' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።”
ገላትያ 3፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።”
ገላትያ 3፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 8:18-30
እንደ ጳውሎስ ከባድ የሥቃይ ሕይወት የደረሰባቸው ሰዎች በጣም ጥቂት ናቸው (2ቆሮ. 6፥4–10፤ 11፥23-28)። ይህም ቢሆን ከሚመጣው ክብር ጋር ሲወዳደር የተቀበለው ሥቃይ ከቁም ነገር የሚቆጠር አይደለም (2ቆሮ. 4፥17)።
ጳውሎስ እዚህ ላይ በእኛ ውስጥ ስለሚገለጠው ክብር ይናገራል። በእኛ ውስጥ የሚገለጠው ክብር የማን ክብር ነው? የክርስቶስ ክብር ነው። እኛ ከክርስቶስ ጋር ስንነሣ የእርሱን ክብር እንቀበላለን፤ ልክ እርሱን እንመስላለን (1ዮሐ. 3፥2)። በመንፈስ ቅዱስ ለሚመሩ ሰዎች፥ ይህ ክብር አስቀድሞ በዚህ ምድር ላይ ጀምሮአል (2ቆሮ 3፥18)።
በዚህ ጥቅስ ላይ ፍጥረት የሚለው ቃል እንስሳትንና ተክሎችን ጨምሮ ሕይወት ያላቸውን ነገሮች በሙሉ ያጠቃልላል። ፍጥረት በሙሉ የእግዚአብሔርን ልጆች (በክርስቶስ ያመኑትን) መገለጥ (መክበር) ይጠባበቃል። መቼ ነው እነርሱ የሚገለጡት? ያለ እግዚአብሔር ይህንን ሊያውቅ የሚችል ማንም የለም። ይሁን እንጂ፥ በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መሠረት በዓለም መጨረሻ ላይ ይገለጣሉ፤ ይህም ጊዜ ክርስቶስ በክብሩ ሊነግሥ የሚመጣበት ጊዜ ነው (ማር. 13፥23-27 31-32 2. 3፥13 ራእ. 21:1-4)። ያንን ቀን ፍጥረት በሙሉ ይጠባበቀዋል፤ ምክንያቱም በዚያን ቀን የሚገለጡት (የሚከብሩት) አማኞች ብቻ አይደሉም፤ ነገር ግን ፍጥረት ራሱም በልዩ ሁኔታ አዲስ ይሆናል።
ዓለምን ስንመለከት ያለችበት ሁኔታ በአንዳንድ መንገድ ከንቱ ነው፤ የምታደርገው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው። ሁሉም ነገር የሚኖረው ለአጭር ጊዜ ሲሆን፤ ከዚያ በኋላ ሁሉ ሕመምተኛ ሆኖ ይሞታል፤ እንደዚህ በቶሎ የሚቀጠፍ ከሆነ የሕይወት ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው? ፍጥረት በመጀመሪያ እንደዚህ አልነበረም።
እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረ በኋላ፥ የፈጠረውን ሁሉ አየ፥ እጅግ መልካም መሆኑንም ተመለከተ (ዘፍ. 1፥31)። በእግዚአብሔር የተፈጠረው ነገር ሁሉ መልካምና ውብ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የፈጠረው ነገር ሁሉ በመጀመሪያዎቹ ወንድና ሴት፥ ማለትም በአዳምና በሔዋን ኃጢአት ምክንያት ተበላሸ (ዘፍ. 3፥1-6)። እግዚአብሔር እነርሱን እንዲህ አላቸው፥ «በእናንተ ምክንያት ምድር ተረገመች» (ዘፍ. 3፥17-18)፡፡ ስለዚህ በአንድ መንገድ በሰው ኃጢአት ምክንያት የሰው ዘር ብቻ ሳይሆን፥ መላው ፍጥረት ለፍርሃት፥ ለሞትና ለመበስበስ ተላልፎ ተሰጠ። አሳልፎ የሰጠውም እግዚአብሔር ነበር። ነገር ግን ፍጥረቱ በሙሉ በእንዲህ ዓይነት ተስፋ መቁረጥና ጭንቀት ውስጥ እንዲቀር የእግዚአብሔር ዕቅድ አልነበረም። እርሱ ፍጥረቱን አሳልፎ የሰጠው ለመደናቀፍና ለተስፋ መቁረጥ ብቻ ሳይሆን ለተስፋም ነበር። ይህም ተስፋ ወደፊት ፍጥረት ራሱ ከመበስበስ፥ ከሕመምና፥ ከሞት እስራት ነፃ እንደሚወጣ ነው (ቁ. 21)
የአሁኑ ሰማይና ምድር ሲያልፍ፥ መላው ፍጥረት በአንድ መንገድ ትንሣኤ ያገኛል። አዲስም ይሆናል፤ ዳግመኛም መበስበስና ሞት አይኖርም። ጳውሎስ ይህንን አዲስ የትንሣኤ ሁኔታ የእግዚአብሔር ልጆች ክብርና ነፃነት ይለዋል። በቀላሉ የዘላለም ሕይወት ማለት ነው። የዚህን ክብርና ነፃነት ማለትም የዚህ ዘላለማዊ ሕይወት መገለጥ ነው ፍጥረት በሙሉ በታላቅ ተስፋ የሚጠባበቀው (ቁ. 19):: ፍጥረት ሁሉ እስከ ዛሬ ድረስ በምጥ ጭንቀት ተይዞ በመቃተት ላይ መኖሩን እናውቃለን። ከገዛ ሕይወታችን ልምድ ይህ እውነት መሆኑን እናረጋግጣለን። በዚህ ዓለም በምንኖረው በሁላችንም ሕይወት ልፋት፥ ትግል፥ ሐዘን፥ ሕማምና ሞት ሁልጊዜ ይገኛሉ። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ችግሮች እንደ ምጥ ጭንቅ ናቸው። አንድ ሕፃን ሲወለድ እናቱ የምጥ ጭንቅ የሚይዛት አዲስ ሕይወት ለመምጣቱ ምልክት ነው። ልክ በዚሁ ዓይነት ይህ ፍጥረት አሁን ታግሦ የሚቀበለው መከራ፤ ለመበስበስ ከታሰረበት ነፃ እንደሚወጣ ምልክት ነው (ቁ. 21)፡፡ ውጤቱም አዲስ ልደት፥ አዲስ ሕይወት፥ አዲስ ፍጥረት ይሆናል።
እኛ አማኞች የእግዚአብሔር ልጆች ነን። እኛ የምንመራውም በእግዚአብሔር መንፈስ ነው። ይሁን እንጂ፥ በውስጣዊ ሕይወታችን እንቃትታለን፡ ሥጋችንም የመበስበስ እስረኛ ነው። የመንፈስን በኩራት፥ ማለትም በክርስቶስ አዲስ ሕይወት ያለን ብንሆንም፥ በሰማይ ተዘጋጅቶ የሚቆየንን ሙሉ ርስት ገና አልተቀበልንም (2ቆሮ. 5፥5፤ ኤፌ. 1፥13- 14)። ያም ውርስ ከመበስበስና ከሞት ነፃ ወጥተን የምንከብርበት የዘላለም ሕይወት ነው (ቁ. 21)
በክርስቶስ ያመኑት ግን አስቀድመው «እግዚአብሔር የተቀበላቸው ልጆች» ሆነዋል (ቁ. 15)። ሙሉ የልጅነት ክብር እንዳንቀበልና ሙሉ መብታችንን እንዳናገኝ ግን ዕድሜአችን ገና አልደረስም ወይም ገና አላደግንም። በዚያን ቀን ሥጋችን ሙሉ ደኅንነትን በሚያገኝበት ጊዜ ወይም ሥጋችን ከሞት በሚነሣበት ጊዜ ሙሉ የልጅነት መብታችንን እንቀበላለን። በዚያን ቀን የደኅንነታችንንና የመዋጀታችንን ሙሉ በረከት እናገኛለን፤ ስለዚህ እኛም ከፍጥረት ሁሉ ጋር ያንን ቀን በናፍቆት እንጠባበቃለን (ኤፌ. 4:30)::
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 368-369
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 8:18-30
እንደ ጳውሎስ ከባድ የሥቃይ ሕይወት የደረሰባቸው ሰዎች በጣም ጥቂት ናቸው (2ቆሮ. 6፥4–10፤ 11፥23-28)። ይህም ቢሆን ከሚመጣው ክብር ጋር ሲወዳደር የተቀበለው ሥቃይ ከቁም ነገር የሚቆጠር አይደለም (2ቆሮ. 4፥17)።
ጳውሎስ እዚህ ላይ በእኛ ውስጥ ስለሚገለጠው ክብር ይናገራል። በእኛ ውስጥ የሚገለጠው ክብር የማን ክብር ነው? የክርስቶስ ክብር ነው። እኛ ከክርስቶስ ጋር ስንነሣ የእርሱን ክብር እንቀበላለን፤ ልክ እርሱን እንመስላለን (1ዮሐ. 3፥2)። በመንፈስ ቅዱስ ለሚመሩ ሰዎች፥ ይህ ክብር አስቀድሞ በዚህ ምድር ላይ ጀምሮአል (2ቆሮ 3፥18)።
በዚህ ጥቅስ ላይ ፍጥረት የሚለው ቃል እንስሳትንና ተክሎችን ጨምሮ ሕይወት ያላቸውን ነገሮች በሙሉ ያጠቃልላል። ፍጥረት በሙሉ የእግዚአብሔርን ልጆች (በክርስቶስ ያመኑትን) መገለጥ (መክበር) ይጠባበቃል። መቼ ነው እነርሱ የሚገለጡት? ያለ እግዚአብሔር ይህንን ሊያውቅ የሚችል ማንም የለም። ይሁን እንጂ፥ በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መሠረት በዓለም መጨረሻ ላይ ይገለጣሉ፤ ይህም ጊዜ ክርስቶስ በክብሩ ሊነግሥ የሚመጣበት ጊዜ ነው (ማር. 13፥23-27 31-32 2. 3፥13 ራእ. 21:1-4)። ያንን ቀን ፍጥረት በሙሉ ይጠባበቀዋል፤ ምክንያቱም በዚያን ቀን የሚገለጡት (የሚከብሩት) አማኞች ብቻ አይደሉም፤ ነገር ግን ፍጥረት ራሱም በልዩ ሁኔታ አዲስ ይሆናል።
ዓለምን ስንመለከት ያለችበት ሁኔታ በአንዳንድ መንገድ ከንቱ ነው፤ የምታደርገው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው። ሁሉም ነገር የሚኖረው ለአጭር ጊዜ ሲሆን፤ ከዚያ በኋላ ሁሉ ሕመምተኛ ሆኖ ይሞታል፤ እንደዚህ በቶሎ የሚቀጠፍ ከሆነ የሕይወት ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው? ፍጥረት በመጀመሪያ እንደዚህ አልነበረም።
እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረ በኋላ፥ የፈጠረውን ሁሉ አየ፥ እጅግ መልካም መሆኑንም ተመለከተ (ዘፍ. 1፥31)። በእግዚአብሔር የተፈጠረው ነገር ሁሉ መልካምና ውብ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የፈጠረው ነገር ሁሉ በመጀመሪያዎቹ ወንድና ሴት፥ ማለትም በአዳምና በሔዋን ኃጢአት ምክንያት ተበላሸ (ዘፍ. 3፥1-6)። እግዚአብሔር እነርሱን እንዲህ አላቸው፥ «በእናንተ ምክንያት ምድር ተረገመች» (ዘፍ. 3፥17-18)፡፡ ስለዚህ በአንድ መንገድ በሰው ኃጢአት ምክንያት የሰው ዘር ብቻ ሳይሆን፥ መላው ፍጥረት ለፍርሃት፥ ለሞትና ለመበስበስ ተላልፎ ተሰጠ። አሳልፎ የሰጠውም እግዚአብሔር ነበር። ነገር ግን ፍጥረቱ በሙሉ በእንዲህ ዓይነት ተስፋ መቁረጥና ጭንቀት ውስጥ እንዲቀር የእግዚአብሔር ዕቅድ አልነበረም። እርሱ ፍጥረቱን አሳልፎ የሰጠው ለመደናቀፍና ለተስፋ መቁረጥ ብቻ ሳይሆን ለተስፋም ነበር። ይህም ተስፋ ወደፊት ፍጥረት ራሱ ከመበስበስ፥ ከሕመምና፥ ከሞት እስራት ነፃ እንደሚወጣ ነው (ቁ. 21)
የአሁኑ ሰማይና ምድር ሲያልፍ፥ መላው ፍጥረት በአንድ መንገድ ትንሣኤ ያገኛል። አዲስም ይሆናል፤ ዳግመኛም መበስበስና ሞት አይኖርም። ጳውሎስ ይህንን አዲስ የትንሣኤ ሁኔታ የእግዚአብሔር ልጆች ክብርና ነፃነት ይለዋል። በቀላሉ የዘላለም ሕይወት ማለት ነው። የዚህን ክብርና ነፃነት ማለትም የዚህ ዘላለማዊ ሕይወት መገለጥ ነው ፍጥረት በሙሉ በታላቅ ተስፋ የሚጠባበቀው (ቁ. 19):: ፍጥረት ሁሉ እስከ ዛሬ ድረስ በምጥ ጭንቀት ተይዞ በመቃተት ላይ መኖሩን እናውቃለን። ከገዛ ሕይወታችን ልምድ ይህ እውነት መሆኑን እናረጋግጣለን። በዚህ ዓለም በምንኖረው በሁላችንም ሕይወት ልፋት፥ ትግል፥ ሐዘን፥ ሕማምና ሞት ሁልጊዜ ይገኛሉ። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ችግሮች እንደ ምጥ ጭንቅ ናቸው። አንድ ሕፃን ሲወለድ እናቱ የምጥ ጭንቅ የሚይዛት አዲስ ሕይወት ለመምጣቱ ምልክት ነው። ልክ በዚሁ ዓይነት ይህ ፍጥረት አሁን ታግሦ የሚቀበለው መከራ፤ ለመበስበስ ከታሰረበት ነፃ እንደሚወጣ ምልክት ነው (ቁ. 21)፡፡ ውጤቱም አዲስ ልደት፥ አዲስ ሕይወት፥ አዲስ ፍጥረት ይሆናል።
እኛ አማኞች የእግዚአብሔር ልጆች ነን። እኛ የምንመራውም በእግዚአብሔር መንፈስ ነው። ይሁን እንጂ፥ በውስጣዊ ሕይወታችን እንቃትታለን፡ ሥጋችንም የመበስበስ እስረኛ ነው። የመንፈስን በኩራት፥ ማለትም በክርስቶስ አዲስ ሕይወት ያለን ብንሆንም፥ በሰማይ ተዘጋጅቶ የሚቆየንን ሙሉ ርስት ገና አልተቀበልንም (2ቆሮ. 5፥5፤ ኤፌ. 1፥13- 14)። ያም ውርስ ከመበስበስና ከሞት ነፃ ወጥተን የምንከብርበት የዘላለም ሕይወት ነው (ቁ. 21)
በክርስቶስ ያመኑት ግን አስቀድመው «እግዚአብሔር የተቀበላቸው ልጆች» ሆነዋል (ቁ. 15)። ሙሉ የልጅነት ክብር እንዳንቀበልና ሙሉ መብታችንን እንዳናገኝ ግን ዕድሜአችን ገና አልደረስም ወይም ገና አላደግንም። በዚያን ቀን ሥጋችን ሙሉ ደኅንነትን በሚያገኝበት ጊዜ ወይም ሥጋችን ከሞት በሚነሣበት ጊዜ ሙሉ የልጅነት መብታችንን እንቀበላለን። በዚያን ቀን የደኅንነታችንንና የመዋጀታችንን ሙሉ በረከት እናገኛለን፤ ስለዚህ እኛም ከፍጥረት ሁሉ ጋር ያንን ቀን በናፍቆት እንጠባበቃለን (ኤፌ. 4:30)::
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 368-369
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የቅዱሳን ልብ በአንተ ስራ ስለ ዐረፈ፥ ወንድሜ ሆይ፥ በፍቅርህ ብዙ ደስታንና መጽናናትን አግኝቼአለሁና።”
ፊልሞና 1፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የቅዱሳን ልብ በአንተ ስራ ስለ ዐረፈ፥ ወንድሜ ሆይ፥ በፍቅርህ ብዙ ደስታንና መጽናናትን አግኝቼአለሁና።”
ፊልሞና 1፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
መዝገበ ቃላት.pdf
57.3 MB
📔ርዕስ፦ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ
ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ
👤አዘጋጅ፦ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
📑የገጽ ብዛት፦ 908 💾መጠን፦57.3MB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ
👤አዘጋጅ፦ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
📑የገጽ ብዛት፦ 908 💾መጠን፦57.3MB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5❤1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?”
ያዕቆብ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?”
ያዕቆብ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤7
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ያዕቆብ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
¹⁵ ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
¹⁶ ከእናንተ አንዱም፦ በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
¹⁷ እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
¹⁸ ነገር ግን አንድ ሰው፦ አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
¹⁹ እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
²⁰ አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
²¹ አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
²² እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
²³ መጽሐፍም፦ አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
²⁴ ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።
²⁵ እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?
²⁶ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ያዕቆብ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
¹⁵ ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
¹⁶ ከእናንተ አንዱም፦ በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
¹⁷ እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
¹⁸ ነገር ግን አንድ ሰው፦ አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
¹⁹ እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
²⁰ አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
²¹ አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
²² እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
²³ መጽሐፍም፦ አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
²⁴ ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።
²⁵ እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?
²⁶ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።”
ማቴዎስ 6፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።”
ማቴዎስ 6፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤8👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል።”
ሮሜ 4፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል።”
ሮሜ 4፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1
የመናኝ ጉዞ.pdf
6.4 MB
❤5👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤”
1ኛ ጴጥሮስ 3፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤”
1ኛ ጴጥሮስ 3፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የቀጠለ ...
ሮሜ 8:18-30
ለክርስቲያኖች ተስፋ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። በዚህ ዓለም ላይ ርስታችንን በሙሉ አንቀበልም፤ ማለትም የተሟላ ደኅንነትን አናገኝም። አሁን የምናገኘው የውርሳችንን የወደፊት መያዛ ብቻ ነው (ኤፌ. 1፥14)። የተሟላ ውርስ ወይም ደኅንነት፥ የሥጋችን መዋጀት በኋላ ይመጣል። ስለዚህ ወደፊት የሚመጣውን ነገር ተስፋ እናደርጋለን።
እኛ የዳነው በዚሁ ተስፋ ነው (ቁ. 24)። ይህም ተስፋ የሥጋችን መዋጀት ተስፋ ነው (ቁ. 23)። ጳውሎስ በእምነት አማካይነት በዚህ ተስፋ እንድናለን ነው የሚለን። እምነት ተስፋ የምናደርገው ነገር እውነት እንደሚሆን ማረጋገጫ ነው (ዕብ. 11፥1)። ተስፋ የሚመጣው ከእምነት ነው፤ እግዚአብሔር የሰጠውን የተስፋ ቃል እንደሚፈጸም እናምናለን። ስለሆነም ቃል የገባልንን እንደምንቀበል ተስፋ አለን።
መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ከሚያደርግልን ከብዙ ነገሮች መካከል አንዱ፤ እንድንጸልይ መርዳት ነው። አንዳንድ ጊዜ ስለምን መጸለይ እንደሚገባን አናውቅም። እኛ ምንም እንደማያውቅ፤ አባቱን የማይገባውን ወይም የሚጎዳውን ነገር እንዲሰጠው እንደሚጠይቅ ሕፃን ነን። እኛ ብዙ ጊዜ ለራሳችንም ሆነ ለሌሎች መጸለይ የሚገባንን አናውቅም።
ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ በጸሎታችን ሊረዳን የተዘጋጀ በመሆኑ፥ ልናመሰግነው ይገባናል። ልክ ክርስቶስ ለእኛ በሰማይ እንደሚማልድልን (ሮሜ 8፥34፤ ዕብ. 7፥25) ሁሉ፥ መንፈስ ቅዱስም በእኛ ውስጥ በመኖር ቃላት ሊገልጡት በማይችሉት መቃተት ለእኛ ይማልዳል።
እኛው ራሳችን ለመጸለይ ብርቱ ጥረት ካላደረግን መንፈስ ቅዱስ በእርግጥ አይረዳንም። የምንችለውን ያህል መጸለይ አለብን፤ ይህም ማለት ለጸሎት ብዙ ጊዜ መውሰድ ይገባናል።
በ1ዮሐ. 5፥14 ዮሐንስ እንዲህ ብሎ ተጽፎአል፤" . . እንደ ፈቃዱ የሆነውን ማናቸውንም ነገር ብንጠይቅ እርሱ ይሰማናል።" የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደሆነ የሚያሳየን መንፈስ ቅዱስ ነው። ከዚህም የተነሣ በእግዚአብሔር ፈቃድ መጸለይ እንችላለን።
ልባችንን የሚመረምረው እርሱ (እግዚአብሔር) የመንፈስን አእምሮ ያውቃል። ይህ መንፈስ የእግዚአብሔር የራሱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የራሱን መንፈስ "አእምሮ ያውቃል" ማለት ነው። የእግዚአብሔር የራሱ መንፈስ ከመሆኑ የተነሣ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ መሠረት ይማልድልናል።
እግዚአብሔር በልባችን ውስጥ ያስቀመጥነውን ነገር ሁሉ ያያል፤ ገና እርሱን ሳንለምነው የልብ ፍላጎታችንን ሁሉ ያውቃል። እግዚአብሔር ጸሎታችን በእውነት ክልብ ይሁን ወይም ለማስመሰል ከከንፈራችን ይሁን ያውቃል። በማርቆስ 7፤6 እንደተጻፈው «እነርሱ እግዚአብሔርን የሚያመልኩት በከንፈራቸው ብቻ ነው!» ተብሎ ስለ እኛ አይነገርብን።
ይህ ጥቅስ (ቁ. 28) በአዲስ ኪዳን ከሚገኙት ጥቅሶች በጣም ታላቅ ነው። በዘመናት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ታላላቅ መጽናናትና ተስፋ አግኝተውበታል። «በሁሉ ነገር እግዚአብሔር ለእኛ መልካም ነገር ያደርግልናል»። በሁሉ ነገር የሚለው አነጋገር የሚያጠቃልለው በሕይወታችን መልካምና አስደሳች የሆኑትን ነገሮች ብቻ ሳይሆን፥ ክፉውና የማያስደስት ነገሮችን ክፉው፥ በሽታና ሞትንም ያጠቃልላል። እግዚአብሔር ክፉ ነገሮችንም እንኳ ለእኛ መልካም እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። መልካም የሚያደርገው ግን ለማንም ሰው ሳይሆን “እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት...” ነው።
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 369
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የቀጠለ ...
ሮሜ 8:18-30
ለክርስቲያኖች ተስፋ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። በዚህ ዓለም ላይ ርስታችንን በሙሉ አንቀበልም፤ ማለትም የተሟላ ደኅንነትን አናገኝም። አሁን የምናገኘው የውርሳችንን የወደፊት መያዛ ብቻ ነው (ኤፌ. 1፥14)። የተሟላ ውርስ ወይም ደኅንነት፥ የሥጋችን መዋጀት በኋላ ይመጣል። ስለዚህ ወደፊት የሚመጣውን ነገር ተስፋ እናደርጋለን።
እኛ የዳነው በዚሁ ተስፋ ነው (ቁ. 24)። ይህም ተስፋ የሥጋችን መዋጀት ተስፋ ነው (ቁ. 23)። ጳውሎስ በእምነት አማካይነት በዚህ ተስፋ እንድናለን ነው የሚለን። እምነት ተስፋ የምናደርገው ነገር እውነት እንደሚሆን ማረጋገጫ ነው (ዕብ. 11፥1)። ተስፋ የሚመጣው ከእምነት ነው፤ እግዚአብሔር የሰጠውን የተስፋ ቃል እንደሚፈጸም እናምናለን። ስለሆነም ቃል የገባልንን እንደምንቀበል ተስፋ አለን።
መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ከሚያደርግልን ከብዙ ነገሮች መካከል አንዱ፤ እንድንጸልይ መርዳት ነው። አንዳንድ ጊዜ ስለምን መጸለይ እንደሚገባን አናውቅም። እኛ ምንም እንደማያውቅ፤ አባቱን የማይገባውን ወይም የሚጎዳውን ነገር እንዲሰጠው እንደሚጠይቅ ሕፃን ነን። እኛ ብዙ ጊዜ ለራሳችንም ሆነ ለሌሎች መጸለይ የሚገባንን አናውቅም።
ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ በጸሎታችን ሊረዳን የተዘጋጀ በመሆኑ፥ ልናመሰግነው ይገባናል። ልክ ክርስቶስ ለእኛ በሰማይ እንደሚማልድልን (ሮሜ 8፥34፤ ዕብ. 7፥25) ሁሉ፥ መንፈስ ቅዱስም በእኛ ውስጥ በመኖር ቃላት ሊገልጡት በማይችሉት መቃተት ለእኛ ይማልዳል።
እኛው ራሳችን ለመጸለይ ብርቱ ጥረት ካላደረግን መንፈስ ቅዱስ በእርግጥ አይረዳንም። የምንችለውን ያህል መጸለይ አለብን፤ ይህም ማለት ለጸሎት ብዙ ጊዜ መውሰድ ይገባናል።
በ1ዮሐ. 5፥14 ዮሐንስ እንዲህ ብሎ ተጽፎአል፤" . . እንደ ፈቃዱ የሆነውን ማናቸውንም ነገር ብንጠይቅ እርሱ ይሰማናል።" የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደሆነ የሚያሳየን መንፈስ ቅዱስ ነው። ከዚህም የተነሣ በእግዚአብሔር ፈቃድ መጸለይ እንችላለን።
ልባችንን የሚመረምረው እርሱ (እግዚአብሔር) የመንፈስን አእምሮ ያውቃል። ይህ መንፈስ የእግዚአብሔር የራሱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የራሱን መንፈስ "አእምሮ ያውቃል" ማለት ነው። የእግዚአብሔር የራሱ መንፈስ ከመሆኑ የተነሣ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ መሠረት ይማልድልናል።
እግዚአብሔር በልባችን ውስጥ ያስቀመጥነውን ነገር ሁሉ ያያል፤ ገና እርሱን ሳንለምነው የልብ ፍላጎታችንን ሁሉ ያውቃል። እግዚአብሔር ጸሎታችን በእውነት ክልብ ይሁን ወይም ለማስመሰል ከከንፈራችን ይሁን ያውቃል። በማርቆስ 7፤6 እንደተጻፈው «እነርሱ እግዚአብሔርን የሚያመልኩት በከንፈራቸው ብቻ ነው!» ተብሎ ስለ እኛ አይነገርብን።
ይህ ጥቅስ (ቁ. 28) በአዲስ ኪዳን ከሚገኙት ጥቅሶች በጣም ታላቅ ነው። በዘመናት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ታላላቅ መጽናናትና ተስፋ አግኝተውበታል። «በሁሉ ነገር እግዚአብሔር ለእኛ መልካም ነገር ያደርግልናል»። በሁሉ ነገር የሚለው አነጋገር የሚያጠቃልለው በሕይወታችን መልካምና አስደሳች የሆኑትን ነገሮች ብቻ ሳይሆን፥ ክፉውና የማያስደስት ነገሮችን ክፉው፥ በሽታና ሞትንም ያጠቃልላል። እግዚአብሔር ክፉ ነገሮችንም እንኳ ለእኛ መልካም እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። መልካም የሚያደርገው ግን ለማንም ሰው ሳይሆን “እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት...” ነው።
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 369
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ቃል ኪዳኔ ከእርሱ ጋር የሕይወትና የሰላም ቃል ኪዳን ነበረ፤ ይፈራ ዘንድም እነርሱን ሰጠሁት፤ እርሱም ፈራኝ፥ ከስሜም የተነሣ ደነገጠ።”
ሚልክያስ 2፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ቃል ኪዳኔ ከእርሱ ጋር የሕይወትና የሰላም ቃል ኪዳን ነበረ፤ ይፈራ ዘንድም እነርሱን ሰጠሁት፤ እርሱም ፈራኝ፥ ከስሜም የተነሣ ደነገጠ።”
ሚልክያስ 2፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2
ቅዱሳት መጻሕፍት
ኢየሱስና የመከራ ሕይወት በእግዚአብሔር ሕልውና የማያምኑ ሰዎች “እግዚአብሔር የለም” ለማለት በየዘመናቱ ከሚያነሧቸው ጥያቄዎች አንዱ በምድር ላይ የመከራ መኖር ነው፡፡ ʻእግዚአብሔር ቢኖር ይህ ሁሉ ጥፋት በሰዎች ላይ ለምን ይደርሳል?ʼ ይላሉ፤ እግዚአብሔርን የሚያምኑ ሰዎችም ጥያቄውን ደጋግመው ያነሡታል፡፡ ሰዎች መከራን በተለያየ መልኩ ሲጋፈጡ በእግዚአብሔር ሕልውና፣ በእግዚአብሔር መልካምነት ወይም በእግዚአብሔር…
የቀጠለ...
ኢየሱስና የመከራ ሕይወት
አሳዛኙ ነገር ግን በአደጋው ወቅት አብሮ ያልነበረው ልጁ የነበረበት ሁኔታ ነው፡፡ በአደጋው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸውን የቤተሰቡን አባላት በማስታመም እና ከአባቱ ድንገተኛ ሞት ለመጽናናት በሚጥርበት ወቅት እነዚህ በክርስቲያኖች አንደበት ይነገሩ የነበሩ መላምቶች መጽናናትን ከባድ አድርገውበታል፡፡ የመኪና አደጋ በማንም ሰው ሊደርስ የሚችል ሆኖ ሳለ፣ ይህ ልጅም በዚህ አደጋ ከእግዚአብሔር ጋር የመሟገቱ አይቀሬነት እየታወቀ የየሰዉ ግዴለሽ አስተያየት ኀዘኑን የሚያብስ እንጂ የሚያጽናና አልነበረም፤ በተለይ የቅዱሳንን እገዛ በሚፈልግበት በዚያ ጊዜ! ከብዙ ጊዜ በኋላም ከዚህ ወጣት ጋር ጥቂት ጊዜ ሳሳልፍ በወቅቱ ወገኖች በሚሰነዝሩት መላምት ዛሬም ድረስ ምን ያህል እንደ ተጎዳ ለመረዳት አልከበደኝም፡፡
አደጋ በሚደርስበት ጊዜ ሁሉ መንሥኤውን (ሰበቡን) ፈልገን አንችለውም፡፡ ሰዎች ላይ አደጋ የሚደርሰው ከሌሎች የበለጡ ኀጢአተኞች ስለሆኑ አይደለም፡፡ ጌታ ኢየሱስ የጅምላ አደጋና ሥቃይ መድረሱን ለነገሩት ሰዎች ይህንኑ ነው የመለሰላቸው (ሉቃ 13፥1-5)፡፡ መከራ ከእግዚአብሔር ጋር ትክክለኛ እርምጃ በሚራመዱ ሰዎችም ላይ ይደርሳል፡፡ ስለዚህ በመከራ የሚያልፉ ሰዎችን ማጽናናት ቀዳሚ ሥራችን መሆን ይኖርበታል፡፡ በተለይ ሰዎች እግዚአብሔር ለምን ጣልቃ ገብቶ እንዳላዳናቸው በጥያቄ ተወጥረው በሚሠቃዩበት ጊዜ በቁስላቸው ላይ ጨው እንዳንነሰንስ መጠንቀቅ ይኖርብናል፡፡ መከራ ሰው አይመርጥም፤ ማንንም አይምርም፤ እግዚአብሔርም ጣልቃ ላይገባ ይችላል፡፡ በብሉይ ኪዳን የምናየው የኀዘን እንጉርጉሮ ብዛት እግዚአብሔር ሁልጊዜም በቀጥታ ጣልቃ እንደሚገባ እርግጠኛ እንዳንሆን ያደርገናል፡፡ ጣልቃ ገብቶ የሚታደግበት ጊዜ አለ፤ የማይገባበትም ጊዜ ሞልቶአል፡፡ ምክንያቱን የሚያውቀው እርሱ ብቻ ነው፡፡ ሙሴ እንዳለው ምስጢሩ ለአምላካችን ነው (ዘዳ. 29፥29)፡፡
ሆኖም ጌታ ኢየሱስ ሲመጣ መከራ በሰው ልጆች ላይ የሚደርስበትን ምስጢር አልነገረንም፤ መከራንም አላስቀረም፡፡ ለምን? ይልቁኑ በመከራ የሚያልፉ ሰዎችን አብሮአቸው በመሆን፣ በማጽናናትና በመፈወስ የእግዚአብሔርን አብሮ ኋኚነትና ሰው ወዳድነት አጸናልን፡፡ እግዚአብሔር ሁልጊዜም ከሕዝቡ ጋር ነው፡፡ በሞት ጥላ መካከል ስንሄድ እርሱ አብሮን አለ (መዝ. 23፥4)፤ በእሳት ውስጥ ስንጣል አብሮ አለ (ዳን. 3፥19-27)፡፡
እግዚአብሔር ከምናልፍበት መከራ ሁሌ አያስጥለን ይሆናል፤ ሁሌም ግን አብሮን አለ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ራሱን የሚሰውር አምላክ ነውና (ኢሳ. 45፥15) አብሮን መሆኑ አይታወቀን ይሆናል፡፡ ስለዚህ ከመከረኞች ጋር አብረን ስንሆን፣ በሚያልፉበት ነገር ውስጥ አልታያቸው ያለውን እግዚአብሔርን ማሳየት እንችላለን፡፡
በተለይ በምድራችን እዚህም እዚያም እየተረጨ ያለው “የብልጽግና ወንጌል” የተሰኘው አስተምህሮ አማኝነት መከራ እንዳይደርስብን ዋስትና እንደሚሆነን ማስተማሩ ይህ ዐይነቱን አለመግባባት በመፍጠር ውስጥ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡ ስለዚህ ሰዎች በሽታ ወይም ችግር ሲደርስባቸው እምነት እንደጎደላቸው ማሰብ ለብዙዎች ቀላል ነው፡፡ ችግር ውስጥ ያሉ ሰዎችን ከማጽናናት እና በችግራቸው አብሮ ከመቸገር ይልቅ እምነትን በተግባር ያለ መለማመድ ምሳሌ ሲደረጉ ይታያል፡፡ ስለዚህ እነርሱም የአማኞች አብሮነት እጅግ በሚያስፈልጋቸው በችግራቸው ጊዜ ከአማኞች ለመሸሽ ይገደዳሉ፡፡ በችግር ጊዜ ደራሽና አጽናኝ መሆን የሚጠበቅባቸው አማኞች ችግርን አባባሽ ሆነው ያርፉታል፡፡ ለመሆኑ የኢዮብ “ወዳጆችስ” ከዚህ የተለየ ምን አደረጉ? እግዚአብሔር ደጋግሞ “ጻድቅና ከክፋት የራቀ” በማለት የተናገረለትን ሰው እምነት እንዳጣና ኀጢአት እንደሚለማመድ ስለዚህም መከራው እንደ ደረሰበት መናገር ምን ይባላል? እግዚአብሔር መጨረሻ የገሠጸው ግን እነርሱን ነበር፡፡ ኢዮብን ለማጽናናት ቢመጡም ተጨማሪ ሥቃይ ፈጥረውበት ሄዱ፡፡
አማኞች በሰው የሚደርስ ችግር እንደማይደርስብን ዋስትና አልተሰጠንም፡፡ እንዲያውም መከራ ሲደርስ ሰዎች ከተደጋገፉ ችግሩ ይቀልላቸዋልና እንደ አማኝ ይህን ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
ጌታ ኢየሱስ በየትኛውም የመከራ ጕዳይ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡ ፈውስና መጽናናትን ፍለጋ ወደ እርሱ የመጡ ሰዎችን “መጀመሪያውኑ ይህ የደረሰባችሁ እምነት ስለ ጎደላችሁ፣ አዎንታዊ ቃል ስላላወጃችሁ፣ ቅርጫት ውስጥ ገንዘብ ስላልወረወራችሁ፣ የተሰበከውን ቃል የራሳችሁ ስላላደረጋችሁ፣ የተደበቀ ኀጢአት ስላለባችሁ ነው” የሚል ትንታኔ አልሰጠም፡፡ መከራ የሰዎች የአርባ ቀን ዕድል በመሆኑ ዐይናቸውን ጨፍነው እንዲቀበሉትም አላግባባም፡፡ ጌታ ኢየሱስ ሲያደርግ የኖረው አንድ ነገር ነው፤ ወደ እርሱ የመጡትን ሕመምተኞች ሁሉ ፈወሳቸው፤ ያዘኑትንም አጽናናቸው፡፡ ወደ እርሱ ያልመጡትንም ወደ እነርሱ እየሄደ ተመሳሳይ ነገር አደረገ፡፡ ፍቅርን በተግባር አስተማረ፡፡ ለነገሩማ “በአዲስ ኪዳን ውስጥ የምናገኘው እያንዳንዱ ስለ መከራ የሚያወራ ምንባብ ከመንሥኤው ይልቅ ለመከራው የሚኖረን ምላሽ ላይ የሚያተኲር ነው፡፡” እኛስ ማንን መምሰል እንፈልጋለን?
በጳውሎስ ፈቃዱ
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ hintset.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ኢየሱስና የመከራ ሕይወት
አሳዛኙ ነገር ግን በአደጋው ወቅት አብሮ ያልነበረው ልጁ የነበረበት ሁኔታ ነው፡፡ በአደጋው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸውን የቤተሰቡን አባላት በማስታመም እና ከአባቱ ድንገተኛ ሞት ለመጽናናት በሚጥርበት ወቅት እነዚህ በክርስቲያኖች አንደበት ይነገሩ የነበሩ መላምቶች መጽናናትን ከባድ አድርገውበታል፡፡ የመኪና አደጋ በማንም ሰው ሊደርስ የሚችል ሆኖ ሳለ፣ ይህ ልጅም በዚህ አደጋ ከእግዚአብሔር ጋር የመሟገቱ አይቀሬነት እየታወቀ የየሰዉ ግዴለሽ አስተያየት ኀዘኑን የሚያብስ እንጂ የሚያጽናና አልነበረም፤ በተለይ የቅዱሳንን እገዛ በሚፈልግበት በዚያ ጊዜ! ከብዙ ጊዜ በኋላም ከዚህ ወጣት ጋር ጥቂት ጊዜ ሳሳልፍ በወቅቱ ወገኖች በሚሰነዝሩት መላምት ዛሬም ድረስ ምን ያህል እንደ ተጎዳ ለመረዳት አልከበደኝም፡፡
አደጋ በሚደርስበት ጊዜ ሁሉ መንሥኤውን (ሰበቡን) ፈልገን አንችለውም፡፡ ሰዎች ላይ አደጋ የሚደርሰው ከሌሎች የበለጡ ኀጢአተኞች ስለሆኑ አይደለም፡፡ ጌታ ኢየሱስ የጅምላ አደጋና ሥቃይ መድረሱን ለነገሩት ሰዎች ይህንኑ ነው የመለሰላቸው (ሉቃ 13፥1-5)፡፡ መከራ ከእግዚአብሔር ጋር ትክክለኛ እርምጃ በሚራመዱ ሰዎችም ላይ ይደርሳል፡፡ ስለዚህ በመከራ የሚያልፉ ሰዎችን ማጽናናት ቀዳሚ ሥራችን መሆን ይኖርበታል፡፡ በተለይ ሰዎች እግዚአብሔር ለምን ጣልቃ ገብቶ እንዳላዳናቸው በጥያቄ ተወጥረው በሚሠቃዩበት ጊዜ በቁስላቸው ላይ ጨው እንዳንነሰንስ መጠንቀቅ ይኖርብናል፡፡ መከራ ሰው አይመርጥም፤ ማንንም አይምርም፤ እግዚአብሔርም ጣልቃ ላይገባ ይችላል፡፡ በብሉይ ኪዳን የምናየው የኀዘን እንጉርጉሮ ብዛት እግዚአብሔር ሁልጊዜም በቀጥታ ጣልቃ እንደሚገባ እርግጠኛ እንዳንሆን ያደርገናል፡፡ ጣልቃ ገብቶ የሚታደግበት ጊዜ አለ፤ የማይገባበትም ጊዜ ሞልቶአል፡፡ ምክንያቱን የሚያውቀው እርሱ ብቻ ነው፡፡ ሙሴ እንዳለው ምስጢሩ ለአምላካችን ነው (ዘዳ. 29፥29)፡፡
ሆኖም ጌታ ኢየሱስ ሲመጣ መከራ በሰው ልጆች ላይ የሚደርስበትን ምስጢር አልነገረንም፤ መከራንም አላስቀረም፡፡ ለምን? ይልቁኑ በመከራ የሚያልፉ ሰዎችን አብሮአቸው በመሆን፣ በማጽናናትና በመፈወስ የእግዚአብሔርን አብሮ ኋኚነትና ሰው ወዳድነት አጸናልን፡፡ እግዚአብሔር ሁልጊዜም ከሕዝቡ ጋር ነው፡፡ በሞት ጥላ መካከል ስንሄድ እርሱ አብሮን አለ (መዝ. 23፥4)፤ በእሳት ውስጥ ስንጣል አብሮ አለ (ዳን. 3፥19-27)፡፡
እግዚአብሔር ከምናልፍበት መከራ ሁሌ አያስጥለን ይሆናል፤ ሁሌም ግን አብሮን አለ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ራሱን የሚሰውር አምላክ ነውና (ኢሳ. 45፥15) አብሮን መሆኑ አይታወቀን ይሆናል፡፡ ስለዚህ ከመከረኞች ጋር አብረን ስንሆን፣ በሚያልፉበት ነገር ውስጥ አልታያቸው ያለውን እግዚአብሔርን ማሳየት እንችላለን፡፡
በተለይ በምድራችን እዚህም እዚያም እየተረጨ ያለው “የብልጽግና ወንጌል” የተሰኘው አስተምህሮ አማኝነት መከራ እንዳይደርስብን ዋስትና እንደሚሆነን ማስተማሩ ይህ ዐይነቱን አለመግባባት በመፍጠር ውስጥ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡ ስለዚህ ሰዎች በሽታ ወይም ችግር ሲደርስባቸው እምነት እንደጎደላቸው ማሰብ ለብዙዎች ቀላል ነው፡፡ ችግር ውስጥ ያሉ ሰዎችን ከማጽናናት እና በችግራቸው አብሮ ከመቸገር ይልቅ እምነትን በተግባር ያለ መለማመድ ምሳሌ ሲደረጉ ይታያል፡፡ ስለዚህ እነርሱም የአማኞች አብሮነት እጅግ በሚያስፈልጋቸው በችግራቸው ጊዜ ከአማኞች ለመሸሽ ይገደዳሉ፡፡ በችግር ጊዜ ደራሽና አጽናኝ መሆን የሚጠበቅባቸው አማኞች ችግርን አባባሽ ሆነው ያርፉታል፡፡ ለመሆኑ የኢዮብ “ወዳጆችስ” ከዚህ የተለየ ምን አደረጉ? እግዚአብሔር ደጋግሞ “ጻድቅና ከክፋት የራቀ” በማለት የተናገረለትን ሰው እምነት እንዳጣና ኀጢአት እንደሚለማመድ ስለዚህም መከራው እንደ ደረሰበት መናገር ምን ይባላል? እግዚአብሔር መጨረሻ የገሠጸው ግን እነርሱን ነበር፡፡ ኢዮብን ለማጽናናት ቢመጡም ተጨማሪ ሥቃይ ፈጥረውበት ሄዱ፡፡
አማኞች በሰው የሚደርስ ችግር እንደማይደርስብን ዋስትና አልተሰጠንም፡፡ እንዲያውም መከራ ሲደርስ ሰዎች ከተደጋገፉ ችግሩ ይቀልላቸዋልና እንደ አማኝ ይህን ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
ጌታ ኢየሱስ በየትኛውም የመከራ ጕዳይ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡ ፈውስና መጽናናትን ፍለጋ ወደ እርሱ የመጡ ሰዎችን “መጀመሪያውኑ ይህ የደረሰባችሁ እምነት ስለ ጎደላችሁ፣ አዎንታዊ ቃል ስላላወጃችሁ፣ ቅርጫት ውስጥ ገንዘብ ስላልወረወራችሁ፣ የተሰበከውን ቃል የራሳችሁ ስላላደረጋችሁ፣ የተደበቀ ኀጢአት ስላለባችሁ ነው” የሚል ትንታኔ አልሰጠም፡፡ መከራ የሰዎች የአርባ ቀን ዕድል በመሆኑ ዐይናቸውን ጨፍነው እንዲቀበሉትም አላግባባም፡፡ ጌታ ኢየሱስ ሲያደርግ የኖረው አንድ ነገር ነው፤ ወደ እርሱ የመጡትን ሕመምተኞች ሁሉ ፈወሳቸው፤ ያዘኑትንም አጽናናቸው፡፡ ወደ እርሱ ያልመጡትንም ወደ እነርሱ እየሄደ ተመሳሳይ ነገር አደረገ፡፡ ፍቅርን በተግባር አስተማረ፡፡ ለነገሩማ “በአዲስ ኪዳን ውስጥ የምናገኘው እያንዳንዱ ስለ መከራ የሚያወራ ምንባብ ከመንሥኤው ይልቅ ለመከራው የሚኖረን ምላሽ ላይ የሚያተኲር ነው፡፡” እኛስ ማንን መምሰል እንፈልጋለን?
በጳውሎስ ፈቃዱ
ይቀጥላል ...
ምንጭ፦ hintset.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አጵሎስ ወደ አካይያ ለመሄድ በፈለገ ጊዜ፣ ወንድሞች አበረታቱት፤ በዚያ የነበሩት ደቀ መዛሙርትም እንዲቀበሉት ደብዳቤ ጻፉለት። እዚያም በደረሰ ጊዜ ከጸጋው የተነሣ አምነው ለነበሩት ትልቅ ረዳት ሆናቸው፤”
ሐዋርያት 18፥27 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አጵሎስ ወደ አካይያ ለመሄድ በፈለገ ጊዜ፣ ወንድሞች አበረታቱት፤ በዚያ የነበሩት ደቀ መዛሙርትም እንዲቀበሉት ደብዳቤ ጻፉለት። እዚያም በደረሰ ጊዜ ከጸጋው የተነሣ አምነው ለነበሩት ትልቅ ረዳት ሆናቸው፤”
ሐዋርያት 18፥27 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3
ከሚከተሉት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ጥቅስ የጠቀሰው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
28%
ሀ. የዮሐንስ ራእይ
56%
ለ. የዮሐንስ ወንጌል
8%
ሐ. ፊልጵስዩስ
9%
መ. ቆላስይስ
👍8
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤”
1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤”
1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥18
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ደብረ_ዘይት፤ የወይራ ዛፍ ያለበት ተራራ ማለት ነው። ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ ይገኛል። በደብረ ዘይትና በኢየሩሳሌም መካከል የቄድሮን ሸለቆ ይገኛል። ከቤተ መቅደስ አደባባይ ደብረ ዘይት ሰባ አምስት ሜትር ገደማ ከፍ ይላል። ዳዊት ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ ወደ ደብረ ዘይት ዐቀበት ወጣ፤ 2ሳሙ. 15፥30። ቤተ ፋጌና ቢታንያ ከደብረ ዘይት ተራራ ግርጌ ናቸው፤
👉ኢየሱስ በሆሳዕና ዕለት ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፤ ማር. 11፥1።
👉ኢየሱስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ስለ ኢየሩሳሌም መፍረስና ስለ ዓለም መጨረሻ አስተማረ፤ ማር. 13፥3።
👉ኢየሱስ ከደብረ ዘይት ግርጌ ባለው በጌቴሴማኒ በአይሁድ ጭፍሮች ተያዘ፤ ማቴ. 26፥30:36።
👉 ኢየሱስ ከደብረ ዘይት ወደ ሰማይ ዐረገ (ሉቃ. 24፥51:52፤ ሐ.ሥ. 1፥12)፤
👉እንደገናም በዓለም ፍጻሜ በደብረ ዘይት ይወርዳል የሚል ትንቢት ተነግሯል፤ ዘካ. 14፥4።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 228
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ደብረ_ዘይት፤ የወይራ ዛፍ ያለበት ተራራ ማለት ነው። ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ ይገኛል። በደብረ ዘይትና በኢየሩሳሌም መካከል የቄድሮን ሸለቆ ይገኛል። ከቤተ መቅደስ አደባባይ ደብረ ዘይት ሰባ አምስት ሜትር ገደማ ከፍ ይላል። ዳዊት ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ ወደ ደብረ ዘይት ዐቀበት ወጣ፤ 2ሳሙ. 15፥30። ቤተ ፋጌና ቢታንያ ከደብረ ዘይት ተራራ ግርጌ ናቸው፤
👉ኢየሱስ በሆሳዕና ዕለት ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፤ ማር. 11፥1።
👉ኢየሱስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ስለ ኢየሩሳሌም መፍረስና ስለ ዓለም መጨረሻ አስተማረ፤ ማር. 13፥3።
👉ኢየሱስ ከደብረ ዘይት ግርጌ ባለው በጌቴሴማኒ በአይሁድ ጭፍሮች ተያዘ፤ ማቴ. 26፥30:36።
👉 ኢየሱስ ከደብረ ዘይት ወደ ሰማይ ዐረገ (ሉቃ. 24፥51:52፤ ሐ.ሥ. 1፥12)፤
👉እንደገናም በዓለም ፍጻሜ በደብረ ዘይት ይወርዳል የሚል ትንቢት ተነግሯል፤ ዘካ. 14፥4።
ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 228
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሎጥ ከተለየው በኋላም እግዚአብሔር አብራምን አለው፦ ዓይንህን አንሣና አንተ ካለህበት ስፍራ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ እይ፤”
ዘፍጥረት 13፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሎጥ ከተለየው በኋላም እግዚአብሔር አብራምን አለው፦ ዓይንህን አንሣና አንተ ካለህበት ስፍራ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ እይ፤”
ዘፍጥረት 13፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
#እራሳችንን_እንመርምር
የእግዚአብሔር ፈቃድ ሕይወታችንን እንዲቆጣጠረው እና በብርሃኑ መውጣት እና መግባት እንፈልጋለን? የእግዚአብሔርስ አፍ መሆንስ? ስለዚህ ምን ላድርግ?
“ስለ ሌዊም እንዲህ አለ፦ ቱሚምህና ኡሪምህ ለቅዱስህ ሰው ነው፥ በማሳህ ለፈተንኸው፥ በመሪባ ውኃም ለተከራከርኸው፤”
ዘዳግም 33፥8
“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ብትመለስ እመልስሃለሁ በፊቴም ትቆማለህ፤ የከበረውንም ከተዋረደው ብትለይ እንደ አፌ ትሆናለህ፤ እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ፥ አንተ ግን ወደ እነርሱ አትመለስም።”
ኤርምያስ 15፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የእግዚአብሔር ፈቃድ ሕይወታችንን እንዲቆጣጠረው እና በብርሃኑ መውጣት እና መግባት እንፈልጋለን? የእግዚአብሔርስ አፍ መሆንስ? ስለዚህ ምን ላድርግ?
“ስለ ሌዊም እንዲህ አለ፦ ቱሚምህና ኡሪምህ ለቅዱስህ ሰው ነው፥ በማሳህ ለፈተንኸው፥ በመሪባ ውኃም ለተከራከርኸው፤”
ዘዳግም 33፥8
“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ብትመለስ እመልስሃለሁ በፊቴም ትቆማለህ፤ የከበረውንም ከተዋረደው ብትለይ እንደ አፌ ትሆናለህ፤ እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ፥ አንተ ግን ወደ እነርሱ አትመለስም።”
ኤርምያስ 15፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1