HaqCheck
429 subscribers
324 photos
39 videos
541 links
HaqCheck is an Ethiopia based fact-checking project that verifies media content from social to the mainstream. We fact-check in English and on local languages widely spoken in the Horn of Africa.

https://haqcheck.org
Download Telegram
በአማራ ክልል ያለውን ግጭት ተከትሎ ብዛት ያላቸው መረጃዎች በማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት እየተሰራጩ ነው። አንዳንዶቹ የቆዩና የሌላ ጊዜ ምስልና ቪድዮችን፣ የቅርብ እና አሁን ባለው ውቅታዊ ሁኔታ የተፈጠሩ በማስመሰል እያጋሩ ይገኛሉ።

ከሰሞኑ በፍኖተ ሰላም መንግስት በወሰደው የድሮን ጥቃት ሰዎች እንደተገደሉ የሚያሳዩ የተለያዩ መረጃዎች በማህበራዊ ሚድያ እና በአንዳንድ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት እየተገለጹ ነው።

ይህን ተከትሎ ከ 40ሺ በላይ ተከታይ ያሉት የፌስቡክ ገፅ በፍኖተ ሰላም መንግስት በወሰደው የድሮን ጥቃት 270 ንጹሃን ዜጎች፣ ህጻናትን ጨምሮ እንደሞቱ የሚገልጽ ጹሑፍ እና ምስል ለጥፎ በስፋት ሲዘዋወር ነበር።

ሀቅቼክ እንዳጣራው መርጃውን ለመደገፍ የተጠቀሙበት ምስል የቆየና ከአሁን በፊት በሌላ ፌስቡክ ግጽ ተለጥፎ የነበረ እንደሆነ ማረጋገጥ ተችሏል።

ሙሉውን ያንብቡ 👇👇👇
https://bityl.co/KV64
በማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚያጋጥሙህን/ሽን ምስሎች ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የምስል ማረጋገጫ መሳሪያዎችን ተጠቅመህ/ሽ ታውቃለህ/ቂያለሽ?
Anonymous Poll
13%
አዎ ሁል ጊዜ
23%
አዎ አልፎ አልፎ
20%
አይ ስለ ምስል ማረጋገጫ መሳርያዎች ምንም አላውቅም
43%
አላውቅም ግን ስለ ምስል ማረጋገጫ መሳሪያዎች መማር እፈልጋለሁ
በአማራ ክልል ያለውን የትጥቅ ግጭት ተከትሎ
ከ46 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ "በታንክ ታጅቦ የመጣ ሃይል በሞጣ ፋኖ ዶግ አመድ ተደርጓል" በሚል የመግለጫ ጹሑፍ ስር የምትመለከቱትን ምስል ለጥፎ ፣ ብዙ ግብረ መልሶችንም አግኝቷል።

በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ የኢትዮጵያ ወታደሮች እና ታንኮች መመታታቸውንም ልጥፉ አክሎ ገልጿል።

የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ  ሃይሎችን ለመበተን መወሰኑን በመቃወም የተጀመረው አለመግባባት በአማራ ክልል ከሰሞኑ ብዙ ሂወትን የቀጠፈ ግጭትን አስከስትሏል።

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ በሰው አልባ አውሮፕላን በደረሰ ጥቃት 26 ሰዎች መሞታቸውን በቅርቡ እየወጡ ያሉ ዜናዎች ያሳያሉ።

ሀቅቼክ መረጃውን ለመደገፍ የተጠቀሙበትን  ምስል እንዳጣራው ምስሉ ቀደም ሲል  በትዊተር ላይ በነሐሴ 8 ቀን 2022  'የሩስያ ጦር በቅርቡ ባደረገው ጦርነት የዩክሬን መድፍ ተሽከርካሪዎችን እንዳወደመ' ከሚገልጽ የመግለጫ ጽሁፍ ጋር የተጋራ እንደነበር ማረጋገጥ ተችሏል።

መሉውን ጹሑፍ ለማንበብ https://tinyurl.com/3yzw5cbt
👍1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሀቅቼክ በቲክቶክ ላይ “አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ አሁን ሀገሪቱ ያለችበትን ችግር ቀድሞ ተንብዮ ነበር።” በሚል መግለጫ ስር ተጋርቶ የነበረን አንድ ቪድዮ አጣርቷል።

ቪድዮውን ይመልከቱ 👆🏻

TikTok|Facebook|website|Twitter
👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🎉 መልካም  ዜና

ከውሸቱ ባሻገር/ Beyond disinfo የተሰኘ አዲስ ፕሮግራም ይዘን መጥተናል

ፕሮግራሙ በሃሰተኛ መረጃ ስርጭት ፣ በንግግር ነፃነት እና በቴክኖሎጂ ላይ የሚያጠነጥን ነው።

ዘወትር ማክሰኞ ከምሽቱ 1: 30 ላይ በሀገሬ ቲቪ ይጠብቁን📺
1👏1
በማህበራዊ ሚድያ ላይ ያገኘነውን መረጃ ከመማመናችን በፊት ልንጠይቃቸው የሚግቡ 5 ጥያቄዎች

ምንጩ ማን ነው? 🕵️‍♂️
    የመረጃው ምንጭ ተአማኒነት እና በመረጃው ላይ ያለውን እውቀት መለየት ያስፈልጋል። እምነት የሚጣልበት ነው? አድልዎ ወይም ሌላ አጀንዳ የለውም?

ምን ማስረጃ ቀርቧል? 📚
   የቀረበውን መረጃ  የሚያረጋግጡ ደጋፊ ማስረጃዎችን ወይም ማጣቀሻዎችን ማካተቱን ልብ ይበሉ።

መረጃው ወቅታዊ ነው?
    መረጃው የታተመበት ወይም የተለጠፈብትን ቀን ያረጋግጡ።

መረጃው አማራጭ እይታዎች አሉት ? 🔄
  መረጃው በተለያዩ አመለካከቶች ወይም እይታዎች ምን እንድሚመስል መገምገም ያስፈልጋል።

መረጃው ከታማኝ ምንጮች ጋር ይጣጣማል?
መረጃውን ከሚያምኗቸው ታዋቂ ምንጮች ጋር ያገናዝቡ። በአስተማማኝ ምንጮች ላይ መረጃው መሰራጨቱን ያረጋግጡ።

TikTok|Facebook|website|Twitter
👍2👌1
በመንግስትና በአማራ ክልል በሚገኙ ታጣቂዎች መካክል ያለውን ግጭት ተከትሎ ፣ በማህበራዊ ሚድያ ላይ ብዙ መረጃዎች እየተዘዋወሩ ይገኛሉ።

ከሰሞኑ ይህን የምትመለከቱትን ምስል የፋኖ ታጣቂዎች የመንግስትን ሄሊኮፕተር መተው እንደጣሉና ጉዳት እንዳደረሱ ከሚገልጽ ጹሑፍ ጋር በፌስቡክ በስፋት ሲዘዋወር ነበር።

ነገር ግን ሀቅቼክ የመረጃውን እውነትነት እንዳጣራው፣ መረጃውን ለመደገፍ የተጠቀሙት  ምስል በፈረንጆቹ 2022 የሮማንያ ሄሊኮፕተር ስትከሰከስ ከሚያሳይ የጹሑፍ መግለጫ ጋር ተጋርቶ አግኝቶታል።

ሙሉ ጹሑፉን ለማንበብ 👇

ሙሉውን ያንብቡ http://bit.ly/3OJYIYl

TikTok|Facebook|website|Twitter
በአሁኑ ሰዓት የጥላቻ ንግግርን በዋናነት በመፍጠር ወይም መጀመርያ በመናገር ወደ ማህበረሰቡ ማስረጽ የሚፈልግ አካል ማን ነው ብለው ያስባሉ?
Anonymous Poll
5%
የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች
22%
ግለሰቦች
24%
የማህበረሰብ አንቂዎች
49%
የመንግስት ባለስልጣኖች
ኢንተርኔትን በሐላፊነት የሚጠቀሙ  ሰዎች

🤝  አካታች ናቸው
በኦንላየን ላይ ከሌሎች ጋር የአክብሮት እና ጥሩ ስሜት ያለው ግንኙነት ያላቸው ናቸው።

ℹ️  አገናዛቢ ናቸው
የኦንላይን መረጃዎችን ትክክለኛነት፣ እና እርግጠኛነት  መገምገም የሚችሉ ናቸው።

🧑‍💻 ቴክኖሎጂን ለበጎ አላማ ያውላሉ
ቴክኖሎጂን ለዜጎች ጠቃሚ ለሆኑ ነገሮች የሚጠቀሙ ናቸው።

ሚዛናዊ ናቸው
በኢንተርኔት ላይ የሚያሳልፉትን ጊዜና በሌላው የህይወታቸው እንቅስቃሴ ላይ የተመጣጠነ ጊዜን ያሳልፋሉ

⚠️ ንቁ ናቸው
የኦንላይን እንቅስቃሴ ደህንነታቸውን ይጠብቃሉ እንዲሁም ለሌሎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራሉ

TikTok|Facebook|website|Twitter
👍2🙏1
ቢጣራ የሚሉትን መረጃ ይላኩልን

🔊 በማህበራዊ ሚዲያ፣ በተለያዩ ጽሁፎች፣ በቪዲዮዎች እና በዜና ዘገባዎች ላይ ያገኛችሁት መረጃ እውነት መሆኑ ካጠራጠራችሁ፣ ጥያቄ ከፈጠረባችሁ፣ ወደ ሀቅቼክ መረጃውን ያገኙበትን ምንጭ አያይዘው ይላኩልን። የመረጃውን እውነትነት አጣርተን መልሰን ለእናንተው እናቀርባለን።

መረጃ ለመላክ:-
   በቴሌግራም: @haqcheckbot ላይ ገብተው መላክ ይችላሉ።

ለተጨማሪ መረጃ: የሀቅቼክ ድህረ ገጽ እና ማህበራዊ ሚድያ ገጾችን ይጎብኙ👇

TikTok|Facebook|website|Twitter
👍1👌1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ያለው ሰው በተለያዩ መንገዶች መረጃን የማግኘት፣ የመተንተን ፣ የመገምገም እና  ለሚዲያ የሚሆኑ መረጃዎችን የማዘጋጀት አቅም ይኖረዋል።

ለተጨማሪ መረጃ: የሀቅቼክ ድህረ ገጽ እና ማህበራዊ ሚድያ ገጾችን ይጎብኙ👇

TikTok|Facebook|website|Twitter
👍41🔥1
ከውሸቱ ባሻገር/ Beyond disinfo.

📢 በሃሰተኛ መረጃ ስርጭት ፣ በንግግር ነፃነት እና በቴክኖሎጂ ላይ የሚያጠነጥን  ፕሮግራም ሲሆን፣

ዘወትር ማክሰኞ ከምሽቱ 1:30 ላይ በሀገሬ ቲቪ ይተላለፋል።
👍3
ባሳለፍነው ሳምንት በተለያዩ ሚድያዎች ሲዘዋወሩ ከነበሩ መረጃዎች ውስጥ አወዛጋቢ እና ሃሰተኛ የሆኑ መረጃዎች እንዲሁም ስለ ፕሮግራማችን አጠቃላይ ይዘት አንስተን በዛሬው ከውሸቱ ባሻገር/Beyond disinfo ፕሮግራማችን ተወያይተናል።

ይከታተሉን👇
https://youtu.be/a_hEFZ6bRJ4
👍21
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"Deepfake" ማለት አርቴፊሻል ኢንቴሌጀንስ (Ai) በመጠቀም የሰዎችን ምስል ፣ ቪድዮ እና ድምፅ በማስመሰል ለተለያዩ አላማ የማዋል ሂደት ነው።  በአለማችን የተለያዩ ሃገራት  መሪዎችን እና ታዋቂ ሰዎችን ድምፅና ምስል በመጠቀም እነሱ እንደተናገሩትና ድርጊቱን እንደፈፀሙት በማስመሰል አሳሳች መረጃዎችን መመልከት የተለመደ ሆኗል፣ በሃገራችንም  ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በ Ai  የተቀነባበሩ ቪድዮችን ተመልከተናል።
ቪድዮውን ይመልከቱ 👆🏻

✍️ ለተጨማሪ መረጃ: የሀቅቼክ ድህረ ገጽ እና ማህበራዊ ሚድያ ገጾችን ይጎብኙ👇

TikTok|Facebook|website|Twitter
👍4🙏21
ቪድዮው በደብረ ማርቆስ በፋኖ የተማረከ ሂሊኮፕተርን አያሳይም

ከ46,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስ ቡክ ገፅ እ.ኤ.አ. በ ነሐሴ 28/ 2023 በአንድ ቪዲዮ በደብረ ማርቆስ የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር በፋኖ ታጣቂዎች የተማረከ እንደሆነ ከሚገልጽ ጹሑፍ ጋር አጋርቷል። የፌስቡክ ልጥፉ ይህ ጽሑፍ እስከተዘጋጀበት ድረስ ወደ 300 የሚጠጉ ግብረ ምላሾችን እና ከሰባት ሺህ በላይ ሰዎች ተመልክተውታል። 

የፌድራል መንግስት የክልል ልዩ ሃይልን አፈርሳለሁ ማለቱን ተከትሎ የተነሳው አለመግባባት በተለይም በነሀሴ ወር መጀመሪያ አካባቢ የፋኖ ታጣቂዎች በርካታ ከተሞችን እና አካባቢዎችን ሲቆጣጠሩ ግጭቱ ተባብሶ ቀጥሏል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከተሞቹን መልሶ ለመያዝ  መከላከያ ሰራዊትን በማሰማራት አብዛኞቹን ዋና ዋና ከተሞች መልሶ ይዟል ነገር ግን ግጭቱ በአንዳንድ አካባቢዎች እንደቀጠለ መረጃዎች ያመለክታሉ።

ይህን ተከትሎ  የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር በደብረ ማርቆስ በፋኖ ታጣቂዎች መማረኩን ከሚገልጽ የጹህፍ መግለጫ ጋር ቪድዮው ተጋርቷል።

ሀቅቼክ እንዳጣራው ቪዲዮው የቆየና ወቅታዊ እንዳልሆነ ማረጋገጥ ችሏል። ዋናው ቪዲዮ ሚያዝያ 26 ቀን 2019 በአንድ የፌስቡክ ገጽ ላይ የተለጠፈ ሲሆን የትራንስ ኔሽን ኤርዌይስ (ሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ) ንብረት የሆነው ሄሊኮፕተር በሞተር ብልሽት ምክንያት ተከስክሶ እንደነበር የተያያዘው  መግለጫው ይገልጻል። ሙሉ ጹሁፍን ለማንበብ👇

https://haqcheck.org/does-the-image-show-fano-militants-downed-an-ethiopian-helicopter-in-debre-markos/?amp=1
👍3
ይህ የምትመለከቱት የሂሊፕተር ምስል ወታደሮችን ወደ አማራ ክልል ሲያጓጉዝ አያሳይም።

ከሰሞኑ ከ50,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የትዊተር አካውንት በአማራ ክልል ያለውን ግጭት ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊቱን በሄሊኮፕተር ወደ አማራ ክልል ሲጓጉዝ የሚያሳይ ምስል እንደሆነ በመግለጽ አጋርቷል። ልጥፉ ወደ 61 ጊዜ የተጋራ ሲሆን ከ 88 በላይ ግብረ መልሶችን አግኝቷል።

የፌዴራል መንግስት የክልል ልዩ ሃይል ፓሊስን አፈርሳለሁ ማለቱን ተከትሎ የተነሳው ተቃውሞና ግጭት እስካሁን ከመቀጠሉ ጋር ተያይዞ ብዙ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተዘዋወሩ ይገኛሉ።  ከነዚህም ውስጥ ከላይ የጠቀስነው የትዊተር ልጥፍ ይገኝበታል።

ሀቅቼክ እንዳረጋገጠው ምስሉ ወቅታዊ  ያልሆነ እና የቆየ እንደሆነ ማረጋገጥ ችሏል ። ዋናው ምስል በፌስቡክ ነሐሴ 2 ቀን 2021 በተሰራጨ ቪዲዮ ላይ ተጋርቶ እንደነበር ማረጋገጥ ተችሏል።

በአማራ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ብዛት ያላቸው መረጃዎች እየተዘዋወሩ ስለሆነ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ከማመናችን በፊት ማጣራትና ምረጋገጥ ይኖርብናል።

ሙሉ ጹሑፍን ለመማንበብ 👇👇👇
https://haqcheck.org/does-the-image-show-a-plane-transporting-soldiers-to-the-amhara-region/
👍2👎1
#የሀሰተኛ_መረጃ_ጥቆማ

ከሰሞኑ የህዝብ ተወካዩ እና የአብን ፓርቲ የቀድሞ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ክርስትያን ታደለ ከእስር እንደተፈቱ የሚገልጹ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚድያው ላይ ተመልክተናል። ከነዚህ መካከል አንዱ በቲክቶክ ላይ ‘አቶ ክርስትያን ታደለ ከእስር ተፈተዋል” ከሚል ጽሁፍ ጋር አንድ ቪድዮ ተሰራጭቶ ነበር።

ይሁን እንጂ አቶ ክርስትያን ከእስር መፈታታቸው ያሳያል የተባለው ቪድዮ ከ3 አመት በፊት ተሰራጭቶ የነበረ ሲሆን ቪድዮው ከ3 አመት በፊት የአብን የፖለቲካ ጉዳዮች ሀላፊ የነበሩት አቶ ክርስቲያን ታደለ “አንድ አማራ ለሁሉም አማራ" በሚል መሪ ቃል አዲስ አበባ በተዘጋጀው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ ካስተላለፉት መልእክት የተወሰደ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል።

አቶ ክርስትያን በአማራ ክልል የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ከታወጀ በኋላ ታስረው አዋሽ አርባ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ሰብኣዊ መብቶች ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል።
👍21🙏1
📢 ገዱ አንዳርጋቸው ወልቃይትን ሸጠዋል ስለሚለው ቪድዮ፣ በድብረ ማርቆስ በፋኖ ተማረኩ ስለተባሉት ሄሊኮፕተሮች፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሰዎችን ድምፅ እና ምስል በማስመሰል እየወጡ  ያሉ መረጃዎችን በተመለከተ ፣ በ BBC ስም ስለወጣው ሃሰተኛ መረጃ እንዲሁም ከትዊተር ማረጋገጫ ጋር ተያይዞ ስላሉ እውነታዎች አንስተን በዛሬው ከውሸቱ ባሻገር Beyond disinfo ፕሮግራማችን ላይ በሰፊው ተወያይተናል።

ቪድዮውን ለማየት👇
https://youtu.be/PYQ5a1ohLiM
2🔥1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በቪድዮው ላይ የሚታዩት ባንዲራዎች የኦሮሚያ ክልል መሆናቸው እና በዚያ አካባቢ ያሉት ሰዎች የሚያወሩት ቋንቋ ኦሮሚኛ መሆኑ የመረጃውን ሐሰተኛነት ያመለክታሉ።

ሙሉ ቪዲዮውን ለማየት👇
https://youtu.be/PYQ5a1ohLiM
👍2👌1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አቶ ገዱ አንዳርጋቸው 'ወልቃይትን ለትግራይ እንደሸጡ' የሚያሳይው ቪድዮ ከየት ተገኘ ?

ሙሉ ቪዲዮውን ለማየት👇
https://youtu.be/PYQ5a1ohLiM
👍2🔥1👏1