' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም የተናገራቸውን ቃል በልባቸው አሳደሩት፤ ነገር ግን፣ 'ከሙታን መነሣት' ምን ማለት እንደሆነ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።”
ማርቆስ 9፥10 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እነርሱም የተናገራቸውን ቃል በልባቸው አሳደሩት፤ ነገር ግን፣ 'ከሙታን መነሣት' ምን ማለት እንደሆነ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።”
ማርቆስ 9፥10 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1🤔1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ኢየሱስም፦ ገና ጥቂት ጊዜ ብርሃን ከእናንተ ጋር ነው። ጨለማ እንዳይደርስባችሁ ብርሃን ሳለላችሁ ተመላለሱ፤ በጨለማም የሚመላለስ ወዴት እንዲሄድ አያውቅም።”
ዮሐንስ 12፥35
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ኢየሱስም፦ ገና ጥቂት ጊዜ ብርሃን ከእናንተ ጋር ነው። ጨለማ እንዳይደርስባችሁ ብርሃን ሳለላችሁ ተመላለሱ፤ በጨለማም የሚመላለስ ወዴት እንዲሄድ አያውቅም።”
ዮሐንስ 12፥35
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ዕብራውያን 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።
³ በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።
⁴ ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም፤
⁵-⁶ እንደ ልጆችም ከእናንተ ጋር፦ ልጄ ሆይ፥ የጌታን ቅጣት አታቅልል፥ በሚገሥጽህም ጊዜ አትድከም፤ ጌታ የሚወደውን ይቀጣዋልና፥ የሚቀበለውንም ልጅ ሁሉ ይገርፈዋል ብሎ የሚነጋገረውን ምክር ረስታችኋል።
⁷ ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርግላችኋልና፤ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው?
⁸ ነገር ግን ሁሉ የቅጣት ተካፋይ ሆኖአልና ያለ ቅጣት ብትኖሩ ዲቃላዎች እንጂ ልጆች አይደላችሁም።
⁹ ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤ እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን?
¹⁰ እነርሱ መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል።
¹¹ ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።
¹² ስለዚህ የላሉትን እጆች የሰለሉትንም ጉልበቶች አቅኑ፤
¹³ ያነከሰውም እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ፥ ለእግራችሁ ቅን መንገድ አድርጉ።
¹⁴ ከሰው ሁሉ ጋር ሰላምን ተከታተሉ ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና።
¹⁵ የእግዚአብሔር ጸጋ ለማንም እንዳይጎድለው፥ ብዙዎቹም የሚረክሱበት አንድ መራራ ሥር ወደ ላይ በቅሎ እንዳያስጨንቅ፥ ሴሰኛም የሚሆን እንዳይገኝ፥
¹⁶ ወይም ስለ አንድ መብል በኵርነቱን እንደ ሸጠ እንደ ዔሳው ለዚህ ዓለም የሚመች ሰው እንዳይሆን ተጠንቀቁ።
¹⁷ ከዚያ በኋላ እንኳ በረከቱን ሊወርስ በወደደ ጊዜ እንደ ተጣለ ታውቃላችሁና፤ በእንባ ተግቶ ምንም ቢፈልገው ለንስሐ ስፍራ አላገኘምና።
¹⁸ ሊዳሰስ ወደሚችል ወደሚቃጠልም እሳት ወደ ጭጋግም ወደ ጨለማም ወደ ዐውሎ ነፋስም ወደ መለከት ድምፅም ወደ ቃሎችም ነገር አልደረሳችሁምና፤
¹⁹ ያንም ነገር የሰሙት ሌላ ቃል እንዳይጨመርባቸው ለመኑ፤
²⁰ እንስሳ እንኳ ተራራውን ቢነካ ተወግሮ ይሙት የምትለውን ትእዛዝ ሊታገሡ አልቻሉምና፤
²¹ ሙሴም፦ እጅግ እፈራለሁ እንቀጠቀጥማለሁ እስኪል ድረስ የሚታየው እጅግ የሚያስፈራ ነበር፤
²² ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥
²³ በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች፥
²⁴ የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።
²⁵ ለሚናገረው እምቢ እንዳትሉ ተጠንቀቁ፤ እነዚያ በምድር ላስረዳቸው እምቢ ባሉ ጊዜ ካላመለጡ፥ ከሰማይ ከመጣው ፈቀቅ የምንል እኛስ እንዴት እናመልጣለን?
²⁶ በዚያም ጊዜ ድምፁ ምድርን አናወጠ፥ አሁን ግን፦ አንድ ጊዜ ደግሜ እኔ ሰማይን አናውጣለሁ እንጂ ምድርን ብቻ አይደለም ብሎ ተስፋ ሰጥቶአል።
²⁷ ዳሩ ግን፦ አንድ ጊዜ ደግሜ የሚል ቃል፥ የማይናወጡት ጸንተው እንዲኖሩ፥ የሚናወጡት የተፈጠሩ እንደሚሆኑ ይለወጡ ዘንድ ያሳያል።
²⁸ ስለዚህ የማይናወጥን መንግሥት ስለምንቀበል በማክበርና በፍርሃት እግዚአብሔርን ደስ እያሰኘን የምናመልክበትን ጸጋ እንያዝ፤
²⁹ አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ዕብራውያን 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።
³ በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።
⁴ ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም፤
⁵-⁶ እንደ ልጆችም ከእናንተ ጋር፦ ልጄ ሆይ፥ የጌታን ቅጣት አታቅልል፥ በሚገሥጽህም ጊዜ አትድከም፤ ጌታ የሚወደውን ይቀጣዋልና፥ የሚቀበለውንም ልጅ ሁሉ ይገርፈዋል ብሎ የሚነጋገረውን ምክር ረስታችኋል።
⁷ ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርግላችኋልና፤ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው?
⁸ ነገር ግን ሁሉ የቅጣት ተካፋይ ሆኖአልና ያለ ቅጣት ብትኖሩ ዲቃላዎች እንጂ ልጆች አይደላችሁም።
⁹ ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤ እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን?
¹⁰ እነርሱ መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል።
¹¹ ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።
¹² ስለዚህ የላሉትን እጆች የሰለሉትንም ጉልበቶች አቅኑ፤
¹³ ያነከሰውም እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ፥ ለእግራችሁ ቅን መንገድ አድርጉ።
¹⁴ ከሰው ሁሉ ጋር ሰላምን ተከታተሉ ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና።
¹⁵ የእግዚአብሔር ጸጋ ለማንም እንዳይጎድለው፥ ብዙዎቹም የሚረክሱበት አንድ መራራ ሥር ወደ ላይ በቅሎ እንዳያስጨንቅ፥ ሴሰኛም የሚሆን እንዳይገኝ፥
¹⁶ ወይም ስለ አንድ መብል በኵርነቱን እንደ ሸጠ እንደ ዔሳው ለዚህ ዓለም የሚመች ሰው እንዳይሆን ተጠንቀቁ።
¹⁷ ከዚያ በኋላ እንኳ በረከቱን ሊወርስ በወደደ ጊዜ እንደ ተጣለ ታውቃላችሁና፤ በእንባ ተግቶ ምንም ቢፈልገው ለንስሐ ስፍራ አላገኘምና።
¹⁸ ሊዳሰስ ወደሚችል ወደሚቃጠልም እሳት ወደ ጭጋግም ወደ ጨለማም ወደ ዐውሎ ነፋስም ወደ መለከት ድምፅም ወደ ቃሎችም ነገር አልደረሳችሁምና፤
¹⁹ ያንም ነገር የሰሙት ሌላ ቃል እንዳይጨመርባቸው ለመኑ፤
²⁰ እንስሳ እንኳ ተራራውን ቢነካ ተወግሮ ይሙት የምትለውን ትእዛዝ ሊታገሡ አልቻሉምና፤
²¹ ሙሴም፦ እጅግ እፈራለሁ እንቀጠቀጥማለሁ እስኪል ድረስ የሚታየው እጅግ የሚያስፈራ ነበር፤
²² ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥
²³ በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች፥
²⁴ የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።
²⁵ ለሚናገረው እምቢ እንዳትሉ ተጠንቀቁ፤ እነዚያ በምድር ላስረዳቸው እምቢ ባሉ ጊዜ ካላመለጡ፥ ከሰማይ ከመጣው ፈቀቅ የምንል እኛስ እንዴት እናመልጣለን?
²⁶ በዚያም ጊዜ ድምፁ ምድርን አናወጠ፥ አሁን ግን፦ አንድ ጊዜ ደግሜ እኔ ሰማይን አናውጣለሁ እንጂ ምድርን ብቻ አይደለም ብሎ ተስፋ ሰጥቶአል።
²⁷ ዳሩ ግን፦ አንድ ጊዜ ደግሜ የሚል ቃል፥ የማይናወጡት ጸንተው እንዲኖሩ፥ የሚናወጡት የተፈጠሩ እንደሚሆኑ ይለወጡ ዘንድ ያሳያል።
²⁸ ስለዚህ የማይናወጥን መንግሥት ስለምንቀበል በማክበርና በፍርሃት እግዚአብሔርን ደስ እያሰኘን የምናመልክበትን ጸጋ እንያዝ፤
²⁹ አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍2🔥1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ብዙ ጊዜም በብዙ ነገር መርምረን ትጉ እንደ ሆነ ያገኘነውን፥ አሁንም በእናንተ እጅግ ስለሚታመን ከፊት ይልቅ እጅግ ትጉ የሚሆነውን ወንድማችንን ከእነርሱ ጋር እንልካለን።”
2ኛ ቆሮ 8፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ብዙ ጊዜም በብዙ ነገር መርምረን ትጉ እንደ ሆነ ያገኘነውን፥ አሁንም በእናንተ እጅግ ስለሚታመን ከፊት ይልቅ እጅግ ትጉ የሚሆነውን ወንድማችንን ከእነርሱ ጋር እንልካለን።”
2ኛ ቆሮ 8፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1🔥1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በጎውን ማን ያሳየናል? የሚሉ ብዙ ናቸው። አቤቱ፥ የፊትህ ብርሃን በላያችን ታወቀ።”
መዝሙር 4፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በጎውን ማን ያሳየናል? የሚሉ ብዙ ናቸው። አቤቱ፥ የፊትህ ብርሃን በላያችን ታወቀ።”
መዝሙር 4፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1🥰1👏1
#መጻሕፍትን_እንመርምር
አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?
ክፍል-8
በኢየሱስ ከማመናችን በፊት የኃጢአትና «የሰይጣን» ባርያዎች ነበርን (ሮሜ 6፥17)። ካመንን በኋላ ግን የጽድቅ ባርያዎች ሆነናል (ሮሜ 6፥18)። እንዲህ ሲባል የእግዚአብሔርን ጸጋ መቃወምና ደኅንነታችንን ማጣት አይቻልም ማለት ነውን?
በርካታ ክርስቲያኖች ያመኑ ሰዎች ሁሉ ደኅንነታቸውን ማጣት አይችሉም ብለው ያስባሉ። እነዚህ ክርስቲያኖች እንደሚሉት፥ ያመኑ ሰዎች ኃጢአት ሊሠሩና የካዱም ሊመስሉ ይችላሉ ነገር ግን እግዚአብሔር ሁሉጊዜ ወደ ጸጋው ይመልሳቸዋል። ይህንንም «የዘላለም ዋስትና» ብለው ይጠሩታል። እንዲህ ሲሉ «አንዴ የዳነ ሠርክ ድኗል» ማለታቸው ነው።
ሌሎች አያሌ ክርስቲያኖች ግን፥ ያመኑ ሰዎች በእርግጥ እግዚአብሔርን ሊክዱና ደኅንነታቸውንም ሊያጡ ይችላሉ ብለው ያስባሉ። እግዚአብሔር ሊመልሳቸው ይችላል፤ ሆኖም በክህደታቸው ከጸኑ ግን ዳግም ደኅንነትን እንዲቀበሉ አያስገድዳቸውም።
ዋስትና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
ቅዱሳት መጻሕፍት የዘላለም ዋስትናን አስመልክቶ ለሚነሱ ጥያቄዎች ግልጽ መልስ አይሰጡም። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ደኅንነታችንን እንደማናጣ የሚናገሩ ይመስላሉ፤ ሌሎች ክፍሎች ደግሞ ደኅንነታችንን እንደምናጣ የሚናገሩ ይመስላሉ።
ያመኑ ሰዎች እግዚአብሔርን መካድና ደኅንነታቸውንም ማጣት አይችሉም ብለው የሚያስቡት ክርስቲያኖች ሁሉጊዜ የሚያቀርቡት ማስረጃ፥ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት እንደሰጠ የሚናገሩትን ጥቅሶች ነው (ዮሐ. 3፥16፤ 6፥54፤ 11፥26)። ኢየሱስ ሲናገር የእርሱ ለሆኑት በጎች የዘላለምን ሕይወት ሰጥቷቸዋል፤ ስለዚህ ከቶ አይጠፉም፤ "ከእኔ እጅ ማንም ነጥቆ አይወስዳቸውም" ብሏል (ዮሐ 10፥28)። እንዲሁም ወደ እርሱ የሚመጣውን ሁሉ «ወደ ውጪ አላባርረውም» ደግሞም አብ የሚሰጠኝን ሁሉ አንድ እንኳ አላጠፋም ብሏል (ዮሐ. 6፥37፤ 39)። ጳውሎስ በበኩሉ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የሚችል ምንም ነገር እንደሌለና (ሮሜ 8፥38–39) «የርስታችን መያዣ» በሆነው በመንፈስ ቅዱስ እንደታተምንም ተናግሯል (ኤፌ. 1፥14)። በሌላም ቦታ «ይህን መልካም ሥራ በእናንተ ሕይወት ውስጥ የጀመረ አምላክ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ለፍርድ በሚመለስበት ቀን ወደ ፍጻሜ እንደሚያደርሰው እርግጠኛ ነኝ» ብሏል (ፊል. 1፥6)። እግዚአብሔር የሰጠነውን ዐደራ መጠበቅ የሚችል ነው (2ጢሞ. 1፥12)፤ ከፈተና ሊታደገንና (2ጴጥ. 2፥9) እንዳንወድቅም ሊያደርገን የሚችል ነው (ይሁዳ 24)። ከእነዚህ ጥቅሶች እንደምንረዳው አማኞች የዘላለም ዋስትና አላቸው።
ነገር ግን ያመኑ ሰዎች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ብለው የሚናገሩት ክርስቲያኖች፣ ደኅንነታችንን ልናጣ እንደምንችል የሚያስጠነቅቁ ንባቦችን ለምሳሌ፥ «እስከ መጨረሻ በትዕግስት የሚጸና ግን ይድናል» የሚሉትን እንድናይ ይጠቁሙናል (ማር. 13፥13)። ከዚህ በተጨማሪ 1ቆሮ. 15፥12፤ ቆላ. 1፥21-23፤ ዕብ. 3፥6፤ 12፤ 10፥35–36 እንድንመለከት ይጋብዙናል። እንዲሁም ኢየሱስ በዮሐንስ 15፥1–6 ላይ «በእኔ ጸንቶ የማይኖር ሁሉ እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ተጥሎ ይደርቃል ወደ እሳት ይጣልና ይቃጠላል» በማለት የተናገረውንም እንድናጤን ያሳስባሉ። ጳውሎስ በሮሜ 11፥22 ላይ ሲናገር፥ በእግዚአብሔር ምሕረትና ጸጋ ጸንተው የማይኖሩ አረማውያንን «እናንተም ተቆርጣችሁ ትወድቃላችሁ» ብሏል። እንዲሁም የገላትያን ሰዎች ሲያሳስብ ወደ ብሉይ ኪዳን ሕግ የሚመለሱ አማኞችን «ከጸጋው ወድቃችኋል» ብሏል (ገላ. 5፥1–4)። ኢየሱስ ራሱ የዘሪውን ምሳሌ እያብራራ ሳለ «እነርሱ የሚያምኑት ለጊዜው ነው... በፈተና ጊዜ ወዲያውኑ ይክዳሉ» (ሉቃ. 8፥13) በማለት ተናግሯል። ጳውሎስ ሲያስታውቅ «አንዳንድ ሰዎች ሃይማኖትን ይክዳሉ» (1ጢሞ. 4፥1) ብሏል። የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ ደግሞ «የመንፈስ ቅዱስ ተካፋዮች» የነበሩ ሰዎች ወይም በክርስቶስ ደም «የተቀደሱ» ሰዎች ክርስቶስን ሊክዱ እንደሚችሉ ጠቁሟል (ዕብ. 6፥4-6፤ 10፥28–29፤ 39)። አዲስ ኪዳን ሌሎችንም ማስጠንቀቂያዎች ይሰጣል (2ጴጥ. 2፥20–21፤ ራእ. 3፥5፤ 22፥19)። እነዚህ ክርስቲያኖች ደኅንነታችንን የማናጣ ከሆነ እነዚህ ማስጠንቀቂያዎች ለምን ተሰጡ? በማለት ይጠይቃሉ።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?
ክፍል-8
በኢየሱስ ከማመናችን በፊት የኃጢአትና «የሰይጣን» ባርያዎች ነበርን (ሮሜ 6፥17)። ካመንን በኋላ ግን የጽድቅ ባርያዎች ሆነናል (ሮሜ 6፥18)። እንዲህ ሲባል የእግዚአብሔርን ጸጋ መቃወምና ደኅንነታችንን ማጣት አይቻልም ማለት ነውን?
በርካታ ክርስቲያኖች ያመኑ ሰዎች ሁሉ ደኅንነታቸውን ማጣት አይችሉም ብለው ያስባሉ። እነዚህ ክርስቲያኖች እንደሚሉት፥ ያመኑ ሰዎች ኃጢአት ሊሠሩና የካዱም ሊመስሉ ይችላሉ ነገር ግን እግዚአብሔር ሁሉጊዜ ወደ ጸጋው ይመልሳቸዋል። ይህንንም «የዘላለም ዋስትና» ብለው ይጠሩታል። እንዲህ ሲሉ «አንዴ የዳነ ሠርክ ድኗል» ማለታቸው ነው።
ሌሎች አያሌ ክርስቲያኖች ግን፥ ያመኑ ሰዎች በእርግጥ እግዚአብሔርን ሊክዱና ደኅንነታቸውንም ሊያጡ ይችላሉ ብለው ያስባሉ። እግዚአብሔር ሊመልሳቸው ይችላል፤ ሆኖም በክህደታቸው ከጸኑ ግን ዳግም ደኅንነትን እንዲቀበሉ አያስገድዳቸውም።
ዋስትና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
ቅዱሳት መጻሕፍት የዘላለም ዋስትናን አስመልክቶ ለሚነሱ ጥያቄዎች ግልጽ መልስ አይሰጡም። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ደኅንነታችንን እንደማናጣ የሚናገሩ ይመስላሉ፤ ሌሎች ክፍሎች ደግሞ ደኅንነታችንን እንደምናጣ የሚናገሩ ይመስላሉ።
ያመኑ ሰዎች እግዚአብሔርን መካድና ደኅንነታቸውንም ማጣት አይችሉም ብለው የሚያስቡት ክርስቲያኖች ሁሉጊዜ የሚያቀርቡት ማስረጃ፥ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት እንደሰጠ የሚናገሩትን ጥቅሶች ነው (ዮሐ. 3፥16፤ 6፥54፤ 11፥26)። ኢየሱስ ሲናገር የእርሱ ለሆኑት በጎች የዘላለምን ሕይወት ሰጥቷቸዋል፤ ስለዚህ ከቶ አይጠፉም፤ "ከእኔ እጅ ማንም ነጥቆ አይወስዳቸውም" ብሏል (ዮሐ 10፥28)። እንዲሁም ወደ እርሱ የሚመጣውን ሁሉ «ወደ ውጪ አላባርረውም» ደግሞም አብ የሚሰጠኝን ሁሉ አንድ እንኳ አላጠፋም ብሏል (ዮሐ. 6፥37፤ 39)። ጳውሎስ በበኩሉ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የሚችል ምንም ነገር እንደሌለና (ሮሜ 8፥38–39) «የርስታችን መያዣ» በሆነው በመንፈስ ቅዱስ እንደታተምንም ተናግሯል (ኤፌ. 1፥14)። በሌላም ቦታ «ይህን መልካም ሥራ በእናንተ ሕይወት ውስጥ የጀመረ አምላክ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ለፍርድ በሚመለስበት ቀን ወደ ፍጻሜ እንደሚያደርሰው እርግጠኛ ነኝ» ብሏል (ፊል. 1፥6)። እግዚአብሔር የሰጠነውን ዐደራ መጠበቅ የሚችል ነው (2ጢሞ. 1፥12)፤ ከፈተና ሊታደገንና (2ጴጥ. 2፥9) እንዳንወድቅም ሊያደርገን የሚችል ነው (ይሁዳ 24)። ከእነዚህ ጥቅሶች እንደምንረዳው አማኞች የዘላለም ዋስትና አላቸው።
ነገር ግን ያመኑ ሰዎች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ብለው የሚናገሩት ክርስቲያኖች፣ ደኅንነታችንን ልናጣ እንደምንችል የሚያስጠነቅቁ ንባቦችን ለምሳሌ፥ «እስከ መጨረሻ በትዕግስት የሚጸና ግን ይድናል» የሚሉትን እንድናይ ይጠቁሙናል (ማር. 13፥13)። ከዚህ በተጨማሪ 1ቆሮ. 15፥12፤ ቆላ. 1፥21-23፤ ዕብ. 3፥6፤ 12፤ 10፥35–36 እንድንመለከት ይጋብዙናል። እንዲሁም ኢየሱስ በዮሐንስ 15፥1–6 ላይ «በእኔ ጸንቶ የማይኖር ሁሉ እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ተጥሎ ይደርቃል ወደ እሳት ይጣልና ይቃጠላል» በማለት የተናገረውንም እንድናጤን ያሳስባሉ። ጳውሎስ በሮሜ 11፥22 ላይ ሲናገር፥ በእግዚአብሔር ምሕረትና ጸጋ ጸንተው የማይኖሩ አረማውያንን «እናንተም ተቆርጣችሁ ትወድቃላችሁ» ብሏል። እንዲሁም የገላትያን ሰዎች ሲያሳስብ ወደ ብሉይ ኪዳን ሕግ የሚመለሱ አማኞችን «ከጸጋው ወድቃችኋል» ብሏል (ገላ. 5፥1–4)። ኢየሱስ ራሱ የዘሪውን ምሳሌ እያብራራ ሳለ «እነርሱ የሚያምኑት ለጊዜው ነው... በፈተና ጊዜ ወዲያውኑ ይክዳሉ» (ሉቃ. 8፥13) በማለት ተናግሯል። ጳውሎስ ሲያስታውቅ «አንዳንድ ሰዎች ሃይማኖትን ይክዳሉ» (1ጢሞ. 4፥1) ብሏል። የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ ደግሞ «የመንፈስ ቅዱስ ተካፋዮች» የነበሩ ሰዎች ወይም በክርስቶስ ደም «የተቀደሱ» ሰዎች ክርስቶስን ሊክዱ እንደሚችሉ ጠቁሟል (ዕብ. 6፥4-6፤ 10፥28–29፤ 39)። አዲስ ኪዳን ሌሎችንም ማስጠንቀቂያዎች ይሰጣል (2ጴጥ. 2፥20–21፤ ራእ. 3፥5፤ 22፥19)። እነዚህ ክርስቲያኖች ደኅንነታችንን የማናጣ ከሆነ እነዚህ ማስጠንቀቂያዎች ለምን ተሰጡ? በማለት ይጠይቃሉ።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 28
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከእናንተ እግዚአብሔርን የሚፈራ፣ የባሪያውንም ቃል የሚሰማ ማን ነው? ያ ሰው በጨለማ የሚሄድ ከሆነና፣ ብርሃንም ከሌለው፣ በእግዚአብሔር ስም ይታመን፤ በአምላኩም ይደገፍ።”
ኢሳይያስ 50፥10 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ከእናንተ እግዚአብሔርን የሚፈራ፣ የባሪያውንም ቃል የሚሰማ ማን ነው? ያ ሰው በጨለማ የሚሄድ ከሆነና፣ ብርሃንም ከሌለው፣ በእግዚአብሔር ስም ይታመን፤ በአምላኩም ይደገፍ።”
ኢሳይያስ 50፥10 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1🔥1🥰1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥9-11
የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በአማኝ ሕይወት ውስጥ
ነገር ግን አያሌ ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት፥ ቅድስና ጊዜ የሚወስድና በሞትንም ጊዜ እንኳ ፍጻሜ የማያገኝ ረጅም ሂደት ነው። እንዲህ የሚሉት ክርስቲያኖች ለቅድስና ልዩ የሆነ ልምምድ አለ የሚለውን አባባል አይቀበሉም። ከዚህ ይልቅ መጻሕፍት ፍጹማን «ሆነናል» (ገላ. 3፥3፤ ዕብ. 10፥14፤ 12፥10–11) ወይም ኃጢአትን እየታገልን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ በማለት የሚያስተምሩትን እንድናነብ ይጠቁሙናል (ዕብ. 12፥12)። በርካታ አዲስ ኪዳናዊ ንባባት ሰውነታችንን «እንድናለማምድ»፥ ራሳችንን «መሥዋዕት አድርገን እንድናቀርብ»፥ ሩጫችንን በትዕግስት «እንድንሮጥና» እንደሚገባም «እንድንታገል» ያሳስቡናል። ከእነዚህ ንባባት እንደምንረዳው ገና ፈጽሞ ቅዱሳን አልሆንም።
ራሱ ጳውሎስ እንደተናገረው ምንም እንኳን በመንፈሳዊ ሕይወት ከበሰሉት መካከል ቢሆንም (ፊል. 3፥15) ፍጹም ቅዱስ እንዳልሆነና ወደዚያ ቅድስና ለመድረስ ግን እንደሚጣጣር (ፊል. 3፥12-14) አስታውቋል። አንዳንዶች ደግሞ ዮሐንስ፥ በ1ኛ ዮሐንስ 1፥8 ላይ «ኃጢአት የለብንም ብንል እውነተኞች አይደለንም» በማለት የተናገረውን ያመለክቱናል። በክርስቶስ «የበሰሉ» ሰዎች እየሆንን በመጣን ቁጥር ኃጢአታችንንና ደካማነታችንን የበለጠ እየተረዳን እንመጣለን። ጳውሎስ ወደ ሕይወቱ ማብቂያ ግድም ላይ ከኃጢአተኞች ሁሉ «የባስሁ» ኃጢአተኛ ነበርኩ በማለት ተናግሯል (1ጢሞ. 1፥15)። ይህን ሁለተኛውን አመለካከት የሚቀበሉ ክርስቲያኖች እንደሚናገሩት፥ ሮሜ ምዕራፍ 7 የሚያስተምረው በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ከኃጢአት ጋር ስለሚታገሉ ክርስቲያኖች ነው። አንድ ክርስቲያን በሮሜ ምዕራፍ 8 ላይ የተገለጠውን የድል ሕይወት መለማመድ የሚጀምረው ቀስ በቀስ ነው። ይሁንና በዚህ ዓለም ከአሮጌው የሥጋ ፈቃድ ጋር የሚያደርገው ፍልሚያ ከቶ ፍጻሜ አያገኝም።
የእያንዳንዱ ክርስቲያን ልምምድ ለየቅል ነው። በርካታ ክርስቲያኖች ይህን «ሁለተኛ በረከት» ወይም ልዩ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት እንደተቀበሉ ይናገራሉ። አንዳንድ ክርስቲያኖች በየጊዜው ወይም ቀስ በቀስ ከሚለማመዱት ቅድስና በተጨማሪ ድንገት የሚለማመዱት ቅድስናም እንዳለ ይናገራሉ። እግዚአብሔር በተለያዩ ሰዎች ሕይወት ውስጥ በተለያየ መንገድ ይሠራል። የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በእኛ ውሱን ልምምድ መወሰን የለብንም።
ስለ ቅድስና ልምምድ ያለን አመለካከት የቱንም ያህል ቢለያይ፥ አንድ ግልጽ የሆነ ኀላፊነት ግን አለብን። ይኸውም ቅዱሳን እንድንሆን ታዘናል። ጴጥሮስ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፥ «… በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ» (1ጴጥ. 1፥15)። «ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ፤ በቅድስናም ለመኖር ትጉ፤ ምክንያቱም ያለ ቅድስና ማንም እግዚአብሔርን ማየት አይችልም» (ዕብ. 12፥14)።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 33
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
የቀጠለ...
ሮሜ 8፥9-11
የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በአማኝ ሕይወት ውስጥ
ነገር ግን አያሌ ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት፥ ቅድስና ጊዜ የሚወስድና በሞትንም ጊዜ እንኳ ፍጻሜ የማያገኝ ረጅም ሂደት ነው። እንዲህ የሚሉት ክርስቲያኖች ለቅድስና ልዩ የሆነ ልምምድ አለ የሚለውን አባባል አይቀበሉም። ከዚህ ይልቅ መጻሕፍት ፍጹማን «ሆነናል» (ገላ. 3፥3፤ ዕብ. 10፥14፤ 12፥10–11) ወይም ኃጢአትን እየታገልን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ በማለት የሚያስተምሩትን እንድናነብ ይጠቁሙናል (ዕብ. 12፥12)። በርካታ አዲስ ኪዳናዊ ንባባት ሰውነታችንን «እንድናለማምድ»፥ ራሳችንን «መሥዋዕት አድርገን እንድናቀርብ»፥ ሩጫችንን በትዕግስት «እንድንሮጥና» እንደሚገባም «እንድንታገል» ያሳስቡናል። ከእነዚህ ንባባት እንደምንረዳው ገና ፈጽሞ ቅዱሳን አልሆንም።
ራሱ ጳውሎስ እንደተናገረው ምንም እንኳን በመንፈሳዊ ሕይወት ከበሰሉት መካከል ቢሆንም (ፊል. 3፥15) ፍጹም ቅዱስ እንዳልሆነና ወደዚያ ቅድስና ለመድረስ ግን እንደሚጣጣር (ፊል. 3፥12-14) አስታውቋል። አንዳንዶች ደግሞ ዮሐንስ፥ በ1ኛ ዮሐንስ 1፥8 ላይ «ኃጢአት የለብንም ብንል እውነተኞች አይደለንም» በማለት የተናገረውን ያመለክቱናል። በክርስቶስ «የበሰሉ» ሰዎች እየሆንን በመጣን ቁጥር ኃጢአታችንንና ደካማነታችንን የበለጠ እየተረዳን እንመጣለን። ጳውሎስ ወደ ሕይወቱ ማብቂያ ግድም ላይ ከኃጢአተኞች ሁሉ «የባስሁ» ኃጢአተኛ ነበርኩ በማለት ተናግሯል (1ጢሞ. 1፥15)። ይህን ሁለተኛውን አመለካከት የሚቀበሉ ክርስቲያኖች እንደሚናገሩት፥ ሮሜ ምዕራፍ 7 የሚያስተምረው በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ከኃጢአት ጋር ስለሚታገሉ ክርስቲያኖች ነው። አንድ ክርስቲያን በሮሜ ምዕራፍ 8 ላይ የተገለጠውን የድል ሕይወት መለማመድ የሚጀምረው ቀስ በቀስ ነው። ይሁንና በዚህ ዓለም ከአሮጌው የሥጋ ፈቃድ ጋር የሚያደርገው ፍልሚያ ከቶ ፍጻሜ አያገኝም።
የእያንዳንዱ ክርስቲያን ልምምድ ለየቅል ነው። በርካታ ክርስቲያኖች ይህን «ሁለተኛ በረከት» ወይም ልዩ የሆነ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት እንደተቀበሉ ይናገራሉ። አንዳንድ ክርስቲያኖች በየጊዜው ወይም ቀስ በቀስ ከሚለማመዱት ቅድስና በተጨማሪ ድንገት የሚለማመዱት ቅድስናም እንዳለ ይናገራሉ። እግዚአብሔር በተለያዩ ሰዎች ሕይወት ውስጥ በተለያየ መንገድ ይሠራል። የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በእኛ ውሱን ልምምድ መወሰን የለብንም።
ስለ ቅድስና ልምምድ ያለን አመለካከት የቱንም ያህል ቢለያይ፥ አንድ ግልጽ የሆነ ኀላፊነት ግን አለብን። ይኸውም ቅዱሳን እንድንሆን ታዘናል። ጴጥሮስ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፥ «… በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ» (1ጴጥ. 1፥15)። «ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ፤ በቅድስናም ለመኖር ትጉ፤ ምክንያቱም ያለ ቅድስና ማንም እግዚአብሔርን ማየት አይችልም» (ዕብ. 12፥14)።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 33
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍2🔥1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የእርሱ ለመሆናችን ማኅተሙን ያተመብን ደግሞም ወደ ፊት ለምናገኘው ነገር የመንፈሱን ዋስትና በልባችን ያኖረ እርሱ ነው።”
2ኛ ቆሮንቶስ 1፥22 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የእርሱ ለመሆናችን ማኅተሙን ያተመብን ደግሞም ወደ ፊት ለምናገኘው ነገር የመንፈሱን ዋስትና በልባችን ያኖረ እርሱ ነው።”
2ኛ ቆሮንቶስ 1፥22 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1👏1
ከእግዚአብሔር ስሞች መካከል "ጆሆቫ ራፋ" አንዱ ነው። ትርጉሙ ምን ማለት ነው?
Anonymous Quiz
24%
ሀ. እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ
16%
ለ. እግዚአብሔር ዓለማዬ ነው
39%
ሐ. እግዚአብሔር ፈዋሽ
6%
መ. ጌታ
14%
ሠ. እግዚአብሔር ያዘጋጃል
👍3❤1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕዳ አለብን፥ እንደ ሥጋ ፈቃድ ግን እንኖር ዘንድ ለሥጋ አይደለም።
¹³ እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ።
¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
¹⁵ አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።
¹⁶ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።
¹⁷ ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።
ሮሜ 8 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፤ ግዴታ አለብን፤ ይሁን እንጂ እንደ ሥጋ እንድንኖር ለሥጋ አይደለም።
¹³ እንደ ሥጋ ብትኖሩ ትሞታላችሁና፤ ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ በመንፈስ ብትገድሉ ግን፣ በሕይወት ትኖራላችሁ፤
¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
¹⁵ እንደ ገና የፍርሀት ባሪያ የሚያደርጋችሁን መንፈስ ሳይሆን፣ “አባ፣ አባት” ብለን የምንጠራበትን የልጅነት መንፈስ ተቀብላችኋልና፤
¹⁶ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ሆኖ ይመሰክርልናል።
¹⁷ ልጆች ከሆን ወራሾች ደግሞ ነን፤ የክብሩ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ በርግጥ የመከራው ተካፋዮች ብንሆን፣ የእግዚአብሔር ወራሾች፣ ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።
ሮሜ 8 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ስለዚህ ወንድሞቼ ሆይ ፥ ለሥጋዊ ፈቃድ ተሸንፋችሁ ልትገዙለት አይገባም።
¹³ ለሥጋ ፈቃዳችሁ ተገዢዎች ከሆናችሁ ትሞታላችሁ። የሥጋ ፈቃዳችሁን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ድል ከነሳችሁት ግን በሕይወት ትኖራላችሁ።
¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው።
¹⁵ ስለዚህ የተሰጠን መንፈስ በአባቱ እቅፍ እንዳለ ልጅ ፥ 'አባ ፥ አባባ!' ብለን በድፍረት እግዚአብሔርን የምንጠራበት የልጅነት መንፈስ እንጂ ፥ የሚያስፈራና የሚያሸማቅቅ የተገዢነት መንፈስ አይደለም።
¹⁶ በእርግጥም የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ፥ ራሱ መንፈስ ቅዱስም ሆነ የራሳችንም መንፈስ ያረጋግጥልናል።
¹⁷ የእግዚአብ ሔር ልጆች ከሆንን ፥ ወራሾች ነን ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስም ጋር አብረን የርስቱ ተካፋዮች እንሆናለን። ከእርሱ ጋር አብረን መክበር የምንችለውም ፥ የክርስቶስ የመከራው ተካፋዮች ሆነን ስንገኝ ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕዳ አለብን፥ እንደ ሥጋ ፈቃድ ግን እንኖር ዘንድ ለሥጋ አይደለም።
¹³ እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ።
¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
¹⁵ አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።
¹⁶ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።
¹⁷ ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።
ሮሜ 8 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፤ ግዴታ አለብን፤ ይሁን እንጂ እንደ ሥጋ እንድንኖር ለሥጋ አይደለም።
¹³ እንደ ሥጋ ብትኖሩ ትሞታላችሁና፤ ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ በመንፈስ ብትገድሉ ግን፣ በሕይወት ትኖራላችሁ፤
¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
¹⁵ እንደ ገና የፍርሀት ባሪያ የሚያደርጋችሁን መንፈስ ሳይሆን፣ “አባ፣ አባት” ብለን የምንጠራበትን የልጅነት መንፈስ ተቀብላችኋልና፤
¹⁶ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ሆኖ ይመሰክርልናል።
¹⁷ ልጆች ከሆን ወራሾች ደግሞ ነን፤ የክብሩ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ በርግጥ የመከራው ተካፋዮች ብንሆን፣ የእግዚአብሔር ወራሾች፣ ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።
ሮሜ 8 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ስለዚህ ወንድሞቼ ሆይ ፥ ለሥጋዊ ፈቃድ ተሸንፋችሁ ልትገዙለት አይገባም።
¹³ ለሥጋ ፈቃዳችሁ ተገዢዎች ከሆናችሁ ትሞታላችሁ። የሥጋ ፈቃዳችሁን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ድል ከነሳችሁት ግን በሕይወት ትኖራላችሁ።
¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው።
¹⁵ ስለዚህ የተሰጠን መንፈስ በአባቱ እቅፍ እንዳለ ልጅ ፥ 'አባ ፥ አባባ!' ብለን በድፍረት እግዚአብሔርን የምንጠራበት የልጅነት መንፈስ እንጂ ፥ የሚያስፈራና የሚያሸማቅቅ የተገዢነት መንፈስ አይደለም።
¹⁶ በእርግጥም የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ፥ ራሱ መንፈስ ቅዱስም ሆነ የራሳችንም መንፈስ ያረጋግጥልናል።
¹⁷ የእግዚአብ ሔር ልጆች ከሆንን ፥ ወራሾች ነን ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስም ጋር አብረን የርስቱ ተካፋዮች እንሆናለን። ከእርሱ ጋር አብረን መክበር የምንችለውም ፥ የክርስቶስ የመከራው ተካፋዮች ሆነን ስንገኝ ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1🔥1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ለራስሽ የመንገድ ምልክት አድርጊ፥ መንገድንም የሚመሩ ዓምዶችን ትከዪ፥ ልብሽንም ወደ ሄድሽበት መንገድ ወደ ጥርጊያው አቅኚ፤ አንቺ የእስራኤል ድንግል ሆይ፥ ተመለሺ፥ ወደ እነዚህም ወደ ከተሞችሽ ተመለሺ።”
ኤርምያስ 31፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ለራስሽ የመንገድ ምልክት አድርጊ፥ መንገድንም የሚመሩ ዓምዶችን ትከዪ፥ ልብሽንም ወደ ሄድሽበት መንገድ ወደ ጥርጊያው አቅኚ፤ አንቺ የእስራኤል ድንግል ሆይ፥ ተመለሺ፥ ወደ እነዚህም ወደ ከተሞችሽ ተመለሺ።”
ኤርምያስ 31፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1👏1
#እራሳችንን_እንመርምር
ከጌታችን እና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረን ወራሽ መሆን እንፈልጋለን? ታዲያ እርሱ ያለፈበትን መንገድ ጠልተን እንዴት ከእርሱ ጋር ወራሽ እንሆናለን? ጌታችን በምን ጎዳና ይሆን ያለፈው?
“ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።”
ሮሜ 8፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ከጌታችን እና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረን ወራሽ መሆን እንፈልጋለን? ታዲያ እርሱ ያለፈበትን መንገድ ጠልተን እንዴት ከእርሱ ጋር ወራሽ እንሆናለን? ጌታችን በምን ጎዳና ይሆን ያለፈው?
“ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።”
ሮሜ 8፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4👍1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤”
ቆላስይስ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤”
ቆላስይስ 2፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤4🔥1🥰1
#መጻሕፍትን_እንመርምር
አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?
ክፍል-9
(የመጨረሻ ክፍል)
ዮሐንስ ሲጽፍ፥ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች «የወጡት ከእኛ መካከል ነው። ይሁን እንጂ ድሮውንም ከእኛ ወገን አልነበሩም ... ከእኛ ወገን አለመሆናቸው እንዲታወቅ ከእኛ መካከል ተለይተው ወጥተዋል» ብሏል (1ዮሐ. 2፥19)። አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ አይችሉም የሚሉት ሰዎች ከመንገድ የወጡ ወይም የካዱ ሰዎች ገና ከመጀመሪያው እውነተኛ አማኞች አልነበሩም ይላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ የሚሉት ሰዎች፤ ከመንገድ የወጡ ወይም የካዱ ሰዎች ቀድሞ እውነተኛ አማኞች ሊሆኑና አንዳንዶቹ ደግሞ እውነተኛ አማኞች ላይሆኑ ይችላሉ፤ እውነተኛ አማኞች የነበሩና ክርስቶስን የካዱ ሰዎች ግን ከእኛ ወገን አይደሉም ይላሉ። ሐሰተኛው ክርስቲያን የቱ እንደሆነና እውነተኛው ክርስቲያን ደግሞ የቱ እንደሆነ ዳኝነት ስንሰጥ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን (ማቴ. 7፥12)። ከዚህ በተጨማሪ ከመንገድ ከቶ አንወጣም ወይም ከሀዲያንም ከቶ አንሆንም የሚል ትምክህተኝነት እንዳይዘን ልንጠነቀቅ ይገባል። ጳውሎስ ሲናገር፥ «… የቆመ የሚመስለው ሰው፥ እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ» ብሏል (1ቆሮ. 10፥12)። ዮሐንስ ሲጽፍ ደግሞ እንዲህ በማለት አሳስቧል፥ «እናንተ ግን ከመጀመሪያው የሰማችሁት ቃል በልባችሁ ጸንቶ ከኖረ፥ ከወልድና ከአብ ጋር ኅብረት ይኖራችኋል» (1ዮሐ. 2፥24)።
እንግዲህ እስከ አሁን ድረስ እንደተመለከትነው፥ አንዳንድ አዲስ ኪዳናዊ ንባባት አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ አይችሉም የሚለውን ሀሳብ ይደግፋሉ። ሌሎች ንባባት ደግሞ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ የሚለውን ሀሳብ ይደግፋሉ። በእርግጥ ከዚህ ላይ የምናየው አዕምሮአችን ሙሉ በሙሉ ሊጨብጠው የማይችለውን ሁለት ገጽታ ያለውን ታላቅ እውነት ነው። ከእኛ ይልቅ የእግዚአብሔር ጥበብ እጅግ ታላቅ ነውና።
አማኞች እነዚህን ሁለት እውነቶች አጣምረው መያዝ አለባቸው ሲል አንድ ሰው ተናግሯል። ይሁን እንጂ ስለ ደኅንነቱ ብዙ የሚያሳስበው አማኝ ደኅንነቱ ዋስትና እንዳለው አጽንኦት መስጠት አለበት። በሌላ በኩል ደግሞ ከመንገድ አልወጣም እያለ ከልክ በላይ የሚታመን አማኝ በእርግጥ ከመንገድ ሊወጣ እንደሚችል አጽንኦት ሊሰጥ ይገባል። አሁንም ከዚህ ላይ የምናየው፥ መጽሐፍ ቅዱስ ጥልቅና ሰፊ መሆኑን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሰዎችን ሁሉ ፍላጎት ያሟላል።
ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት አለ» ሲባል ምን ማለት ነው?
በ1ዮሐ. 5፥16–17 ላይ «ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት» ለሠራ ወንድም (ክርስቲያን) እንዳንጸልይ ታዘናል። ዮሐንስ በዚህ ቦታ የሚናገረው ስለ መንፈሳዊ ሞት ሊሆን ይችላል። ሆኖም ጸሐፊው በዚህ ቦታ የሚናገረው ነፍሱ ስለማትጠፋው (1ቆሮ. 5፥5) ነገር ግን ኃጢአትን ስለሚሠራ ክርስቲያን ሥጋዊ ሞት ሊሆንም ይችላል። ዮሐንስ የሚናገረው ስለ መንፈሳዊ ሞት ከሆነ ይህ ንባብ አማኝ ደኅንነቱን ሊያጣ ይችላል የሚሉትን ሰዎች ይደግፋል። ይሁንና ዮሐንስ ያ ኃጢአት ምን እንደሆነ በትክክል አልተናገረም።
ምናልባት ይህ «ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት» በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል መናገር ሊሆን ይችላል። ኢየሱስም ቢሆን እንዲህ ዓይነቱ ኃጢአት ስርየት አያገኝም ብሏል (ማር. 3፥28–29)። እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ኢየሱስ አንድ ክርስቲያን እንዲህ ያለውን ኃጢአት ሊፈጽም ይችላል ወይም አይችልም ብሎ ያልተናገረ መሆኑን ነው። ነገር ግን የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ እንዲህ ያለው አጋጣሚ ሊከስት እንደሚችል ማለትም አማኝ የነበረ ሰው («የመንፈስ ቅዱስ ተካፋይ» የነበረ ሰው) እግዚአብሔርን ሊክድና ጌታንም ሊያዋርድ እንደሚችል ተናግሯል። "ከዚህ ሁሉ በኋላ ከመንገድ ከወጡ፥ እነርሱን ወደ ንስሓ መመለስ አይቻልም" (ዕብ. 6፥4–6)። በዚሁ መልእክት ምዕራፍ 10 ላይ ጸሐፊው ሲናገር እንዲህ ብሏል፦"እውነትን ካወቅን በኋላ ሆነ ብለን ኃጢአት ብንሠራ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኃጢአት የሚቀርብ ምንም መሥዋዕት አይኖረንም" (ዕብ. 10፥26)። ከዚህ በኋላ ጸሐፊው አማኝ ስለነበሩና በኢየሱስም ደም «ስለተቀደሱ» እንዲሁም «የእግዚአብሔርን ልጅ ስለናቁ» እና «የጸጋን መንፈስ ስለሰደቡ» ሰዎች ያወሳል (ዕብ. 10፥29)። እንግዲህ የእግዚአብሔርን መንፈስ የካዱና ኃጢአትም በመሥራት የቀጠሉ ሰዎች የእግዚአብሔርን ድምጽ ከቶ ሊሰሙ አይችሉም። ሁሉን ከተረዱ በኋላ በኃጢአት ጸንተው የሚቀጥሉ ሰዎች ልባቸው ይደነድናል። እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት አይችሉም፣ እግዚአብሔርም ከእንግዲህ በኋላ ዳግም ላይጠራቸው ይችላሉ።
በርካታ ክርስቲያኖች አንድ አማኝ ከመንገድ ሊወጣና የክርስቶስንም ጥሪ አልቀበልም በማለት በእምቢተኝነት ጸንቶ ሊቀጥል እንደሚችልና እነዚህም ንባቦች (ዕብ. 6፥4–6፤ 10፥26–31) የሚያስጠነቅቁት ይኼንኑ ሁኔታ እንደሆነ ይናገራሉ። ሌሎች ክርስቲያኖች ደግሞ እውነተኛ አማኞች እስከመጥፋት ደረጃ አይደርሱም፥ ይልቁንም ወደ ሞት ከመድረሳቸው በፊት ዘወትር ንስሓ በመግባትና በጽኑም በማመን በእምነት ይቀጥላሉ ይላሉ።
ማጠቃለያ
ክርስቲያን የሆኑ ሁሉ እንደሚያምኑት ደኅንነትን ያገኘነው በእግዚአብሔር ጸጋና ምሕረት ብቻ፥ እንዲሁም በእምነት አማካይነት በኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ኤፌ. 2፥8–9)። ደግሞም ክርስቲያን የሆኑ ሁሉ እንደሚያምኑት በእምነት ጸንተን የምንዘልቀው በመንፈስ ቅዱስ እገዛ ብቻ ነው (ገላ. 3፥3)። ይሁንና አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ ክርስቲያኖች አንድ እውነተኛ አማኝ ደኅንነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም በሚለው ጉዳይ ላይ ያላቸው የተለያየ አመለካከት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ጉዳይ ላይ ቁርጥ ያለ ትምህርት አይሰጥም። ስለሆነም የትኛውንም አቋም ብንይዝ የያዝነው አቋም ግን በዚህ ጥያቄ ላይ የተለየ አመለላለት ካላቸው ከሌሎች ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች ጋር ሊለየን አይገባም። እነዚህ ሁለት አመለካከቶች ማለትም አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ወይም አይችሉም የሚሉት በይሁዳ መልእክት ላይ ጎን ለጎን ተጠቅሰዋል። በቁጥር 21 ላይ ይሁዳ ሲጽፍ፥ «...በምሕረቱ የዘላለም ሕይወት እንዲሰጣችሁ በመጠባበቅ ራሳችሁን በእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ ጠብቁት» ብሏል። በቁጥር 24 ላይ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንድንመለከት እየጠቆመን እንዲህ በማለት ይናገራል፥ «እንዳትወድቁ ሊያድርጋችሁና ያለ ነቀፋም አድርጎ በደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችል፥ ... አሁንም፥ ለዘላለምም ክብርና ግርማ፥ ኃይልና ሥልጣንም ይሁን አሜን»።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?
ክፍል-9
(የመጨረሻ ክፍል)
ዮሐንስ ሲጽፍ፥ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች «የወጡት ከእኛ መካከል ነው። ይሁን እንጂ ድሮውንም ከእኛ ወገን አልነበሩም ... ከእኛ ወገን አለመሆናቸው እንዲታወቅ ከእኛ መካከል ተለይተው ወጥተዋል» ብሏል (1ዮሐ. 2፥19)። አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ አይችሉም የሚሉት ሰዎች ከመንገድ የወጡ ወይም የካዱ ሰዎች ገና ከመጀመሪያው እውነተኛ አማኞች አልነበሩም ይላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ የሚሉት ሰዎች፤ ከመንገድ የወጡ ወይም የካዱ ሰዎች ቀድሞ እውነተኛ አማኞች ሊሆኑና አንዳንዶቹ ደግሞ እውነተኛ አማኞች ላይሆኑ ይችላሉ፤ እውነተኛ አማኞች የነበሩና ክርስቶስን የካዱ ሰዎች ግን ከእኛ ወገን አይደሉም ይላሉ። ሐሰተኛው ክርስቲያን የቱ እንደሆነና እውነተኛው ክርስቲያን ደግሞ የቱ እንደሆነ ዳኝነት ስንሰጥ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን (ማቴ. 7፥12)። ከዚህ በተጨማሪ ከመንገድ ከቶ አንወጣም ወይም ከሀዲያንም ከቶ አንሆንም የሚል ትምክህተኝነት እንዳይዘን ልንጠነቀቅ ይገባል። ጳውሎስ ሲናገር፥ «… የቆመ የሚመስለው ሰው፥ እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ» ብሏል (1ቆሮ. 10፥12)። ዮሐንስ ሲጽፍ ደግሞ እንዲህ በማለት አሳስቧል፥ «እናንተ ግን ከመጀመሪያው የሰማችሁት ቃል በልባችሁ ጸንቶ ከኖረ፥ ከወልድና ከአብ ጋር ኅብረት ይኖራችኋል» (1ዮሐ. 2፥24)።
እንግዲህ እስከ አሁን ድረስ እንደተመለከትነው፥ አንዳንድ አዲስ ኪዳናዊ ንባባት አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ አይችሉም የሚለውን ሀሳብ ይደግፋሉ። ሌሎች ንባባት ደግሞ አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ የሚለውን ሀሳብ ይደግፋሉ። በእርግጥ ከዚህ ላይ የምናየው አዕምሮአችን ሙሉ በሙሉ ሊጨብጠው የማይችለውን ሁለት ገጽታ ያለውን ታላቅ እውነት ነው። ከእኛ ይልቅ የእግዚአብሔር ጥበብ እጅግ ታላቅ ነውና።
አማኞች እነዚህን ሁለት እውነቶች አጣምረው መያዝ አለባቸው ሲል አንድ ሰው ተናግሯል። ይሁን እንጂ ስለ ደኅንነቱ ብዙ የሚያሳስበው አማኝ ደኅንነቱ ዋስትና እንዳለው አጽንኦት መስጠት አለበት። በሌላ በኩል ደግሞ ከመንገድ አልወጣም እያለ ከልክ በላይ የሚታመን አማኝ በእርግጥ ከመንገድ ሊወጣ እንደሚችል አጽንኦት ሊሰጥ ይገባል። አሁንም ከዚህ ላይ የምናየው፥ መጽሐፍ ቅዱስ ጥልቅና ሰፊ መሆኑን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሰዎችን ሁሉ ፍላጎት ያሟላል።
ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት አለ» ሲባል ምን ማለት ነው?
በ1ዮሐ. 5፥16–17 ላይ «ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት» ለሠራ ወንድም (ክርስቲያን) እንዳንጸልይ ታዘናል። ዮሐንስ በዚህ ቦታ የሚናገረው ስለ መንፈሳዊ ሞት ሊሆን ይችላል። ሆኖም ጸሐፊው በዚህ ቦታ የሚናገረው ነፍሱ ስለማትጠፋው (1ቆሮ. 5፥5) ነገር ግን ኃጢአትን ስለሚሠራ ክርስቲያን ሥጋዊ ሞት ሊሆንም ይችላል። ዮሐንስ የሚናገረው ስለ መንፈሳዊ ሞት ከሆነ ይህ ንባብ አማኝ ደኅንነቱን ሊያጣ ይችላል የሚሉትን ሰዎች ይደግፋል። ይሁንና ዮሐንስ ያ ኃጢአት ምን እንደሆነ በትክክል አልተናገረም።
ምናልባት ይህ «ለሞት የሚያደርስ ኃጢአት» በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል መናገር ሊሆን ይችላል። ኢየሱስም ቢሆን እንዲህ ዓይነቱ ኃጢአት ስርየት አያገኝም ብሏል (ማር. 3፥28–29)። እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ኢየሱስ አንድ ክርስቲያን እንዲህ ያለውን ኃጢአት ሊፈጽም ይችላል ወይም አይችልም ብሎ ያልተናገረ መሆኑን ነው። ነገር ግን የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ እንዲህ ያለው አጋጣሚ ሊከስት እንደሚችል ማለትም አማኝ የነበረ ሰው («የመንፈስ ቅዱስ ተካፋይ» የነበረ ሰው) እግዚአብሔርን ሊክድና ጌታንም ሊያዋርድ እንደሚችል ተናግሯል። "ከዚህ ሁሉ በኋላ ከመንገድ ከወጡ፥ እነርሱን ወደ ንስሓ መመለስ አይቻልም" (ዕብ. 6፥4–6)። በዚሁ መልእክት ምዕራፍ 10 ላይ ጸሐፊው ሲናገር እንዲህ ብሏል፦"እውነትን ካወቅን በኋላ ሆነ ብለን ኃጢአት ብንሠራ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኃጢአት የሚቀርብ ምንም መሥዋዕት አይኖረንም" (ዕብ. 10፥26)። ከዚህ በኋላ ጸሐፊው አማኝ ስለነበሩና በኢየሱስም ደም «ስለተቀደሱ» እንዲሁም «የእግዚአብሔርን ልጅ ስለናቁ» እና «የጸጋን መንፈስ ስለሰደቡ» ሰዎች ያወሳል (ዕብ. 10፥29)። እንግዲህ የእግዚአብሔርን መንፈስ የካዱና ኃጢአትም በመሥራት የቀጠሉ ሰዎች የእግዚአብሔርን ድምጽ ከቶ ሊሰሙ አይችሉም። ሁሉን ከተረዱ በኋላ በኃጢአት ጸንተው የሚቀጥሉ ሰዎች ልባቸው ይደነድናል። እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት አይችሉም፣ እግዚአብሔርም ከእንግዲህ በኋላ ዳግም ላይጠራቸው ይችላሉ።
በርካታ ክርስቲያኖች አንድ አማኝ ከመንገድ ሊወጣና የክርስቶስንም ጥሪ አልቀበልም በማለት በእምቢተኝነት ጸንቶ ሊቀጥል እንደሚችልና እነዚህም ንባቦች (ዕብ. 6፥4–6፤ 10፥26–31) የሚያስጠነቅቁት ይኼንኑ ሁኔታ እንደሆነ ይናገራሉ። ሌሎች ክርስቲያኖች ደግሞ እውነተኛ አማኞች እስከመጥፋት ደረጃ አይደርሱም፥ ይልቁንም ወደ ሞት ከመድረሳቸው በፊት ዘወትር ንስሓ በመግባትና በጽኑም በማመን በእምነት ይቀጥላሉ ይላሉ።
ማጠቃለያ
ክርስቲያን የሆኑ ሁሉ እንደሚያምኑት ደኅንነትን ያገኘነው በእግዚአብሔር ጸጋና ምሕረት ብቻ፥ እንዲሁም በእምነት አማካይነት በኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ኤፌ. 2፥8–9)። ደግሞም ክርስቲያን የሆኑ ሁሉ እንደሚያምኑት በእምነት ጸንተን የምንዘልቀው በመንፈስ ቅዱስ እገዛ ብቻ ነው (ገላ. 3፥3)። ይሁንና አዲስ ኪዳን ከተጻፈበት ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ ክርስቲያኖች አንድ እውነተኛ አማኝ ደኅንነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም በሚለው ጉዳይ ላይ ያላቸው የተለያየ አመለካከት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ጉዳይ ላይ ቁርጥ ያለ ትምህርት አይሰጥም። ስለሆነም የትኛውንም አቋም ብንይዝ የያዝነው አቋም ግን በዚህ ጥያቄ ላይ የተለየ አመለላለት ካላቸው ከሌሎች ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች ጋር ሊለየን አይገባም። እነዚህ ሁለት አመለካከቶች ማለትም አማኞች ደኅንነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ወይም አይችሉም የሚሉት በይሁዳ መልእክት ላይ ጎን ለጎን ተጠቅሰዋል። በቁጥር 21 ላይ ይሁዳ ሲጽፍ፥ «...በምሕረቱ የዘላለም ሕይወት እንዲሰጣችሁ በመጠባበቅ ራሳችሁን በእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ ጠብቁት» ብሏል። በቁጥር 24 ላይ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንድንመለከት እየጠቆመን እንዲህ በማለት ይናገራል፥ «እንዳትወድቁ ሊያድርጋችሁና ያለ ነቀፋም አድርጎ በደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችል፥ ... አሁንም፥ ለዘላለምም ክብርና ግርማ፥ ኃይልና ሥልጣንም ይሁን አሜን»።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 28-29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በብዙ መከራ ተፈትነው ሳሉ የደስታቸው ብዛትና የድህነታቸው ጥልቅነት የልግስናቸውን ባለ ጠግነት አብዝቶአል፤”
2ኛ ቆሮ 8፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በብዙ መከራ ተፈትነው ሳሉ የደስታቸው ብዛትና የድህነታቸው ጥልቅነት የልግስናቸውን ባለ ጠግነት አብዝቶአል፤”
2ኛ ቆሮ 8፥2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🥰1👏1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 8፥12-17
«መንፈስ ወርሷችኋል» (ሮሜ 8፡12-17)
እኛ መንፈስ ስላለን ብቻ በቂ አይደለም፤ መንፈስ እኛን ሊወርሰንም ያስፈልጋል፡፡ የተትረፈረፈው የድል ሕይወት በክርስቶስ በኩል የእኛ የሚሆነው በዚህ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ሥጋችን ለሕይወታችን ከችግር በቀር ያመጣልን ነገር ስለሌለ፣ የሥጋ ዕዳ የለብንም፡፡ ክርስቶስን ባመንን ጊዜ በኃጢአታችን የወቀሰን፣ ክርስቶስን የገለጠልንና የዘለዓለም ሕይወት ያካፈለን መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ የእርሱ ዕዳ አለብን፡፡
በክርስቶስ ኢየሱስ ከሆንን መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር አለ። ስለዚህም
1. በእርሱ ኃይል የሰውነትን ሥራ እንድንገድል ያስችለናል። (ቁ. 13)
ኀጢአት ሁልጊዜ የራሱ ሊያደርገን ስለሚፈልግ፣ በሕይወታችን የእግዚአብሔርን ሥራ ሊገድብ ከሚችል ነገር ሁሉ ጋር ያለማቋረጥ መጋደል እንደሚገባ ጳውሎስ አሳስቧል (ከ6፥11-19):: ይህ መንፈሳዊ መጋደል በሰይጣንና በክፉ መንፈሳውያን ሰራዊት ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም (ኤፌ 6፡12) ዋነኛ ዐላማው የኀጢአተኛ ተፈጥሮን ስሜትና ፍላጎት መቃወም ነው (ገላ 5፥16-21፤ ያዕ 4፥1፡ 1ጴጥ 2፡11)። አማኞች እንደ መሆናችን መጠን ሁልጊዜ ለኀጢአተኛ መሻታችን ነው ወይስ ተካፋይ ለምንሆንበት መለኮታዊ ማንነት ነው የምንታዘዘው በማለት መጠየቅ አለብን (ገላ 5፥16፡18፤ 2ጴጥ 1፥4)፡፡
ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ መግደል ያለመቻል መንፈሳዊ ሞት (ቊ 6:13) እና በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ርስትን ማጣት ሊያስከትል ይችላል (ገሳ 5፥9-21)፡፡ ትሞታላችሁና የሚለው ቃል አንድ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ሕይወት ወደ መንፈሳዊ ሞት ሊሄድ እንደሚችል ያመለክታል፡፡ ስለዚህም በአዲስ ልደት የምንቀበለው የእግዚአብሔር ሕይወት (ዮሐ. 3፥3-6) ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ለመግደል ከማይፈልግ አማኝ ነፍስ ውስጥ እየታጣ ሊሄድ ይችላል።
በኃጢአት ባሕሪ ልማድ የምንኖር ከሆነ እንሞታለን። ይህም የእግዚአብሔርን ፍርድ በመቀበል የዘላለም ሞት እንሞታለን ማለት ነው። ስለዚህ ይህን በጣም አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ መጠየቅ አለብን። ከዘላለም ሞት አምልጠን የዘላለም ሕይወት መቀበል የምንችለው እንዴት ነው?
አንዳንድ ሰዎች እንዲህ በማለት ለዚህ ጥያቄ መልስ ይሰጣሉ፥ እኛ ማድረግ ያለብን በክርስቶስ ማመን ነው፤ ከዚያም በኋላ የቀረውን ነገር ሁሉ ክርስቶስ ያደርገዋል። እኛ ከልባችን ማድረግ የሚገባን «እኔ አምናለሁ» ማለት ብቻ ነው። ወዲያውኑ በቅጽበት እንድናለን። ነገር ግን ጳውሎስ እዚህ ላይ ለየት ያለ መልስ ይሰጣል። በእርግጥ በመጀመሪያ በክርስቶስ ማመን አለብን። ከዚያን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የሥጋን የስህተት ሥራ (ሃጢያተኛ ባህሪን) ሁሉ መግደል አለብን። ይህንን ካደረግን ብቻ ነው በሕይወት የምንኖረው፤ ማለትም መዳን የምንችለው። ለምን ይህ ይሆናል? ምክንያቱም በኃጢአት ባሕሪ ልማድ አለበለዚያም በመንፈስ ልማድ መኖር አለብን፣ በሁለቱም ልማዶች በአንድ ጊዜ መኖር አንችልም። በኃጢአት ልማድ የምንኖር ከሆነ እንሞታለን፤ ይህ እርግጥ ነው። በመንፈስ ልማድ ለመኖር ግን አንድ ነገር ማድረግ ያስፈልገናል፤ የሥጋ ሥራዎችን መግደል ይኖርብናል። እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ትምህርት አለ። ሰዎች ክርስቶስን መከተል በጣም ቀላል ነው ብለው በስሕተት ያስባሉ። እነዚሁ ሰዎች እኛ ክርስቲያኖች መልካም ሥራ መሥራት የለብንም ወይም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችንም መፈጸም አያስፈልገንም ይላሉ። ኃጢአት ብንሠራም መጨነቅ የለብንም፤ ምክንያቱም ወዲያው ይቅርታ እናገኛለን በማለት ያስባሉ። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ አባባሎች እውነት አይደሉም። ከሁሉም ክርስቶስን መከተል በጣም አስቸጋሪ መንገድ ነው፤ ለምን? ምክንያቱም ክርስቶስን ለመከተል የሥጋን ሥራዎች በሙሉ መግደል አለብን፤ ይህም ራስን እንደመግደል ይቆጠራል። ራስን መግደል ወይም መስቀል ቀላል ነገር ነውን? በእርግጥ ቀላል አይደለም። ከዚህ የበለጠ ከባድ ነገር የለም። ይሁን እንጂ፥ በሕይወት ለመኖር አሮጌው ኃጢአተኛ ሰውነታችን መሞት ያስፈልገዋል። አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ከማግኘታችን በፊት አሮጌው ኃጢአተኛ ሰውነት መሞት ይገባዋል፤ ትንሣኤ ከመሆኑ በፊት መጀመሪያ ሞት መቅደም አለበት።
የሥጋን ሥራ ወደ ሞት ለማምጣት፥ በመጀመሪያ የኃጢአተኛ ምኞታችንን ወደ ሞት ማምጣት አለብን። ምክንያቱም የሥጋ ሥራዎች የሚነሡት ከምኞታችን ስለሆነ ነው (ያዕ. 1፥14–15)። ኃጢአት መሥራትን ብቻ መተው ሳይሆን፥ ኃጢአት ስለ መሥራት ማሰብን ማቆም አለብን። ጽድቃችን ከውጪ ብቻ መሆን የለበትም፤ ከውስጣችንም ጭምር እንጂ። ኃጢአት የሚመነጭባቸውን የልባችንንና የአእምሮአችንን ምስጥራዊ ክፍሎች እንዲሞቱ ማድረግ አለብን። ምክንያቱም ኃጢአት በመጀመሪያ የሚነሣው ከእነዚህ ቦታዎች ስለሆነ ነው። እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር መሰቀል ለሚለው አሳብ አንዱ ትርጉም ይህ ነው (ሮሜ 6፥6፥12፤ ቆላ. 3፥5፤ ገላ. 5፥17፥24)።
የሥጋን ሥራዎች እየፈጸሙ በአንድ ጊዜ ደግሞ በመንፈስ መኖር የሚቻል አይደለም። የሥጋን ሥራዎች ያልገደልናቸው ከሆነ፥ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን የለም፤ የክርስቶስም ወገኖች አይደለንም። የክርስቶስ ወገኖች ካልሆንን ደግሞ ደኅንነትንም አልተቀበልንም ማለት ነው። ነገር ግን አንድ ነገር ማስታወስ አለብን። የሥጋን ሥራዎች መግደል ካስፈለገን የመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ያስፈልገናል። ያለ መንፈስ ቅዱስ ይህን ለብቻችን ማድረግ አንችልም። መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ሁልጊዜ ከእኛ ጋር ነው፤ የጽድቅ ሕይወት እንድንኖር ሁልጊዜ ይረዳናል። እንግዲህ የሮሜ ምዕራፍ 8 አስደሳች ዜና ይህ ነው።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 84፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 367፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1753
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሮሜ 8፥12-17
«መንፈስ ወርሷችኋል» (ሮሜ 8፡12-17)
እኛ መንፈስ ስላለን ብቻ በቂ አይደለም፤ መንፈስ እኛን ሊወርሰንም ያስፈልጋል፡፡ የተትረፈረፈው የድል ሕይወት በክርስቶስ በኩል የእኛ የሚሆነው በዚህ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ሥጋችን ለሕይወታችን ከችግር በቀር ያመጣልን ነገር ስለሌለ፣ የሥጋ ዕዳ የለብንም፡፡ ክርስቶስን ባመንን ጊዜ በኃጢአታችን የወቀሰን፣ ክርስቶስን የገለጠልንና የዘለዓለም ሕይወት ያካፈለን መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ የእርሱ ዕዳ አለብን፡፡
በክርስቶስ ኢየሱስ ከሆንን መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር አለ። ስለዚህም
1. በእርሱ ኃይል የሰውነትን ሥራ እንድንገድል ያስችለናል። (ቁ. 13)
ኀጢአት ሁልጊዜ የራሱ ሊያደርገን ስለሚፈልግ፣ በሕይወታችን የእግዚአብሔርን ሥራ ሊገድብ ከሚችል ነገር ሁሉ ጋር ያለማቋረጥ መጋደል እንደሚገባ ጳውሎስ አሳስቧል (ከ6፥11-19):: ይህ መንፈሳዊ መጋደል በሰይጣንና በክፉ መንፈሳውያን ሰራዊት ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም (ኤፌ 6፡12) ዋነኛ ዐላማው የኀጢአተኛ ተፈጥሮን ስሜትና ፍላጎት መቃወም ነው (ገላ 5፥16-21፤ ያዕ 4፥1፡ 1ጴጥ 2፡11)። አማኞች እንደ መሆናችን መጠን ሁልጊዜ ለኀጢአተኛ መሻታችን ነው ወይስ ተካፋይ ለምንሆንበት መለኮታዊ ማንነት ነው የምንታዘዘው በማለት መጠየቅ አለብን (ገላ 5፥16፡18፤ 2ጴጥ 1፥4)፡፡
ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ መግደል ያለመቻል መንፈሳዊ ሞት (ቊ 6:13) እና በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ርስትን ማጣት ሊያስከትል ይችላል (ገሳ 5፥9-21)፡፡ ትሞታላችሁና የሚለው ቃል አንድ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ሕይወት ወደ መንፈሳዊ ሞት ሊሄድ እንደሚችል ያመለክታል፡፡ ስለዚህም በአዲስ ልደት የምንቀበለው የእግዚአብሔር ሕይወት (ዮሐ. 3፥3-6) ክፉ የሆነውን የሥጋ ሥራ በመንፈስ ቅዱስ ለመግደል ከማይፈልግ አማኝ ነፍስ ውስጥ እየታጣ ሊሄድ ይችላል።
በኃጢአት ባሕሪ ልማድ የምንኖር ከሆነ እንሞታለን። ይህም የእግዚአብሔርን ፍርድ በመቀበል የዘላለም ሞት እንሞታለን ማለት ነው። ስለዚህ ይህን በጣም አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ መጠየቅ አለብን። ከዘላለም ሞት አምልጠን የዘላለም ሕይወት መቀበል የምንችለው እንዴት ነው?
አንዳንድ ሰዎች እንዲህ በማለት ለዚህ ጥያቄ መልስ ይሰጣሉ፥ እኛ ማድረግ ያለብን በክርስቶስ ማመን ነው፤ ከዚያም በኋላ የቀረውን ነገር ሁሉ ክርስቶስ ያደርገዋል። እኛ ከልባችን ማድረግ የሚገባን «እኔ አምናለሁ» ማለት ብቻ ነው። ወዲያውኑ በቅጽበት እንድናለን። ነገር ግን ጳውሎስ እዚህ ላይ ለየት ያለ መልስ ይሰጣል። በእርግጥ በመጀመሪያ በክርስቶስ ማመን አለብን። ከዚያን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የሥጋን የስህተት ሥራ (ሃጢያተኛ ባህሪን) ሁሉ መግደል አለብን። ይህንን ካደረግን ብቻ ነው በሕይወት የምንኖረው፤ ማለትም መዳን የምንችለው። ለምን ይህ ይሆናል? ምክንያቱም በኃጢአት ባሕሪ ልማድ አለበለዚያም በመንፈስ ልማድ መኖር አለብን፣ በሁለቱም ልማዶች በአንድ ጊዜ መኖር አንችልም። በኃጢአት ልማድ የምንኖር ከሆነ እንሞታለን፤ ይህ እርግጥ ነው። በመንፈስ ልማድ ለመኖር ግን አንድ ነገር ማድረግ ያስፈልገናል፤ የሥጋ ሥራዎችን መግደል ይኖርብናል። እዚህ ላይ በጣም ጠቃሚ የሆነ ትምህርት አለ። ሰዎች ክርስቶስን መከተል በጣም ቀላል ነው ብለው በስሕተት ያስባሉ። እነዚሁ ሰዎች እኛ ክርስቲያኖች መልካም ሥራ መሥራት የለብንም ወይም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችንም መፈጸም አያስፈልገንም ይላሉ። ኃጢአት ብንሠራም መጨነቅ የለብንም፤ ምክንያቱም ወዲያው ይቅርታ እናገኛለን በማለት ያስባሉ። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ አባባሎች እውነት አይደሉም። ከሁሉም ክርስቶስን መከተል በጣም አስቸጋሪ መንገድ ነው፤ ለምን? ምክንያቱም ክርስቶስን ለመከተል የሥጋን ሥራዎች በሙሉ መግደል አለብን፤ ይህም ራስን እንደመግደል ይቆጠራል። ራስን መግደል ወይም መስቀል ቀላል ነገር ነውን? በእርግጥ ቀላል አይደለም። ከዚህ የበለጠ ከባድ ነገር የለም። ይሁን እንጂ፥ በሕይወት ለመኖር አሮጌው ኃጢአተኛ ሰውነታችን መሞት ያስፈልገዋል። አዲስ መንፈሳዊ ሕይወት ከማግኘታችን በፊት አሮጌው ኃጢአተኛ ሰውነት መሞት ይገባዋል፤ ትንሣኤ ከመሆኑ በፊት መጀመሪያ ሞት መቅደም አለበት።
የሥጋን ሥራ ወደ ሞት ለማምጣት፥ በመጀመሪያ የኃጢአተኛ ምኞታችንን ወደ ሞት ማምጣት አለብን። ምክንያቱም የሥጋ ሥራዎች የሚነሡት ከምኞታችን ስለሆነ ነው (ያዕ. 1፥14–15)። ኃጢአት መሥራትን ብቻ መተው ሳይሆን፥ ኃጢአት ስለ መሥራት ማሰብን ማቆም አለብን። ጽድቃችን ከውጪ ብቻ መሆን የለበትም፤ ከውስጣችንም ጭምር እንጂ። ኃጢአት የሚመነጭባቸውን የልባችንንና የአእምሮአችንን ምስጥራዊ ክፍሎች እንዲሞቱ ማድረግ አለብን። ምክንያቱም ኃጢአት በመጀመሪያ የሚነሣው ከእነዚህ ቦታዎች ስለሆነ ነው። እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር መሰቀል ለሚለው አሳብ አንዱ ትርጉም ይህ ነው (ሮሜ 6፥6፥12፤ ቆላ. 3፥5፤ ገላ. 5፥17፥24)።
የሥጋን ሥራዎች እየፈጸሙ በአንድ ጊዜ ደግሞ በመንፈስ መኖር የሚቻል አይደለም። የሥጋን ሥራዎች ያልገደልናቸው ከሆነ፥ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን የለም፤ የክርስቶስም ወገኖች አይደለንም። የክርስቶስ ወገኖች ካልሆንን ደግሞ ደኅንነትንም አልተቀበልንም ማለት ነው። ነገር ግን አንድ ነገር ማስታወስ አለብን። የሥጋን ሥራዎች መግደል ካስፈለገን የመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ያስፈልገናል። ያለ መንፈስ ቅዱስ ይህን ለብቻችን ማድረግ አንችልም። መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ሁልጊዜ ከእኛ ጋር ነው፤ የጽድቅ ሕይወት እንድንኖር ሁልጊዜ ይረዳናል። እንግዲህ የሮሜ ምዕራፍ 8 አስደሳች ዜና ይህ ነው።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 84፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 367፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1753
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1🥰1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ተግሣጽን ያዝ፥ አትተውም፤ ጠብቀው፥ እርሱ ሕይወትህ ነውና።”
ምሳሌ 4፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ተግሣጽን ያዝ፥ አትተውም፤ ጠብቀው፥ እርሱ ሕይወትህ ነውና።”
ምሳሌ 4፥13
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍2🔥1👏1
ኢየሱስ በወንጌል "እውነት እውነት እላችኋለሁ" ሲል ምን ማለቱ ነው?
በዘመናዊ አጠቃቀም፣ "አሜን" የሚለው ቃል በተለምዶ በጸሎት መጨረሻ ላይ ጥቅም ላይ ይውላል። እንዲሁም ከአንዳንድ መግለጫዎች ወይም ሃሳቦች ጋር ስምምነትን ለማሳየት ይነገር ይሆናል። ይህ በብሉይ ኪዳን እንደታየው ከዋናው የቃሉ አጠቃቀም ትንሽ የተለየ ነው ነገር ግን በቅርበት የተያያዘ ነው። የዕብራይስጥ ቃል āˈmēn በቀጥታ ሲተረጎም “ይሁን” ማለት ነው። ቃሉ የተሟላ እና አጠቃላይ ስምምነት መግለጫ ነው። እንደ 1ኛ ዜና 16፥36 ወይም ዘዳግም 27፥15–26 ባሉ ምንባቦች ቃሉ በዚህ መልኩ ጥቅም ላይ ውሏል። አሜን የሚለውን ቃል በመግለጫው መጨረሻ ላይ ማስቀመጥ ከዚህ በፊት የነበረውን የመቀበል፣ የመስማማት ወይም የማጽደቅ መንገድ ነው።
ኢየሱስ ግን መግለጫ ከመስጠቱ ወይም መልእክት ከመስጠቱ በፊት “አሜን” ማለት ይወድ ነበር። በዚህ መንገድ ጥቅም ላይ ሲውል አሜን የሚለው ቃል ትንሽ የተለየ አንድምታ አለው። በአሜን መጀመር የሚከተለው እውነት መሆኑን ብቻ ሳይሆን መግለጫውን የሰጠው ሰው ስለነገሩ እውቀት እና ስልጣን እንዳለው ያሳያል። መግለጫ ከመስጠታችን በፊት “እውነት እውነት” ማለት ከሞላ ጎደል ድፍረት ከተሞላበት አመለካከት የመነጨ ለእውነት ጠንካራ ማረጋገጫ ነው። ስለ ዓለማዊም ሆነ ዓለማዊ ጉዳዮች መናገር፣ “እውነት ፣ እውነት” ማለት የሚከተለው ንግግር የዚያ ሰው የራሱ ሐሳብ (የአሳቡ ምንጭ ተናጋሪው) መሆኑን ያሳያል።
ስለዚህ፣ ኢየሱስ "እውነት እላችኋለሁ" ብሎ፣ እንደ ማቴዎስ 18፥3፣ ማርቆስ 3፥28፣ ሉቃስ 23፥43 እና ዮሐንስ 8፥51 ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ሲጀምር፣ “እመኑኝ፣ ይህ እውነት ነው” ማለቱ ብቻ አይደለም። በእውነቱ፣ “ይህ እውነት እንደሆነ አውቃለሁ” እያለ ነው። ከእነዚህ አስተያየቶች ውስጥ ብዙዎቹ በሰማያዊ፣ በመንፈሳዊ ወይም በአምላካዊ ጉዳዮች ላይ፣ የኢየሱስ የመለኮትነት የይገባኛል ጥያቄ አካል ነው። ኢየሱስ እነዚህን እውነቶች የሚያውቅ ብቻ አይደለም። የፈጠረው እርሱ ነው!
ደቀ መዛሙርቱ እና ሌሎች የኢየሱስን ቃላት የሚያዳምጡ ሰዎች እነዚህን ሐረጎች የተጠቀመበትን መንገድ በትክክል ተረድተውት ነበር። እንግዲያው፣ የኢየሱስን ቃላት ስናነብ “እውነት እውነት” በማለት የሚጀምሩትን መግለጫዎች ስንመለከት ጥልቅ ትርጉሙን ማስታወስ አለብን። እነዚህ የይገባኛል ጥያቄዎች ኢየሱስ እውነት ላይ ያለውን አመለካከት ብቻ የሚያመለክት አይደለም። እነዚያ ስለ እሱ የቅርብ ፣ ግላዊ ፣ የመጀመሪያ እውቀቱ እንዳለው የሚያሳዩ ናቸው።
ምንጭ፦ www.gotquestions.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ኢየሱስ በተለያዩ ጊዜያት በወንጌል ውስጥ “እውነት እላችኋለሁ” የሚሉ ሐረጎችን ተጠቅሟል። በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ፣ ኢየሱስ “እውነት እውነት” የሚለውን ሐረግ ደጋግሞ ይጠቀማል። እነዚህ አገላለጾች ሁሉም በቀጥታ "āˈmēn" ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተወሰደውን "amēn" የሚለውን የግሪክ ቃል ይጠቀማሉ። ይህ ቃል እንዴት እና የት ጥቅም ላይ እንደሚውል በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ በመመስረት የተለያየ አንድምታ አለው። የኢየሱስ የቃሉ አተገባበር ከቀደምት አጠቃቀሞች በተለየ ሁኔታ ይታያል።በዘመናዊ አጠቃቀም፣ "አሜን" የሚለው ቃል በተለምዶ በጸሎት መጨረሻ ላይ ጥቅም ላይ ይውላል። እንዲሁም ከአንዳንድ መግለጫዎች ወይም ሃሳቦች ጋር ስምምነትን ለማሳየት ይነገር ይሆናል። ይህ በብሉይ ኪዳን እንደታየው ከዋናው የቃሉ አጠቃቀም ትንሽ የተለየ ነው ነገር ግን በቅርበት የተያያዘ ነው። የዕብራይስጥ ቃል āˈmēn በቀጥታ ሲተረጎም “ይሁን” ማለት ነው። ቃሉ የተሟላ እና አጠቃላይ ስምምነት መግለጫ ነው። እንደ 1ኛ ዜና 16፥36 ወይም ዘዳግም 27፥15–26 ባሉ ምንባቦች ቃሉ በዚህ መልኩ ጥቅም ላይ ውሏል። አሜን የሚለውን ቃል በመግለጫው መጨረሻ ላይ ማስቀመጥ ከዚህ በፊት የነበረውን የመቀበል፣ የመስማማት ወይም የማጽደቅ መንገድ ነው።
ኢየሱስ ግን መግለጫ ከመስጠቱ ወይም መልእክት ከመስጠቱ በፊት “አሜን” ማለት ይወድ ነበር። በዚህ መንገድ ጥቅም ላይ ሲውል አሜን የሚለው ቃል ትንሽ የተለየ አንድምታ አለው። በአሜን መጀመር የሚከተለው እውነት መሆኑን ብቻ ሳይሆን መግለጫውን የሰጠው ሰው ስለነገሩ እውቀት እና ስልጣን እንዳለው ያሳያል። መግለጫ ከመስጠታችን በፊት “እውነት እውነት” ማለት ከሞላ ጎደል ድፍረት ከተሞላበት አመለካከት የመነጨ ለእውነት ጠንካራ ማረጋገጫ ነው። ስለ ዓለማዊም ሆነ ዓለማዊ ጉዳዮች መናገር፣ “እውነት ፣ እውነት” ማለት የሚከተለው ንግግር የዚያ ሰው የራሱ ሐሳብ (የአሳቡ ምንጭ ተናጋሪው) መሆኑን ያሳያል።
ስለዚህ፣ ኢየሱስ "እውነት እላችኋለሁ" ብሎ፣ እንደ ማቴዎስ 18፥3፣ ማርቆስ 3፥28፣ ሉቃስ 23፥43 እና ዮሐንስ 8፥51 ባሉት ቁጥሮች ውስጥ ሲጀምር፣ “እመኑኝ፣ ይህ እውነት ነው” ማለቱ ብቻ አይደለም። በእውነቱ፣ “ይህ እውነት እንደሆነ አውቃለሁ” እያለ ነው። ከእነዚህ አስተያየቶች ውስጥ ብዙዎቹ በሰማያዊ፣ በመንፈሳዊ ወይም በአምላካዊ ጉዳዮች ላይ፣ የኢየሱስ የመለኮትነት የይገባኛል ጥያቄ አካል ነው። ኢየሱስ እነዚህን እውነቶች የሚያውቅ ብቻ አይደለም። የፈጠረው እርሱ ነው!
ደቀ መዛሙርቱ እና ሌሎች የኢየሱስን ቃላት የሚያዳምጡ ሰዎች እነዚህን ሐረጎች የተጠቀመበትን መንገድ በትክክል ተረድተውት ነበር። እንግዲያው፣ የኢየሱስን ቃላት ስናነብ “እውነት እውነት” በማለት የሚጀምሩትን መግለጫዎች ስንመለከት ጥልቅ ትርጉሙን ማስታወስ አለብን። እነዚህ የይገባኛል ጥያቄዎች ኢየሱስ እውነት ላይ ያለውን አመለካከት ብቻ የሚያመለክት አይደለም። እነዚያ ስለ እሱ የቅርብ ፣ ግላዊ ፣ የመጀመሪያ እውቀቱ እንዳለው የሚያሳዩ ናቸው።
ምንጭ፦ www.gotquestions.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3👍1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁና፤”
ሮሜ 1፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁና፤”
ሮሜ 1፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤6👍1🥰1👏1
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ቆሮንቶስ
ቆሮንቶስ የግሪክ ከተማ ናት፤ ከአቴናም 75 ኪ.ሜ. ያህል ትርቃለች። አቀማመጥዋ በሁለቱ የግሪክ አውራጃዎች በመቄዶንያና በአካይያ መካከል በሚገኘው ልሳነ ምድር ላይ ነበረ። ጳውሎስ በነበረበት ዘመን 250,000 ሰዎችና 400,000 ባሪያዎች በቆሮንቶስ ይኖሩ እንደ ነበር ይገመታል፡፡ ቆሮንቶስ ከሌሎቹ የግሪክ ከተሞች ይልቅ በአንዳንድ ነገሮች በልጣ ትታይ ነበር፤ ምክንያቶቹም የሚከተሉት ናቸው፦
1) ንግዷ፤ ከተማዋ በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር አጠገብ የምትገኝ የመንገደኞች መተላለፊያ የነጋዴዎች መናኸሪያ ነበረች፡፡ ከተማይቱ ሁለት ወደቦች አሏት፤ እነዚህም:-
ሀ) በስተ ምሥራቅ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በሰሮኖ ባሕረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የክንክራኦስ ወደብ፣
ለ) በስተ ምዕራብ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በቆሮንቶስ ባህረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የሌቻዶም ወደብ ናቸው፡፡
ልዩ ልዩ ዕቃዎች በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር በዳዮልኮስ ጐዳና ላይ በትናንሽ መርከቦች ሞልተው እየተሳቡ ከወዲህ ማዶ ወዚያኛው ይሽጋገሩ ነበር፡፡ በትልልቅ መርከቦች የተጫኑ ዕቃዎችም በፉርጎ ሆነው እንደዚሁ ከአንዱ ዳር ወደ ሌላው ዳር ይጓጓዙ ነበር፡፡ በዚህ ዓይነት ሸቀጣ ሸቀጦች ከኢጣሊያ ከእስፓኝ ወደ ምዕራብ፣ እንዲሁም ከትንሹ እስያ፣ ከፊንቄና ከግብፅ ወደ ምሥራቁ ዓለም የሚጓጓዙበት በቆሮንቶስ ከተማ በኩል አድርገው ነበር።
2) ባህሏ፤ ቆሮንቶስ እንደ አቴንስ ሁሉ እስከዚህ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ባይኖራትም በሠለጠነው የግሪክ ባህል የመጠቀች ነበረች፤ ሕዝብዋም ለግሪክ ፍልስፍና ጥልቅ ፍቅር ስለነበረው ለጥበብ ከፍተኛ ወጪ ያደርግ ነበር።
3) ሃይማኖቷ፤ የቆሮንቶስ ከተማ በትንሹ አሥራ ሁለት ቤተ ጣዖቶች ነበሩባት፤ ጳውሎስ በነበረበት ዘመን እነዚህ ሁሉ ቤተ ጣዖቶች ለአገልግሎት ክፍት ይሁኑ አይሁኑ እስከዚህ የሚታወቅ ነገር የለም:: ከእነዚህ ቤተ ጣዖቶች መካከል አንዱ በግሪክ የተረታ ተረት ታሪክ ውስጥ የፍቅር አምላክ ተብላ የምትታወቀው የአፍሮዲጡስ ቤተ ጣዖት ሲሆን በቤተ ጣዖቱም ውስጥ ከሥርዓት አምልኮው ጋር በተያያዘ የዝሙት ሥራ መፈጸም የተለመደ ነበር፡፡ ከትያትር ቤቱ ሕንፃ በስተ ሰሜን ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የፈውስ አምላክ እያሉ ለሚጠሩት ለአስክሌፕደስ የተሠራ ቤተ ጣዖት አለ፡፡ በከተማይ ቱም መሃልም በ6ኛው ምዕተ ዓመት ቅድመ ልደት ክርስቶስ ላይ የተሠራ የአፖሎ ቤተ ጣዖት ቆሞአል፡፡ አይሁድ በከተማይቱ ውስጥ የሠሩትም ምኵራብ ነበር፡፡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ጽሑፍ የተቀረጸበት የመስኮት ጒበን በአሁኑ ጊዜ ተገኝቶ በጥንቲቱ የቆሮንቶስ ከተማ ቤተ መዘክር በክብር ተቀምጦአል፡፡
4) ምግባረ ብልሹነትዋ፤ ቆሮንቶስ እንደማንኛውም ትልቅ የንግድ ከተማ ሁሉ ለሥነ ምግባር ብልሹነት በሰፊው የተጋለጠች ነበረች፡፡ የአፍሮዲጡስ የጣዖት አምልኮ በሃይማኖት ስም ዝሙት እንዲ ስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጎአል፡፡ በአንድ ዘመንማ ለዚሁ ሥራ የተለዩ አንድ ሺህ ዘማውያት በቤተ ጣዖቱ ውስጥ ያገለግሉ ነበር፡፡ ቆሮንቶስ ምግባረ ብልሹነትዋ የታወቀች ከመሆንዋ የተነሣ በግሪኩ የሰዋሰው ግሥ “መቆታንተስ” ማለት “በአሳፋሪ የዝሙት ተግባር መሰማራት” ማለት እንደሆነ የተቍጠረበት ወቅት ነበር፡፡ እንግዲህ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የነበረችው የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ መከራ ችግር ውስጥ እንደምትገባ መገመት አያዳግትም፡፡
ቆሮንቶስ ጥንታዊት የግሪክ ከተማ ስትሆን፣ በጳውሎስ ዘመን በብዙ መንገድ ታዋቂ የነበረች የግሪክ መዲና ናት:: በአሁን ዘመን እንዳሉት ሀብታም ከተሞች ቆሮንቶስ በዕውቀት የታበየች፣ በሀብት የበለጠገችና በኢግብረገባዊ ሕይወት የረከሰች ነበረች፡፡ ማንኛውም ዐይነት ኀጢአት በዚህች በወጣላት ዓለማዊ ከተማ ተስፋፋ፡፡
ከጵርስቅላና ከአቂላ (1ቆሮ 16፥19) እንዲሁም ከራሱ ሐዋርያዊ ቡድን (ሐሥ 18፥5) ጋር በመጣመር፤ ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞው (ሐሥ 18፥1-17) ዐሥራ ስምንት ወር በቆሮንቶስ ከተማ ለአገልግሎት በቈየበት ጊዜ የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን መሠረተ፡፡ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምእመናን ጥቂቶቹ አይሁድ ሲሆኑ፣ በአብዛኛው ጣዖት አምላኪዎች የነበሩ አሕዛብ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር፤ ገጽ 1734፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 99፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1776
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
#ቆሮንቶስ
ቆሮንቶስ የግሪክ ከተማ ናት፤ ከአቴናም 75 ኪ.ሜ. ያህል ትርቃለች። አቀማመጥዋ በሁለቱ የግሪክ አውራጃዎች በመቄዶንያና በአካይያ መካከል በሚገኘው ልሳነ ምድር ላይ ነበረ። ጳውሎስ በነበረበት ዘመን 250,000 ሰዎችና 400,000 ባሪያዎች በቆሮንቶስ ይኖሩ እንደ ነበር ይገመታል፡፡ ቆሮንቶስ ከሌሎቹ የግሪክ ከተሞች ይልቅ በአንዳንድ ነገሮች በልጣ ትታይ ነበር፤ ምክንያቶቹም የሚከተሉት ናቸው፦
1) ንግዷ፤ ከተማዋ በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር አጠገብ የምትገኝ የመንገደኞች መተላለፊያ የነጋዴዎች መናኸሪያ ነበረች፡፡ ከተማይቱ ሁለት ወደቦች አሏት፤ እነዚህም:-
ሀ) በስተ ምሥራቅ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በሰሮኖ ባሕረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የክንክራኦስ ወደብ፣
ለ) በስተ ምዕራብ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በቆሮንቶስ ባህረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የሌቻዶም ወደብ ናቸው፡፡
ልዩ ልዩ ዕቃዎች በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር በዳዮልኮስ ጐዳና ላይ በትናንሽ መርከቦች ሞልተው እየተሳቡ ከወዲህ ማዶ ወዚያኛው ይሽጋገሩ ነበር፡፡ በትልልቅ መርከቦች የተጫኑ ዕቃዎችም በፉርጎ ሆነው እንደዚሁ ከአንዱ ዳር ወደ ሌላው ዳር ይጓጓዙ ነበር፡፡ በዚህ ዓይነት ሸቀጣ ሸቀጦች ከኢጣሊያ ከእስፓኝ ወደ ምዕራብ፣ እንዲሁም ከትንሹ እስያ፣ ከፊንቄና ከግብፅ ወደ ምሥራቁ ዓለም የሚጓጓዙበት በቆሮንቶስ ከተማ በኩል አድርገው ነበር።
2) ባህሏ፤ ቆሮንቶስ እንደ አቴንስ ሁሉ እስከዚህ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ባይኖራትም በሠለጠነው የግሪክ ባህል የመጠቀች ነበረች፤ ሕዝብዋም ለግሪክ ፍልስፍና ጥልቅ ፍቅር ስለነበረው ለጥበብ ከፍተኛ ወጪ ያደርግ ነበር።
3) ሃይማኖቷ፤ የቆሮንቶስ ከተማ በትንሹ አሥራ ሁለት ቤተ ጣዖቶች ነበሩባት፤ ጳውሎስ በነበረበት ዘመን እነዚህ ሁሉ ቤተ ጣዖቶች ለአገልግሎት ክፍት ይሁኑ አይሁኑ እስከዚህ የሚታወቅ ነገር የለም:: ከእነዚህ ቤተ ጣዖቶች መካከል አንዱ በግሪክ የተረታ ተረት ታሪክ ውስጥ የፍቅር አምላክ ተብላ የምትታወቀው የአፍሮዲጡስ ቤተ ጣዖት ሲሆን በቤተ ጣዖቱም ውስጥ ከሥርዓት አምልኮው ጋር በተያያዘ የዝሙት ሥራ መፈጸም የተለመደ ነበር፡፡ ከትያትር ቤቱ ሕንፃ በስተ ሰሜን ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የፈውስ አምላክ እያሉ ለሚጠሩት ለአስክሌፕደስ የተሠራ ቤተ ጣዖት አለ፡፡ በከተማይ ቱም መሃልም በ6ኛው ምዕተ ዓመት ቅድመ ልደት ክርስቶስ ላይ የተሠራ የአፖሎ ቤተ ጣዖት ቆሞአል፡፡ አይሁድ በከተማይቱ ውስጥ የሠሩትም ምኵራብ ነበር፡፡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ጽሑፍ የተቀረጸበት የመስኮት ጒበን በአሁኑ ጊዜ ተገኝቶ በጥንቲቱ የቆሮንቶስ ከተማ ቤተ መዘክር በክብር ተቀምጦአል፡፡
4) ምግባረ ብልሹነትዋ፤ ቆሮንቶስ እንደማንኛውም ትልቅ የንግድ ከተማ ሁሉ ለሥነ ምግባር ብልሹነት በሰፊው የተጋለጠች ነበረች፡፡ የአፍሮዲጡስ የጣዖት አምልኮ በሃይማኖት ስም ዝሙት እንዲ ስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጎአል፡፡ በአንድ ዘመንማ ለዚሁ ሥራ የተለዩ አንድ ሺህ ዘማውያት በቤተ ጣዖቱ ውስጥ ያገለግሉ ነበር፡፡ ቆሮንቶስ ምግባረ ብልሹነትዋ የታወቀች ከመሆንዋ የተነሣ በግሪኩ የሰዋሰው ግሥ “መቆታንተስ” ማለት “በአሳፋሪ የዝሙት ተግባር መሰማራት” ማለት እንደሆነ የተቍጠረበት ወቅት ነበር፡፡ እንግዲህ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የነበረችው የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ መከራ ችግር ውስጥ እንደምትገባ መገመት አያዳግትም፡፡
ቆሮንቶስ ጥንታዊት የግሪክ ከተማ ስትሆን፣ በጳውሎስ ዘመን በብዙ መንገድ ታዋቂ የነበረች የግሪክ መዲና ናት:: በአሁን ዘመን እንዳሉት ሀብታም ከተሞች ቆሮንቶስ በዕውቀት የታበየች፣ በሀብት የበለጠገችና በኢግብረገባዊ ሕይወት የረከሰች ነበረች፡፡ ማንኛውም ዐይነት ኀጢአት በዚህች በወጣላት ዓለማዊ ከተማ ተስፋፋ፡፡
ከጵርስቅላና ከአቂላ (1ቆሮ 16፥19) እንዲሁም ከራሱ ሐዋርያዊ ቡድን (ሐሥ 18፥5) ጋር በመጣመር፤ ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞው (ሐሥ 18፥1-17) ዐሥራ ስምንት ወር በቆሮንቶስ ከተማ ለአገልግሎት በቈየበት ጊዜ የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን መሠረተ፡፡ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምእመናን ጥቂቶቹ አይሁድ ሲሆኑ፣ በአብዛኛው ጣዖት አምላኪዎች የነበሩ አሕዛብ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር፤ ገጽ 1734፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 99፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1776
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍8❤2😁1