' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።”
ሉቃስ 7፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።”
ሉቃስ 7፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍1🔥1
#እራሳችንን_እንመርምር
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል። ታዲያ ብፁዕ ለመባልና ወደ ደስታው ለመግባት ምን ያስፈልጋል? ለመሆኑ እኔ አሟላ የተባልኩትን ነገር አሟልቼ ይሆን?
“ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።”
ሉቃስ 12፥37
“ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።”
ራእይ 3፥4
“ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 22፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል። ታዲያ ብፁዕ ለመባልና ወደ ደስታው ለመግባት ምን ያስፈልጋል? ለመሆኑ እኔ አሟላ የተባልኩትን ነገር አሟልቼ ይሆን?
“ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።”
ሉቃስ 12፥37
“ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።”
ራእይ 3፥4
“ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 22፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1🔥1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
ሐዋርያት 24፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
ሐዋርያት 24፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1👏1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሉቃስ 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
²¹ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
²² ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ፦ ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
²³ እነርሱም፦ እነሆ በዚህ፥ ወይም፦ እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
²⁴ መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
²⁵ አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
²⁶ በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
²⁷ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
²⁸ እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
²⁹ ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
³⁰ የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
³¹ በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
³² የሎጥን ሚስት አስቡአት።
³³ ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
³⁴ እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁵ ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
³⁶ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁷ መልሰውም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም፦ ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሉቃስ 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
²¹ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
²² ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ፦ ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
²³ እነርሱም፦ እነሆ በዚህ፥ ወይም፦ እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
²⁴ መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
²⁵ አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
²⁶ በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
²⁷ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
²⁸ እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
²⁹ ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
³⁰ የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
³¹ በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
³² የሎጥን ሚስት አስቡአት።
³³ ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
³⁴ እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁵ ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
³⁶ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁷ መልሰውም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም፦ ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተ እጅግ የተወደድህ ነህና በልመናህ መጀመሪያ ላይ ትእዛዝ ወጥቶአል፥ እኔም እነግርህ ዘንድ መጥቻለሁ፤ አሁንም ነገሩን መርምር፥ ራእዩንም አስተውል።”
ዳንኤል 9፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተ እጅግ የተወደድህ ነህና በልመናህ መጀመሪያ ላይ ትእዛዝ ወጥቶአል፥ እኔም እነግርህ ዘንድ መጥቻለሁ፤ አሁንም ነገሩን መርምር፥ ራእዩንም አስተውል።”
ዳንኤል 9፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1
የእግዚአብሔር ሦስቱ የምሪት ደረጃዎች
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል እንደማወቅ የሚያሳርፍና የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር የተስፋ ቃሎች ንፁህ ናቸው፡፡የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው፡፡
"በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።" መዝሙር 12፡6
"የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።"
ምሳሌ 30፥5
እግዚአብሄር በተስፋ ቃሉ እንዲህ ይላል፡፡
1. አስተምርሃለሁ
እግዚአብሔር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሔር የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡ ከመፈጠራችን በፊት በምድር ላይ ይምንሰራው ስራ ነበር፡፡ የተፈጠረንው እኛ የምንሰራው ስራ ስለነበረ ነው፡፡ ያንን ስራ ሊያሳየን ሊያስተምረን እግዚአብሔር ይፈልጋል፡፡
በእግዚአብሄር ካልተማርንና ካለ እውቀት ከሆንን እንደምንጠፋ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ በእግዚአብሔር ካልተማርን የተፈጠረንበትን አላማ መፈፀም አንደማንችልና ሰላም እንደማይኖረን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡
"ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።"
ኢሳያስ 54፡13
እኛ መማር ከምንፈልግው በላይ እግዚአብሔር እንድንማርለት ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በመረጠው መንገድ ሃሳቡን ይገልጣል ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ሲያስተምር ልባችን ያውቀዋል፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ደረጃ ወርዶ በሚገባን ቋንቋ ያስተምረናል፡፡
"እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤"
ኢዮብ 33፡14
2. በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤
ያስተማረንን እንዴት እንደምንተገብረው ደግሞ ያሳየናል፡፡ አስተምሮን ብቻ ዘወር አይልም፡፡ ያስተማረንን እንዴት እንደምንለማመደው ያሳየናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተማር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ይመራናል፡፡ ስንለማመድ አብሮን ይሆናል፡፡ ማስተማር ብቻ ሳይሆን መንገዱን ያሳየናል፡፡ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በተግባር ይመራናል፡፡ መንፈሱ የተማርነውን ያሳስበናል፡፡ ያ በሃሳብ ደረጃ የተማራችሁት በተግባር ይህ ነው ይለናል፡፡
"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።"
ዮሐንስ 14፡26
3. ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ
እግዚአብሔር ማስተማርና መምራት ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው መሄዳችንን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር አይኑን ከእኛ ላይ አይነቅልም፡፡ እግዚአብሔር ከመንገዱ አለመውጣታችንንና በመንገዱ ውስጥ መሆናችንን ይከታተለናል፡፡
"ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።"
መዝሙር 23፡6
እግዚአብሔር በቸርነቱና በምህረቱ በህይወታችን ዘመን ሁሉ ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር ስለእኛ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡
"እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።"
መዝሙር 121፡3-4
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
ምንጭ፦ አብይ ዋቁማ ዲንሳ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል እንደማወቅ የሚያሳርፍና የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር የተስፋ ቃሎች ንፁህ ናቸው፡፡የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው፡፡
"በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።" መዝሙር 12፡6
"የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።"
ምሳሌ 30፥5
እግዚአብሄር በተስፋ ቃሉ እንዲህ ይላል፡፡
1. አስተምርሃለሁ
እግዚአብሔር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሔር የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡ ከመፈጠራችን በፊት በምድር ላይ ይምንሰራው ስራ ነበር፡፡ የተፈጠረንው እኛ የምንሰራው ስራ ስለነበረ ነው፡፡ ያንን ስራ ሊያሳየን ሊያስተምረን እግዚአብሔር ይፈልጋል፡፡
በእግዚአብሄር ካልተማርንና ካለ እውቀት ከሆንን እንደምንጠፋ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ በእግዚአብሔር ካልተማርን የተፈጠረንበትን አላማ መፈፀም አንደማንችልና ሰላም እንደማይኖረን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡
"ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።"
ኢሳያስ 54፡13
እኛ መማር ከምንፈልግው በላይ እግዚአብሔር እንድንማርለት ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በመረጠው መንገድ ሃሳቡን ይገልጣል ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ሲያስተምር ልባችን ያውቀዋል፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ደረጃ ወርዶ በሚገባን ቋንቋ ያስተምረናል፡፡
"እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤"
ኢዮብ 33፡14
2. በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤
ያስተማረንን እንዴት እንደምንተገብረው ደግሞ ያሳየናል፡፡ አስተምሮን ብቻ ዘወር አይልም፡፡ ያስተማረንን እንዴት እንደምንለማመደው ያሳየናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተማር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ይመራናል፡፡ ስንለማመድ አብሮን ይሆናል፡፡ ማስተማር ብቻ ሳይሆን መንገዱን ያሳየናል፡፡ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በተግባር ይመራናል፡፡ መንፈሱ የተማርነውን ያሳስበናል፡፡ ያ በሃሳብ ደረጃ የተማራችሁት በተግባር ይህ ነው ይለናል፡፡
"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።"
ዮሐንስ 14፡26
3. ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ
እግዚአብሔር ማስተማርና መምራት ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው መሄዳችንን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር አይኑን ከእኛ ላይ አይነቅልም፡፡ እግዚአብሔር ከመንገዱ አለመውጣታችንንና በመንገዱ ውስጥ መሆናችንን ይከታተለናል፡፡
"ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።"
መዝሙር 23፡6
እግዚአብሔር በቸርነቱና በምህረቱ በህይወታችን ዘመን ሁሉ ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር ስለእኛ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡
"እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።"
መዝሙር 121፡3-4
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
ምንጭ፦ አብይ ዋቁማ ዲንሳ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤4🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጌታ ቃል እንዲሮጥ በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን እንዲከበር፥ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን ከዓመፀኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ስለ እኛ ጸልዩ።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥1-2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጌታ ቃል እንዲሮጥ በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን እንዲከበር፥ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን ከዓመፀኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ስለ እኛ ጸልዩ።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥1-2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1🥰1
ቅዱሳት መጻሕፍት
፺፭ቱ_የማርቲን_ሉተር_የመከራከሪያ_ነጥቦች.pdf
1517 ኦክቶበር 31 ልክ በዛሬው ቀን፣ ማርቲን ሉተር 95 መከራከሪያ ነጥቦችን ለጠፈ። ነጥቦቹ ምንድን ናቸው? መጽሐፍ ቅዱሳዊ ናቸው ወይስ ሌላ? ተወያዩበት፤ እንወያይበትም።
👍4❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
ዕብራውያን 10፥38
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
ዕብራውያን 10፥38
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1👏1
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች፣ #መጻሕፍትን_እንመርምር በሚል ርዕስ በሚቀርበው ዝግጅት ሊነሱ ወይም ሊብራሩ ይገባል የምትሉትን መጻሕፍ ቅዱሳዊ አሳብ ወይም ጥያቄ ካላችሁ በነጻነት እንድታቀርቡ ትበረታታላችሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍2👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም አሉት፦ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንዳለ በእርግጥ አየን፤ ስለዚህም፦ በእኛና በአንተ መካከል መሐላ ይሁን እኛ አንተን እንዳልነካንህ፥ በጎነትንም ብቻ እንዳሳየንህ፥ በደኅናም እንደ ሰደድንህ፥ አንተም ክፉ እንዳትሠራብን ቃል ኪዳን ከአንተ ጋር እናድርግ አልን አንተ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረክህ ነህ።”
ዘፍጥረት 26፥28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም አሉት፦ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንዳለ በእርግጥ አየን፤ ስለዚህም፦ በእኛና በአንተ መካከል መሐላ ይሁን እኛ አንተን እንዳልነካንህ፥ በጎነትንም ብቻ እንዳሳየንህ፥ በደኅናም እንደ ሰደድንህ፥ አንተም ክፉ እንዳትሠራብን ቃል ኪዳን ከአንተ ጋር እናድርግ አልን አንተ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረክህ ነህ።”
ዘፍጥረት 26፥28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3🥰2👍1
የ12ቱ ደቀ መዛሙርት(ሐዋርያት) አጭር ታሪክ
፩. ጴጥሮስ(ስሞኦን)
በመጀመሪያ ስሞኦን ተባለ በኋላ ኢየሱስ ኬፋ አለው። በአረማይክ ኬፋ በግሪክ ጴጥሮስ ሁለቱም አለት ማለት ነው። የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ነበር። ጴጥሮስ እንደ አይሁድ ሊቃውንት የተማረ አልነበረም። ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በቅፍርናሆም አሳ በማጥመድ ይኖር ነበር። ሚስት ነበረችው(ማር። ፩፡፳፱-፴)። ጴጥሮስን በመጀመሪያ ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀው እንድርያስ ነበር(ዮሐ. ፩፡፵፩-፵፫)። ይህ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለኢየሱስ በተለየ ሁኔታ ቅርብ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከወረደም በኋላ መሪ ሆኖም አገልግሏል።በተጨማሪም ጴጥሮስ ሁለት መልእክቶችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። አሟሟቱም በመጽሐፍ ቅዱስም ባይጻፍም በመስቀል ተዘቅዝቆ እንደ ሞተ የቤ.ክ ታሪክ ይናገራል።
፪. ዮሐንስ
የያዕቆብ ወንድም የዘብዴዎስ ልጅ ነው እናቱም ሰሎሜ ሳትሆን አትቀርም ይባላል። ዮሐንስ ማለት የስሙ ትርጉም እግዚኣብሔር ጸጋ ነው ማለት ሲሆን ወላጆቹ ሃብታሞች ነበሩ። የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይገመታል(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፪)። ከወንድሙና ከአባቱ ጋር አሳ እያጠመዱ ሳሉ ኢየሱስ ወንድሙንና እርሱን ጠራው። ሁለቱም ወንድማማቾች ሃይለኞች ስለነበሩ ኢየሱስ "ቦአኔርጌስ" ብሎ ጠርቷቸዋል። ትርጉሙም የነገድጓድ ልጆች ማለት ነው።ዮሐንስ አንድ ወንጌል ሶስት መልእክቶችን እና ራእይን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። በተጨማሪም ዮሐንስ እራሱን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር በማለት ይገልጻል። በመጨረሻም ከኤፌሶን ተሰዶ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ኖረ(ራእ. ፩፡፱)።
፫. ያዕቆብ
የዘብዴዎስ ልጅ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም ነው። የስሙ ትርጉም ተረከዝን ይይዛል ማለት ነው። ከደቀ መዛሙርት መካከል ቀድሞ የሞተው እርሱ ሲሆን ሄሮድስ በሰይፍ አስገደለው።
፬. ያዕቆብ(የእልፍዮስ ልጅ)
አንዳንድ ጊዜ ታናሹ ያእቆብ ይባላል።
፭. የአስቆሮቱ ይሁዳ
ይሁዳ ማለት ማመስገን ሲሆን አስቆሮት ማለት እርሱ የመጣበትን አካባቢ/መንደር ይገልጻል። አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባለው መንደር ይሆናል(ኢያ. ፲፭፡፳፭)። ከዚህ በመነሳት ይሁዳ ከተማ ቀመስ ሰው እንደሆን እንገምታለን። ገንዘብ ያዥ ሆኖ ሳለ ሌባ እንደሆን ወንጌላት ይናገራሉ። በመጨረሻም ሰይጣን ገብቶበት ኢየሱስን ጌታውን ሽጦ በገንዘቡ ሳይጠቀም ታንቆ ሞቷል።
፮. ይሁዳ(የያዕቆብ ልጅ)
ይህኛው ይሁዳ ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ ሳይሆን አይቀርም(ማቴ. ፲፡፫)።
፯. ማቴዎስ
የእልፍዮስ ልጅ ሲሆን ቀራጭና የቅፍርናሆም ነዋሪ ነበር። ማቴዎስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማቴዎስ ወንጌልን የጻፈ ሲሆን ሉቃስና ማርቆስ በቤተሰቡ ስም ሌዊ እያሉ የሚጠሩት ሲሆን እርሱ እራሱን ደግሞ ቀራጭ እያለ ይጠራ ነበር።
፰. ፊሊጶስ
የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን ናትናኤልን ወደ ኢየሱስ ያመጣ ደቀ መዝሙር ነበር።
፱. እንድርያስ
የጴጥሮስ ወንድም ሲሆን ከእርሱ ጋር ሆኖ አሳ ሲያጠምድ ኢየሱስ ጠራቸው። እንድርያስ የዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሲሆን ኢየሱስን እንዲከተል ከነገረው በኋላ ኢየሱስ ቤት ውሏል። ጴጥሮስንም ወደ ኢየሱስ ጠራው(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፮)። መጥምቁ ዮሐንስ የሚዜነቱን ስራ በሚገባ እንደተወጣ የእንድርያስ ሕይወት በሚገባ ያሳያል። እንድርያስም ሰውን ወደ ጌታ በማምጣት ይታወቅ ነበር።
፲. ቶማስ
ቶማስ በአረማይክ ዲዲሞስ በግሪክ ሁለቱም ትርጉማቸው መንታ ማለት ነው። ብዙዎች በተጠራጣሪነቱ ቢያውቁትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ስለኢየሱስ ሰብኳል። እንዲያውም የቤ.ክ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ቶማስ በሕንድና በፋርስ ወንጌል እንዳስተማረ ይነገራል።
፲፩. በርተሎሜዎስ
በርተሎሜዎስ ማለት የተሎሜዎስ ልጅ ማለት ነው። ምናልባት በርተሎሜዎስ የተባለው ናትናኤል ሳይሆን አይቀርም።
፲፪. ቀናተኛው ስምኦን
አንዳንዶቹ ናትናኤል ነው ይሉታል።
ምንጭ:- የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
፩. ጴጥሮስ(ስሞኦን)
በመጀመሪያ ስሞኦን ተባለ በኋላ ኢየሱስ ኬፋ አለው። በአረማይክ ኬፋ በግሪክ ጴጥሮስ ሁለቱም አለት ማለት ነው። የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ነበር። ጴጥሮስ እንደ አይሁድ ሊቃውንት የተማረ አልነበረም። ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በቅፍርናሆም አሳ በማጥመድ ይኖር ነበር። ሚስት ነበረችው(ማር። ፩፡፳፱-፴)። ጴጥሮስን በመጀመሪያ ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀው እንድርያስ ነበር(ዮሐ. ፩፡፵፩-፵፫)። ይህ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለኢየሱስ በተለየ ሁኔታ ቅርብ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከወረደም በኋላ መሪ ሆኖም አገልግሏል።በተጨማሪም ጴጥሮስ ሁለት መልእክቶችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። አሟሟቱም በመጽሐፍ ቅዱስም ባይጻፍም በመስቀል ተዘቅዝቆ እንደ ሞተ የቤ.ክ ታሪክ ይናገራል።
፪. ዮሐንስ
የያዕቆብ ወንድም የዘብዴዎስ ልጅ ነው እናቱም ሰሎሜ ሳትሆን አትቀርም ይባላል። ዮሐንስ ማለት የስሙ ትርጉም እግዚኣብሔር ጸጋ ነው ማለት ሲሆን ወላጆቹ ሃብታሞች ነበሩ። የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይገመታል(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፪)። ከወንድሙና ከአባቱ ጋር አሳ እያጠመዱ ሳሉ ኢየሱስ ወንድሙንና እርሱን ጠራው። ሁለቱም ወንድማማቾች ሃይለኞች ስለነበሩ ኢየሱስ "ቦአኔርጌስ" ብሎ ጠርቷቸዋል። ትርጉሙም የነገድጓድ ልጆች ማለት ነው።ዮሐንስ አንድ ወንጌል ሶስት መልእክቶችን እና ራእይን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። በተጨማሪም ዮሐንስ እራሱን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር በማለት ይገልጻል። በመጨረሻም ከኤፌሶን ተሰዶ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ኖረ(ራእ. ፩፡፱)።
፫. ያዕቆብ
የዘብዴዎስ ልጅ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም ነው። የስሙ ትርጉም ተረከዝን ይይዛል ማለት ነው። ከደቀ መዛሙርት መካከል ቀድሞ የሞተው እርሱ ሲሆን ሄሮድስ በሰይፍ አስገደለው።
፬. ያዕቆብ(የእልፍዮስ ልጅ)
አንዳንድ ጊዜ ታናሹ ያእቆብ ይባላል።
፭. የአስቆሮቱ ይሁዳ
ይሁዳ ማለት ማመስገን ሲሆን አስቆሮት ማለት እርሱ የመጣበትን አካባቢ/መንደር ይገልጻል። አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባለው መንደር ይሆናል(ኢያ. ፲፭፡፳፭)። ከዚህ በመነሳት ይሁዳ ከተማ ቀመስ ሰው እንደሆን እንገምታለን። ገንዘብ ያዥ ሆኖ ሳለ ሌባ እንደሆን ወንጌላት ይናገራሉ። በመጨረሻም ሰይጣን ገብቶበት ኢየሱስን ጌታውን ሽጦ በገንዘቡ ሳይጠቀም ታንቆ ሞቷል።
፮. ይሁዳ(የያዕቆብ ልጅ)
ይህኛው ይሁዳ ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ ሳይሆን አይቀርም(ማቴ. ፲፡፫)።
፯. ማቴዎስ
የእልፍዮስ ልጅ ሲሆን ቀራጭና የቅፍርናሆም ነዋሪ ነበር። ማቴዎስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማቴዎስ ወንጌልን የጻፈ ሲሆን ሉቃስና ማርቆስ በቤተሰቡ ስም ሌዊ እያሉ የሚጠሩት ሲሆን እርሱ እራሱን ደግሞ ቀራጭ እያለ ይጠራ ነበር።
፰. ፊሊጶስ
የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን ናትናኤልን ወደ ኢየሱስ ያመጣ ደቀ መዝሙር ነበር።
፱. እንድርያስ
የጴጥሮስ ወንድም ሲሆን ከእርሱ ጋር ሆኖ አሳ ሲያጠምድ ኢየሱስ ጠራቸው። እንድርያስ የዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሲሆን ኢየሱስን እንዲከተል ከነገረው በኋላ ኢየሱስ ቤት ውሏል። ጴጥሮስንም ወደ ኢየሱስ ጠራው(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፮)። መጥምቁ ዮሐንስ የሚዜነቱን ስራ በሚገባ እንደተወጣ የእንድርያስ ሕይወት በሚገባ ያሳያል። እንድርያስም ሰውን ወደ ጌታ በማምጣት ይታወቅ ነበር።
፲. ቶማስ
ቶማስ በአረማይክ ዲዲሞስ በግሪክ ሁለቱም ትርጉማቸው መንታ ማለት ነው። ብዙዎች በተጠራጣሪነቱ ቢያውቁትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ስለኢየሱስ ሰብኳል። እንዲያውም የቤ.ክ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ቶማስ በሕንድና በፋርስ ወንጌል እንዳስተማረ ይነገራል።
፲፩. በርተሎሜዎስ
በርተሎሜዎስ ማለት የተሎሜዎስ ልጅ ማለት ነው። ምናልባት በርተሎሜዎስ የተባለው ናትናኤል ሳይሆን አይቀርም።
፲፪. ቀናተኛው ስምኦን
አንዳንዶቹ ናትናኤል ነው ይሉታል።
ምንጭ:- የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤3👏2🔥1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልቡም በፊትህ የታመነ ሆኖ አገኘኸው፤ የከነዓናዊውንና የኬጢያዊውን የአሞራዊውንም የፌርዛዊውንም የኢያቡሳዊውንም የጌርጌሳዊውንም ምድር ለእርሱና ለዘሩ ትሰጥ ዘንድ ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን አደረግህ፤ አንተም ጻድቅ ነህና ቃልህን ፈጸምህ።”
ነህምያ 9፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ልቡም በፊትህ የታመነ ሆኖ አገኘኸው፤ የከነዓናዊውንና የኬጢያዊውን የአሞራዊውንም የፌርዛዊውንም የኢያቡሳዊውንም የጌርጌሳዊውንም ምድር ለእርሱና ለዘሩ ትሰጥ ዘንድ ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን አደረግህ፤ አንተም ጻድቅ ነህና ቃልህን ፈጸምህ።”
ነህምያ 9፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2🔥2👍1👏1
💠የእግዚአብሔርን ፀጋ የምንጥልባቸው አራቱ መንገዶች
እኛን ያቆመን የእግዚአብሔር ፀጋ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ፀጋ ውጭ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡
"ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።" (1ኛ ቆሮ.15፡10)
የእግዚአብሔርን ፀጋ ስንጥል ማደግ እናቆማለን፡፡ የእግዚአብሔርን ፀጋ ከጣልን መውደቃችን አይቀሬ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ፀጋ የምናጣበት ሃይል አልባ የሚያደርጉን አራቱ መንገዶች
1. ትህትናን መጣል
ሰው ትህትናን ከጣለ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚወድቅ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ሰው እግዚአብሔር ከሰጠው ደረጃ በላይ ራሱን ከፍ አድርጎ ሲያይ ከእግዚአብሔር ጋር ይተላለፋል፡፡ እግዚአብሔር ፀጋን መስጠትና ማንሳት ከፍ ማድረግ እየፈለገ በራሱ ነገሮችን ማድረግ እንደሚችል የሚያስበውን ትእቢተኛን ሰው ግን ከመቃወም ውጭ ምንም ሊያደርገው አይችልም፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣልይላል።" (ያዕ. 4፡6)
2. እውቀትን መጣል
ሰው ከመሬት ተነስቶ አውቆ የጨረሰ ከመሰለው በህይወቱ ማደግና መለወጥ አቁሟል ማለት ነው፡፡ ይህ ሰው ለአዲስ ተግዳሮት በእውቀት ራሱን ካላስታጠቀ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህ ሰው ያወቀና የጨረሰ ከመሰለው እጅግ አሰቃቂ ነው፡፡
"ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል። ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤" (1ኛ ቆሮ. 8፡1-2)
"ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤" (ሆሴ. 4፡6)
"በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።"( 2ኛ ጴጥ. 1፡2)
3. እምነትን መጣል
ሰው በእግዚአብሔር ላይ መደገፍን ትቶ በራሱ ስራ ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው ለመዳንም ሆነ ከዳነ በኋላ ለመቀደስ ፣ ለእግዚአብሔር መንግስት ለመስራትና እግዚአብሔርን ለማስደሰት በራሱ ጉልበትና ቅልጥፍና ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡
"በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።" (ገላ. 5፡4)
"ነገር ግን፦ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።" (1ኛ ቆሮ.1፡30-31)
4. ምስጋናን መጣል
ሰው ምንም ከማይወጣለት መልካም አምላክ ጋር እየኖረ ካጉረመረመና ማመስገን ካቃተው ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ላይ አቃቂር ማውጣት ከቻለ የሆነ የሳተው ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር በላይ የሚያውቅ ከመሰለው የሆነ የተዛባ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ካልታመነ ከእግዚአብሔር ጋር በየዋህነት መኖር ፣ ራሱን መስጠት ፣ ለእግዚአብሔር በየዋህነት መስራትና ፍሬያማ መሆን ያቅተዋል፡፡
"አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።"(ማቴ. 25፡24-25)
"ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደጠፉ አታንጐርጕሩ።" (1ኛ ቆሮ. 10፡10)
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
እኛን ያቆመን የእግዚአብሔር ፀጋ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ፀጋ ውጭ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡
"ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።" (1ኛ ቆሮ.15፡10)
የእግዚአብሔርን ፀጋ ስንጥል ማደግ እናቆማለን፡፡ የእግዚአብሔርን ፀጋ ከጣልን መውደቃችን አይቀሬ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ፀጋ የምናጣበት ሃይል አልባ የሚያደርጉን አራቱ መንገዶች
1. ትህትናን መጣል
ሰው ትህትናን ከጣለ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚወድቅ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ሰው እግዚአብሔር ከሰጠው ደረጃ በላይ ራሱን ከፍ አድርጎ ሲያይ ከእግዚአብሔር ጋር ይተላለፋል፡፡ እግዚአብሔር ፀጋን መስጠትና ማንሳት ከፍ ማድረግ እየፈለገ በራሱ ነገሮችን ማድረግ እንደሚችል የሚያስበውን ትእቢተኛን ሰው ግን ከመቃወም ውጭ ምንም ሊያደርገው አይችልም፡፡
"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣልይላል።" (ያዕ. 4፡6)
2. እውቀትን መጣል
ሰው ከመሬት ተነስቶ አውቆ የጨረሰ ከመሰለው በህይወቱ ማደግና መለወጥ አቁሟል ማለት ነው፡፡ ይህ ሰው ለአዲስ ተግዳሮት በእውቀት ራሱን ካላስታጠቀ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህ ሰው ያወቀና የጨረሰ ከመሰለው እጅግ አሰቃቂ ነው፡፡
"ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል። ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤" (1ኛ ቆሮ. 8፡1-2)
"ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤" (ሆሴ. 4፡6)
"በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።"( 2ኛ ጴጥ. 1፡2)
3. እምነትን መጣል
ሰው በእግዚአብሔር ላይ መደገፍን ትቶ በራሱ ስራ ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው ለመዳንም ሆነ ከዳነ በኋላ ለመቀደስ ፣ ለእግዚአብሔር መንግስት ለመስራትና እግዚአብሔርን ለማስደሰት በራሱ ጉልበትና ቅልጥፍና ላይ ሲደገፍ ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡
"በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።" (ገላ. 5፡4)
"ነገር ግን፦ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።" (1ኛ ቆሮ.1፡30-31)
4. ምስጋናን መጣል
ሰው ምንም ከማይወጣለት መልካም አምላክ ጋር እየኖረ ካጉረመረመና ማመስገን ካቃተው ከእግዚአብሔር ፀጋ ይጎድላል፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ላይ አቃቂር ማውጣት ከቻለ የሆነ የሳተው ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር በላይ የሚያውቅ ከመሰለው የሆነ የተዛባ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር አሰራር ካልታመነ ከእግዚአብሔር ጋር በየዋህነት መኖር ፣ ራሱን መስጠት ፣ ለእግዚአብሔር በየዋህነት መስራትና ፍሬያማ መሆን ያቅተዋል፡፡
"አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።"(ማቴ. 25፡24-25)
"ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደጠፉ አታንጐርጕሩ።" (1ኛ ቆሮ. 10፡10)
ምንጭ:- አብይ ዋቁማ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍4❤1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
ኤፌሶን 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
ኤፌሶን 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍1🔥1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥12-17
ልጅነት፣ የልጅነት መብት በመስጠት ቤተሰብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህም በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተለያዩ አራት ቦታዎች ተጠቅሶአል (ቍ 23፤ 9፥4፣ ገላ 4፥5፤ ኤፌ 1፥5 )፡፡ ከአብራክ ያልተገኘን ልጅ እንደ ራስ ልጅ አድርጎ ማሳደግና ሀብት የመውረስ መብቱ እንዲጠበቅለት ማድረግ፣ በግሪኮችና በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ነበር። ክርስቲያኖችም የልጅነትን መብት ያገኙት በጸጋ ነው:: ክርስቶስ ግን የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ነው:: አባ አባት ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ልዩ የሆነ ኅብረት ያመለክታል፡፡
መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅነታችንን ያረጋግጥልናል። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ከሆነ ለእግዚአብሔር ልጅነታችን ምንም ዓይነት ጥርጣሬ ሊኖረን አይገባም (ገላ. 4፥67፤ 1ዮሐ 3÷1)።
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚለው፤ መንፈስ ራሱ፥ እርሱም መንፈስ ቅዱስ ከእኛ መንፈስ ማለትም ከራሳችን ሰብአዊ መንፈስ ጋር በመሆን ይመሰክራል። ሰብአዊ መንፈስ ምንድን ነው? ሰብአዊ መንፈስ የሰው መንፈሳዊ ክፍል ነው። በክርስቶስ በምናምንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሕይወት የሚሰጠው የእኛነታችን ክፍል ነው። አንዳንድ ሰዎች ሰብአዊ መንፈስ ማለት የሰው ውስጣዊ ሕያውነት ወይም ኅሊና ነው ይላሉ (ሮሜ 7፥22)። ሰው በሦስት ክፍል ይመደባል፥ መንፈስ፥ ነፍስና ሥጋ (1ተሰ. 5፥23)። በሰብአዊ መንፈሳችን በኩል የእግዚአብሔርን መኖርና የመንፈስ ቅዱስን በረከት በሕይወታችን እንረዳለን።
ልጆች ከሆንን ወራሾችም ነን በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ ወደፊት በመንግሥተ ሰማይ ለሚኖረን ውርስ መያዣ ወይም ዋስትናችን ነው (2ቆሮ. 5፥5፤ ኤፌ. 1፥13–14)።
ጳውሎስ ግን እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ማስታወሻ ይሰጠናል። ከክርስቶስ ጋር አብረን የምንወርስ ስለሆነን፤ የሕይወቱ ወይም የክብሩ ተካፋዮች ብቻ ሳንሆን፥ የመከራውም ተካፋዮች ነን። የመከራው ተካፋዮች መሆን የማንፈልግ ከሆነ የክብሩም ተካፋዮች መሆን ከቶ አንችልም (2ጢሞ. 2፥11-12፤ 3፥12፤ 1ጴጥ. 4፥1214)።
ክርስቲያኖች ሁለት ዓይነት መስቀል አላቸው።
1. አንደኛው መስቀል አሮጌው ሰውነታችን የተሰቀለበት መስቀል ሲሆን (ሮሜ 6፥6)፤
2. ሁለተኛው መስቀል ክርስቶስን በመከተል ምክንያት የሚመጣብን መከራና ስደት ነው።
የመጀመሪያውን መስቀል ክርስቶስ ራሱ ተሸክሞልናል፤ ሁለተኛውን መስቀል ለእርሱ ስንል እኛ መሸከም አለብን። ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ለመሆንና አብረነው ለመንገሥ የምንፈልግ ከሆነ፥ ይህን ሁለተኛውን መስቀል መሸከም ይኖርብናል (ማር. 8፥34)።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 368፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥12-17
ልጅነት፣ የልጅነት መብት በመስጠት ቤተሰብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህም በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተለያዩ አራት ቦታዎች ተጠቅሶአል (ቍ 23፤ 9፥4፣ ገላ 4፥5፤ ኤፌ 1፥5 )፡፡ ከአብራክ ያልተገኘን ልጅ እንደ ራስ ልጅ አድርጎ ማሳደግና ሀብት የመውረስ መብቱ እንዲጠበቅለት ማድረግ፣ በግሪኮችና በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ነበር። ክርስቲያኖችም የልጅነትን መብት ያገኙት በጸጋ ነው:: ክርስቶስ ግን የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ነው:: አባ አባት ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ልዩ የሆነ ኅብረት ያመለክታል፡፡
መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅነታችንን ያረጋግጥልናል። መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ከሆነ ለእግዚአብሔር ልጅነታችን ምንም ዓይነት ጥርጣሬ ሊኖረን አይገባም (ገላ. 4፥67፤ 1ዮሐ 3÷1)።
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚለው፤ መንፈስ ራሱ፥ እርሱም መንፈስ ቅዱስ ከእኛ መንፈስ ማለትም ከራሳችን ሰብአዊ መንፈስ ጋር በመሆን ይመሰክራል። ሰብአዊ መንፈስ ምንድን ነው? ሰብአዊ መንፈስ የሰው መንፈሳዊ ክፍል ነው። በክርስቶስ በምናምንበት ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሕይወት የሚሰጠው የእኛነታችን ክፍል ነው። አንዳንድ ሰዎች ሰብአዊ መንፈስ ማለት የሰው ውስጣዊ ሕያውነት ወይም ኅሊና ነው ይላሉ (ሮሜ 7፥22)። ሰው በሦስት ክፍል ይመደባል፥ መንፈስ፥ ነፍስና ሥጋ (1ተሰ. 5፥23)። በሰብአዊ መንፈሳችን በኩል የእግዚአብሔርን መኖርና የመንፈስ ቅዱስን በረከት በሕይወታችን እንረዳለን።
ልጆች ከሆንን ወራሾችም ነን በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ ወደፊት በመንግሥተ ሰማይ ለሚኖረን ውርስ መያዣ ወይም ዋስትናችን ነው (2ቆሮ. 5፥5፤ ኤፌ. 1፥13–14)።
ጳውሎስ ግን እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ማስታወሻ ይሰጠናል። ከክርስቶስ ጋር አብረን የምንወርስ ስለሆነን፤ የሕይወቱ ወይም የክብሩ ተካፋዮች ብቻ ሳንሆን፥ የመከራውም ተካፋዮች ነን። የመከራው ተካፋዮች መሆን የማንፈልግ ከሆነ የክብሩም ተካፋዮች መሆን ከቶ አንችልም (2ጢሞ. 2፥11-12፤ 3፥12፤ 1ጴጥ. 4፥1214)።
ክርስቲያኖች ሁለት ዓይነት መስቀል አላቸው።
1. አንደኛው መስቀል አሮጌው ሰውነታችን የተሰቀለበት መስቀል ሲሆን (ሮሜ 6፥6)፤
2. ሁለተኛው መስቀል ክርስቶስን በመከተል ምክንያት የሚመጣብን መከራና ስደት ነው።
የመጀመሪያውን መስቀል ክርስቶስ ራሱ ተሸክሞልናል፤ ሁለተኛውን መስቀል ለእርሱ ስንል እኛ መሸከም አለብን። ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ለመሆንና አብረነው ለመንገሥ የምንፈልግ ከሆነ፥ ይህን ሁለተኛውን መስቀል መሸከም ይኖርብናል (ማር. 8፥34)።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 368፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2🔥1👏1