ቅዱሳት መጻሕፍት
፺፭ቱ_የማርቲን_ሉተር_የመከራከሪያ_ነጥቦች.pdf
1517 ኦክቶበር 31 ልክ በዛሬው ቀን፣ ማርቲን ሉተር 95 መከራከሪያ ነጥቦችን ለጠፈ። ነጥቦቹ ምንድን ናቸው? መጽሐፍ ቅዱሳዊ ናቸው ወይስ ሌላ? ተወያዩበት፤ እንወያይበትም።
👍4❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
ዕብራውያን 10፥38
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
ዕብራውያን 10፥38
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1👏1
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች፣ #መጻሕፍትን_እንመርምር በሚል ርዕስ በሚቀርበው ዝግጅት ሊነሱ ወይም ሊብራሩ ይገባል የምትሉትን መጻሕፍ ቅዱሳዊ አሳብ ወይም ጥያቄ ካላችሁ በነጻነት እንድታቀርቡ ትበረታታላችሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍2👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም አሉት፦ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንዳለ በእርግጥ አየን፤ ስለዚህም፦ በእኛና በአንተ መካከል መሐላ ይሁን እኛ አንተን እንዳልነካንህ፥ በጎነትንም ብቻ እንዳሳየንህ፥ በደኅናም እንደ ሰደድንህ፥ አንተም ክፉ እንዳትሠራብን ቃል ኪዳን ከአንተ ጋር እናድርግ አልን አንተ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረክህ ነህ።”
ዘፍጥረት 26፥28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም አሉት፦ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንዳለ በእርግጥ አየን፤ ስለዚህም፦ በእኛና በአንተ መካከል መሐላ ይሁን እኛ አንተን እንዳልነካንህ፥ በጎነትንም ብቻ እንዳሳየንህ፥ በደኅናም እንደ ሰደድንህ፥ አንተም ክፉ እንዳትሠራብን ቃል ኪዳን ከአንተ ጋር እናድርግ አልን አንተ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረክህ ነህ።”
ዘፍጥረት 26፥28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3🥰2👍1
የ12ቱ ደቀ መዛሙርት(ሐዋርያት) አጭር ታሪክ
፩. ጴጥሮስ(ስሞኦን)
በመጀመሪያ ስሞኦን ተባለ በኋላ ኢየሱስ ኬፋ አለው። በአረማይክ ኬፋ በግሪክ ጴጥሮስ ሁለቱም አለት ማለት ነው። የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ነበር። ጴጥሮስ እንደ አይሁድ ሊቃውንት የተማረ አልነበረም። ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በቅፍርናሆም አሳ በማጥመድ ይኖር ነበር። ሚስት ነበረችው(ማር። ፩፡፳፱-፴)። ጴጥሮስን በመጀመሪያ ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀው እንድርያስ ነበር(ዮሐ. ፩፡፵፩-፵፫)። ይህ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለኢየሱስ በተለየ ሁኔታ ቅርብ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከወረደም በኋላ መሪ ሆኖም አገልግሏል።በተጨማሪም ጴጥሮስ ሁለት መልእክቶችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። አሟሟቱም በመጽሐፍ ቅዱስም ባይጻፍም በመስቀል ተዘቅዝቆ እንደ ሞተ የቤ.ክ ታሪክ ይናገራል።
፪. ዮሐንስ
የያዕቆብ ወንድም የዘብዴዎስ ልጅ ነው እናቱም ሰሎሜ ሳትሆን አትቀርም ይባላል። ዮሐንስ ማለት የስሙ ትርጉም እግዚኣብሔር ጸጋ ነው ማለት ሲሆን ወላጆቹ ሃብታሞች ነበሩ። የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይገመታል(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፪)። ከወንድሙና ከአባቱ ጋር አሳ እያጠመዱ ሳሉ ኢየሱስ ወንድሙንና እርሱን ጠራው። ሁለቱም ወንድማማቾች ሃይለኞች ስለነበሩ ኢየሱስ "ቦአኔርጌስ" ብሎ ጠርቷቸዋል። ትርጉሙም የነገድጓድ ልጆች ማለት ነው።ዮሐንስ አንድ ወንጌል ሶስት መልእክቶችን እና ራእይን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። በተጨማሪም ዮሐንስ እራሱን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር በማለት ይገልጻል። በመጨረሻም ከኤፌሶን ተሰዶ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ኖረ(ራእ. ፩፡፱)።
፫. ያዕቆብ
የዘብዴዎስ ልጅ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም ነው። የስሙ ትርጉም ተረከዝን ይይዛል ማለት ነው። ከደቀ መዛሙርት መካከል ቀድሞ የሞተው እርሱ ሲሆን ሄሮድስ በሰይፍ አስገደለው።
፬. ያዕቆብ(የእልፍዮስ ልጅ)
አንዳንድ ጊዜ ታናሹ ያእቆብ ይባላል።
፭. የአስቆሮቱ ይሁዳ
ይሁዳ ማለት ማመስገን ሲሆን አስቆሮት ማለት እርሱ የመጣበትን አካባቢ/መንደር ይገልጻል። አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባለው መንደር ይሆናል(ኢያ. ፲፭፡፳፭)። ከዚህ በመነሳት ይሁዳ ከተማ ቀመስ ሰው እንደሆን እንገምታለን። ገንዘብ ያዥ ሆኖ ሳለ ሌባ እንደሆን ወንጌላት ይናገራሉ። በመጨረሻም ሰይጣን ገብቶበት ኢየሱስን ጌታውን ሽጦ በገንዘቡ ሳይጠቀም ታንቆ ሞቷል።
፮. ይሁዳ(የያዕቆብ ልጅ)
ይህኛው ይሁዳ ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ ሳይሆን አይቀርም(ማቴ. ፲፡፫)።
፯. ማቴዎስ
የእልፍዮስ ልጅ ሲሆን ቀራጭና የቅፍርናሆም ነዋሪ ነበር። ማቴዎስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማቴዎስ ወንጌልን የጻፈ ሲሆን ሉቃስና ማርቆስ በቤተሰቡ ስም ሌዊ እያሉ የሚጠሩት ሲሆን እርሱ እራሱን ደግሞ ቀራጭ እያለ ይጠራ ነበር።
፰. ፊሊጶስ
የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን ናትናኤልን ወደ ኢየሱስ ያመጣ ደቀ መዝሙር ነበር።
፱. እንድርያስ
የጴጥሮስ ወንድም ሲሆን ከእርሱ ጋር ሆኖ አሳ ሲያጠምድ ኢየሱስ ጠራቸው። እንድርያስ የዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሲሆን ኢየሱስን እንዲከተል ከነገረው በኋላ ኢየሱስ ቤት ውሏል። ጴጥሮስንም ወደ ኢየሱስ ጠራው(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፮)። መጥምቁ ዮሐንስ የሚዜነቱን ስራ በሚገባ እንደተወጣ የእንድርያስ ሕይወት በሚገባ ያሳያል። እንድርያስም ሰውን ወደ ጌታ በማምጣት ይታወቅ ነበር።
፲. ቶማስ
ቶማስ በአረማይክ ዲዲሞስ በግሪክ ሁለቱም ትርጉማቸው መንታ ማለት ነው። ብዙዎች በተጠራጣሪነቱ ቢያውቁትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ስለኢየሱስ ሰብኳል። እንዲያውም የቤ.ክ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ቶማስ በሕንድና በፋርስ ወንጌል እንዳስተማረ ይነገራል።
፲፩. በርተሎሜዎስ
በርተሎሜዎስ ማለት የተሎሜዎስ ልጅ ማለት ነው። ምናልባት በርተሎሜዎስ የተባለው ናትናኤል ሳይሆን አይቀርም።
፲፪. ቀናተኛው ስምኦን
አንዳንዶቹ ናትናኤል ነው ይሉታል።
ምንጭ:- የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
፩. ጴጥሮስ(ስሞኦን)
በመጀመሪያ ስሞኦን ተባለ በኋላ ኢየሱስ ኬፋ አለው። በአረማይክ ኬፋ በግሪክ ጴጥሮስ ሁለቱም አለት ማለት ነው። የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ነበር። ጴጥሮስ እንደ አይሁድ ሊቃውንት የተማረ አልነበረም። ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በቅፍርናሆም አሳ በማጥመድ ይኖር ነበር። ሚስት ነበረችው(ማር። ፩፡፳፱-፴)። ጴጥሮስን በመጀመሪያ ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀው እንድርያስ ነበር(ዮሐ. ፩፡፵፩-፵፫)። ይህ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለኢየሱስ በተለየ ሁኔታ ቅርብ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከወረደም በኋላ መሪ ሆኖም አገልግሏል።በተጨማሪም ጴጥሮስ ሁለት መልእክቶችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። አሟሟቱም በመጽሐፍ ቅዱስም ባይጻፍም በመስቀል ተዘቅዝቆ እንደ ሞተ የቤ.ክ ታሪክ ይናገራል።
፪. ዮሐንስ
የያዕቆብ ወንድም የዘብዴዎስ ልጅ ነው እናቱም ሰሎሜ ሳትሆን አትቀርም ይባላል። ዮሐንስ ማለት የስሙ ትርጉም እግዚኣብሔር ጸጋ ነው ማለት ሲሆን ወላጆቹ ሃብታሞች ነበሩ። የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይገመታል(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፪)። ከወንድሙና ከአባቱ ጋር አሳ እያጠመዱ ሳሉ ኢየሱስ ወንድሙንና እርሱን ጠራው። ሁለቱም ወንድማማቾች ሃይለኞች ስለነበሩ ኢየሱስ "ቦአኔርጌስ" ብሎ ጠርቷቸዋል። ትርጉሙም የነገድጓድ ልጆች ማለት ነው።ዮሐንስ አንድ ወንጌል ሶስት መልእክቶችን እና ራእይን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። በተጨማሪም ዮሐንስ እራሱን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር በማለት ይገልጻል። በመጨረሻም ከኤፌሶን ተሰዶ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ኖረ(ራእ. ፩፡፱)።
፫. ያዕቆብ
የዘብዴዎስ ልጅ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም ነው። የስሙ ትርጉም ተረከዝን ይይዛል ማለት ነው። ከደቀ መዛሙርት መካከል ቀድሞ የሞተው እርሱ ሲሆን ሄሮድስ በሰይፍ አስገደለው።
፬. ያዕቆብ(የእልፍዮስ ልጅ)
አንዳንድ ጊዜ ታናሹ ያእቆብ ይባላል።
፭. የአስቆሮቱ ይሁዳ
ይሁዳ ማለት ማመስገን ሲሆን አስቆሮት ማለት እርሱ የመጣበትን አካባቢ/መንደር ይገልጻል። አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባለው መንደር ይሆናል(ኢያ. ፲፭፡፳፭)። ከዚህ በመነሳት ይሁዳ ከተማ ቀመስ ሰው እንደሆን እንገምታለን። ገንዘብ ያዥ ሆኖ ሳለ ሌባ እንደሆን ወንጌላት ይናገራሉ። በመጨረሻም ሰይጣን ገብቶበት ኢየሱስን ጌታውን ሽጦ በገንዘቡ ሳይጠቀም ታንቆ ሞቷል።
፮. ይሁዳ(የያዕቆብ ልጅ)
ይህኛው ይሁዳ ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ ሳይሆን አይቀርም(ማቴ. ፲፡፫)።
፯. ማቴዎስ
የእልፍዮስ ልጅ ሲሆን ቀራጭና የቅፍርናሆም ነዋሪ ነበር። ማቴዎስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማቴዎስ ወንጌልን የጻፈ ሲሆን ሉቃስና ማርቆስ በቤተሰቡ ስም ሌዊ እያሉ የሚጠሩት ሲሆን እርሱ እራሱን ደግሞ ቀራጭ እያለ ይጠራ ነበር።
፰. ፊሊጶስ
የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን ናትናኤልን ወደ ኢየሱስ ያመጣ ደቀ መዝሙር ነበር።
፱. እንድርያስ
የጴጥሮስ ወንድም ሲሆን ከእርሱ ጋር ሆኖ አሳ ሲያጠምድ ኢየሱስ ጠራቸው። እንድርያስ የዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሲሆን ኢየሱስን እንዲከተል ከነገረው በኋላ ኢየሱስ ቤት ውሏል። ጴጥሮስንም ወደ ኢየሱስ ጠራው(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፮)። መጥምቁ ዮሐንስ የሚዜነቱን ስራ በሚገባ እንደተወጣ የእንድርያስ ሕይወት በሚገባ ያሳያል። እንድርያስም ሰውን ወደ ጌታ በማምጣት ይታወቅ ነበር።
፲. ቶማስ
ቶማስ በአረማይክ ዲዲሞስ በግሪክ ሁለቱም ትርጉማቸው መንታ ማለት ነው። ብዙዎች በተጠራጣሪነቱ ቢያውቁትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ስለኢየሱስ ሰብኳል። እንዲያውም የቤ.ክ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ቶማስ በሕንድና በፋርስ ወንጌል እንዳስተማረ ይነገራል።
፲፩. በርተሎሜዎስ
በርተሎሜዎስ ማለት የተሎሜዎስ ልጅ ማለት ነው። ምናልባት በርተሎሜዎስ የተባለው ናትናኤል ሳይሆን አይቀርም።
፲፪. ቀናተኛው ስምኦን
አንዳንዶቹ ናትናኤል ነው ይሉታል።
ምንጭ:- የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤3👏2🔥1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልቡም በፊትህ የታመነ ሆኖ አገኘኸው፤ የከነዓናዊውንና የኬጢያዊውን የአሞራዊውንም የፌርዛዊውንም የኢያቡሳዊውንም የጌርጌሳዊውንም ምድር ለእርሱና ለዘሩ ትሰጥ ዘንድ ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን አደረግህ፤ አንተም ጻድቅ ነህና ቃልህን ፈጸምህ።”
ነህምያ 9፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልቡም በፊትህ የታመነ ሆኖ አገኘኸው፤ የከነዓናዊውንና የኬጢያዊውን የአሞራዊውንም የፌርዛዊውንም የኢያቡሳዊውንም የጌርጌሳዊውንም ምድር ለእርሱና ለዘሩ ትሰጥ ዘንድ ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን አደረግህ፤ አንተም ጻድቅ ነህና ቃልህን ፈጸምህ።”
ነህምያ 9፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2🔥2👍1👏1
💠የእግዚአብሔርን ፀጋ የምንጥልባቸው አራቱ መንገዶች
እኛን ያቆመን የእግዚአብሔር ፀጋ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ፀጋ ውጭ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡
"ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።" (1ኛ ቆሮ.15፡10)
የእግዚአብሔርን ፀጋ ስንጥል ማደግ እናቆማለን፡፡ የእግዚአብሔርን ፀጋ ከጣልን መውደቃችን አይቀሬ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ፀጋ የምናጣበት ሃይል አልባ የሚያደርጉን አራቱ መንገዶች
1. ትህትናን መጣል
ሰው ትህትናን ከጣለ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚወድቅ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ሰው እግዚአብሔር ከሰጠው ደረጃ በላይ ራሱን ከፍ አድርጎ ሲያይ ከእግዚአብሔር ጋር ይተላለፋል፡፡ እግዚአብሔር ፀጋን መስጠትና ማንሳት ከፍ ማድረግ እየፈለገ በራሱ ነገሮችን ማድረግ እንደሚችል የሚያስበውን ትእቢተኛን ሰው ግን ከመቃወም ውጭ ምንም ሊያደርገው አይችልም፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣልይላል።" (ያዕ. 4፡6)
2. እውቀትን መጣል
ሰው ከመሬት ተነስቶ አውቆ የጨረሰ ከመሰለው በህይወቱ ማደግና መለወጥ አቁሟል ማለት ነው፡፡ ይህ ሰው ለአዲስ ተግዳሮት በእውቀት ራሱን ካላስታጠቀ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህ ሰው ያወቀና የጨረሰ ከመሰለው እጅግ አሰቃቂ ነው፡፡
"ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል። ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤" (1ኛ ቆሮ. 8፡1-2)
"ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤" (ሆሴ. 4፡6)
"በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።"( 2ኛ ጴጥ. 1፡2)
3. እምነትን መጣል
ሰው በእግዚአብሔር ላይ መደገፍን ትቶ በራሱ ስራ ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው ለመዳንም ሆነ ከዳነ በኋላ ለመቀደስ ፣ ለእግዚአብሔር መንግስት ለመስራትና እግዚአብሔርን ለማስደሰት በራሱ ጉልበትና ቅልጥፍና ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡
"በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።" (ገላ. 5፡4)
"ነገር ግን፦ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።" (1ኛ ቆሮ.1፡30-31)
4. ምስጋናን መጣል
ሰው ምንም ከማይወጣለት መልካም አምላክ ጋር እየኖረ ካጉረመረመና ማመስገን ካቃተው ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ላይ አቃቂር ማውጣት ከቻለ የሆነ የሳተው ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር በላይ የሚያውቅ ከመሰለው የሆነ የተዛባ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ካልታመነ ከእግዚአብሔር ጋር በየዋህነት መኖር ፣ ራሱን መስጠት ፣ ለእግዚአብሔር በየዋህነት መስራትና ፍሬያማ መሆን ያቅተዋል፡፡
"አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።"(ማቴ. 25፡24-25)
"ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደጠፉ አታንጐርጕሩ።" (1ኛ ቆሮ. 10፡10)
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እኛን ያቆመን የእግዚአብሔር ፀጋ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ፀጋ ውጭ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡
"ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።" (1ኛ ቆሮ.15፡10)
የእግዚአብሔርን ፀጋ ስንጥል ማደግ እናቆማለን፡፡ የእግዚአብሔርን ፀጋ ከጣልን መውደቃችን አይቀሬ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ፀጋ የምናጣበት ሃይል አልባ የሚያደርጉን አራቱ መንገዶች
1. ትህትናን መጣል
ሰው ትህትናን ከጣለ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚወድቅ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ሰው እግዚአብሔር ከሰጠው ደረጃ በላይ ራሱን ከፍ አድርጎ ሲያይ ከእግዚአብሔር ጋር ይተላለፋል፡፡ እግዚአብሔር ፀጋን መስጠትና ማንሳት ከፍ ማድረግ እየፈለገ በራሱ ነገሮችን ማድረግ እንደሚችል የሚያስበውን ትእቢተኛን ሰው ግን ከመቃወም ውጭ ምንም ሊያደርገው አይችልም፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣልይላል።" (ያዕ. 4፡6)
2. እውቀትን መጣል
ሰው ከመሬት ተነስቶ አውቆ የጨረሰ ከመሰለው በህይወቱ ማደግና መለወጥ አቁሟል ማለት ነው፡፡ ይህ ሰው ለአዲስ ተግዳሮት በእውቀት ራሱን ካላስታጠቀ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህ ሰው ያወቀና የጨረሰ ከመሰለው እጅግ አሰቃቂ ነው፡፡
"ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል። ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤" (1ኛ ቆሮ. 8፡1-2)
"ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤" (ሆሴ. 4፡6)
"በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።"( 2ኛ ጴጥ. 1፡2)
3. እምነትን መጣል
ሰው በእግዚአብሔር ላይ መደገፍን ትቶ በራሱ ስራ ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው ለመዳንም ሆነ ከዳነ በኋላ ለመቀደስ ፣ ለእግዚአብሔር መንግስት ለመስራትና እግዚአብሔርን ለማስደሰት በራሱ ጉልበትና ቅልጥፍና ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡
"በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።" (ገላ. 5፡4)
"ነገር ግን፦ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።" (1ኛ ቆሮ.1፡30-31)
4. ምስጋናን መጣል
ሰው ምንም ከማይወጣለት መልካም አምላክ ጋር እየኖረ ካጉረመረመና ማመስገን ካቃተው ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ላይ አቃቂር ማውጣት ከቻለ የሆነ የሳተው ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር በላይ የሚያውቅ ከመሰለው የሆነ የተዛባ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ካልታመነ ከእግዚአብሔር ጋር በየዋህነት መኖር ፣ ራሱን መስጠት ፣ ለእግዚአብሔር በየዋህነት መስራትና ፍሬያማ መሆን ያቅተዋል፡፡
"አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።"(ማቴ. 25፡24-25)
"ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደጠፉ አታንጐርጕሩ።" (1ኛ ቆሮ. 10፡10)
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
ኤፌሶን 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
ኤፌሶን 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍1🔥1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥12-17
ልጅነት፣ የልጅነት መብት በመስጠት ቤተሰብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህም በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተለያዩ አራት ቦታዎች ተጠቅሶአል (ቍ 23፤ 9፥4፣ ገላ 4፥5፤ ኤፌ 1፥5 )፡፡ ከአብራክ ያልተገኘን ልጅ እንደ ራስ ልጅ አድርጎ ማሳደግና ሀብት የመውረስ መብቱ እንዲጠበቅለት ማድረግ፣ በግሪኮችና በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ነበር። ክርስቲያኖችም የልጅነትን መብት ያገኙት በጸጋ ነው:: ክርስቶስ ግን የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ነው:: አባ አባት ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ልዩ የሆነ ኅብረት ያመለክታል፡፡
መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅነታችንን ያረጋግጥልናል። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ከሆነ ለእግዚአብሔር ልጅነታችን ምንም ዓይነት ጥርጣሬ ሊኖረን አይገባም (ገላ. 4፥67፤ 1ዮሐ 3÷1)።
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚለው፤ መንፈስ ራሱ፥ እርሱም መንፈስ ቅዱስ ከእኛ መንፈስ ማለትም ከራሳችን ሰብአዊ መንፈስ ጋር በመሆን ይመሰክራል። ሰብአዊ መንፈስ ምንድን ነው? ሰብአዊ መንፈስ የሰው መንፈሳዊ ክፍል ነው። በክርስቶስ በምናምንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሕይወት የሚሰጠው የእኛነታችን ክፍል ነው። አንዳንድ ሰዎች ሰብአዊ መንፈስ ማለት የሰው ውስጣዊ ሕያውነት ወይም ኅሊና ነው ይላሉ (ሮሜ 7፥22)። ሰው በሦስት ክፍል ይመደባል፥ መንፈስ፥ ነፍስና ሥጋ (1ተሰ. 5፥23)። በሰብአዊ መንፈሳችን በኩል የእግዚአብሔርን መኖርና የመንፈስ ቅዱስን በረከት በሕይወታችን እንረዳለን።
ልጆች ከሆንን ወራሾችም ነን በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ ወደፊት በመንግሥተ ሰማይ ለሚኖረን ውርስ መያዣ ወይም ዋስትናችን ነው (2ቆሮ. 5፥5፤ ኤፌ. 1፥13–14)።
ጳውሎስ ግን እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ማስታወሻ ይሰጠናል። ከክርስቶስ ጋር አብረን የምንወርስ ስለሆነን፤ የሕይወቱ ወይም የክብሩ ተካፋዮች ብቻ ሳንሆን፥ የመከራውም ተካፋዮች ነን። የመከራው ተካፋዮች መሆን የማንፈልግ ከሆነ የክብሩም ተካፋዮች መሆን ከቶ አንችልም (2ጢሞ. 2፥11-12፤ 3፥12፤ 1ጴጥ. 4፥1214)።
ክርስቲያኖች ሁለት ዓይነት መስቀል አላቸው።
1. አንደኛው መስቀል አሮጌው ሰውነታችን የተሰቀለበት መስቀል ሲሆን (ሮሜ 6፥6)፤
2. ሁለተኛው መስቀል ክርስቶስን በመከተል ምክንያት የሚመጣብን መከራና ስደት ነው።
የመጀመሪያውን መስቀል ክርስቶስ ራሱ ተሸክሞልናል፤ ሁለተኛውን መስቀል ለእርሱ ስንል እኛ መሸከም አለብን። ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ለመሆንና አብረነው ለመንገሥ የምንፈልግ ከሆነ፥ ይህን ሁለተኛውን መስቀል መሸከም ይኖርብናል (ማር. 8፥34)።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 368፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥12-17
ልጅነት፣ የልጅነት መብት በመስጠት ቤተሰብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህም በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተለያዩ አራት ቦታዎች ተጠቅሶአል (ቍ 23፤ 9፥4፣ ገላ 4፥5፤ ኤፌ 1፥5 )፡፡ ከአብራክ ያልተገኘን ልጅ እንደ ራስ ልጅ አድርጎ ማሳደግና ሀብት የመውረስ መብቱ እንዲጠበቅለት ማድረግ፣ በግሪኮችና በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ነበር። ክርስቲያኖችም የልጅነትን መብት ያገኙት በጸጋ ነው:: ክርስቶስ ግን የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ነው:: አባ አባት ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ልዩ የሆነ ኅብረት ያመለክታል፡፡
መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅነታችንን ያረጋግጥልናል። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ከሆነ ለእግዚአብሔር ልጅነታችን ምንም ዓይነት ጥርጣሬ ሊኖረን አይገባም (ገላ. 4፥67፤ 1ዮሐ 3÷1)።
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚለው፤ መንፈስ ራሱ፥ እርሱም መንፈስ ቅዱስ ከእኛ መንፈስ ማለትም ከራሳችን ሰብአዊ መንፈስ ጋር በመሆን ይመሰክራል። ሰብአዊ መንፈስ ምንድን ነው? ሰብአዊ መንፈስ የሰው መንፈሳዊ ክፍል ነው። በክርስቶስ በምናምንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሕይወት የሚሰጠው የእኛነታችን ክፍል ነው። አንዳንድ ሰዎች ሰብአዊ መንፈስ ማለት የሰው ውስጣዊ ሕያውነት ወይም ኅሊና ነው ይላሉ (ሮሜ 7፥22)። ሰው በሦስት ክፍል ይመደባል፥ መንፈስ፥ ነፍስና ሥጋ (1ተሰ. 5፥23)። በሰብአዊ መንፈሳችን በኩል የእግዚአብሔርን መኖርና የመንፈስ ቅዱስን በረከት በሕይወታችን እንረዳለን።
ልጆች ከሆንን ወራሾችም ነን በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ ወደፊት በመንግሥተ ሰማይ ለሚኖረን ውርስ መያዣ ወይም ዋስትናችን ነው (2ቆሮ. 5፥5፤ ኤፌ. 1፥13–14)።
ጳውሎስ ግን እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ማስታወሻ ይሰጠናል። ከክርስቶስ ጋር አብረን የምንወርስ ስለሆነን፤ የሕይወቱ ወይም የክብሩ ተካፋዮች ብቻ ሳንሆን፥ የመከራውም ተካፋዮች ነን። የመከራው ተካፋዮች መሆን የማንፈልግ ከሆነ የክብሩም ተካፋዮች መሆን ከቶ አንችልም (2ጢሞ. 2፥11-12፤ 3፥12፤ 1ጴጥ. 4፥1214)።
ክርስቲያኖች ሁለት ዓይነት መስቀል አላቸው።
1. አንደኛው መስቀል አሮጌው ሰውነታችን የተሰቀለበት መስቀል ሲሆን (ሮሜ 6፥6)፤
2. ሁለተኛው መስቀል ክርስቶስን በመከተል ምክንያት የሚመጣብን መከራና ስደት ነው።
የመጀመሪያውን መስቀል ክርስቶስ ራሱ ተሸክሞልናል፤ ሁለተኛውን መስቀል ለእርሱ ስንል እኛ መሸከም አለብን። ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ለመሆንና አብረነው ለመንገሥ የምንፈልግ ከሆነ፥ ይህን ሁለተኛውን መስቀል መሸከም ይኖርብናል (ማር. 8፥34)።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 368፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2🔥1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ካወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ አማካይነት ለተቀደሱት፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።”
1ኛ ጴጥሮስ 1፥2 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ካወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ አማካይነት ለተቀደሱት፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።”
1ኛ ጴጥሮስ 1፥2 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1🥰1👏1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መዝሙር 115
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ለእኛ አይደለም፥ አቤቱ፥ ለእኛ አይደለም፥ ነገር ግን ለስምህ ስለ ምሕረትህ ስለ እውነትህም ምስጋናን ስጥ።
² አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? አይበሉ።
³ አምላካችንስ በላይ በሰማይ ነው፤ በሰማይም በምድርም የፈቀደውን ሁሉ አደረገ።
⁴ የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው።
⁵ አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤
⁶ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤
⁷ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም።
⁸ የሚሠሩአቸውም የሚያምኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።
⁹ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው።
¹⁰ የአሮን ቤት ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው።
¹¹ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው።
¹² እግዚአብሔር አሰበን ይባርከንማል፤ የእስራኤልን ቤት ይባረካል፥ የአሮንንም ቤት ይባረካል።
¹³ እግዚአብሔርን የሚፈሩትን፥ ትንንሾችንና ትልልቆችን ይባርካል።
¹⁴ እግዚአብሔር በላያችሁ፥ በላያችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይጨምር።
¹⁵ እናንተ ሰማይንና ምድርን ለሠራ ለእግዚአብሔር የተባረካችሁ ናችሁ።
¹⁶ የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።
¹⁷ አቤቱ፥ ሙታን የሚያመሰግኑህ አይደሉም፥ ወደ ሲኦልም የሚወርዱ ሁሉ፤
¹⁸ እኛ ሕያዋን ግን ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔርን እንባርካለን። ሃሌ ሉያ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
መዝሙር 115
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ለእኛ አይደለም፥ አቤቱ፥ ለእኛ አይደለም፥ ነገር ግን ለስምህ ስለ ምሕረትህ ስለ እውነትህም ምስጋናን ስጥ።
² አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? አይበሉ።
³ አምላካችንስ በላይ በሰማይ ነው፤ በሰማይም በምድርም የፈቀደውን ሁሉ አደረገ።
⁴ የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው።
⁵ አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤
⁶ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤
⁷ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም።
⁸ የሚሠሩአቸውም የሚያምኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።
⁹ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው።
¹⁰ የአሮን ቤት ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው።
¹¹ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው።
¹² እግዚአብሔር አሰበን ይባርከንማል፤ የእስራኤልን ቤት ይባረካል፥ የአሮንንም ቤት ይባረካል።
¹³ እግዚአብሔርን የሚፈሩትን፥ ትንንሾችንና ትልልቆችን ይባርካል።
¹⁴ እግዚአብሔር በላያችሁ፥ በላያችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይጨምር።
¹⁵ እናንተ ሰማይንና ምድርን ለሠራ ለእግዚአብሔር የተባረካችሁ ናችሁ።
¹⁶ የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።
¹⁷ አቤቱ፥ ሙታን የሚያመሰግኑህ አይደሉም፥ ወደ ሲኦልም የሚወርዱ ሁሉ፤
¹⁸ እኛ ሕያዋን ግን ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔርን እንባርካለን። ሃሌ ሉያ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2👏2🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የእግዚአብሔር ማኅበር እረኛ እንደሌለው መንጋ እንዳይሆን፥ በፊታቸው የሚወጣውን በፊታቸውም የሚገባውን የሚያስወጣቸውንም የሚያስገባቸውንም ሰው የሥጋ ሁሉ መንፈስ አምላክ እግዚአብሔር በማኅበሩ ላይ ይሹመው።”
ዘኍልቁ 27፥16-17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የእግዚአብሔር ማኅበር እረኛ እንደሌለው መንጋ እንዳይሆን፥ በፊታቸው የሚወጣውን በፊታቸውም የሚገባውን የሚያስወጣቸውንም የሚያስገባቸውንም ሰው የሥጋ ሁሉ መንፈስ አምላክ እግዚአብሔር በማኅበሩ ላይ ይሹመው።”
ዘኍልቁ 27፥16-17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1👏1
#እራሳችንን_እንመርምር
ከእግዚአብሔር ጋር እየዋልን ነው። እርሱንም በሚገባ እየፈለግነው ነው። ከእርሱ ጋር መሆን መልካም ነው። የነፍሳችንም መሻት ይህ ነው። እያልን ነገር ግን ከእግዚአብሔር ጋር ተላልፈን ይሆን? ከእግዚአብሔር ጋር ከመተላለፍ እግዚአብሔር ይጠብቀን🙏
"ነገር ግን ዕለት ዕለት ይሹኛል መንገዴንም ያውቁ ዘንድ ይወድዳሉ፤ ጽድቅን እንዳደረጉ የአምላካቸውንም ፍርድ እንዳልተዉ ሕዝብ እውነተኛውን ፍርድ ይለምኑኛል፥ ወደ እግዚአብሔርም ለመቅረብ ይወድዳሉ። ስለ ምን ጾምን፥ አንተም አልተመለከትኸንም? ሰውነታችንንስ ስለ ምን አዋረድን፥ አንተም አላወቅህም? ይላሉ። እነሆ፥ በጾማችሁ ቀን ፈቃዳችሁን ታደርጋላችሁ፥ ሠራተኞቻችሁንም ሁሉ ታስጨንቃላችሁ።
ኢሳይያስ 58፥2-3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከእግዚአብሔር ጋር እየዋልን ነው። እርሱንም በሚገባ እየፈለግነው ነው። ከእርሱ ጋር መሆን መልካም ነው። የነፍሳችንም መሻት ይህ ነው። እያልን ነገር ግን ከእግዚአብሔር ጋር ተላልፈን ይሆን? ከእግዚአብሔር ጋር ከመተላለፍ እግዚአብሔር ይጠብቀን🙏
"ነገር ግን ዕለት ዕለት ይሹኛል መንገዴንም ያውቁ ዘንድ ይወድዳሉ፤ ጽድቅን እንዳደረጉ የአምላካቸውንም ፍርድ እንዳልተዉ ሕዝብ እውነተኛውን ፍርድ ይለምኑኛል፥ ወደ እግዚአብሔርም ለመቅረብ ይወድዳሉ። ስለ ምን ጾምን፥ አንተም አልተመለከትኸንም? ሰውነታችንንስ ስለ ምን አዋረድን፥ አንተም አላወቅህም? ይላሉ። እነሆ፥ በጾማችሁ ቀን ፈቃዳችሁን ታደርጋላችሁ፥ ሠራተኞቻችሁንም ሁሉ ታስጨንቃላችሁ።
ኢሳይያስ 58፥2-3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል።”
ዳንኤል 2፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል።”
ዳንኤል 2፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤2👏1
በመጽሐፍ ቅዱስ "የእግዚአብሔር ልጅ/ልጆች" ትርጓሜ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለያዩ ስፍራዎች የቀረቡትን ማስረጃዎች በማጤን “የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለው ሐረግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ትርጕሞች እንደሚይዝ መረዳት ይቻላል፤
1) የእግዚአብሔርን የፍጥረት ባለቤትነት ማሳያ ነው።
“በውኑ ለዝናብ አባት አለውን? ወይስ የጠልን ነጠብጣብ የወለደ ማን ነው” ከሚለው መረዳት እንደሚቻለው (ኢዮብ 38፥28)፤ የእግዚአብሔር አባትነት እርሱ የፍጥረት ሁሉ ባለቤት መሆኑን የሚያሳይ ዘይቤአዊ አገላለጥ ነው። “የእኛ ዘር ከሌሎች ይበልጣል” በሚል ስሜት የተዋጡት አቴናውያን፣ “እኛም ደግሞ ልጆቹ ነን” በማለት የተናገሩትን ከፈላስፎቻቸው በመውሰድ ሰውን ሁሉ የሚመለከት አድርጎ ሐዋርያው ጳውሎስ ያቀረበው ለዚህ ይመስላል (የሐዋ. 17፥28፤ አ.መ.ት)። የሉቃስ ወንጌል አዳምን “የእግዚአብሔር ልጅ” ማለቱ ምናልባት በዚህ አግባብ የሚታይ ነው (3፥38)። እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ በመሆኑ የፍጥረት ሁሉ አባት ነው። ነገር ግን ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ስለ መሆናቸው መጽሐፍ ቅዱስ እምብዛም የሚናገረው ነገር የለውም።
2) መላእክትን ወይም ሰማያውያን ፍጥረታትን ያመለክታል፤
የእግዚአብሔር ልጆች ተብለዋልና (ኢዮብ 1461 2:11 3871 መዝ. 29፥1፤ 82፥6፤ 89፥6)።
3) እስራኤል የእግዚአብሔር መሆኗን ያመለክታል።
እስራኤል ከምድር ሁሉ ለይቶ የመረጣት በመሆኗ ለእግዚአብሔር የመጀመሪያ ልጅ ናት፤ በዚህ ረገድ እግዚአብሔር ከእርሷ በፊት ልጅ አልነበረውም። ይህንንም ሙሴ በፈርዖን ፊት ቆሞ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡- እስራኤል የበኵር ልጄ ነው” በማለት እንዲናገር አድርጎታል (ዘፀ. 4፥22-23)። “እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፤ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና” በማለትም ተጽፏል (ኤር. 31፥9)። ይህ ከእግዚአብሔር የድነት ዕቅድና ከእስራኤል ተልእኮ ጋር ይያያዛል።
እስራኤላውያን በኪዳን ሕዝብነታቸው፣ “እናንተ የአምላካችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁ” ተብለዋል (ዘዳ. 14፥1)። በዚህ አገባቡ፡ የእግዚአብሔር ልጅ ማለት የእግዚአብሔር መሆንን እና የእግዚአብሔር ቤተ ሰብነትን ያሳያል። አማኞች የአብርሃም ልጆች የሆኑበትና የእግዚአብሔር የተቀበሉበት አግባብም ይኸው ነው (ሮሜ 9፥6-8 እና 24-31 እንዲሁም 11፥7-26ን ይመለከቷል።)
4) ጻድቃንን ይኸውም የእግዚአብሔር ጠባያት የሚታዩባቸው ሰዎችንም ያመለክታል።
ጠላቶቻቸውን የሚወድዱና መልካም የሚያደርጉ (ሉቃ. 6፥35)፣ የሚያስተራርቁ (ማቴ. 5፥9)፣ ጽድቅን የሚያደርጉ (1ዮሐ. 3፥10) “የእግዚአብሔር ልጆች” ናቸው።
5) ከዳዊት ሥርወ መንግሥት የሚመጣ ንጉሥ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሏል።
ዳዊት፣ "ከልጆቼ ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ዙፋን ላይ ተቀምጦ በእስራኤል ላይ ይነግሥ ዘንድ ልጄን ሰሎሞንን መርጦታል። እርሱም፦ ልጅ ይሆነኝ ዘንድ መርጬዋለሁና፥ እኔም አባት እሆነዋለሁና … አለኝ” ሲል የተናገረው ይህንኑ ነው (1ዜና 28፥5-7)።
6) በመጨረሻም፣ “የእግዚአብሔር ልጅ” ወልድ ማለት ነው::
መለኮትነትን ያሳያል። “ከቶውንም እግዚአብሔርን ያየ ማንም የለም፤ ነገር ግን በአብ ዕቅፍ ያለው አንድያ ልጁ የሆነው አምላክ እርሱ ተረከው” (ዮሐ. 1፥18፤ አ.መ.ት)፣ እንዲሁም “ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር” (ዮሐ. 5፥18) የተባለው ለዚህ ነው።
ምንጭ፦ የእግዚአብሔር ልጅ፤ ጳውሎስ ፈቃዱ፤ ገጽ 255-256
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለያዩ ስፍራዎች የቀረቡትን ማስረጃዎች በማጤን “የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለው ሐረግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ትርጕሞች እንደሚይዝ መረዳት ይቻላል፤
1) የእግዚአብሔርን የፍጥረት ባለቤትነት ማሳያ ነው።
“በውኑ ለዝናብ አባት አለውን? ወይስ የጠልን ነጠብጣብ የወለደ ማን ነው” ከሚለው መረዳት እንደሚቻለው (ኢዮብ 38፥28)፤ የእግዚአብሔር አባትነት እርሱ የፍጥረት ሁሉ ባለቤት መሆኑን የሚያሳይ ዘይቤአዊ አገላለጥ ነው። “የእኛ ዘር ከሌሎች ይበልጣል” በሚል ስሜት የተዋጡት አቴናውያን፣ “እኛም ደግሞ ልጆቹ ነን” በማለት የተናገሩትን ከፈላስፎቻቸው በመውሰድ ሰውን ሁሉ የሚመለከት አድርጎ ሐዋርያው ጳውሎስ ያቀረበው ለዚህ ይመስላል (የሐዋ. 17፥28፤ አ.መ.ት)። የሉቃስ ወንጌል አዳምን “የእግዚአብሔር ልጅ” ማለቱ ምናልባት በዚህ አግባብ የሚታይ ነው (3፥38)። እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ በመሆኑ የፍጥረት ሁሉ አባት ነው። ነገር ግን ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ስለ መሆናቸው መጽሐፍ ቅዱስ እምብዛም የሚናገረው ነገር የለውም።
2) መላእክትን ወይም ሰማያውያን ፍጥረታትን ያመለክታል፤
የእግዚአብሔር ልጆች ተብለዋልና (ኢዮብ 1461 2:11 3871 መዝ. 29፥1፤ 82፥6፤ 89፥6)።
3) እስራኤል የእግዚአብሔር መሆኗን ያመለክታል።
እስራኤል ከምድር ሁሉ ለይቶ የመረጣት በመሆኗ ለእግዚአብሔር የመጀመሪያ ልጅ ናት፤ በዚህ ረገድ እግዚአብሔር ከእርሷ በፊት ልጅ አልነበረውም። ይህንንም ሙሴ በፈርዖን ፊት ቆሞ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡- እስራኤል የበኵር ልጄ ነው” በማለት እንዲናገር አድርጎታል (ዘፀ. 4፥22-23)። “እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፤ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና” በማለትም ተጽፏል (ኤር. 31፥9)። ይህ ከእግዚአብሔር የድነት ዕቅድና ከእስራኤል ተልእኮ ጋር ይያያዛል።
እስራኤላውያን በኪዳን ሕዝብነታቸው፣ “እናንተ የአምላካችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁ” ተብለዋል (ዘዳ. 14፥1)። በዚህ አገባቡ፡ የእግዚአብሔር ልጅ ማለት የእግዚአብሔር መሆንን እና የእግዚአብሔር ቤተ ሰብነትን ያሳያል። አማኞች የአብርሃም ልጆች የሆኑበትና የእግዚአብሔር የተቀበሉበት አግባብም ይኸው ነው (ሮሜ 9፥6-8 እና 24-31 እንዲሁም 11፥7-26ን ይመለከቷል።)
4) ጻድቃንን ይኸውም የእግዚአብሔር ጠባያት የሚታዩባቸው ሰዎችንም ያመለክታል።
ጠላቶቻቸውን የሚወድዱና መልካም የሚያደርጉ (ሉቃ. 6፥35)፣ የሚያስተራርቁ (ማቴ. 5፥9)፣ ጽድቅን የሚያደርጉ (1ዮሐ. 3፥10) “የእግዚአብሔር ልጆች” ናቸው።
5) ከዳዊት ሥርወ መንግሥት የሚመጣ ንጉሥ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሏል።
ዳዊት፣ "ከልጆቼ ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ዙፋን ላይ ተቀምጦ በእስራኤል ላይ ይነግሥ ዘንድ ልጄን ሰሎሞንን መርጦታል። እርሱም፦ ልጅ ይሆነኝ ዘንድ መርጬዋለሁና፥ እኔም አባት እሆነዋለሁና … አለኝ” ሲል የተናገረው ይህንኑ ነው (1ዜና 28፥5-7)።
6) በመጨረሻም፣ “የእግዚአብሔር ልጅ” ወልድ ማለት ነው::
መለኮትነትን ያሳያል። “ከቶውንም እግዚአብሔርን ያየ ማንም የለም፤ ነገር ግን በአብ ዕቅፍ ያለው አንድያ ልጁ የሆነው አምላክ እርሱ ተረከው” (ዮሐ. 1፥18፤ አ.መ.ት)፣ እንዲሁም “ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር” (ዮሐ. 5፥18) የተባለው ለዚህ ነው።
ምንጭ፦ የእግዚአብሔር ልጅ፤ ጳውሎስ ፈቃዱ፤ ገጽ 255-256
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሙሴ እጆቹን ጭኖበት ነበርና፣ የነዌ ልጅ ኢያሱ በጥበብ መንፈስ ተሞላ። ስለዚህ እስራኤላውያን አደመጡት፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አዞት የነበረውንም ሁሉ አደረጉ።”
ዘዳግም 34፥9 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ሙሴ እጆቹን ጭኖበት ነበርና፣ የነዌ ልጅ ኢያሱ በጥበብ መንፈስ ተሞላ። ስለዚህ እስራኤላውያን አደመጡት፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አዞት የነበረውንም ሁሉ አደረጉ።”
ዘዳግም 34፥9 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1🔥1👏1
የሙሴ ሕይወት ሲጠቀለል ምን ይመስላል? ሙሴ ምን አይነት ሰው ነበር?
1. ከእግዚአብሔር ጋር
እግዚአብሔርን ፊት ለፊት ያወቀ
“እግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንዳወቀው እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ ከዚያ ወዲህ በእስራኤል ዘንድ አልተነሣም፤”
ዘዳግም 34፥10
2. በጠላቶቹ እና በምድራቸው ላይ
ምልክት እና ድንቅ ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር የላከው
“በግብፅ ምድር በፈርዖንና በባሪያዎቹ ሁሉ ላይ በምድሪቱም ሁሉ ላይ ምልክትንና ድንቅን ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር እንደ ላከው ያለ፥”
ዘዳግም 34፥11
3. በቅዱሳን ወይም በእስራኤል ሕዝብ ፊት
ታላቅ ኃይል እና ማስደንገጥ ያሳየ
“በእስራኤል ሁሉ ፊት በጸናች እጅ ሁሉና በታላቅ ማስደንገጥ ሁሉ እንዳደረገው እንደ ሙሴ ያለ አልተነሣም።”
ዘዳግም 34፥12
በአጭሩ ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት፣ በእግዚአብሔር ሕዝብ እና በጠላት ሰፈር መሆን እና መኖር እንደሚገባው የኖረ ሰው ነው።
ዘዳግም 34
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንዳወቀው እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ ከዚያ ወዲህ በእስራኤል ዘንድ አልተነሣም፤
¹¹ በግብፅ ምድር በፈርዖንና በባሪያዎቹ ሁሉ ላይ በምድሪቱም ሁሉ ላይ ምልክትንና ድንቅን ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር እንደ ላከው ያለ፥
¹² በእስራኤል ሁሉ ፊት በጸናች እጅ ሁሉና በታላቅ ማስደንገጥ ሁሉ እንዳደረገው እንደ ሙሴ ያለ አልተነሣም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1. ከእግዚአብሔር ጋር
እግዚአብሔርን ፊት ለፊት ያወቀ
“እግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንዳወቀው እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ ከዚያ ወዲህ በእስራኤል ዘንድ አልተነሣም፤”
ዘዳግም 34፥10
2. በጠላቶቹ እና በምድራቸው ላይ
ምልክት እና ድንቅ ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር የላከው
“በግብፅ ምድር በፈርዖንና በባሪያዎቹ ሁሉ ላይ በምድሪቱም ሁሉ ላይ ምልክትንና ድንቅን ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር እንደ ላከው ያለ፥”
ዘዳግም 34፥11
3. በቅዱሳን ወይም በእስራኤል ሕዝብ ፊት
ታላቅ ኃይል እና ማስደንገጥ ያሳየ
“በእስራኤል ሁሉ ፊት በጸናች እጅ ሁሉና በታላቅ ማስደንገጥ ሁሉ እንዳደረገው እንደ ሙሴ ያለ አልተነሣም።”
ዘዳግም 34፥12
በአጭሩ ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት፣ በእግዚአብሔር ሕዝብ እና በጠላት ሰፈር መሆን እና መኖር እንደሚገባው የኖረ ሰው ነው።
ዘዳግም 34
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንዳወቀው እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ ከዚያ ወዲህ በእስራኤል ዘንድ አልተነሣም፤
¹¹ በግብፅ ምድር በፈርዖንና በባሪያዎቹ ሁሉ ላይ በምድሪቱም ሁሉ ላይ ምልክትንና ድንቅን ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር እንደ ላከው ያለ፥
¹² በእስራኤል ሁሉ ፊት በጸናች እጅ ሁሉና በታላቅ ማስደንገጥ ሁሉ እንዳደረገው እንደ ሙሴ ያለ አልተነሣም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍5👏2❤1🥰1