አመለካከት ቢኖረውም ወንጌሉን ብዙውን ጊዜ እናውቃለን ከሚሉት የተሰወረው እውነት ልባቸውን ለከፈቱት ተገልጧል።
ከመሢሑ ታሪክ በስተጀርባ መንፈሳዊ ውጊያ አለ፡፡ ሰይጣን መሢሑን ለማጥፋት ፈልጎ ነበር። ይህንንም ያደረገው በዓለም ላይ ያለውን ኃይሉን እንደሚሽርበት ስለ ተገነዘበ ነበር። እግዚአብሔር ግን ልጁ ዕቅዶቹን ፈጽሞ፥ በመስቀል ላይ እንዲሞት ወስኖ ነበር። ስለዚህ ሰይጣን ኢየሱስን ለመግደል በሄሮድስ ልብ ውስጥ ያሴር እንደነበረ እግዚአብሔር በመገንዘብ፥ ዮሴፍ በመጀመሪያ ወደ ግብፅ ይዞት እንዲወርድ ከዚያም ወደ ናዝሬት ይዞት እንዲመለስ አዘዘው። ከዚያም ሄሮድስ ወደ ቤተልሔም ተጉዞ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ የሆናቸውን ሕጻናት ሁሉ አስገደለ። ይህም ሰብዓ ሰገል ኢየሱስን ለማየት የመጡት ቢያንስ ከኣንድ ዓመት ተኩል እስከ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ ሳይሆን አይቀርም ወደሚል ድምዳሚ ይመራናል። በክርስቶስ ልደት ዙሪያ በተከናወኑት በእነዚህ ክስተቶች ሁሉ፥ የእግዚአብሔር እጅ እንደ ነበረበት ማቴዎስ ያውቅ ነበር። የሕጻናቱ መገደል፥ የክርስቶስ ከግብፅና በኋላም ከናዝሬት መምጣት፥ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ተተንብዮአል።
ምንጭ:- ethiopiansite-com
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ አይ ኤም ከታተመውና የዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ያነከሰውም እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ፥ ለእግራችሁ ቅን መንገድ አድርጉ።”
ዕብራውያን 12፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ያነከሰውም እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ፥ ለእግራችሁ ቅን መንገድ አድርጉ።”
ዕብራውያን 12፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤9
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በተነ፥ ለምስኪኖች ሰጠ፥ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔር፥ ሁልጊዜ በነገር ሁሉ ብቃትን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ፥ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል።”
2ኛ ቆሮ 9፥8-9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በተነ፥ ለምስኪኖች ሰጠ፥ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔር፥ ሁልጊዜ በነገር ሁሉ ብቃትን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ፥ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል።”
2ኛ ቆሮ 9፥8-9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1
sparks.pdf
1.7 MB
📔ርዕስ፦ በዚያን ጊዜ
👤ደራሲ፦ ተስፋዬ ጋቢሶ
🖨አሳታሚ፦ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን
👉የዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ የሕይወት ታሪክ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👤ደራሲ፦ ተስፋዬ ጋቢሶ
🖨አሳታሚ፦ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን
👉የዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ የሕይወት ታሪክ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4👏2❤1