የቀጠለ...
📜መጽሐፍ ቅዱሳችን እንዴት ተፃፈ
አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን የተጻፈው በግሪክ ቋንቋ ሲሆን መጻፍ የተጀመረውም ክርስቶስ ከሞተ ከሃያ ዓመት በኋላ ነበር። ክርስቶስ ለደቀመዛሙርቱ የሰጣቸው የመጨረሻ ትእዛዝ፤ ለዓለም በሙሉ ምስክሮቹ እንዲሆኑ ስለነበር (የሐዋ. 1፥8)፤ ከጴንጠቆስጤ ቀን ጀምሮ ደቀመዛሙርቱ ስለ ክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት ለሌሎች መንገር ጀመሩ። ክርስቶስ ከሞተ በኋላ ለመጀመሪያዎቹ ሃያ ዓመታት ደቀመዛሙርቱ ወይም ሐዋርያቱ በአፍ እየተናገሩ ቃሉን ያስተምሩ ነበር። ነገር ግን ሐዋርያቱ እያረጁ ሲሄዱ ትምህርታቸው አንዳች ሳይዛነፍ በጹሑፍ ለመጪው ትውልድ መተላለፉ አስፈላጊ ሆነ። ይህም ለወደፊት ዘመናት በትክክል መተላለፉን ለማረጋገጥ ይጠቅም ነበር፤ ስለዚህ ከሐዋርያት አንዳንዶቹና የቅርብ ተባባሪዎቻቸው ስለ ክርስቶስ ሕይወት መጻፍ ጀመሩ። ሐዋርያው ጴጥሮስ የማርቆስን ወንጌል ለመጻፍ ከማርቆስ ጋር አብሮ ሠራ። ሐዋርያው ማቴዎስ የማቴዎስን ወንጌል ጻፈ። ሐዋርያው ዮሐንስ የዮሐንስን ወንጌል ጻፈ። የሐዋርያው ጳውሎስ የቅርብ ረዳት የነበረው ሉቃስ የሉቃስን ወንጌልና የቀድሞይቱ ቤተክርስቲያን ታሪክ የሆነውን የሐዋርያት ሥራን ጻፈ።
ስለ ክርስቶስ ሕይወት ከመጻፍ በተጨማሪ ሐዋርያቱ ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣበትን ምክንያት አስፋፍተው ለመጻፍ ግድ ሆነባቸው። እንዲሁም በአዳዲስ አብያተክርስቲያናት ዘንድ መብቀል የጀመሩትን አንዳንድ ስሕተቶችና ሐሰተኛ ትምህርቶች ለማረምም መጻፍ ነበረባቸው። ስለዚህ ለመሠረቱአቸው አዳዲስ አብያተክርስቲያናት መልእክት መጻፍ ጀመሩ። ሐዋርያው ጳውሎስ በ50 ዓ.ም. ገደማ ከተፃፈው የገላትያ መልዕክት አንስቶ በአጠቃላይ ዐሥራ ሦስት መልእክቶችን ጻፈ። አንዳንድ ሊቃውንት ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መካከል በመጀመሪያ የተጻፈው የያዕቆብ ማለትም የኢየሱስ ወንድም መልእክት ነው ብለው ያምናሉ።
ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መካከል በመጨረሻ የተጻፈው የራእይ መጽሐፍ ነው፤ ይህም መጽሐፍ የተጻፈው በሐዋርያው ዮሐንስ ሲሆን እርሱም የተጻፈው ከ90–95 ዓ.ም. ገደማ ነው። ስለዚህ መላው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ተጽፈው ያበቁት ከ50 ዓ.ም. እስከ 100 ዓ.ም. መካከል ባለው ዘመን ነው። ከአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ከመጀመሪያዎቹ ጽሑፎች አብዛኛዎቹ የተጻፉት ፓፒረስ ከሚባል ተክል ከተሠራ ወረቀት ነበር፤ ይህ ፓፒረስ እንደ ዘመኑ ወረቀት ነዋሪ አልነበረም፤ ስለሆነም ለብዙ ጊዜ አይቆይም ነበር። ከዚህም የተነሣ የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች በፓፒረስ ጥቅል የጻፉአቸው ጹሑፎች በሙሉ ጠፍተዋል፤ ልክ እንደ ብሉይ ኪዳን ጹሑፎች ሁሉ ዛሬ የሚገኙት የአዲስ ኪዳን ጹሑፎች የዋናው ቅጅ ማለትም ከፓፒረሱ የተቀዱ ናቸው።
ከክርስቶስ በኋላ ለመጀመሪያዎቹ ሦስት መቶ ዓመታት አዲስ ኪዳን ጹሑፎች በጥንቃቄና በትክክል በፓፒረስ ጥቅል በጸሐፊዎች አማካይነት የተገለበጡ ናቸው። 1900 ዓመት እንደገባ ወዲያውኑ፥ ከነዚህ ከፓፒረስ ግልባጮች ከነበሩት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጥቂቶቹ በግብጽ አገር በአሸዋ ውስጥ ተቀብረው ተገኝተዋል። ሌሎቹ ደግሞ በመከላከያ መያዥያዎች በጥንቃቄ ተጣጥፈው ተገኝተዋል። ከነዚህም በጣም ያረጀው ግልባጭ በ135 ዓ.ም. የተሠራ ሲሆን ከዮሐንስ ወንጌል ጥቂቱን ክፍል የያዘ ነበር። በመቀጠል በጣም የቆዩት ጥቅሎች በ200 ዓ.ም. ላይ የተገለበጡና ከአዲስ ኪዳን አብዛኛውን ክፍል የያዙ ነበሩ፤ እነዚህ የጥንት ጥቅሎች በአሁኑ ጊዜ በሙዝየም ውስጥ ተጠብቀው ይገኛሉ።
በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን ሰዎች ይጠቀሙበት የነበረ ሌላው የወረቀት ዐይነት፤ ብራና ከሚባል በተለየ ሁኔታ ለፍቶና ታሽቶ የተሠራ የፍየልና የበግ ቆዳ ነበር። ብራና ከፓፒረስ ይልቅ በጣም ውድ ሲሆን፤ ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጥቂቶቹ በመጀመሪያ የተጻፉት ከብራና እንደነበረ ይገመታል። ይህ ከሆነ ደግሞ በደንብ ተጠብቀው አልተያዙም ማለት ነው። ሙሉው አዲስ ኪዳን በጣም ያረጀው ግልባጭ የተሠራው በአራተኛው መቶ ዓመት ላይ ነበር። የተጻፈውም በብራና ሲሆን ይህም ያረጀ ግልባጭ የተገኘው በ1800 ዓ.ም. መካከለኛ ላይ በግብጽ አገር በሚገኘው በሲና ተራራ በመነኩሳት ገዳም ውስጥ ነበር። ከዚህም ካረጀ ጥቅል ሌላ የግሪክ አዲስ ኪዳን ግልባጮች የሆኑ በብራና ላይ የተጻፉ ሌላ 270 ግልባጮች በአሁኑ ወቅት ይገኛሉ። የተፃፉትም በአራተኛና በዘጠነኛ መቶ ዓመታት መካከል ነበር።
ከዘጠነኛው መቶ ዓመት እስከ ዐሥራ አምስተኛው መቶ ዓመት በግሪክ ብዙ ቋንቋ አዲስ ኪዳን ግልባጮች ተሠርተዋል፤ ከእነርሱም ከ2700 በላይ የሚሆኑ ግልባጮች እስከ አሁኑ ዘመን ተጠብቀዋል። ከዚያም በኋላ በ1456 ዓ.ም. ጆሐን ጎትንበርግ በተባለ በአንድ ጀርመናዊ አንድ ማተሚያ ተስራ፣ የመጀመሪያው የታተመ መጽሐፍ በመሆን መጽሐፍ ቅዱስ ታተመ። ከዚያ ጊዜ በኋላ መጻሕፍት በእጅ መገልበጣቸው አበቃ፤ በማተሚያ ቤቶች አማካይነት በፍጥነትና በቀላል ዋጋ ሊታተሙ ቻሉ። የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በብዙ ቋንቋዎች ይደረግ ስለነበር፥ አሁን መጽሐፍ ቅዱስ በማንኛውም ተራ ሰው እጅ ሊገኝ ቻለ። በዛሬ ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከዓለም ቋንቋዎች 1200 በሚያህሉት ተተርጉሞአል፤ በዓለም ታሪክ ውስጥ ይህን በሚያህል ቋንቋዎች የተተረጎመ ወይም ይህን በሚያህል ሕዝብ የተነበበ ሌላ መጽሐፍ ጨርሶ አይገኝም።
እነዚህ በመቶና በሺ የሚቆጠሩ ጥንታውያን ጽሑፎች እስከ አሁን ጊዜ ድረስ ተጠብቀው መቆየታቸው፤ መጽሐፍ ቅዱስ ከመጀመሪያው የግሪክ ጹሑፎች በትክክል ተገልብጦ ወደ እኛ ለመድረሱ ማረጋገጫ ነው። ምንም እንኳ አንዳንድ ጸሐፊዎች ሲገለብጡ አልፎ አልፎ ስሕተት ማድረጋቸው የሚታወቅ ቢሆንም ብዙዎቹ ጹሑፎች በአንድነት በሚጠኑበት ጊዜ የመጀመሪያዎቹ ጸሐፊዎች በእያንዳንዱ ሁኔታ ምን ለማለት እንደፈለጉ መወሰን ይቻላል። ይህን ያህል የጥንት ግልባጭ ያለው ሌላ የጥንት መጽሐፍ በጭራሽ አይገኝም። የዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች እግዚአብሔር አስቀድሞ ለመጀመሪያዎቹ ፀሐፊዎች የሰጣቸው ቃል ነው ብለን የምንታመነውም ስለዚህ ነው።
ዛሬ የሚገኙ መጽሐፍ ቅዱሶች ትክክለኛ መሆናቸውን የምናረጋግጥበት ሌላም በጣም ጠቃሚ የሆነ ምክንያት አለ። ይኸውም እግዚአብሔር ቃሉን ጠብቆ ለትውልዶች ሁሉ አንዲተላለፍ የሰጠው ተስፋ ነው (መዝ. 119፥89፤152፤160)። እግዚአብሔር ቃሉ እንዳይጠፋና መሠረታዊ ለውጥ እንዳይደረግበት በማድረጉ በጣም ልንተማመን እንችላለን።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 90-91
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
📜መጽሐፍ ቅዱሳችን እንዴት ተፃፈ
አዲስ ኪዳን
አዲስ ኪዳን የተጻፈው በግሪክ ቋንቋ ሲሆን መጻፍ የተጀመረውም ክርስቶስ ከሞተ ከሃያ ዓመት በኋላ ነበር። ክርስቶስ ለደቀመዛሙርቱ የሰጣቸው የመጨረሻ ትእዛዝ፤ ለዓለም በሙሉ ምስክሮቹ እንዲሆኑ ስለነበር (የሐዋ. 1፥8)፤ ከጴንጠቆስጤ ቀን ጀምሮ ደቀመዛሙርቱ ስለ ክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት ለሌሎች መንገር ጀመሩ። ክርስቶስ ከሞተ በኋላ ለመጀመሪያዎቹ ሃያ ዓመታት ደቀመዛሙርቱ ወይም ሐዋርያቱ በአፍ እየተናገሩ ቃሉን ያስተምሩ ነበር። ነገር ግን ሐዋርያቱ እያረጁ ሲሄዱ ትምህርታቸው አንዳች ሳይዛነፍ በጹሑፍ ለመጪው ትውልድ መተላለፉ አስፈላጊ ሆነ። ይህም ለወደፊት ዘመናት በትክክል መተላለፉን ለማረጋገጥ ይጠቅም ነበር፤ ስለዚህ ከሐዋርያት አንዳንዶቹና የቅርብ ተባባሪዎቻቸው ስለ ክርስቶስ ሕይወት መጻፍ ጀመሩ። ሐዋርያው ጴጥሮስ የማርቆስን ወንጌል ለመጻፍ ከማርቆስ ጋር አብሮ ሠራ። ሐዋርያው ማቴዎስ የማቴዎስን ወንጌል ጻፈ። ሐዋርያው ዮሐንስ የዮሐንስን ወንጌል ጻፈ። የሐዋርያው ጳውሎስ የቅርብ ረዳት የነበረው ሉቃስ የሉቃስን ወንጌልና የቀድሞይቱ ቤተክርስቲያን ታሪክ የሆነውን የሐዋርያት ሥራን ጻፈ።
ስለ ክርስቶስ ሕይወት ከመጻፍ በተጨማሪ ሐዋርያቱ ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣበትን ምክንያት አስፋፍተው ለመጻፍ ግድ ሆነባቸው። እንዲሁም በአዳዲስ አብያተክርስቲያናት ዘንድ መብቀል የጀመሩትን አንዳንድ ስሕተቶችና ሐሰተኛ ትምህርቶች ለማረምም መጻፍ ነበረባቸው። ስለዚህ ለመሠረቱአቸው አዳዲስ አብያተክርስቲያናት መልእክት መጻፍ ጀመሩ። ሐዋርያው ጳውሎስ በ50 ዓ.ም. ገደማ ከተፃፈው የገላትያ መልዕክት አንስቶ በአጠቃላይ ዐሥራ ሦስት መልእክቶችን ጻፈ። አንዳንድ ሊቃውንት ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መካከል በመጀመሪያ የተጻፈው የያዕቆብ ማለትም የኢየሱስ ወንድም መልእክት ነው ብለው ያምናሉ።
ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መካከል በመጨረሻ የተጻፈው የራእይ መጽሐፍ ነው፤ ይህም መጽሐፍ የተጻፈው በሐዋርያው ዮሐንስ ሲሆን እርሱም የተጻፈው ከ90–95 ዓ.ም. ገደማ ነው። ስለዚህ መላው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ተጽፈው ያበቁት ከ50 ዓ.ም. እስከ 100 ዓ.ም. መካከል ባለው ዘመን ነው። ከአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ከመጀመሪያዎቹ ጽሑፎች አብዛኛዎቹ የተጻፉት ፓፒረስ ከሚባል ተክል ከተሠራ ወረቀት ነበር፤ ይህ ፓፒረስ እንደ ዘመኑ ወረቀት ነዋሪ አልነበረም፤ ስለሆነም ለብዙ ጊዜ አይቆይም ነበር። ከዚህም የተነሣ የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች በፓፒረስ ጥቅል የጻፉአቸው ጹሑፎች በሙሉ ጠፍተዋል፤ ልክ እንደ ብሉይ ኪዳን ጹሑፎች ሁሉ ዛሬ የሚገኙት የአዲስ ኪዳን ጹሑፎች የዋናው ቅጅ ማለትም ከፓፒረሱ የተቀዱ ናቸው።
ከክርስቶስ በኋላ ለመጀመሪያዎቹ ሦስት መቶ ዓመታት አዲስ ኪዳን ጹሑፎች በጥንቃቄና በትክክል በፓፒረስ ጥቅል በጸሐፊዎች አማካይነት የተገለበጡ ናቸው። 1900 ዓመት እንደገባ ወዲያውኑ፥ ከነዚህ ከፓፒረስ ግልባጮች ከነበሩት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጥቂቶቹ በግብጽ አገር በአሸዋ ውስጥ ተቀብረው ተገኝተዋል። ሌሎቹ ደግሞ በመከላከያ መያዥያዎች በጥንቃቄ ተጣጥፈው ተገኝተዋል። ከነዚህም በጣም ያረጀው ግልባጭ በ135 ዓ.ም. የተሠራ ሲሆን ከዮሐንስ ወንጌል ጥቂቱን ክፍል የያዘ ነበር። በመቀጠል በጣም የቆዩት ጥቅሎች በ200 ዓ.ም. ላይ የተገለበጡና ከአዲስ ኪዳን አብዛኛውን ክፍል የያዙ ነበሩ፤ እነዚህ የጥንት ጥቅሎች በአሁኑ ጊዜ በሙዝየም ውስጥ ተጠብቀው ይገኛሉ።
በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን ሰዎች ይጠቀሙበት የነበረ ሌላው የወረቀት ዐይነት፤ ብራና ከሚባል በተለየ ሁኔታ ለፍቶና ታሽቶ የተሠራ የፍየልና የበግ ቆዳ ነበር። ብራና ከፓፒረስ ይልቅ በጣም ውድ ሲሆን፤ ከአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጥቂቶቹ በመጀመሪያ የተጻፉት ከብራና እንደነበረ ይገመታል። ይህ ከሆነ ደግሞ በደንብ ተጠብቀው አልተያዙም ማለት ነው። ሙሉው አዲስ ኪዳን በጣም ያረጀው ግልባጭ የተሠራው በአራተኛው መቶ ዓመት ላይ ነበር። የተጻፈውም በብራና ሲሆን ይህም ያረጀ ግልባጭ የተገኘው በ1800 ዓ.ም. መካከለኛ ላይ በግብጽ አገር በሚገኘው በሲና ተራራ በመነኩሳት ገዳም ውስጥ ነበር። ከዚህም ካረጀ ጥቅል ሌላ የግሪክ አዲስ ኪዳን ግልባጮች የሆኑ በብራና ላይ የተጻፉ ሌላ 270 ግልባጮች በአሁኑ ወቅት ይገኛሉ። የተፃፉትም በአራተኛና በዘጠነኛ መቶ ዓመታት መካከል ነበር።
ከዘጠነኛው መቶ ዓመት እስከ ዐሥራ አምስተኛው መቶ ዓመት በግሪክ ብዙ ቋንቋ አዲስ ኪዳን ግልባጮች ተሠርተዋል፤ ከእነርሱም ከ2700 በላይ የሚሆኑ ግልባጮች እስከ አሁኑ ዘመን ተጠብቀዋል። ከዚያም በኋላ በ1456 ዓ.ም. ጆሐን ጎትንበርግ በተባለ በአንድ ጀርመናዊ አንድ ማተሚያ ተስራ፣ የመጀመሪያው የታተመ መጽሐፍ በመሆን መጽሐፍ ቅዱስ ታተመ። ከዚያ ጊዜ በኋላ መጻሕፍት በእጅ መገልበጣቸው አበቃ፤ በማተሚያ ቤቶች አማካይነት በፍጥነትና በቀላል ዋጋ ሊታተሙ ቻሉ። የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በብዙ ቋንቋዎች ይደረግ ስለነበር፥ አሁን መጽሐፍ ቅዱስ በማንኛውም ተራ ሰው እጅ ሊገኝ ቻለ። በዛሬ ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከዓለም ቋንቋዎች 1200 በሚያህሉት ተተርጉሞአል፤ በዓለም ታሪክ ውስጥ ይህን በሚያህል ቋንቋዎች የተተረጎመ ወይም ይህን በሚያህል ሕዝብ የተነበበ ሌላ መጽሐፍ ጨርሶ አይገኝም።
እነዚህ በመቶና በሺ የሚቆጠሩ ጥንታውያን ጽሑፎች እስከ አሁን ጊዜ ድረስ ተጠብቀው መቆየታቸው፤ መጽሐፍ ቅዱስ ከመጀመሪያው የግሪክ ጹሑፎች በትክክል ተገልብጦ ወደ እኛ ለመድረሱ ማረጋገጫ ነው። ምንም እንኳ አንዳንድ ጸሐፊዎች ሲገለብጡ አልፎ አልፎ ስሕተት ማድረጋቸው የሚታወቅ ቢሆንም ብዙዎቹ ጹሑፎች በአንድነት በሚጠኑበት ጊዜ የመጀመሪያዎቹ ጸሐፊዎች በእያንዳንዱ ሁኔታ ምን ለማለት እንደፈለጉ መወሰን ይቻላል። ይህን ያህል የጥንት ግልባጭ ያለው ሌላ የጥንት መጽሐፍ በጭራሽ አይገኝም። የዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች እግዚአብሔር አስቀድሞ ለመጀመሪያዎቹ ፀሐፊዎች የሰጣቸው ቃል ነው ብለን የምንታመነውም ስለዚህ ነው።
ዛሬ የሚገኙ መጽሐፍ ቅዱሶች ትክክለኛ መሆናቸውን የምናረጋግጥበት ሌላም በጣም ጠቃሚ የሆነ ምክንያት አለ። ይኸውም እግዚአብሔር ቃሉን ጠብቆ ለትውልዶች ሁሉ አንዲተላለፍ የሰጠው ተስፋ ነው (መዝ. 119፥89፤152፤160)። እግዚአብሔር ቃሉ እንዳይጠፋና መሠረታዊ ለውጥ እንዳይደረግበት በማድረጉ በጣም ልንተማመን እንችላለን።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 90-91
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤3👍3👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና።”
1ኛ ጴጥሮስ 3፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና።”
1ኛ ጴጥሮስ 3፥9
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤4👏2👍1🥰1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
መዝሙር 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አቤቱ፥ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል?
² በቅንነት የሚሄድ፥ ጽድቅንም የሚያደርግ፥ በልቡም እውነትን የሚናገር።
³ በአንደበቱ የማይሸነግል፥ በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ፥ ዘመዶቹንም የማይሰድብ።
⁴ ኃጢአተኛ በፊቱ የተናቀ፥ እግዚአብሔርንም የሚፈሩትን የሚያከብር፥ ለባልንጀራው የሚምል የማይከዳም።
⁵ ገንዘቡን በአራጣ የማያበድር፥ በንጹሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል። እንዲህ የሚያደርግ ለዘላለም አይታወክም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
መዝሙር 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አቤቱ፥ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል?
² በቅንነት የሚሄድ፥ ጽድቅንም የሚያደርግ፥ በልቡም እውነትን የሚናገር።
³ በአንደበቱ የማይሸነግል፥ በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ፥ ዘመዶቹንም የማይሰድብ።
⁴ ኃጢአተኛ በፊቱ የተናቀ፥ እግዚአብሔርንም የሚፈሩትን የሚያከብር፥ ለባልንጀራው የሚምል የማይከዳም።
⁵ ገንዘቡን በአራጣ የማያበድር፥ በንጹሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል። እንዲህ የሚያደርግ ለዘላለም አይታወክም።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤2👍1🔥1🥰1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።”
1 ዜና 16፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።”
1 ዜና 16፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤3👍3🔥1
#የሮሜ_መልእክት_ጥናት
ሮሜ 8፥9-11
የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በአማኝ ሕይወት ውስጥ
ክርስቲያኖች «ደኅንነትን» በተቀበሉ ጊዜ እንደ «ጻድቃን» ተቆጥረዋል። ይሁንና አሁንም ቢሆን ኃጢአተኞችና ቅዱስም መሆን የሚያስፈልጋቸው ናቸው። በዕለት ተዕለት ኑሮአችን ቅዱሳን የምንሆነው በእኛ አድሮ ሥራውን በሚሠራው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ነው፤ አማኞችን መቀደስ የመንፈስ ቅዱስ ቋሚ ሥራ ነው።
“እኛ ግን፥ በጌታ የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን ልናመሰግን ግድ አለብን፥ እግዚአብሔር በመንፈስ መቀደስ እውነትንም በማመን ለመዳን እንደ በኵራት መርጦአችኋልና፤”
2ኛ ተሰሎንቄ 2፥13
“እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ካወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ አማካይነት ለተቀደሱት፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።”
1ኛ ጴጥሮስ 1፥2 (አዲሱ መ.ት)
እግዚአብሔር የተቀደሰ ሕይወት እንድንኖር ጠርቶናል።
“ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።”
ኤፌሶን 1፥4
“እግዚአብሔር በቅድስና እንድንመላለስ እንጂ ለርኵሰት አልጠራንምና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 4፥7 (አዲሱ መ.ት)
እንዲሁም ኢየሱስ ቅዱሳን ወይም «ፍጹማን» እንድንሆን አዞናል (ማቴ. 5፥4-8)። ሆኖም በእርግጥ ቅዱሳን ወይም ፍጹማን እንድንሆን የሚያደርገን መንፈስ ቅዱስ ነው።
ደኅንነት ያገኙ ሰዎች ቅዱሳን መሆን አለባቸው (2ተሰ. 2፥13)። ምክንያቱም ያለ ቅድስና ሕይወት እግዚአብሔርን ማየት ከቶ አይቻልም (ዕብ. 12፥14)። ቅዱሳን ሆነን መገኘት ያለብን ደኅንነትን ለማግኘት ስንል አይደለም። ነገር ግን ደኅንነትን በማግኘታችን ቅዱሳን መሆን አለብን።
“አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው።”
ሮሜ 6፥22
በራሳችን ጥረት ብቻ ቅዱሳን መሆን አንችልም። መንፈስ ቅዱስ ግን ቅዱሳን እንድንሆን ያግዘናል። ሥጋዊ ሥራችንን መግደል የምንችለው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ነው (ሮሜ 8፥13)፡ ጳውሎስ በአንድ ወቅት የገላትያ ሰዎች እግዚአብሔር በነፃ በሰጣቸው ደኅንነት የእምነት ጉዞአቸውን ከጀመሩ በኋላ ተመልሰው በራሳቸው ጥረት ፍጹማንና ቅዱሳን ለመሆን ይሞክሩ ይሆናል የሚል ስጋት አድሮበት ነበር።
“እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጸማላችሁን?”
ገላትያ 3፥3
ቅዱሳን መሆን የምንችለው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ብቻ ነው። እንዲህ ሲባል ግን በቅድስናው ሂደት ውስጥ ምንም ድርሻ የለንም ማለት አይደለም።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 32
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
ሮሜ 8፥9-11
የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በአማኝ ሕይወት ውስጥ
ክርስቲያኖች «ደኅንነትን» በተቀበሉ ጊዜ እንደ «ጻድቃን» ተቆጥረዋል። ይሁንና አሁንም ቢሆን ኃጢአተኞችና ቅዱስም መሆን የሚያስፈልጋቸው ናቸው። በዕለት ተዕለት ኑሮአችን ቅዱሳን የምንሆነው በእኛ አድሮ ሥራውን በሚሠራው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ነው፤ አማኞችን መቀደስ የመንፈስ ቅዱስ ቋሚ ሥራ ነው።
“እኛ ግን፥ በጌታ የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን ልናመሰግን ግድ አለብን፥ እግዚአብሔር በመንፈስ መቀደስ እውነትንም በማመን ለመዳን እንደ በኵራት መርጦአችኋልና፤”
2ኛ ተሰሎንቄ 2፥13
“እግዚአብሔር አብ አስቀድሞ ካወቃቸው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመታዘዝ በደሙ ለተረጩትና በመንፈስ አማካይነት ለተቀደሱት፤ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።”
1ኛ ጴጥሮስ 1፥2 (አዲሱ መ.ት)
እግዚአብሔር የተቀደሰ ሕይወት እንድንኖር ጠርቶናል።
“ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።”
ኤፌሶን 1፥4
“እግዚአብሔር በቅድስና እንድንመላለስ እንጂ ለርኵሰት አልጠራንምና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 4፥7 (አዲሱ መ.ት)
እንዲሁም ኢየሱስ ቅዱሳን ወይም «ፍጹማን» እንድንሆን አዞናል (ማቴ. 5፥4-8)። ሆኖም በእርግጥ ቅዱሳን ወይም ፍጹማን እንድንሆን የሚያደርገን መንፈስ ቅዱስ ነው።
ደኅንነት ያገኙ ሰዎች ቅዱሳን መሆን አለባቸው (2ተሰ. 2፥13)። ምክንያቱም ያለ ቅድስና ሕይወት እግዚአብሔርን ማየት ከቶ አይቻልም (ዕብ. 12፥14)። ቅዱሳን ሆነን መገኘት ያለብን ደኅንነትን ለማግኘት ስንል አይደለም። ነገር ግን ደኅንነትን በማግኘታችን ቅዱሳን መሆን አለብን።
“አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው።”
ሮሜ 6፥22
በራሳችን ጥረት ብቻ ቅዱሳን መሆን አንችልም። መንፈስ ቅዱስ ግን ቅዱሳን እንድንሆን ያግዘናል። ሥጋዊ ሥራችንን መግደል የምንችለው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ነው (ሮሜ 8፥13)፡ ጳውሎስ በአንድ ወቅት የገላትያ ሰዎች እግዚአብሔር በነፃ በሰጣቸው ደኅንነት የእምነት ጉዞአቸውን ከጀመሩ በኋላ ተመልሰው በራሳቸው ጥረት ፍጹማንና ቅዱሳን ለመሆን ይሞክሩ ይሆናል የሚል ስጋት አድሮበት ነበር።
“እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጸማላችሁን?”
ገላትያ 3፥3
ቅዱሳን መሆን የምንችለው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ብቻ ነው። እንዲህ ሲባል ግን በቅድስናው ሂደት ውስጥ ምንም ድርሻ የለንም ማለት አይደለም።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 32
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤2👍2👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ደግሞም፣ 'የሰው ሕይወቱ በሀብቱ ብዛት የተመሠረተ ስላልሆነ፣ ተጠንቀቁ፤ ከስግብግ ብነትም ሁሉ ራሳችሁንም ጠብቁ' አላቸው።”
ሉቃስ 12፥15 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ደግሞም፣ 'የሰው ሕይወቱ በሀብቱ ብዛት የተመሠረተ ስላልሆነ፣ ተጠንቀቁ፤ ከስግብግ ብነትም ሁሉ ራሳችሁንም ጠብቁ' አላቸው።”
ሉቃስ 12፥15 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
👍3❤1🔥1👏1
የቀጠለ...
📜መጽሐፍ ቅዱሳችን እንዴት ተፃፈ
የአዲስ ኪዳን ቀኖና
ገና ከመጀመሪያው በአዲስ ኪዳን ቀኖና ውስጥ ሊገቡ ስለሚገባቸው መጻሕፍት አንድ አጠቃላይ ስምምነት ተደርጎአል። በ200 ዓ.ም. አዲስ ኪዳን ያጠቃለላቸው መጽሐፍት አሁን እኛ ያሉን መጽሐፍ ቅዱሶች ከያዙት የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ጋር አንድ ዐይነት ናቸው። ይሁን እንጂ በአንዳንድ መጻሕፍት ላይ አለመስማማት ነበር፤ ይህም አለመስማማት እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ቀጠለ። በተለይ አንዳንድ ክርስቲያኖች በአዲስ ኪዳን ውስጥ ዕብራውያን፥ ያዕቆብ፥ 2ጴጥሮስ፥ 2 እና 3ዮሐንስ፥ ይሁዳና ራእይ መግባት አይኖርባቸውምን? ብለው ጠየቁ። ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ጽሑፎች በመጀመሪያው መቶ ዓመት ገደማ በአንዳንድ ክርስቲያን መሪዎች የተጻፉ ሲሆኑ አንዳንድ ሰዎች በቀኖናት ውስጥ መግባት አለባቸው ሲሉ ሌሎች ደግሞ ጨርሶ መግባት የለባቸውም ይሉነበር። በአራተኛው መቶ ዓመት መጨረሻ ላይ እነዚህ ሁሉ አለመስማማቶች ተወግደው ነበር። በዓለም ላይ የሚገኝ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ዘመን የሚገኘውን አዲስ ኪዳን ቀኖና በሙሉ ልብ ተቀብለው ኦፊሲላዊ አድርገውት ነበር፤ ከዚያን ጊዜም ጀምሮ በአዲስ ኪዳን ቀኖና ውስጥ በሚገኘውም ክፍል አለመስማማት አልተፈጠረም።
በአዲስ ኪዳን ውስጥ የትኛው መጽሐፍ መግባት አለበት ለሚለው ውሳኔ አራት መለኪያዎች ነበሩ።
1. መጀመሪያ አንድ መጽሐፍ በሐዋርያ ወይም ለሐዋርያው ቅርብ ረዳት በነበረ ሰው መጻፍ ይኖርበታል።
2. ሁለተኛ መጽሐፉ የያዘው ምስጢር ከፍተኛ መንፈሳዊነት ሊኖረው ይገባል፤ እንዲሁም ከብሉይ ኪዳን ትምህርትና ከሐዋርያት ትምህርት ጋር ተመሳሳይነት ሊኖረው ይገባል።
3. ሦስተኛ መጽሐፉ ከአብያተክርስቲያናት አብዛኛው ክፍል ሊቀበለው ያስፈልጋል።
4. አራተኛ መጽሐፉ ግልጽ በሆነ ሁኔታ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ሊኖረው ያስፈልጋል። የትኞቹን መጻሕፍት በቀኖና ውስጥ ማስገባት እንደሚያስፈልግ ውሳኔ ሲደረግ የጥንት ቤተክርስቲያንን ትመራ የነበረው በመንፈስ ቅዱስ ነበር፤ ሰዎች በራሳቸው ውሳኔ ብቻ መጻሕፍትን መርጠው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለማስገባት አይወስኑም፤ ይልቁንም መንፈስ ቅዱስ እየመራቸው የትኞቹ መጻሕፍት የእግዚአብሔር ቃል እንደሆኑ ያሳያቸዋል።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 91
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
📜መጽሐፍ ቅዱሳችን እንዴት ተፃፈ
የአዲስ ኪዳን ቀኖና
ገና ከመጀመሪያው በአዲስ ኪዳን ቀኖና ውስጥ ሊገቡ ስለሚገባቸው መጻሕፍት አንድ አጠቃላይ ስምምነት ተደርጎአል። በ200 ዓ.ም. አዲስ ኪዳን ያጠቃለላቸው መጽሐፍት አሁን እኛ ያሉን መጽሐፍ ቅዱሶች ከያዙት የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ጋር አንድ ዐይነት ናቸው። ይሁን እንጂ በአንዳንድ መጻሕፍት ላይ አለመስማማት ነበር፤ ይህም አለመስማማት እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ቀጠለ። በተለይ አንዳንድ ክርስቲያኖች በአዲስ ኪዳን ውስጥ ዕብራውያን፥ ያዕቆብ፥ 2ጴጥሮስ፥ 2 እና 3ዮሐንስ፥ ይሁዳና ራእይ መግባት አይኖርባቸውምን? ብለው ጠየቁ። ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ጽሑፎች በመጀመሪያው መቶ ዓመት ገደማ በአንዳንድ ክርስቲያን መሪዎች የተጻፉ ሲሆኑ አንዳንድ ሰዎች በቀኖናት ውስጥ መግባት አለባቸው ሲሉ ሌሎች ደግሞ ጨርሶ መግባት የለባቸውም ይሉነበር። በአራተኛው መቶ ዓመት መጨረሻ ላይ እነዚህ ሁሉ አለመስማማቶች ተወግደው ነበር። በዓለም ላይ የሚገኝ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ዘመን የሚገኘውን አዲስ ኪዳን ቀኖና በሙሉ ልብ ተቀብለው ኦፊሲላዊ አድርገውት ነበር፤ ከዚያን ጊዜም ጀምሮ በአዲስ ኪዳን ቀኖና ውስጥ በሚገኘውም ክፍል አለመስማማት አልተፈጠረም።
በአዲስ ኪዳን ውስጥ የትኛው መጽሐፍ መግባት አለበት ለሚለው ውሳኔ አራት መለኪያዎች ነበሩ።
1. መጀመሪያ አንድ መጽሐፍ በሐዋርያ ወይም ለሐዋርያው ቅርብ ረዳት በነበረ ሰው መጻፍ ይኖርበታል።
2. ሁለተኛ መጽሐፉ የያዘው ምስጢር ከፍተኛ መንፈሳዊነት ሊኖረው ይገባል፤ እንዲሁም ከብሉይ ኪዳን ትምህርትና ከሐዋርያት ትምህርት ጋር ተመሳሳይነት ሊኖረው ይገባል።
3. ሦስተኛ መጽሐፉ ከአብያተክርስቲያናት አብዛኛው ክፍል ሊቀበለው ያስፈልጋል።
4. አራተኛ መጽሐፉ ግልጽ በሆነ ሁኔታ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ሊኖረው ያስፈልጋል። የትኞቹን መጻሕፍት በቀኖና ውስጥ ማስገባት እንደሚያስፈልግ ውሳኔ ሲደረግ የጥንት ቤተክርስቲያንን ትመራ የነበረው በመንፈስ ቅዱስ ነበር፤ ሰዎች በራሳቸው ውሳኔ ብቻ መጻሕፍትን መርጠው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለማስገባት አይወስኑም፤ ይልቁንም መንፈስ ቅዱስ እየመራቸው የትኞቹ መጻሕፍት የእግዚአብሔር ቃል እንደሆኑ ያሳያቸዋል።
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 91
ይቀጥላል...
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
👍2❤1
📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንግዲህ እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ? ይላል ቅዱሱ።”
ኢሳይያስ 40፥25
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“እንግዲህ እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ? ይላል ቅዱሱ።”
ኢሳይያስ 40፥25
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤2👍1👏1
📜ርዕስ፦ "ለታማኝ አገልጋይነት የሚጠቅሙ ባሕርያት"
🖨አሳታሚ:- SIM ማተሚያ ቤት
📅የታተመበት ዓ.ም፦ 1983
🔢የገጽ ብዛት፦ 99
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
🖨አሳታሚ:- SIM ማተሚያ ቤት
📅የታተመበት ዓ.ም፦ 1983
🔢የገጽ ብዛት፦ 99
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤3👍1🥰1
CFS_01.pdf
630.9 KB
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
Follow the ቅዱሳት መጻሕፍት channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaA94PKFsn0ejWkJe012
❤3👍3
📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የሰላምም ጌታ ራሱ በሁሉ መንገድ ዘወትር ሰላምን ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“የሰላምም ጌታ ራሱ በሁሉ መንገድ ዘወትር ሰላምን ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።”
2ኛ ተሰሎንቄ 3፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤3🥰2👍1
ቤት ውስጥ ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሶች አሉዎት? አብዛኞቻችን ብዙ መጽሐፍ ቅዱሶች አሉን። የእንግሊዘኛ መጽሐፍ ቅዱስ አባት ተብሎ የሚጠራው ዊልያም ቲንደል ዛሬ ለእንግሊዝኛ ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ መኖር ዋነኛው ሰው ነው። ምንም እንኳን 90% የኪንግ ጀምስ ቨርዥን(KJV) እና 75% የተሻሻለው ስታንዳርድ ቨርሽን(RSV) ምንጭ የሆነው የዊልያም ቲንደል የእንግሊዘኛ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ቢሆንም ቲንደል በዚህ ቀን ኦክቶበር 6፣ በ1536 መጽሐፍ ቅዱስ ስለተረጎመ በአደባባይ በእንጨት ላይ በእሳት ተቃጥሏል። በእጃችን ላይ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋውን እንድንረዳው እግዚአብሔር ይርዳን!
ምንጭ፦ biblestudytools.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ምንጭ፦ biblestudytools.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤5👍1🔥1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥ በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል።”
ምሳሌ 16፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥ በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል።”
ምሳሌ 16፥32
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤2👍1🔥1👏1
#እራሳችንን_እንመርምር
ለመሆኑ እግዚአብሔርን የምናስበው ሁልጊዜ ለእኛ መልካም አሳብ የሚያስብ አምላክ አድርገን ነው ወይስ አልፎ አልፎ የሚጎዳንን ነገር የሚያደርግ አምላክ ብለን? ቁጣው እና ተግሳጹን፣ ቅጣቱን እና ማስጨነቁን እንደጉዳት ቆጥረነው ይሆን?
“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።”
ኤርምያስ 29፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ለመሆኑ እግዚአብሔርን የምናስበው ሁልጊዜ ለእኛ መልካም አሳብ የሚያስብ አምላክ አድርገን ነው ወይስ አልፎ አልፎ የሚጎዳንን ነገር የሚያደርግ አምላክ ብለን? ቁጣው እና ተግሳጹን፣ ቅጣቱን እና ማስጨነቁን እንደጉዳት ቆጥረነው ይሆን?
“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።”
ኤርምያስ 29፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1🥰1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።”
ኤፌሶን 1፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።”
ኤፌሶን 1፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍3❤2🔥1🥰1
#መጻሕፍትን_እንመርምር
አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?
ክፍል-7
እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ ጠርቷልን?
እግዚአብሔር የሚፈልገው እያንዳንዱ ሰው ደኅንነትን እንዲያገኝ ነው ወይስ ጥቂቶች ብቻ? በማቴዎስ 22፥14 ላይ ኢየሱስ ሲናገር፥ «የተጠሩ ብዙዎች ናቸው፤ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸው» ብሏል። ኢየሱስ የዓለም አዳኝ እንደሆነና (ዮሐ. 4፥42፤ 1ዮሐ. 4፥14) የዓለምንም ኃጢአት ለማስወገድ ሲል እንደሞተ በግልጽ መረዳት ይቻላል (ዮሐ. 1፥29፤ 1ዮሐ. 2፥2)። ከዚህ በተጨማሪ ጳውሎስ ሲናገር እግዚአብሔር «ሰዎችን ሁሉ» እንዲድኑ እግዚአብሔር ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል (ሮሜ 11፥32፤ 1ጢሞ. 2፥46፤ 2ጴጥ. 3፥9)። ግን «ሰዎችን ሁሉ» ማለት ምን ማለት ነው? «ሰዎችን ሁሉ» የሚለውስ ሐረግ ምንን ያመለክታል?
1. አንዳንድ ክርስቲያኖች እንደሚሉት «ሰዎችን ሁሉ» ማለት «ከሁሉም የኀብረተሰብ ክፍሎች» ማለት ነው። እንዲህም ሲባል እግዚአብሔር ከሁሉም የኀብረተሰብ ክፍሎች አንዳንድ ሰዎችን ጠርቷል ወይም መርጧል ማለት ነው። እንዲህ የሚሉት ክርስቲያኖች እግዚአብሔር የክርስቶስ ወንጌል በዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ፍላጎቱ ነው፤ ይሁንና የእምነትን ስጦታ የሚሰጠው ከእያንዳንዱ የኀብረተሰብ ክፍል ውስጥ ለጥቂቶች ብቻ ነው ይላሉ።
2. እንደ ሌሎች ክርስቲያኖች አባባል ግን «ሰዎችን ሁሉ» ማለት «አንድም ሳይቀር ሁሉንም ሰዎች» ማለት ነው። ምንም እንኳን እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ ቢጠራም፥ አማኞች ብቻ ናቸው «የተመረጡ» ተብለው መጠራት ያለባቸው ይላሉ (በግሪኩ ንባብ ላይ ሁለቱም ፍቺዎች ያስኬዳሉ)።'
የሆነ ሆኖ ስለ ኢየሱስ ምንም ያልሰሙ ሰዎች እንዴት ይሆናሉ? የሚድኑበትስ መንገድ ይኖራልን? አያሌ ክርስቲያኖች ከቶ አይድኑም ይላሉ። ሰዎች ሁሉ በተፈጥሮዋቸው ኃጢአተኞች ናቸው። ሁሉም ሰው ሞት ይገባዋል (ሮሜ 3፥10–12፤ 6፥23)። በክርስቶስ ካልሆነ በቀር በሌላ በምንም መንገድ መዳን አይቻልም (ዮሐ. 14፥6፤ የሐዋ. 4፥12)። ስለዚህ ጳውሎስ በሮሜ 10፥13–14 ላይ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፥ «የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል ተብሎ ተጽፎአል። ነገር ግን ሳያምኑበት እንዴት ሊጠሩት ይችላሉ?። ስለ እርሱስ ሳይሰሙስ እንዴት ያምናሉ? የምሥራቹን ቃል የሚያበሥርላቸው ሳይኖርስ እንዴት ሊሰሙ ይችላሉ?» እግዚአብሔር ስለ ኢየሱስ ምንም ላልሰሙ ሰዎች ምሕረቱን ሊያሳይ ይችላል (ሉቃ. 12፥47-48፤ ሮሜ 2፥12)፤ ነገር ግን ይህ የእግዚአብሔር ውሣኔ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ምንም ስላልሰሙ ሰዎች ግልጽ የሆነ ትምህርት የለውም። ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ የመመስከር ኃላፊነት እንዳለብን በግልጽ ያወሳል።
በዚህ ክፍል የተነሱት ጥያቄዎች አስቸጋሪዎች ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ለእነዚህ ጥያቄዎች ሁሉ ቁርጥ መልስ አይሰጠንም። የእግዚአብሔር አሳብ እኮ ፍጹም ምስጢር ነው! ጥበቡና ዕውቀቱም እጅግ ጥልቅ ነው! (ሮሜ 11፥33–36)። ምናልባት እነዚህ ሁሉ አማራጮች በከፊል እውነትነት ይኖራቸዋል። ዮሐንስ ሲጽፍ፥ «እግዚአብሔር አስቀድሞ ስላፈቀረን እኛም እናፈቅራለን» (1ዮሐ. 4፥19) ብሏል። ምናልባትም እንዲህ ማለት ይቻላል፥ «እግዚአብሔር አስቀድሞ ስለመረጠን እኛም እርሱን መረጥነው» ደኅንነት የእግዚአብሔር ሥራ ቢሆንም እኛም ግን ድርሻ ያለን ይመስላል። ጳውሎስ እነዚህን ሁለት ሀሳቦች አያይዞ ሲጽፍ፥ «እያንዳንዳችሁ ያላችሁን ደኅንነት ፍጹም ለማድረግ በፍርሃትና በአክብሮት ተግታችሁ ሥሩ። ምክንያቱም እግዚአብሔር ፈቃደኛነትንና ታዛዥነትን ለእናንተ እየሰጠ ዓላማውን ከፍጻሜ ለማድረስ በእናንተ ውስጥ ይሠራል» ብሏል (ፊል. 2፥12–13)።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 26
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
አማኝ ወይም የዳነ ሰው ድነቱን ሊያጣ ይችላል ወይስ አይችልም?
ክፍል-7
እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ ጠርቷልን?
እግዚአብሔር የሚፈልገው እያንዳንዱ ሰው ደኅንነትን እንዲያገኝ ነው ወይስ ጥቂቶች ብቻ? በማቴዎስ 22፥14 ላይ ኢየሱስ ሲናገር፥ «የተጠሩ ብዙዎች ናቸው፤ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸው» ብሏል። ኢየሱስ የዓለም አዳኝ እንደሆነና (ዮሐ. 4፥42፤ 1ዮሐ. 4፥14) የዓለምንም ኃጢአት ለማስወገድ ሲል እንደሞተ በግልጽ መረዳት ይቻላል (ዮሐ. 1፥29፤ 1ዮሐ. 2፥2)። ከዚህ በተጨማሪ ጳውሎስ ሲናገር እግዚአብሔር «ሰዎችን ሁሉ» እንዲድኑ እግዚአብሔር ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል (ሮሜ 11፥32፤ 1ጢሞ. 2፥46፤ 2ጴጥ. 3፥9)። ግን «ሰዎችን ሁሉ» ማለት ምን ማለት ነው? «ሰዎችን ሁሉ» የሚለውስ ሐረግ ምንን ያመለክታል?
1. አንዳንድ ክርስቲያኖች እንደሚሉት «ሰዎችን ሁሉ» ማለት «ከሁሉም የኀብረተሰብ ክፍሎች» ማለት ነው። እንዲህም ሲባል እግዚአብሔር ከሁሉም የኀብረተሰብ ክፍሎች አንዳንድ ሰዎችን ጠርቷል ወይም መርጧል ማለት ነው። እንዲህ የሚሉት ክርስቲያኖች እግዚአብሔር የክርስቶስ ወንጌል በዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ፍላጎቱ ነው፤ ይሁንና የእምነትን ስጦታ የሚሰጠው ከእያንዳንዱ የኀብረተሰብ ክፍል ውስጥ ለጥቂቶች ብቻ ነው ይላሉ።
2. እንደ ሌሎች ክርስቲያኖች አባባል ግን «ሰዎችን ሁሉ» ማለት «አንድም ሳይቀር ሁሉንም ሰዎች» ማለት ነው። ምንም እንኳን እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ ቢጠራም፥ አማኞች ብቻ ናቸው «የተመረጡ» ተብለው መጠራት ያለባቸው ይላሉ (በግሪኩ ንባብ ላይ ሁለቱም ፍቺዎች ያስኬዳሉ)።'
የሆነ ሆኖ ስለ ኢየሱስ ምንም ያልሰሙ ሰዎች እንዴት ይሆናሉ? የሚድኑበትስ መንገድ ይኖራልን? አያሌ ክርስቲያኖች ከቶ አይድኑም ይላሉ። ሰዎች ሁሉ በተፈጥሮዋቸው ኃጢአተኞች ናቸው። ሁሉም ሰው ሞት ይገባዋል (ሮሜ 3፥10–12፤ 6፥23)። በክርስቶስ ካልሆነ በቀር በሌላ በምንም መንገድ መዳን አይቻልም (ዮሐ. 14፥6፤ የሐዋ. 4፥12)። ስለዚህ ጳውሎስ በሮሜ 10፥13–14 ላይ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፥ «የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል ተብሎ ተጽፎአል። ነገር ግን ሳያምኑበት እንዴት ሊጠሩት ይችላሉ?። ስለ እርሱስ ሳይሰሙስ እንዴት ያምናሉ? የምሥራቹን ቃል የሚያበሥርላቸው ሳይኖርስ እንዴት ሊሰሙ ይችላሉ?» እግዚአብሔር ስለ ኢየሱስ ምንም ላልሰሙ ሰዎች ምሕረቱን ሊያሳይ ይችላል (ሉቃ. 12፥47-48፤ ሮሜ 2፥12)፤ ነገር ግን ይህ የእግዚአብሔር ውሣኔ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ምንም ስላልሰሙ ሰዎች ግልጽ የሆነ ትምህርት የለውም። ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ የመመስከር ኃላፊነት እንዳለብን በግልጽ ያወሳል።
በዚህ ክፍል የተነሱት ጥያቄዎች አስቸጋሪዎች ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ ለእነዚህ ጥያቄዎች ሁሉ ቁርጥ መልስ አይሰጠንም። የእግዚአብሔር አሳብ እኮ ፍጹም ምስጢር ነው! ጥበቡና ዕውቀቱም እጅግ ጥልቅ ነው! (ሮሜ 11፥33–36)። ምናልባት እነዚህ ሁሉ አማራጮች በከፊል እውነትነት ይኖራቸዋል። ዮሐንስ ሲጽፍ፥ «እግዚአብሔር አስቀድሞ ስላፈቀረን እኛም እናፈቅራለን» (1ዮሐ. 4፥19) ብሏል። ምናልባትም እንዲህ ማለት ይቻላል፥ «እግዚአብሔር አስቀድሞ ስለመረጠን እኛም እርሱን መረጥነው» ደኅንነት የእግዚአብሔር ሥራ ቢሆንም እኛም ግን ድርሻ ያለን ይመስላል። ጳውሎስ እነዚህን ሁለት ሀሳቦች አያይዞ ሲጽፍ፥ «እያንዳንዳችሁ ያላችሁን ደኅንነት ፍጹም ለማድረግ በፍርሃትና በአክብሮት ተግታችሁ ሥሩ። ምክንያቱም እግዚአብሔር ፈቃደኛነትንና ታዛዥነትን ለእናንተ እየሰጠ ዓላማውን ከፍጻሜ ለማድረስ በእናንተ ውስጥ ይሠራል» ብሏል (ፊል. 2፥12–13)።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 26
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1👏1
' 📜📜📜===📜📜📜
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ኢያሱም በጋይ የሚኖሩትን ሁሉ ፈጽሞ እስኪያጠፋ ድረስ ጦር የዘረጋባትን እጁን አላጠፈም።”
ኢያሱ 8፥26
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
📜 የዕለቱ ጥቅስ 📜
📜📜📜===📜📜📜
“ኢያሱም በጋይ የሚኖሩትን ሁሉ ፈጽሞ እስኪያጠፋ ድረስ ጦር የዘረጋባትን እጁን አላጠፈም።”
ኢያሱ 8፥26
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
👍2❤1🔥1
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ሐጌ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በንጉሡ በዳርዮስ በሁለተኛው ዓመት በስድስተኛው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል በነቢዩ በሐጌ እጅ ወደ ይሁዳ አለቃ ወደ ሰላትያል ልጅ ወደ ዘሩባቤል፥ ወደ ታላቁም ካህን ወደ ኢዮሴዴቅ ልጅ ወደ ኢያሱ እንዲህ ሲል መጣ፦
² የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦ ይህ ሕዝብ፦ ዘመኑ አልደረሰም፥ የእግዚአብሔር ቤት የሚሠራበት ዘመን አልደረሰም ይላል ብሎ ተናገረ።
³ የእግዚአብሔርም ቃል በነቢዩ በሐጌ እጅ እንዲህ ሲል መጣ፦
⁴ በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?
⁵ አሁንም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ።
⁶ ብዙ ዘራችሁ፥ ጥቂትም አገባችሁ፤ በላችሁ፥ ነገር ግን አልጠገባችሁም፤ ጠጣችሁ፥ ነገር ግን አልረካችሁም፤ ለበሳችሁ፥ ነገር ግን አልሞቃችሁም፤ ደመወዙን የተቀበለ ሰው በቀዳዳ ከረጢት ያደርገው ዘንድ ደመወዙን ተቀበለ።
⁷ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ።
⁸ ወደ ተራራው ውጡ፥ እንጨትንም አምጡ፥ ቤቱንም ሥሩ፤ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል፥ እኔም እመሰገናለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።
⁹ እናንተ ብዙ ነገርን ተስፋ አደረጋችሁ፥ እነሆም፥ ጥቂት ሆነ ወደ ቤትም ባገባችሁት ጊዜ እፍ አልሁበት። ይህ ስለ ምንድር ነው? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። እናንተ ሁሉ ወደ እየቤታችሁ እየሮጣችሁ የእኔ ቤት ፈርሶ ስለ ተቀመጠ ነው።
¹⁰ ስለዚህ ሰማያት በላያችሁ ጠልን ከልክለዋል፥ ምድሪቱም ፍሬዋን ከልክላለች።
¹¹ እኔም በምድርና በተራሮች፥ በእህልና በወይንም፥ በዘይትና ምድርም በምታበቅለው ላይ፥ በሰዎችና በእንስሶችም ላይ፥ እጅም በሚደክምበት ሁሉ ላይ ድርቅን ጠርቻለሁ።
¹² የሰላትያልም ልጅ ዘሩባቤል፥ ታላቁም ካህን የኢዮሴዴቅ ልጅ ኢያሱ፥ የቀሩትም ሕዝብ ሁሉ የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ድምፅ የነቢዩንም የሐጌን ቃል፥ አምላካቸው እግዚአብሔር እንደ ላከው ሁሉ ሰሙ፤ ሕዝቡም በእግዚአብሔር ፊት ፈሩ።
¹³ የእግዚአብሔርም መልእክተኛ ሐጌ በእግዚአብሔር መልእክት ሕዝቡን፦ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ይላል እግዚአብሔር ብሎ ተናገረ።
¹⁴-¹⁵ እግዚአብሔርም የይሁዳን አለቃ የሰላትያልን ልጅ የዘሩባቤልን መንፈስ፥ የታላቁንም ካህን የኢዮሴዴቅን ልጅ የኢያሱን መንፈስ፥ የቀሩትንም ሕዝብ ሁሉ መንፈስ አስነሣ፤ በንጉሡም በዳርዮስ በሁለተኛው ዓመት በስድስተኛው ወር ከወሩም በሀያ አራተኛው ቀን መጡ፥ የአምላካቸውንም የሠራዊትን ጌታ የእግዚአብሔርን ቤት ሠሩ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
ሐጌ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በንጉሡ በዳርዮስ በሁለተኛው ዓመት በስድስተኛው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል በነቢዩ በሐጌ እጅ ወደ ይሁዳ አለቃ ወደ ሰላትያል ልጅ ወደ ዘሩባቤል፥ ወደ ታላቁም ካህን ወደ ኢዮሴዴቅ ልጅ ወደ ኢያሱ እንዲህ ሲል መጣ፦
² የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦ ይህ ሕዝብ፦ ዘመኑ አልደረሰም፥ የእግዚአብሔር ቤት የሚሠራበት ዘመን አልደረሰም ይላል ብሎ ተናገረ።
³ የእግዚአብሔርም ቃል በነቢዩ በሐጌ እጅ እንዲህ ሲል መጣ፦
⁴ በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?
⁵ አሁንም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ።
⁶ ብዙ ዘራችሁ፥ ጥቂትም አገባችሁ፤ በላችሁ፥ ነገር ግን አልጠገባችሁም፤ ጠጣችሁ፥ ነገር ግን አልረካችሁም፤ ለበሳችሁ፥ ነገር ግን አልሞቃችሁም፤ ደመወዙን የተቀበለ ሰው በቀዳዳ ከረጢት ያደርገው ዘንድ ደመወዙን ተቀበለ።
⁷ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ።
⁸ ወደ ተራራው ውጡ፥ እንጨትንም አምጡ፥ ቤቱንም ሥሩ፤ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል፥ እኔም እመሰገናለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።
⁹ እናንተ ብዙ ነገርን ተስፋ አደረጋችሁ፥ እነሆም፥ ጥቂት ሆነ ወደ ቤትም ባገባችሁት ጊዜ እፍ አልሁበት። ይህ ስለ ምንድር ነው? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። እናንተ ሁሉ ወደ እየቤታችሁ እየሮጣችሁ የእኔ ቤት ፈርሶ ስለ ተቀመጠ ነው።
¹⁰ ስለዚህ ሰማያት በላያችሁ ጠልን ከልክለዋል፥ ምድሪቱም ፍሬዋን ከልክላለች።
¹¹ እኔም በምድርና በተራሮች፥ በእህልና በወይንም፥ በዘይትና ምድርም በምታበቅለው ላይ፥ በሰዎችና በእንስሶችም ላይ፥ እጅም በሚደክምበት ሁሉ ላይ ድርቅን ጠርቻለሁ።
¹² የሰላትያልም ልጅ ዘሩባቤል፥ ታላቁም ካህን የኢዮሴዴቅ ልጅ ኢያሱ፥ የቀሩትም ሕዝብ ሁሉ የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ድምፅ የነቢዩንም የሐጌን ቃል፥ አምላካቸው እግዚአብሔር እንደ ላከው ሁሉ ሰሙ፤ ሕዝቡም በእግዚአብሔር ፊት ፈሩ።
¹³ የእግዚአብሔርም መልእክተኛ ሐጌ በእግዚአብሔር መልእክት ሕዝቡን፦ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ይላል እግዚአብሔር ብሎ ተናገረ።
¹⁴-¹⁵ እግዚአብሔርም የይሁዳን አለቃ የሰላትያልን ልጅ የዘሩባቤልን መንፈስ፥ የታላቁንም ካህን የኢዮሴዴቅን ልጅ የኢያሱን መንፈስ፥ የቀሩትንም ሕዝብ ሁሉ መንፈስ አስነሣ፤ በንጉሡም በዳርዮስ በሁለተኛው ዓመት በስድስተኛው ወር ከወሩም በሀያ አራተኛው ቀን መጡ፥ የአምላካቸውንም የሠራዊትን ጌታ የእግዚአብሔርን ቤት ሠሩ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
❤1👍1👏1