ቅዱሳት መጻሕፍት
7.46K subscribers
1.38K photos
61 videos
333 files
808 links
በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures
Download Telegram
#እራሳችንን_እንመርምር

ከጌታችን እና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረን ወራሽ መሆን እንፈልጋለን? ታዲያ እርሱ ያለፈበትን መንገድ ጠልተን እንዴት ከእርሱ ጋር ወራሽ እንሆናለን? ጌታችን በምን ጎዳና ይሆን ያለፈው?


“ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።”
ሮሜ 8፥17




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍1👏1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤”
                   ቆላስይስ 2፥14




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4🔥1🥰1
#መጻሕፍትን_እንመርምር

አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?



                        ክፍል-9
(የመጨረሻ ክፍል)


ዮሐንስ ሲጽፍ፥ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች «የወጡት ከእኛ መካከል ነው። ይሁን እንጂ ድሮውንም ከእኛ ወገን አልነበሩም ... ከእኛ ወገን አለመሆናቸው እንዲታወቅ ከእኛ መካከል ተለይተው ወጥተዋል» ብሏል (1ዮሐ. 2፥19)። አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ አይችሉም የሚሉት ሰዎች ከመንገድ የወጡ ወይም የካዱ ሰዎች ገና ከመጀመሪያው እውነተኛ አማኞች አልነበሩም ይላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ የሚሉት ሰዎች፤ ከመንገድ የወጡ ወይም የካዱ ሰዎች ቀድሞ እውነተኛ አማኞች ሊሆኑና አንዳንዶቹ ደግሞ እውነተኛ አማኞች ላይሆኑ ይችላሉ፤ እውነተኛ አማኞች የነበሩና ክርስቶስን የካዱ ሰዎች ግን ከእኛ ወገን አይደሉም ይላሉ። ሐሰተኛው ክርስቲያን የቱ እንደሆነና እውነተኛው ክርስቲያን ደግሞ የቱ እንደሆነ ዳኝነት ስንሰጥ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን (ማቴ. 7፥12)። ከዚህ በተጨማሪ ከመንገድ ከቶ አንወጣም ወይም ከሀዲያንም ከቶ አንሆንም የሚል ትምክህተኝነት እንዳይዘን ልንጠነቀቅ ይገባል። ጳውሎስ ሲናገር፥ «… የቆመ የሚመስለው ሰው፥ እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ» ብሏል (1ቆሮ. 10፥12)። ዮሐንስ ሲጽፍ ደግሞ እንዲህ በማለት አሳስቧል፥ «እናንተ ግን ከመጀመሪያው የሰማችሁት ቃል በልባችሁ ጸንቶ ከኖረ፥ ከወልድና ከአብ ጋር ኅብረት ይኖራችኋል» (1ዮሐ. 2፥24)።

እንግዲህ እስከ አሁን ድረስ እንደተመለከትነው፥ አንዳንድ አዲስ ኪዳናዊ ንባባት አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ አይችሉም የሚለውን ሀሳብ ይደግፋሉ። ሌሎች ንባባት ደግሞ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ የሚለውን ሀሳብ ይደግፋሉ። በእርግጥ ከዚህ ላይ የምናየው አዕምሮአችን ሙሉ በሙሉ ሊጨብጠው የማይችለውን ሁለት ገጽታ ያለውን ታላቅ እውነት ነው። ከእኛ ይልቅ የእግዚአብሔር ጥበብ እጅግ ታላቅ ነውና።

አማኞች እነዚህን ሁለት እውነቶች አጣምረው መያዝ አለባቸው ሲል አንድ ሰው ተናግሯል። ይሁን እንጂ ስለ ደኅንነቱ ብዙ የሚያሳስበው አማኝ ደኅንነቱ ዋስትና እንዳለው አጽንኦት መስጠት አለበት። በሌላ በኩል ደግሞ ከመንገድ አልወጣም እያለ ከልክ በላይ የሚታመን አማኝ በእርግጥ ከመንገድ ሊወጣ እንደሚችል አጽንኦት ሊሰጥ ይገባል። አሁንም ከዚህ ላይ የምናየው፥ መጽሐፍ ቅዱስ ጥልቅና ሰፊ መሆኑን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሰዎችን ሁሉ ፍላጎት ያሟላል።

ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት አለ» ሲባል ምን ማለት ነው?

በ1ዮሐ. 5፥16–17 ላይ «ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት» ለሠራ ወንድም (ክርስቲያን) እንዳንጸልይ ታዘናል። ዮሐንስ በዚህ ቦታ የሚናገረው ስለ መንፈሳዊ ሞት ሊሆን ይችላል። ሆኖም ጸሐፊው በዚህ ቦታ የሚናገረው ነፍሱ ስለማትጠፋው (1ቆሮ. 5፥5) ነገር ግን ኃጢአትን ስለሚሠራ ክርስቲያን ሥጋዊ ሞት ሊሆንም ይችላል። ዮሐንስ የሚናገረው ስለ መንፈሳዊ ሞት ከሆነ ይህ ንባብ አማኝ ደኅንነቱን ሊያጣ ይችላል የሚሉትን ሰዎች ይደግፋል። ይሁንና ዮሐንስ ያ ኃጢአት ምን እንደሆነ በትክክል አልተናገረም።

ምናልባት ይህ «ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት» በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል መናገር ሊሆን ይችላል። ኢየሱስም ቢሆን እንዲህ ዓይነቱ ኃጢአት ስርየት አያገኝም ብሏል (ማር. 3፥28–29)። እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ኢየሱስ አንድ ክርስቲያን እንዲህ ያለውን ኃጢአት ሊፈጽም ይችላል ወይም አይችልም ብሎ ያልተናገረ መሆኑን ነው። ነገር ግን የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ እንዲህ ያለው አጋጣሚ ሊከስት እንደሚችል ማለትም አማኝ የነበረ ሰው («የመንፈስ ቅዱስ ተካፋይ» የነበረ ሰው) እግዚአብሔርን ሊክድና ጌታንም ሊያዋርድ እንደሚችል ተናግሯል። "ከዚህ ሁሉ በኋላ ከመንገድ ከወጡ፥ እነርሱን ወደ ንስሓ መመለስ አይቻልም" (ዕብ. 6፥4–6)። በዚሁ መልእክት ምዕራፍ 10 ላይ ጸሐፊው ሲናገር እንዲህ ብሏል፦"እውነትን ካወቅን በኋላ ሆነ ብለን ኃጢአት ብንሠራ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኃጢአት የሚቀርብ ምንም መሥዋዕት አይኖረንም" (ዕብ. 10፥26)። ከዚህ በኋላ ጸሐፊው አማኝ ስለነበሩና በኢየሱስም ደም «ስለተቀደሱ» እንዲሁም «የእግዚአብሔርን ልጅ ስለናቁ» እና «የጸጋን መንፈስ ስለሰደቡ» ሰዎች ያወሳል (ዕብ. 10፥29)። እንግዲህ የእግዚአብሔርን መንፈስ የካዱና ኃጢአትም በመሥራት የቀጠሉ ሰዎች የእግዚአብሔርን ድምጽ ከቶ ሊሰሙ አይችሉም። ሁሉን ከተረዱ በኋላ በኃጢአት ጸንተው የሚቀጥሉ ሰዎች ልባቸው ይደነድናል። እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት አይችሉም፣ እግዚአብሔርም ከእንግዲህ በኋላ ዳግም ላይጠራቸው ይችላሉ።

በርካታ ክርስቲያኖች አንድ አማኝ ከመንገድ ሊወጣና የክርስቶስንም ጥሪ አልቀበልም በማለት በእምቢተኝነት ጸንቶ ሊቀጥል እንደሚችልና እነዚህም ንባቦች (ዕብ. 6፥4–6፤ 10፥26–31) የሚያስጠነቅቁት ይኼንኑ ሁኔታ እንደሆነ ይናገራሉ። ሌሎች ክርስቲያኖች ደግሞ እውነተኛ አማኞች እስከመጥፋት ደረጃ አይደርሱም፥ ይልቁንም ወደ ሞት ከመድረሳቸው በፊት ዘወትር ንስሓ በመግባትና በጽኑም በማመን በእምነት ይቀጥላሉ ይላሉ።


ማጠቃለያ

ክርስቲያን የሆኑ ሁሉ እንደሚያምኑት ደኅንነትን ያገኘነው በእግዚአብሔር ጸጋና ምሕረት ብቻ፥ እንዲሁም በእምነት አማካይነት በኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ኤፌ. 2፥8–9)። ደግሞም ክርስቲያን የሆኑ ሁሉ እንደሚያምኑት በእምነት ጸንተን የምንዘልቀው በመንፈስ ቅዱስ እገዛ ብቻ ነው (ገላ. 3፥3)። ይሁንና አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ ክርስቲያኖች አንድ እውነተኛ አማኝ ደኅንነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም በሚለው ጉዳይ ላይ ያላቸው የተለያየ አመለካከት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ጉዳይ ላይ ቁርጥ ያለ ትምህርት አይሰጥም። ስለሆነም የትኛውንም አቋም ብንይዝ የያዝነው አቋም ግን በዚህ ጥያቄ ላይ የተለየ አመለላለት ካላቸው ከሌሎች ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች ጋር ሊለየን አይገባም። እነዚህ ሁለት አመለካከቶች ማለትም አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ወይም አይችሉም የሚሉት በይሁዳ መልእክት ላይ ጎን ለጎን ተጠቅሰዋል። በቁጥር 21 ላይ ይሁዳ ሲጽፍ፥ «...በምሕረቱ የዘላለም ሕይወት እንዲሰጣችሁ በመጠባበቅ ራሳችሁን በእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ ጠብቁት» ብሏል። በቁጥር 24 ላይ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንድንመለከት እየጠቆመን እንዲህ በማለት ይናገራል፥ «እንዳትወድቁ ሊያድርጋችሁና ያለ ነቀፋም አድርጎ በደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችል፥ ... አሁንም፥ ለዘላለምም ክብርና ግርማ፥ ኃይልና ሥልጣንም ይሁን አሜን»።




ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 28-29





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1👍1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“በብዙ መከራ ተፈትነው ሳሉ የደስታቸው ብዛትና የድህነታቸው ጥልቅነት የልግስናቸውን ባለ ጠግነት አብዝቶአል፤”
              2ኛ ቆሮ 8፥2




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2👍1🥰1👏1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት




ሮሜ 8፥12-17


«መንፈስ ወርሷችኋል» (ሮሜ 8፡12-17)

እኛ መንፈስ ስላለን ብቻ በቂ አይደለም፤ መንፈስ እኛን ሊወርሰንም ያስፈልጋል፡፡ የተትረፈረፈው የድል ሕይወት በክርስቶስ በኩል የእኛ የሚሆነው በዚህ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ሥጋችን ለሕይወታችን ከችግር በቀር ያመጣልን ነገር ስለሌለ፣ የሥጋ ዕዳ የለብንም፡፡ ክርስቶስን ባመንን ጊዜ በኃጢአታችን የወቀሰን፣ ክርስቶስን የገለጠልንና የዘለዓለም ሕይወት ያካፈለን መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ የእርሱ ዕዳ አለብን፡፡

በክርስቶስ ኢየሱስ ከሆንን መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር አለ። ስለዚህም

1. በእርሱ ኃይል የሰውነትን ሥራ እንድንገድል ያስችለናል። (ቁ. 13)

ኀጢአት ሁልጊዜ የራሱ ሊያደርገን ስለሚፈልግ፣ በሕይወታችን የእግዚአብሔርን ሥራ ሊገድብ ከሚችል ነገር ሁሉ ጋር ያለማቋረጥ መጋደል እንደሚገባ ጳውሎስ አሳስቧል (ከ6፥11-19):: ይህ መንፈሳዊ መጋደል በሰይጣንና በክፉ መንፈሳውያን ሰራዊት ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም (ኤፌ 6፡12) ዋነኛ ዐላማው የኀጢአተኛ ተፈጥሮን ስሜትና ፍላጎት መቃወም ነው (ገላ 5፥16-21፤ ያዕ 4፥1፡ 1ጴጥ 2፡11)። አማኞች እንደ መሆናችን መጠን ሁልጊዜ ለኀጢአተኛ መሻታችን ነው ወይስ ተካፋይ ለምንሆንበት መለኮታዊ ማንነት ነው የምንታዘዘው በማለት መጠየቅ አለብን (ገላ 5፥16፡18፤ 2ጴጥ 1፥4)፡፡

ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ መግደል ያለመቻል መንፈሳዊ ሞት (ቊ 6:13) እና በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ርስትን ማጣት ሊያስከትል ይችላል (ገሳ 5፥9-21)፡፡ ትሞታላችሁና የሚለው ቃል አንድ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ሕይወት ወደ መንፈሳዊ ሞት ሊሄድ እንደሚችል ያመለክታል፡፡ ስለዚህም በአዲስ ልደት የምንቀበለው የእግዚአብሔር ሕይወት (ዮሐ. 3፥3-6) ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ለመግደል ከማይፈልግ አማኝ ነፍስ ውስጥ እየታጣ ሊሄድ ይችላል።

በኃጢአት ባሕሪ ልማድ የምንኖር ከሆነ እንሞታለን። ይህም የእግዚአብሔርን ፍርድ በመቀበል የዘላለም ሞት እንሞታለን ማለት ነው። ስለዚህ ይህን በጣም አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ መጠየቅ አለብን። ከዘላለም ሞት አምልጠን የዘላለም ሕይወት መቀበል የምንችለው እንዴት ነው?

አንዳንድ ሰዎች እንዲህ በማለት ለዚህ ጥያቄ መልስ ይሰጣሉ፥ እኛ ማድረግ ያለብን በክርስቶስ ማመን ነው፤ ከዚያም በኋላ የቀረውን ነገር ሁሉ ክርስቶስ ያደርገዋል። እኛ ከልባችን ማድረግ የሚገባን «እኔ አምናለሁ» ማለት ብቻ ነው። ወዲያውኑ በቅጽበት እንድናለን። ነገር ግን ጳውሎስ እዚህ ላይ ለየት ያለ መልስ ይሰጣል። በእርግጥ በመጀመሪያ በክርስቶስ ማመን አለብን። ከዚያን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የሥጋን የስህተት ሥራ (ሃጢያተኛ ባህሪን) ሁሉ መግደል አለብን። ይህንን ካደረግን ብቻ ነው በሕይወት የምንኖረው፤ ማለትም መዳን የምንችለው። ለምን ይህ ይሆናል? ምክንያቱም በኃጢአት ባሕሪ ልማድ አለበለዚያም በመንፈስ ልማድ መኖር አለብን፣ በሁለቱም ልማዶች በአንድ ጊዜ መኖር አንችልም። በኃጢአት ልማድ የምንኖር ከሆነ እንሞታለን፤ ይህ እርግጥ ነው። በመንፈስ ልማድ ለመኖር ግን አንድ ነገር ማድረግ ያስፈልገናል፤ የሥጋ ሥራዎችን መግደል ይኖርብናል። እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ትምህርት አለ። ሰዎች ክርስቶስን መከተል በጣም ቀላል ነው ብለው በስሕተት ያስባሉ። እነዚሁ ሰዎች እኛ ክርስቲያኖች መልካም ሥራ መሥራት የለብንም ወይም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችንም መፈጸም አያስፈልገንም ይላሉ። ኃጢአት ብንሠራም መጨነቅ የለብንም፤ ምክንያቱም ወዲያው ይቅርታ እናገኛለን በማለት ያስባሉ። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ አባባሎች እውነት አይደሉም። ከሁሉም ክርስቶስን መከተል በጣም አስቸጋሪ መንገድ ነው፤ ለምን? ምክንያቱም ክርስቶስን ለመከተል የሥጋን ሥራዎች በሙሉ መግደል አለብን፤ ይህም ራስን እንደመግደል ይቆጠራል። ራስን መግደል ወይም መስቀል ቀላል ነገር ነውን? በእርግጥ ቀላል አይደለም። ከዚህ የበለጠ ከባድ ነገር የለም። ይሁን እንጂ፥ በሕይወት ለመኖር አሮጌው ኃጢአተኛ ሰውነታችን መሞት ያስፈልገዋል። አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ከማግኘታችን በፊት አሮጌው ኃጢአተኛ ሰውነት መሞት ይገባዋል፤ ትንሣኤ ከመሆኑ በፊት መጀመሪያ ሞት መቅደም አለበት።

የሥጋን ሥራ ወደ ሞት ለማምጣት፥ በመጀመሪያ የኃጢአተኛ ምኞታችንን ወደ ሞት ማምጣት አለብን። ምክንያቱም የሥጋ ሥራዎች የሚነሡት ከምኞታችን ስለሆነ ነው (ያዕ. 1፥14–15)። ኃጢአት መሥራትን ብቻ መተው ሳይሆን፥ ኃጢአት ስለ መሥራት ማሰብን ማቆም አለብን። ጽድቃችን ከውጪ ብቻ መሆን የለበትም፤ ከውስጣችንም ጭምር እንጂ። ኃጢአት የሚመነጭባቸውን የልባችንንና የአእምሮአችንን ምስጥራዊ ክፍሎች እንዲሞቱ ማድረግ አለብን። ምክንያቱም ኃጢአት በመጀመሪያ የሚነሣው ከእነዚህ ቦታዎች ስለሆነ ነው። እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር መሰቀል ለሚለው አሳብ አንዱ ትርጉም ይህ ነው (ሮሜ 6፥6፥12፤ ቆላ. 3፥5፤ ገላ. 5፥17፥24)።

የሥጋን ሥራዎች እየፈጸሙ በአንድ ጊዜ ደግሞ በመንፈስ መኖር የሚቻል አይደለም። የሥጋን ሥራዎች ያልገደልናቸው ከሆነ፥ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን የለም፤ የክርስቶስም ወገኖች አይደለንም። የክርስቶስ ወገኖች ካልሆንን ደግሞ ደኅንነትንም አልተቀበልንም ማለት ነው። ነገር ግን አንድ ነገር ማስታወስ አለብን። የሥጋን ሥራዎች መግደል ካስፈለገን የመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ያስፈልገናል። ያለ መንፈስ ቅዱስ ይህን ለብቻችን ማድረግ አንችልም። መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ሁልጊዜ ከእኛ ጋር ነው፤ የጽድቅ ሕይወት እንድንኖር ሁልጊዜ ይረዳናል። እንግዲህ የሮሜ ምዕራፍ 8 አስደሳች ዜና ይህ ነው።



ይቀጥላል...




ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 84፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 367፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1753





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1👍1🥰1👏1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“ተግሣጽን ያዝ፥ አትተውም፤ ጠብቀው፥ እርሱ ሕይወትህ ነውና።”
             ምሳሌ 4፥13




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2👍2🔥1👏1
ኢየሱስ በወንጌል "እውነት እውነት እላችኋለሁ" ሲል ምን ማለቱ ነው?



ኢየሱስ በተለያዩ ጊዜያት በወንጌል ውስጥ “እውነት እላችኋለሁ” የሚሉ ሐረጎችን ተጠቅሟል። በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ፣ ኢየሱስ “እውነት እውነት” የሚለውን ሐረግ ደጋግሞ ይጠቀማል። እነዚህ አገላለጾች ሁሉም በቀጥታ "āˈmēn" ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተወሰደውን "amēn" የሚለውን የግሪክ ቃል ይጠቀማሉ። ይህ ቃል እንዴት እና የት ጥቅም ላይ እንደሚውል በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ በመመስረት የተለያየ አንድምታ አለው። የኢየሱስ የቃሉ አተገባበር ከቀደምት አጠቃቀሞች በተለየ ሁኔታ ይታያል።

በዘመናዊ አጠቃቀም፣ "አሜን" የሚለው ቃል በተለምዶ በጸሎት መጨረሻ ላይ ጥቅም ላይ ይውላል። እንዲሁም ከአንዳንድ መግለጫዎች ወይም ሃሳቦች ጋር ስምምነትን ለማሳየት ይነገር ይሆናል። ይህ በብሉይ ኪዳን እንደታየው ከዋናው የቃሉ አጠቃቀም ትንሽ የተለየ ነው ነገር ግን በቅርበት የተያያዘ ነው። የዕብራይስጥ ቃል āˈmēn በቀጥታ ሲተረጎም “ይሁን” ማለት ነው። ቃሉ የተሟላ እና አጠቃላይ ስምምነት መግለጫ ነው። እንደ 1ኛ ዜና 16፥36 ወይም ዘዳግም 27፥15–26 ባሉ ምንባቦች ቃሉ በዚህ መልኩ ጥቅም ላይ ውሏል። አሜን የሚለውን ቃል በመግለጫው መጨረሻ ላይ ማስቀመጥ ከዚህ በፊት የነበረውን የመቀበል፣ የመስማማት ወይም የማጽደቅ መንገድ ነው።

ኢየሱስ ግን መግለጫ ከመስጠቱ ወይም መልእክት ከመስጠቱ በፊት “አሜን” ማለት ይወድ ነበር። በዚህ መንገድ ጥቅም ላይ ሲውል አሜን የሚለው ቃል ትንሽ የተለየ አንድምታ አለው። በአሜን መጀመር የሚከተለው እውነት መሆኑን ብቻ ሳይሆን መግለጫውን የሰጠው ሰው ስለነገሩ እውቀት እና ስልጣን እንዳለው ያሳያል። መግለጫ ከመስጠታችን በፊት “እውነት እውነት” ማለት ከሞላ ጎደል ድፍረት ከተሞላበት አመለካከት የመነጨ ለእውነት ጠንካራ ማረጋገጫ ነው። ስለ ዓለማዊም ሆነ ዓለማዊ ጉዳዮች መናገር፣ “እውነት ፣ እውነት” ማለት የሚከተለው ንግግር የዚያ ሰው የራሱ ሐሳብ (የአሳቡ ምንጭ ተናጋሪው) መሆኑን ያሳያል።

ስለዚህ፣ ኢየሱስ "እውነት እላችኋለሁ" ብሎ፣ እንደ ማቴዎስ 18፥3፣ ማርቆስ 3፥28፣ ሉቃስ 23፥43 እና ዮሐንስ 8፥51 ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ሲጀምር፣ “እመኑኝ፣ ይህ እውነት ነው” ማለቱ ብቻ አይደለም። በእውነቱ፣ “ይህ እውነት እንደሆነ አውቃለሁ” እያለ ነው። ከእነዚህ አስተያየቶች ውስጥ ብዙዎቹ በሰማያዊ፣ በመንፈሳዊ ወይም በአምላካዊ ጉዳዮች ላይ፣ የኢየሱስ የመለኮትነት የይገባኛል ጥያቄ አካል ነው። ኢየሱስ እነዚህን እውነቶች የሚያውቅ ብቻ አይደለም። የፈጠረው እርሱ ነው!

ደቀ መዛሙርቱ እና ሌሎች የኢየሱስን ቃላት የሚያዳምጡ ሰዎች እነዚህን ሐረጎች የተጠቀመበትን መንገድ በትክክል ተረድተውት ነበር። እንግዲያው፣ የኢየሱስን ቃላት ስናነብ “እውነት እውነት” በማለት የሚጀምሩትን መግለጫዎች ስንመለከት ጥልቅ ትርጉሙን ማስታወስ አለብን። እነዚህ የይገባኛል ጥያቄዎች ኢየሱስ እውነት ላይ ያለውን አመለካከት ብቻ የሚያመለክት አይደለም። እነዚያ ስለ እሱ የቅርብ ፣ ግላዊ ፣ የመጀመሪያ እውቀቱ እንዳለው የሚያሳዩ ናቸው።


ምንጭ፦ www.gotquestions.org




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3👍1👏1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁና፤”
                    ሮሜ 1፥11




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
6👍1🥰1👏1
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ቆሮንቶስ


ቆሮንቶስ የግሪክ ከተማ ናት፤ ከአቴናም 75 ኪ.ሜ. ያህል ትርቃለች። አቀማመጥዋ በሁለቱ የግሪክ አውራጃዎች በመቄዶንያና በአካይያ መካከል በሚገኘው ልሳነ ምድር ላይ ነበረ። ጳውሎስ በነበረበት ዘመን 250,000 ሰዎችና 400,000 ባሪያዎች በቆሮንቶስ ይኖሩ እንደ ነበር ይገመታል፡፡ ቆሮንቶስ ከሌሎቹ የግሪክ ከተሞች ይልቅ በአንዳንድ ነገሮች በልጣ ትታይ ነበር፤ ምክንያቶቹም የሚከተሉት ናቸው፦

1) ንግዷ፤ ከተማዋ በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር አጠገብ የምትገኝ የመንገደኞች መተላለፊያ የነጋዴዎች መናኸሪያ ነበረች፡፡ ከተማይቱ ሁለት ወደቦች አሏት፤ እነዚህም:-

ሀ) በስተ ምሥራቅ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በሰሮኖ ባሕረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የክንክራኦስ ወደብ፣

ለ) በስተ ምዕራብ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በቆሮንቶስ ባህረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የሌቻዶም ወደብ ናቸው፡፡

ልዩ ልዩ ዕቃዎች በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር በዳዮልኮስ ጐዳና ላይ በትናንሽ መርከቦች ሞልተው እየተሳቡ ከወዲህ ማዶ ወዚያኛው ይሽጋገሩ ነበር፡፡ በትልልቅ መርከቦች የተጫኑ ዕቃዎችም በፉርጎ ሆነው እንደዚሁ ከአንዱ ዳር ወደ ሌላው ዳር ይጓጓዙ ነበር፡፡ በዚህ ዓይነት ሸቀጣ ሸቀጦች ከኢጣሊያ ከእስፓኝ ወደ ምዕራብ፣ እንዲሁም ከትንሹ እስያ፣ ከፊንቄና ከግብፅ ወደ ምሥራቁ ዓለም የሚጓጓዙበት በቆሮንቶስ ከተማ በኩል አድርገው ነበር።

2) ባህሏ፤ ቆሮንቶስ እንደ አቴንስ ሁሉ እስከዚህ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ባይኖራትም በሠለጠነው የግሪክ ባህል የመጠቀች ነበረች፤ ሕዝብዋም ለግሪክ ፍልስፍና ጥልቅ ፍቅር ስለነበረው ለጥበብ ከፍተኛ ወጪ ያደርግ ነበር።

3) ሃይማኖቷ፤ የቆሮንቶስ ከተማ በትንሹ አሥራ ሁለት ቤተ ጣዖቶች ነበሩባት፤ ጳውሎስ በነበረበት ዘመን እነዚህ ሁሉ ቤተ ጣዖቶች ለአገልግሎት ክፍት ይሁኑ አይሁኑ እስከዚህ የሚታወቅ ነገር የለም:: ከእነዚህ ቤተ ጣዖቶች መካከል አንዱ በግሪክ የተረታ ተረት ታሪክ ውስጥ የፍቅር አምላክ ተብላ የምትታወቀው የአፍሮዲጡስ ቤተ ጣዖት ሲሆን በቤተ ጣዖቱም ውስጥ ከሥርዓት አምልኮው ጋር በተያያዘ የዝሙት ሥራ መፈጸም የተለመደ ነበር፡፡ ከትያትር ቤቱ ሕንፃ በስተ ሰሜን ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የፈውስ አምላክ እያሉ ለሚጠሩት ለአስክሌፕደስ የተሠራ ቤተ ጣዖት አለ፡፡ በከተማይ ቱም መሃልም በ6ኛው ምዕተ ዓመት ቅድመ ልደት ክርስቶስ ላይ የተሠራ የአፖሎ ቤተ ጣዖት ቆሞአል፡፡ አይሁድ በከተማይቱ ውስጥ የሠሩትም ምኵራብ ነበር፡፡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ጽሑፍ የተቀረጸበት የመስኮት ጒበን በአሁኑ ጊዜ ተገኝቶ በጥንቲቱ የቆሮንቶስ ከተማ ቤተ መዘክር በክብር ተቀምጦአል፡፡

4) ምግባረ ብልሹነትዋ፤ ቆሮንቶስ እንደማንኛውም ትልቅ የንግድ ከተማ ሁሉ ለሥነ ምግባር ብልሹነት በሰፊው የተጋለጠች ነበረች፡፡ የአፍሮዲጡስ የጣዖት አምልኮ በሃይማኖት ስም ዝሙት እንዲ ስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጎአል፡፡ በአንድ ዘመንማ ለዚሁ ሥራ የተለዩ አንድ ሺህ ዘማውያት በቤተ ጣዖቱ ውስጥ ያገለግሉ ነበር፡፡ ቆሮንቶስ ምግባረ ብልሹነትዋ የታወቀች ከመሆንዋ የተነሣ በግሪኩ የሰዋሰው ግሥ “መቆታንተስ” ማለት “በአሳፋሪ የዝሙት ተግባር መሰማራት” ማለት እንደሆነ የተቍጠረበት ወቅት ነበር፡፡ እንግዲህ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የነበረችው የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ መከራ ችግር ውስጥ እንደምትገባ መገመት አያዳግትም፡፡

ቆሮንቶስ ጥንታዊት የግሪክ ከተማ ስትሆን፣ በጳውሎስ ዘመን በብዙ መንገድ ታዋቂ የነበረች የግሪክ መዲና ናት:: በአሁን ዘመን እንዳሉት ሀብታም ከተሞች ቆሮንቶስ በዕውቀት የታበየች፣ በሀብት የበለጠገችና በኢግብረገባዊ ሕይወት የረከሰች ነበረች፡፡ ማንኛውም ዐይነት ኀጢአት በዚህች በወጣላት ዓለማዊ ከተማ ተስፋፋ፡፡

ከጵርስቅላና ከአቂላ (1ቆሮ 16፥19) እንዲሁም ከራሱ ሐዋርያዊ ቡድን (ሐሥ 18፥5) ጋር በመጣመር፤ ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞው (ሐሥ 18፥1-17) ዐሥራ ስምንት ወር በቆሮንቶስ ከተማ ለአገልግሎት በቈየበት ጊዜ የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን መሠረተ፡፡ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምእመናን ጥቂቶቹ አይሁድ ሲሆኑ፣ በአብዛኛው ጣዖት አምላኪዎች የነበሩ አሕዛብ ናቸው፡፡




ምንጭ፦ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር፤ ገጽ 1734፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 99፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1776






ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍82😁1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“በዮሴፍ ቤት እሳት እንዳትቃጠል፥ በቤቴል የሚያጠፋትም ሳይኖር እንዳትበላ፥ እግዚአብሔርን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ።”
                አሞጽ 5፥6




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3👍1👏1
"እውነት እላችኋለሁ" ከማለት ይልቅ "እውነት እውነት እላችኋለሁ" በማለት የሚታወቀው ወንጌል የቱ ነው?
Anonymous Quiz
32%
ሀ. የማቴዎስ ወንጌል
6%
ለ. የማርቆስ ወንጌል
8%
ሐ. የሉቃስ ወንጌል
55%
መ. የዮሐንስ ወንጌል
👍51
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።”
               ማቴዎስ 5፥44-45




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2👍1🥰1👏1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት

የቀጠለ...


ሮሜ 8፥12-17


2. ልጅነትን የሚሰጥ መንፈስ ነው (ሮሜ 8፡14-17)

እግዚአብሔር የሁሉ ፈጣሪ በመሆኑ፣ ሁሉን በመቸሩና ለሁሉ የሚያስፈልገውን ነገር በመስጠቱ “የሁሉ አባት ነው” የተባለው ከዚህ የተነሣ ነው (ማቴ 5፥45)፡፡ ይሁን እንጂ ሰዎች ሁሉ የእርሱ ልጆች አይደሉም፤ ኢየሱስ በዚህ ምድር ሳለ ለነበሩት ያላመኑ አይሁድ “እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ” ብሎአልና (ዮሐ 8፥44)።
ሰዎች በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ በማመን፤ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉ (ዮሐ 1፥12-13)፤ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራታቸውም የዚህ ግንኙነት ማረጋገጫ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ልጆች የሚባሉት በመንፈስ ቅዱስ የሚመሩ ብቻ ናቸው።

በእግዚኣብሔር መንፈስ የሚመሩ፣ አማኝ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንዲያስብ፣ እንዲናገርና እንዲኖር መንፈስ ቅዱስ በውስጡ ያድራል፡፡

(1) በመሠረቱ ምሪቱ አማኝን የሚያነሣሣ ነው ይኸውም

(ሀ) የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲደረግና ክፉው የሥጋ ሥራ ይሞት ዘንድ ውስጣዊ ማነሣሣት (ቊ 13፤ ፊል 2:13 ቲቶ 2 ፥ 1 -12)፣

(ለ) ምንጊዜም ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የሚስማማ (1ቆሮ 2፡12-13፤ ከ2ጴጥ 1:20-21 ጋር ያነጻጽሩ)፣

(ሐ) የሕይወትን አቅጣጫ በማሳየት ረገድ የታቀደ (ሉቃ 4፥1፤ ሐሥ 10፥19-20፤ 16፥6-7)፣

(መ) ኀጢአት የሞላበትን መሻት የሚቃወም (ገላ 5፥17-18፣ 1ጴጥ 2፥11)

(ሠ) ስለ በደል ወቀሳን የሚያቀርብ፣ ስለ ክርስቶስ የጽድቅ መለኪያና እግዚኣብሔር ክፉውን እንደሚቀጣ የሚሳስብ (ዮሐ 16፥8-11)

(ረ) አማኞች በእምነት እንዲጸኑ የሚመክርና ክርስቶስን ከማመን ውጪ እንዳይሆኑ የሚያስጠነቅቅ (ቍ 13፤ ዕብ 3፥7-14)

(ሰ) አማኞች ለመንፈስ ቅዱስ ማነሣሣት እንቢተኞች በመሆን ሲቀጥሉ ትቶአቸው እንደሚሄድ በማሳየት (1፥28፣ ኤፌ. 4፥17-19:30-31 1ተሰ 5፥19)

(ሸ) ሲተዉት መንፈሳዊ ሞትን በማስከተል (ቊ- 6፥13)፡ እና

(ቀ) ሲታዘዙት መንፈሳዊ ሕይወትንና ሰላምን በመስጠት (ቊ 6፡10-11፡13፤ ገላ 5፥22-23) ነው::

(2) የመንፈስ ቅዱስ ማነሣሣት የሚመጣው በሚከተሉት መንገዶች ነው፦

(ሀ) የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ (ዮሐ 14፥26፤ 15:7:26: 16:131 2ጢሞ 3፥16-17)

(ለ) በትጋት በመጸለይ (ቊ 26፡ ሐሥ 13፥2-3)

(ሐ) መንፈሳዊ ስብከትና ትምህርት በመከታተል (2ጢሞ 4፥1-2፤ ዕብ 13፥7:17)

(መ) የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን መገለጥ በመለማመድ (1ቆሮ 12፥7-10 እና 14፥6)

(ሠ) የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና የታመኑ መንፈሳዊ መሪዎችን ምክር በመስማት (ኤፌ 6፡1፤ ቈላ 3፥20)።




ይቀጥላል...




ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 84፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 367፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1754፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጹሑፍ ጋር፤ ገጽ 1718





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1👍1🥰1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“በዚያች ሰዓት ከደዌና ከሥቃይ ከክፉዎች መናፍስትም ብዙዎችን ፈወሰ፥ ለብዙ ዕውሮችም ማየትን ሰጠ።”
             ሉቃስ 7፥21





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
6👍1🔥1
#እራሳችንን_እንመርምር

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመጣል። ታዲያ ብፁዕ ለመባልና ወደ ደስታው ለመግባት ምን ያስፈልጋል? ለመሆኑ እኔ አሟላ የተባልኩትን ነገር አሟልቼ ይሆን?


“ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።”
ሉቃስ 12፥37


“ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።”
ራእይ 3፥4


“ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 22፥14






ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍21🔥1🥰1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ።”
             ሐዋርያት 24፥16





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
4👍1👏1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ሉቃስ 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ፈሪሳውያንም፦ የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
²¹ ደግሞም፦ እንኋት በዚህ ወይም፦ እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
²² ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ፦ ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
²³ እነርሱም፦ እነሆ በዚህ፥ ወይም፦ እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሂዱ አትከተሉአቸውም።
²⁴ መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ ይሆናል።
²⁵ አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
²⁶ በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
²⁷ ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
²⁸ እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
²⁹ ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
³⁰ የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
³¹ በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
³² የሎጥን ሚስት አስቡአት።
³³ ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
³⁴ እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁵ ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
³⁶ ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
³⁷ መልሰውም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም፦ ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“አንተ እጅግ የተወደድህ ነህና በልመናህ መጀመሪያ ላይ ትእዛዝ ወጥቶአል፥ እኔም እነግርህ ዘንድ መጥቻለሁ፤ አሁንም ነገሩን መርምር፥ ራእዩንም አስተውል።”
            ዳንኤል 9፥23




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2👍1🔥1
የእግዚአብሔር ሦስቱ የምሪት ደረጃዎች



"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8

የእግዚአብሄርን የተስፋ ቃል እንደማወቅ የሚያሳርፍና የሚያስደስት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር የተስፋ ቃሎች ንፁህ ናቸው፡፡የእግዚአብሄር ቃል የነጠረ ነው፡፡

"በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።" መዝሙር 12፡6

"የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።"
ምሳሌ 30፥5

እግዚአብሄር በተስፋ ቃሉ እንዲህ ይላል፡፡

1. አስተምርሃለሁ

እግዚአብሔር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ እግዚአብሔር የፈጠረን ለአላማው ነው፡፡ ከመፈጠራችን በፊት በምድር ላይ ይምንሰራው ስራ ነበር፡፡ የተፈጠረንው እኛ የምንሰራው ስራ ስለነበረ ነው፡፡ ያንን ስራ ሊያሳየን ሊያስተምረን እግዚአብሔር ይፈልጋል፡፡

በእግዚአብሄር ካልተማርንና ካለ እውቀት ከሆንን እንደምንጠፋ እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ በእግዚአብሔር ካልተማርን የተፈጠረንበትን አላማ መፈፀም አንደማንችልና ሰላም እንደማይኖረን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡

"ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።"
ኢሳያስ 54፡13

እኛ መማር ከምንፈልግው በላይ እግዚአብሔር እንድንማርለት ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በመረጠው መንገድ ሃሳቡን ይገልጣል ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፡፡ እግዚአብሔር ሲያስተምር ልባችን ያውቀዋል፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ደረጃ ወርዶ በሚገባን ቋንቋ ያስተምረናል፡፡

"እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤"
ኢዮብ 33፡14


2. በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤

ያስተማረንን እንዴት እንደምንተገብረው ደግሞ ያሳየናል፡፡ አስተምሮን ብቻ ዘወር አይልም፡፡ ያስተማረንን እንዴት እንደምንለማመደው ያሳየናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተማር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ይመራናል፡፡ ስንለማመድ አብሮን ይሆናል፡፡ ማስተማር ብቻ ሳይሆን መንገዱን ያሳየናል፡፡ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በተግባር ይመራናል፡፡ መንፈሱ የተማርነውን ያሳስበናል፡፡ ያ በሃሳብ ደረጃ የተማራችሁት በተግባር ይህ ነው ይለናል፡፡  

"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።"
ዮሐንስ 14፡26


3. ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ

እግዚአብሔር ማስተማርና መምራት ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው መሄዳችንን ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር አይኑን ከእኛ ላይ አይነቅልም፡፡ እግዚአብሔር ከመንገዱ አለመውጣታችንንና በመንገዱ ውስጥ መሆናችንን ይከታተለናል፡፡

"ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።"
መዝሙር 23፡6

እግዚአብሔር በቸርነቱና በምህረቱ በህይወታችን ዘመን ሁሉ ይከታተለናል፡፡ እግዚአብሔር ስለእኛ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡   

"እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።"
መዝሙር 121፡3-4


"አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ።" መዝሙር 32፡8



ምንጭ፦ አብይ ዋቁማ ዲንሳ





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍64🥰1
'         📜📜📜===📜📜📜  
          📜    የዕለቱ ጥቅስ   📜
          📜📜📜===📜📜📜
“በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጌታ ቃል እንዲሮጥ በእናንተም ዘንድ ደግሞ እንደሚሆን እንዲከበር፥ እምነትም ለሁሉ ስለማይሆን ከዓመፀኞችና ከክፉዎች ሰዎች እንድንድን ስለ እኛ ጸልዩ።”
                2ኛ ተሰሎንቄ 3፥1-2






ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
3👍1🥰1
፺፭ቱ_የማርቲን_ሉተር_የመከራከሪያ_ነጥቦች.pdf
109.6 KB
ርዕስ፦ "፺፭ቱ የማርቲን ሉተር መከራከሪያ ነጥቦች"




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures
2👍1