' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዮሴፍ ቤት እሳት እንዳትቃጠል፥ በቤቴል የሚያጠፋትም ሳይኖር እንዳትበላ፥ እግዚአብሔርን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ።”
አሞጽ 5፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዮሴፍ ቤት እሳት እንዳትቃጠል፥ በቤቴል የሚያጠፋትም ሳይኖር እንዳትበላ፥ እግዚአብሔርን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ።”
አሞጽ 5፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1👏1
"እውነት እላችኋለሁ" ከማለት ይልቅ "እውነት እውነት እላችኋለሁ" በማለት የሚታወቀው ወንጌል የቱ ነው?
Anonymous Quiz
32%
ሀ. የማቴዎስ ወንጌል
6%
ለ. የማርቆስ ወንጌል
8%
ሐ. የሉቃስ ወንጌል
55%
መ. የዮሐንስ ወንጌል
👍5❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።”
ማቴዎስ 5፥44-45
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።”
ማቴዎስ 5፥44-45
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🥰1👏1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥12-17
2. ልጅነትን የሚሰጥ መንፈስ ነው (ሮሜ 8፡14-17)
እግዚአብሔር የሁሉ ፈጣሪ በመሆኑ፣ ሁሉን በመቸሩና ለሁሉ የሚያስፈልገውን ነገር በመስጠቱ “የሁሉ አባት ነው” የተባለው ከዚህ የተነሣ ነው (ማቴ 5፥45)፡፡ ይሁን እንጂ ሰዎች ሁሉ የእርሱ ልጆች አይደሉም፤ ኢየሱስ በዚህ ምድር ሳለ ለነበሩት ያላመኑ አይሁድ “እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ” ብሎአልና (ዮሐ 8፥44)።
ሰዎች በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ በማመን፤ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉ (ዮሐ 1፥12-13)፤ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራታቸውም የዚህ ግንኙነት ማረጋገጫ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጆች የሚባሉት በመንፈስ ቅዱስ የሚመሩ ብቻ ናቸው።
በእግዚኣብሔር መንፈስ የሚመሩ፣ አማኝ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንዲያስብ፣ እንዲናገርና እንዲኖር መንፈስ ቅዱስ በውስጡ ያድራል፡፡
(1) በመሠረቱ ምሪቱ አማኝን የሚያነሣሣ ነው ይኸውም
(ሀ) የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲደረግና ክፉው የሥጋ ሥራ ይሞት ዘንድ ውስጣዊ ማነሣሣት (ቊ 13፤ ፊል 2:13 ቲቶ 2 ፥ 1 -12)፣
(ለ) ምንጊዜም ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የሚስማማ (1ቆሮ 2፡12-13፤ ከ2ጴጥ 1:20-21 ጋር ያነጻጽሩ)፣
(ሐ) የሕይወትን አቅጣጫ በማሳየት ረገድ የታቀደ (ሉቃ 4፥1፤ ሐሥ 10፥19-20፤ 16፥6-7)፣
(መ) ኀጢአት የሞላበትን መሻት የሚቃወም (ገላ 5፥17-18፣ 1ጴጥ 2፥11)
(ሠ) ስለ በደል ወቀሳን የሚያቀርብ፣ ስለ ክርስቶስ የጽድቅ መለኪያና እግዚኣብሔር ክፉውን እንደሚቀጣ የሚሳስብ (ዮሐ 16፥8-11)
(ረ) አማኞች በእምነት እንዲጸኑ የሚመክርና ክርስቶስን ከማመን ውጪ እንዳይሆኑ የሚያስጠነቅቅ (ቍ 13፤ ዕብ 3፥7-14)
(ሰ) አማኞች ለመንፈስ ቅዱስ ማነሣሣት እንቢተኞች በመሆን ሲቀጥሉ ትቶአቸው እንደሚሄድ በማሳየት (1፥28፣ ኤፌ. 4፥17-19:30-31 1ተሰ 5፥19)
(ሸ) ሲተዉት መንፈሳዊ ሞትን በማስከተል (ቊ- 6፥13)፡ እና
(ቀ) ሲታዘዙት መንፈሳዊ ሕይወትንና ሰላምን በመስጠት (ቊ 6፡10-11፡13፤ ገላ 5፥22-23) ነው::
(2) የመንፈስ ቅዱስ ማነሣሣት የሚመጣው በሚከተሉት መንገዶች ነው፦
(ሀ) የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ (ዮሐ 14፥26፤ 15:7:26: 16:131 2ጢሞ 3፥16-17)
(ለ) በትጋት በመጸለይ (ቊ 26፡ ሐሥ 13፥2-3)
(ሐ) መንፈሳዊ ስብከትና ትምህርት በመከታተል (2ጢሞ 4፥1-2፤ ዕብ 13፥7:17)
(መ) የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን መገለጥ በመለማመድ (1ቆሮ 12፥7-10 እና 14፥6)
(ሠ) የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና የታመኑ መንፈሳዊ መሪዎችን ምክር በመስማት (ኤፌ 6፡1፤ ቈላ 3፥20)።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 84፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 367፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1754፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥12-17
2. ልጅነትን የሚሰጥ መንፈስ ነው (ሮሜ 8፡14-17)
እግዚአብሔር የሁሉ ፈጣሪ በመሆኑ፣ ሁሉን በመቸሩና ለሁሉ የሚያስፈልገውን ነገር በመስጠቱ “የሁሉ አባት ነው” የተባለው ከዚህ የተነሣ ነው (ማቴ 5፥45)፡፡ ይሁን እንጂ ሰዎች ሁሉ የእርሱ ልጆች አይደሉም፤ ኢየሱስ በዚህ ምድር ሳለ ለነበሩት ያላመኑ አይሁድ “እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ” ብሎአልና (ዮሐ 8፥44)።
ሰዎች በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ በማመን፤ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉ (ዮሐ 1፥12-13)፤ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራታቸውም የዚህ ግንኙነት ማረጋገጫ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ልጆች የሚባሉት በመንፈስ ቅዱስ የሚመሩ ብቻ ናቸው።
በእግዚኣብሔር መንፈስ የሚመሩ፣ አማኝ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንዲያስብ፣ እንዲናገርና እንዲኖር መንፈስ ቅዱስ በውስጡ ያድራል፡፡
(1) በመሠረቱ ምሪቱ አማኝን የሚያነሣሣ ነው ይኸውም
(ሀ) የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲደረግና ክፉው የሥጋ ሥራ ይሞት ዘንድ ውስጣዊ ማነሣሣት (ቊ 13፤ ፊል 2:13 ቲቶ 2 ፥ 1 -12)፣
(ለ) ምንጊዜም ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የሚስማማ (1ቆሮ 2፡12-13፤ ከ2ጴጥ 1:20-21 ጋር ያነጻጽሩ)፣
(ሐ) የሕይወትን አቅጣጫ በማሳየት ረገድ የታቀደ (ሉቃ 4፥1፤ ሐሥ 10፥19-20፤ 16፥6-7)፣
(መ) ኀጢአት የሞላበትን መሻት የሚቃወም (ገላ 5፥17-18፣ 1ጴጥ 2፥11)
(ሠ) ስለ በደል ወቀሳን የሚያቀርብ፣ ስለ ክርስቶስ የጽድቅ መለኪያና እግዚኣብሔር ክፉውን እንደሚቀጣ የሚሳስብ (ዮሐ 16፥8-11)
(ረ) አማኞች በእምነት እንዲጸኑ የሚመክርና ክርስቶስን ከማመን ውጪ እንዳይሆኑ የሚያስጠነቅቅ (ቍ 13፤ ዕብ 3፥7-14)
(ሰ) አማኞች ለመንፈስ ቅዱስ ማነሣሣት እንቢተኞች በመሆን ሲቀጥሉ ትቶአቸው እንደሚሄድ በማሳየት (1፥28፣ ኤፌ. 4፥17-19:30-31 1ተሰ 5፥19)
(ሸ) ሲተዉት መንፈሳዊ ሞትን በማስከተል (ቊ- 6፥13)፡ እና
(ቀ) ሲታዘዙት መንፈሳዊ ሕይወትንና ሰላምን በመስጠት (ቊ 6፡10-11፡13፤ ገላ 5፥22-23) ነው::
(2) የመንፈስ ቅዱስ ማነሣሣት የሚመጣው በሚከተሉት መንገዶች ነው፦
(ሀ) የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ (ዮሐ 14፥26፤ 15:7:26: 16:131 2ጢሞ 3፥16-17)
(ለ) በትጋት በመጸለይ (ቊ 26፡ ሐሥ 13፥2-3)
(ሐ) መንፈሳዊ ስብከትና ትምህርት በመከታተል (2ጢሞ 4፥1-2፤ ዕብ 13፥7:17)
(መ) የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን መገለጥ በመለማመድ (1ቆሮ 12፥7-10 እና 14፥6)
(ሠ) የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና የታመኑ መንፈሳዊ መሪዎችን ምክር በመስማት (ኤፌ 6፡1፤ ቈላ 3፥20)።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 84፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 367፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1754፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።”
ሉቃስ 7፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።”
ሉቃስ 7፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍1🔥1
#እራሳችንን_እንመርምር
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል። ታዲያ ብፁዕ ለመባልና ወደ ደስታው ለመግባት ምን ያስፈልጋል? ለመሆኑ እኔ አሟላ የተባልኩትን ነገር አሟልቼ ይሆን?
“ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።”
ሉቃስ 12፥37
“ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።”
ራእይ 3፥4
“ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 22፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል። ታዲያ ብፁዕ ለመባልና ወደ ደስታው ለመግባት ምን ያስፈልጋል? ለመሆኑ እኔ አሟላ የተባልኩትን ነገር አሟልቼ ይሆን?
“ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።”
ሉቃስ 12፥37
“ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።”
ራእይ 3፥4
“ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 22፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1🔥1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
ሐዋርያት 24፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
ሐዋርያት 24፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1👏1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሉቃስ 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
²¹ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
²² ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ፦ ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
²³ እነርሱም፦ እነሆ በዚህ፥ ወይም፦ እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
²⁴ መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
²⁵ አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
²⁶ በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
²⁷ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
²⁸ እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
²⁹ ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
³⁰ የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
³¹ በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
³² የሎጥን ሚስት አስቡአት።
³³ ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
³⁴ እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁵ ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
³⁶ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁷ መልሰውም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም፦ ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሉቃስ 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
²¹ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
²² ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ፦ ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
²³ እነርሱም፦ እነሆ በዚህ፥ ወይም፦ እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
²⁴ መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
²⁵ አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
²⁶ በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
²⁷ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
²⁸ እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
²⁹ ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
³⁰ የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
³¹ በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
³² የሎጥን ሚስት አስቡአት።
³³ ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
³⁴ እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁵ ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
³⁶ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁷ መልሰውም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም፦ ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተ እጅግ የተወደድህ ነህና በልመናህ መጀመሪያ ላይ ትእዛዝ ወጥቶአል፥ እኔም እነግርህ ዘንድ መጥቻለሁ፤ አሁንም ነገሩን መርምር፥ ራእዩንም አስተውል።”
ዳንኤል 9፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“አንተ እጅግ የተወደድህ ነህና በልመናህ መጀመሪያ ላይ ትእዛዝ ወጥቶአል፥ እኔም እነግርህ ዘንድ መጥቻለሁ፤ አሁንም ነገሩን መርምር፥ ራእዩንም አስተውል።”
ዳንኤል 9፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1
የእግዚአብሔር ሦስቱ የምሪት ደረጃዎች
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል እንደማወቅ የሚያሳርፍና የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር የተስፋ ቃሎች ንፁህ ናቸው፡፡የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው፡፡
"በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።" መዝሙር 12፡6
"የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።"
ምሳሌ 30፥5
እግዚአብሄር በተስፋ ቃሉ እንዲህ ይላል፡፡
1. አስተምርሃለሁ
እግዚአብሔር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሔር የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡ ከመፈጠራችን በፊት በምድር ላይ ይምንሰራው ስራ ነበር፡፡ የተፈጠረንው እኛ የምንሰራው ስራ ስለነበረ ነው፡፡ ያንን ስራ ሊያሳየን ሊያስተምረን እግዚአብሔር ይፈልጋል፡፡
በእግዚአብሄር ካልተማርንና ካለ እውቀት ከሆንን እንደምንጠፋ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ በእግዚአብሔር ካልተማርን የተፈጠረንበትን አላማ መፈፀም አንደማንችልና ሰላም እንደማይኖረን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡
"ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።"
ኢሳያስ 54፡13
እኛ መማር ከምንፈልግው በላይ እግዚአብሔር እንድንማርለት ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በመረጠው መንገድ ሃሳቡን ይገልጣል ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ሲያስተምር ልባችን ያውቀዋል፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ደረጃ ወርዶ በሚገባን ቋንቋ ያስተምረናል፡፡
"እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤"
ኢዮብ 33፡14
2. በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤
ያስተማረንን እንዴት እንደምንተገብረው ደግሞ ያሳየናል፡፡ አስተምሮን ብቻ ዘወር አይልም፡፡ ያስተማረንን እንዴት እንደምንለማመደው ያሳየናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተማር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ይመራናል፡፡ ስንለማመድ አብሮን ይሆናል፡፡ ማስተማር ብቻ ሳይሆን መንገዱን ያሳየናል፡፡ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በተግባር ይመራናል፡፡ መንፈሱ የተማርነውን ያሳስበናል፡፡ ያ በሃሳብ ደረጃ የተማራችሁት በተግባር ይህ ነው ይለናል፡፡
"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።"
ዮሐንስ 14፡26
3. ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ
እግዚአብሔር ማስተማርና መምራት ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው መሄዳችንን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር አይኑን ከእኛ ላይ አይነቅልም፡፡ እግዚአብሔር ከመንገዱ አለመውጣታችንንና በመንገዱ ውስጥ መሆናችንን ይከታተለናል፡፡
"ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።"
መዝሙር 23፡6
እግዚአብሔር በቸርነቱና በምህረቱ በህይወታችን ዘመን ሁሉ ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር ስለእኛ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡
"እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።"
መዝሙር 121፡3-4
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
ምንጭ፦ አብይ ዋቁማ ዲንሳ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል እንደማወቅ የሚያሳርፍና የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር የተስፋ ቃሎች ንፁህ ናቸው፡፡የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው፡፡
"በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።" መዝሙር 12፡6
"የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።"
ምሳሌ 30፥5
እግዚአብሄር በተስፋ ቃሉ እንዲህ ይላል፡፡
1. አስተምርሃለሁ
እግዚአብሔር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሔር የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡ ከመፈጠራችን በፊት በምድር ላይ ይምንሰራው ስራ ነበር፡፡ የተፈጠረንው እኛ የምንሰራው ስራ ስለነበረ ነው፡፡ ያንን ስራ ሊያሳየን ሊያስተምረን እግዚአብሔር ይፈልጋል፡፡
በእግዚአብሄር ካልተማርንና ካለ እውቀት ከሆንን እንደምንጠፋ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ በእግዚአብሔር ካልተማርን የተፈጠረንበትን አላማ መፈፀም አንደማንችልና ሰላም እንደማይኖረን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡
"ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።"
ኢሳያስ 54፡13
እኛ መማር ከምንፈልግው በላይ እግዚአብሔር እንድንማርለት ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በመረጠው መንገድ ሃሳቡን ይገልጣል ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ሲያስተምር ልባችን ያውቀዋል፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ደረጃ ወርዶ በሚገባን ቋንቋ ያስተምረናል፡፡
"እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤"
ኢዮብ 33፡14
2. በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤
ያስተማረንን እንዴት እንደምንተገብረው ደግሞ ያሳየናል፡፡ አስተምሮን ብቻ ዘወር አይልም፡፡ ያስተማረንን እንዴት እንደምንለማመደው ያሳየናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተማር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ይመራናል፡፡ ስንለማመድ አብሮን ይሆናል፡፡ ማስተማር ብቻ ሳይሆን መንገዱን ያሳየናል፡፡ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በተግባር ይመራናል፡፡ መንፈሱ የተማርነውን ያሳስበናል፡፡ ያ በሃሳብ ደረጃ የተማራችሁት በተግባር ይህ ነው ይለናል፡፡
"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።"
ዮሐንስ 14፡26
3. ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ
እግዚአብሔር ማስተማርና መምራት ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው መሄዳችንን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር አይኑን ከእኛ ላይ አይነቅልም፡፡ እግዚአብሔር ከመንገዱ አለመውጣታችንንና በመንገዱ ውስጥ መሆናችንን ይከታተለናል፡፡
"ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።"
መዝሙር 23፡6
እግዚአብሔር በቸርነቱና በምህረቱ በህይወታችን ዘመን ሁሉ ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር ስለእኛ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡
"እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።"
መዝሙር 121፡3-4
"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8
ምንጭ፦ አብይ ዋቁማ ዲንሳ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍6❤4🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጌታ ቃል እንዲሮጥ በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን እንዲከበር፥ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን ከዓመፀኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ስለ እኛ ጸልዩ።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥1-2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጌታ ቃል እንዲሮጥ በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን እንዲከበር፥ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን ከዓመፀኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ስለ እኛ ጸልዩ።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥1-2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1🥰1
ቅዱሳት መጻሕፍት
፺፭ቱ_የማርቲን_ሉተር_የመከራከሪያ_ነጥቦች.pdf
1517 ኦክቶበር 31 ልክ በዛሬው ቀን፣ ማርቲን ሉተር 95 መከራከሪያ ነጥቦችን ለጠፈ። ነጥቦቹ ምንድን ናቸው? መጽሐፍ ቅዱሳዊ ናቸው ወይስ ሌላ? ተወያዩበት፤ እንወያይበትም።
👍4❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
ዕብራውያን 10፥38
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
ዕብራውያን 10፥38
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1👏1
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች፣ #መጻሕፍትን_እንመርምር በሚል ርዕስ በሚቀርበው ዝግጅት ሊነሱ ወይም ሊብራሩ ይገባል የምትሉትን መጻሕፍ ቅዱሳዊ አሳብ ወይም ጥያቄ ካላችሁ በነጻነት እንድታቀርቡ ትበረታታላችሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለ ፍርሃት እንዲኖር ተጠንቀቁ፤ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና፤ እንግዲህ ማንም አይናቀው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍2👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም አሉት፦ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንዳለ በእርግጥ አየን፤ ስለዚህም፦ በእኛና በአንተ መካከል መሐላ ይሁን እኛ አንተን እንዳልነካንህ፥ በጎነትንም ብቻ እንዳሳየንህ፥ በደኅናም እንደ ሰደድንህ፥ አንተም ክፉ እንዳትሠራብን ቃል ኪዳን ከአንተ ጋር እናድርግ አልን አንተ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረክህ ነህ።”
ዘፍጥረት 26፥28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም አሉት፦ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንዳለ በእርግጥ አየን፤ ስለዚህም፦ በእኛና በአንተ መካከል መሐላ ይሁን እኛ አንተን እንዳልነካንህ፥ በጎነትንም ብቻ እንዳሳየንህ፥ በደኅናም እንደ ሰደድንህ፥ አንተም ክፉ እንዳትሠራብን ቃል ኪዳን ከአንተ ጋር እናድርግ አልን አንተ አሁን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረክህ ነህ።”
ዘፍጥረት 26፥28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3🥰2👍1
የ12ቱ ደቀ መዛሙርት(ሐዋርያት) አጭር ታሪክ
፩. ጴጥሮስ(ስሞኦን)
በመጀመሪያ ስሞኦን ተባለ በኋላ ኢየሱስ ኬፋ አለው። በአረማይክ ኬፋ በግሪክ ጴጥሮስ ሁለቱም አለት ማለት ነው። የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ነበር። ጴጥሮስ እንደ አይሁድ ሊቃውንት የተማረ አልነበረም። ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በቅፍርናሆም አሳ በማጥመድ ይኖር ነበር። ሚስት ነበረችው(ማር። ፩፡፳፱-፴)። ጴጥሮስን በመጀመሪያ ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀው እንድርያስ ነበር(ዮሐ. ፩፡፵፩-፵፫)። ይህ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለኢየሱስ በተለየ ሁኔታ ቅርብ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከወረደም በኋላ መሪ ሆኖም አገልግሏል።በተጨማሪም ጴጥሮስ ሁለት መልእክቶችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። አሟሟቱም በመጽሐፍ ቅዱስም ባይጻፍም በመስቀል ተዘቅዝቆ እንደ ሞተ የቤ.ክ ታሪክ ይናገራል።
፪. ዮሐንስ
የያዕቆብ ወንድም የዘብዴዎስ ልጅ ነው እናቱም ሰሎሜ ሳትሆን አትቀርም ይባላል። ዮሐንስ ማለት የስሙ ትርጉም እግዚኣብሔር ጸጋ ነው ማለት ሲሆን ወላጆቹ ሃብታሞች ነበሩ። የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይገመታል(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፪)። ከወንድሙና ከአባቱ ጋር አሳ እያጠመዱ ሳሉ ኢየሱስ ወንድሙንና እርሱን ጠራው። ሁለቱም ወንድማማቾች ሃይለኞች ስለነበሩ ኢየሱስ "ቦአኔርጌስ" ብሎ ጠርቷቸዋል። ትርጉሙም የነገድጓድ ልጆች ማለት ነው።ዮሐንስ አንድ ወንጌል ሶስት መልእክቶችን እና ራእይን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። በተጨማሪም ዮሐንስ እራሱን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር በማለት ይገልጻል። በመጨረሻም ከኤፌሶን ተሰዶ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ኖረ(ራእ. ፩፡፱)።
፫. ያዕቆብ
የዘብዴዎስ ልጅ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም ነው። የስሙ ትርጉም ተረከዝን ይይዛል ማለት ነው። ከደቀ መዛሙርት መካከል ቀድሞ የሞተው እርሱ ሲሆን ሄሮድስ በሰይፍ አስገደለው።
፬. ያዕቆብ(የእልፍዮስ ልጅ)
አንዳንድ ጊዜ ታናሹ ያእቆብ ይባላል።
፭. የአስቆሮቱ ይሁዳ
ይሁዳ ማለት ማመስገን ሲሆን አስቆሮት ማለት እርሱ የመጣበትን አካባቢ/መንደር ይገልጻል። አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባለው መንደር ይሆናል(ኢያ. ፲፭፡፳፭)። ከዚህ በመነሳት ይሁዳ ከተማ ቀመስ ሰው እንደሆን እንገምታለን። ገንዘብ ያዥ ሆኖ ሳለ ሌባ እንደሆን ወንጌላት ይናገራሉ። በመጨረሻም ሰይጣን ገብቶበት ኢየሱስን ጌታውን ሽጦ በገንዘቡ ሳይጠቀም ታንቆ ሞቷል።
፮. ይሁዳ(የያዕቆብ ልጅ)
ይህኛው ይሁዳ ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ ሳይሆን አይቀርም(ማቴ. ፲፡፫)።
፯. ማቴዎስ
የእልፍዮስ ልጅ ሲሆን ቀራጭና የቅፍርናሆም ነዋሪ ነበር። ማቴዎስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማቴዎስ ወንጌልን የጻፈ ሲሆን ሉቃስና ማርቆስ በቤተሰቡ ስም ሌዊ እያሉ የሚጠሩት ሲሆን እርሱ እራሱን ደግሞ ቀራጭ እያለ ይጠራ ነበር።
፰. ፊሊጶስ
የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን ናትናኤልን ወደ ኢየሱስ ያመጣ ደቀ መዝሙር ነበር።
፱. እንድርያስ
የጴጥሮስ ወንድም ሲሆን ከእርሱ ጋር ሆኖ አሳ ሲያጠምድ ኢየሱስ ጠራቸው። እንድርያስ የዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሲሆን ኢየሱስን እንዲከተል ከነገረው በኋላ ኢየሱስ ቤት ውሏል። ጴጥሮስንም ወደ ኢየሱስ ጠራው(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፮)። መጥምቁ ዮሐንስ የሚዜነቱን ስራ በሚገባ እንደተወጣ የእንድርያስ ሕይወት በሚገባ ያሳያል። እንድርያስም ሰውን ወደ ጌታ በማምጣት ይታወቅ ነበር።
፲. ቶማስ
ቶማስ በአረማይክ ዲዲሞስ በግሪክ ሁለቱም ትርጉማቸው መንታ ማለት ነው። ብዙዎች በተጠራጣሪነቱ ቢያውቁትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ስለኢየሱስ ሰብኳል። እንዲያውም የቤ.ክ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ቶማስ በሕንድና በፋርስ ወንጌል እንዳስተማረ ይነገራል።
፲፩. በርተሎሜዎስ
በርተሎሜዎስ ማለት የተሎሜዎስ ልጅ ማለት ነው። ምናልባት በርተሎሜዎስ የተባለው ናትናኤል ሳይሆን አይቀርም።
፲፪. ቀናተኛው ስምኦን
አንዳንዶቹ ናትናኤል ነው ይሉታል።
ምንጭ:- የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
፩. ጴጥሮስ(ስሞኦን)
በመጀመሪያ ስሞኦን ተባለ በኋላ ኢየሱስ ኬፋ አለው። በአረማይክ ኬፋ በግሪክ ጴጥሮስ ሁለቱም አለት ማለት ነው። የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ነበር። ጴጥሮስ እንደ አይሁድ ሊቃውንት የተማረ አልነበረም። ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በቅፍርናሆም አሳ በማጥመድ ይኖር ነበር። ሚስት ነበረችው(ማር። ፩፡፳፱-፴)። ጴጥሮስን በመጀመሪያ ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀው እንድርያስ ነበር(ዮሐ. ፩፡፵፩-፵፫)። ይህ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለኢየሱስ በተለየ ሁኔታ ቅርብ ነበር። መንፈስ ቅዱስ ከወረደም በኋላ መሪ ሆኖም አገልግሏል።በተጨማሪም ጴጥሮስ ሁለት መልእክቶችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። አሟሟቱም በመጽሐፍ ቅዱስም ባይጻፍም በመስቀል ተዘቅዝቆ እንደ ሞተ የቤ.ክ ታሪክ ይናገራል።
፪. ዮሐንስ
የያዕቆብ ወንድም የዘብዴዎስ ልጅ ነው እናቱም ሰሎሜ ሳትሆን አትቀርም ይባላል። ዮሐንስ ማለት የስሙ ትርጉም እግዚኣብሔር ጸጋ ነው ማለት ሲሆን ወላጆቹ ሃብታሞች ነበሩ። የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደሆነ ይገመታል(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፪)። ከወንድሙና ከአባቱ ጋር አሳ እያጠመዱ ሳሉ ኢየሱስ ወንድሙንና እርሱን ጠራው። ሁለቱም ወንድማማቾች ሃይለኞች ስለነበሩ ኢየሱስ "ቦአኔርጌስ" ብሎ ጠርቷቸዋል። ትርጉሙም የነገድጓድ ልጆች ማለት ነው።ዮሐንስ አንድ ወንጌል ሶስት መልእክቶችን እና ራእይን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ጽፏል። በተጨማሪም ዮሐንስ እራሱን በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙር በማለት ይገልጻል። በመጨረሻም ከኤፌሶን ተሰዶ ፍጥሞ በምትባል ደሴት ኖረ(ራእ. ፩፡፱)።
፫. ያዕቆብ
የዘብዴዎስ ልጅ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም ነው። የስሙ ትርጉም ተረከዝን ይይዛል ማለት ነው። ከደቀ መዛሙርት መካከል ቀድሞ የሞተው እርሱ ሲሆን ሄሮድስ በሰይፍ አስገደለው።
፬. ያዕቆብ(የእልፍዮስ ልጅ)
አንዳንድ ጊዜ ታናሹ ያእቆብ ይባላል።
፭. የአስቆሮቱ ይሁዳ
ይሁዳ ማለት ማመስገን ሲሆን አስቆሮት ማለት እርሱ የመጣበትን አካባቢ/መንደር ይገልጻል። አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባለው መንደር ይሆናል(ኢያ. ፲፭፡፳፭)። ከዚህ በመነሳት ይሁዳ ከተማ ቀመስ ሰው እንደሆን እንገምታለን። ገንዘብ ያዥ ሆኖ ሳለ ሌባ እንደሆን ወንጌላት ይናገራሉ። በመጨረሻም ሰይጣን ገብቶበት ኢየሱስን ጌታውን ሽጦ በገንዘቡ ሳይጠቀም ታንቆ ሞቷል።
፮. ይሁዳ(የያዕቆብ ልጅ)
ይህኛው ይሁዳ ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ ሳይሆን አይቀርም(ማቴ. ፲፡፫)።
፯. ማቴዎስ
የእልፍዮስ ልጅ ሲሆን ቀራጭና የቅፍርናሆም ነዋሪ ነበር። ማቴዎስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማቴዎስ ወንጌልን የጻፈ ሲሆን ሉቃስና ማርቆስ በቤተሰቡ ስም ሌዊ እያሉ የሚጠሩት ሲሆን እርሱ እራሱን ደግሞ ቀራጭ እያለ ይጠራ ነበር።
፰. ፊሊጶስ
የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን ናትናኤልን ወደ ኢየሱስ ያመጣ ደቀ መዝሙር ነበር።
፱. እንድርያስ
የጴጥሮስ ወንድም ሲሆን ከእርሱ ጋር ሆኖ አሳ ሲያጠምድ ኢየሱስ ጠራቸው። እንድርያስ የዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሲሆን ኢየሱስን እንዲከተል ከነገረው በኋላ ኢየሱስ ቤት ውሏል። ጴጥሮስንም ወደ ኢየሱስ ጠራው(ዮሐ. ፩፡፴፭-፵፮)። መጥምቁ ዮሐንስ የሚዜነቱን ስራ በሚገባ እንደተወጣ የእንድርያስ ሕይወት በሚገባ ያሳያል። እንድርያስም ሰውን ወደ ጌታ በማምጣት ይታወቅ ነበር።
፲. ቶማስ
ቶማስ በአረማይክ ዲዲሞስ በግሪክ ሁለቱም ትርጉማቸው መንታ ማለት ነው። ብዙዎች በተጠራጣሪነቱ ቢያውቁትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን ስለኢየሱስ ሰብኳል። እንዲያውም የቤ.ክ ታሪክ እንደሚለው ከሆነ ቶማስ በሕንድና በፋርስ ወንጌል እንዳስተማረ ይነገራል።
፲፩. በርተሎሜዎስ
በርተሎሜዎስ ማለት የተሎሜዎስ ልጅ ማለት ነው። ምናልባት በርተሎሜዎስ የተባለው ናትናኤል ሳይሆን አይቀርም።
፲፪. ቀናተኛው ስምኦን
አንዳንዶቹ ናትናኤል ነው ይሉታል።
ምንጭ:- የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍11❤3👏2🔥1🥰1