HaqCheck
428 subscribers
324 photos
39 videos
541 links
HaqCheck is an Ethiopia based fact-checking project that verifies media content from social to the mainstream. We fact-check in English and on local languages widely spoken in the Horn of Africa.

https://haqcheck.org
Download Telegram
የቀጠለ.......

ሌላኛው ደግሞ ከቀድሞ የነፃነት ታጋይ እና ፖለቲከኛ ኔልሰን ማንዴላ የተናገሩት ተብሎ የተሰራጨ ነው።
“የአፓርታይድ አገዛዝ እና መንግስት ላይ ያደረጋችሁትን በአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ላይ አርጉ” የሚል ሲሆን አፍሪካ ቼክ በዚህ አባባል ላይ ጥልቅ የሆነ ጥናትን ያካሄዱ ሲሆን ንግግሩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንጆቹ 1994 5ተኛው የደቡብ አፍሪካ የንግድ ህብረት ብሄራዊ ኮንግረስ ስብሰባ ላይ ኔልሰን ማንዴላ ካደረጉት ንግግር ላይ የተወሰደ ነው።

ከዚያ በኋላ ግን ንግግሩ እየተነካካ እና እየተቀየረ እዚህ ላይ መድረሱ ተረጋግጧል። ነገር ግን ኔልሰን ማንዴላ ደጋፊዎቻቸውን “የአፓርታይድ አገዛዝ እና መንግስት ላይ ያደረጋችሁትን በአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ላይ አርጉ” ለማለታቸው ምንም አይነት ተጨባጭ የሆነ መረጃ መገኘት አልተቻለም።

ሶስተኛው በክሪስ ሃኒ የተነገረ የተባለው አባባል “እኔ የምፈራው ደቡብ አፍሪካን ነፃ ያወጡ ሰዎች በከተማው መሀል ማርቼዲስ እና ቤንዝ እየነዱ እና የሀገሪቱን ሀብት እየበዘበዙ በቅንጡ ቤተ-መንግስት ውስጥ እየኖሩ ሀብትን እንዳያካብቱ ነው።” የሚል ነበር።

ይህ ንግግር ትክክለኛው መሆኑ ተረጋግጧል። ይህም በፖለቲከኛው በፈረንጆቹ ጥቅምት 29 ቀን 1992 ዓ.ም የተነገረ እንደሆነ ሲረጋገጥ፡ የደቡብ አፍሪካው ኮሙኒስት ፓርቲ አመራር የሆኑት ክሪስ ሃኒ ከመገደላቸው ከ6 ወር በፊት የተናገሩት እንደሆነ ተረጋግጧል።
#የተለወጠ_ምስል
ምስሎች የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ፣ ስሜትን ለመኮርኮር እንዲሁም ሀሳብን ለማስቀየር ይውላሉ። ከዚህ ባለፈ ሰዎችን የማሳመን እና የማደናገር ሚናቸው ከፍተኛ ነው። ይህን ተከትሎ አውዳቸውን የሳቱ፣ የተቀናበሩ እና የተቀየሩ ምስሎች ሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎችን ለማሰራጨት በስፋት ጥቅም ላይ ይውላሉ።

መረጃዎችን ከማጋራታችን በፊት እውነት መሆናቸውን እናረጋግጥ!
👍1
#የጥንቃቄ_መልዕክት
#Alert

ከትላንት ሚያዝያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በማህበራዊ ሚድያ በተለይም በፌስቡክ ላይ “የፌደራል መንግስት በአማራ ክልል ላይ በፈፀመው የአየር ድብደባ እንስሳት በዚህ መልኩ ተቃጥለዋል” በሚል ፅሁፍ ስር ይህ ምስል በስፋት ሲዘዋወር ቆይቷል።

ነገር ግን ምስሉ ሚያዝያ 24 ቀን 2015 ዓ.ም “በጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በዶኮ ካሌ ቀበሌ በልዩ ስሙ ኤተሎ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቀን 23/08/2015 ዓ/ም ከምሽቱ ሦስት ሠዓት አካባቢ የተከሰተ የእሳት አደጋ በእንሰሳትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።" በሚል ፅሁፍ ስር ከሌሎች ምስሎች ጋር ተጋርቶ ነበር።

ስለዚህ በአማራ ክልል ግጭት እንዳለ ቢነገርም ይሄንን ምስል በክልሉ የአየር ድብደባ እየተደረገ እንደሆነ አያሳይም።
👍1
📣 Calling all Ethiopian journalists! 📰🎙
Inform Africa, in partnership with @Africa Check, proudly presents a transformative workshop: "Fact-checking and Verification Masterclass for Journalists." 🌍🔎

📅 Dates: 22 to 23 June 2023
Time: 9 am to 4 pm
📍 Venue: To be confirmed

Seize this incredible opportunity to enhance your fact-checking skills and become a trusted source of information in the world of journalism. 📚
🔒Limited Spaces Available! Only committed participants who can attend the full two-day session should apply.

✍️: Fill this form now
https://docs.google.com/forms/d/1EgpiTS82mv-71pxVGefmrKZjBQ0Szl7Pul2tc2X_TwA/edit
👎1
Opportunities are still open for participants from Addis Ababa.

Inform Africa, in collaboration with Africa Check, is delighted to announce an empowering workshop: Fact-checking and Verification Masterclass for Journalists. We have limited slots remaining for individuals from Addis Ababa. Don't delay, register today!
The workshop will take place
Dates: 22 to 23 June 2023
Time: 9 am to 4 pm
Venue: Best Western Plus Pearl Addis
Register Now: https://lnkd.in/eWNGJZSD
1
ስለ ሀቅቼክ

🎤በኢንፎርም አፍሪካ ስር የሚገኝ ሀገር በቀል እንሼቲቭ ሲሆን፣ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎችን ከማህበራዊ እና መደበኛ ሚድያዎች ላይ እያጣራ ያቀርባል።

🎤 ከእንግሊዘኛ በተጨማሪ በአማርኛ፣ በኦሮሚፋ፣ በትግርኛና በሶማሊኛ ቋንቋዎች መረጃዎችን እያጣራ ያቀርባል።

🎤 ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመሆን የሚድያ አጠቃቀም ክህሎት ስልጠና ይሰጣል፣ ጥናቶችን ያካሄዳል።

🎤 አላማው በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሀሰት መረጃን ማጋለጥና እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል የሀገር ውስጥ የልህቀት ማዕከል መገንባት ነው።

#HaqCheck #FactTalksEthiopia #MediaLiteracy
👍21
ሐሰተኛ መረጃ በየትኛው የማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት የሚሰራጭ ይመስሎታል?
Anonymous Poll
81%
Facebook
2%
Twitter
16%
TikTok
2%
Telegram
📣 Calling all Ethiopian journalists! 📰🎙
Inform Africa, in partnership with @Africa Check, proudly presents the second round transformative workshop: "Fact-checking and Verification Masterclass for Journalists." 🌍🔎

📅 Dates: 20 to 21 July 2023
Time: 9 am to 4 pm
📍 Venue: To be confirmed

Seize this incredible opportunity to enhance your fact-checking skills and become a trusted source of information in the world of journalism. 📚
🔒Limited Spaces Available! Only committed participants who can attend the full two-day session should apply.

✍️: Fill this form now

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScdtVnMYhclv9jEFxunK1gaNqSkRZ9meZOVJet80wgwO4egaw/viewform
HaqCheck pinned «ሐሰተኛ መረጃ በየትኛው የማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት የሚሰራጭ ይመስሎታል?»
📻 በኢትዮጵያ ሞዴል የማህበረሰብ ሬዲዮ ፕሮግራም ተጀመረ

ባለፈው ሳምንት በአውስትራሊያ ኤምባሲ፣ በዩኔስኮ እና በ ኢንፎርም አፍሪካ ትብብር በኢትዮጵያ ሞዴል የማህበረሰብ ሬዲዮ ፕሮግራሞች ተጀምረዋል።
የፕሮግራሙ አላማ ማህበረሰቡን ስለ ሰላም ግንባታ እና የጥላቻ ንግግርን ስለመከላከል ግንዛቤ መፍጠርና ማስተማር ነው፡፡
እነዚህ ሞዴል የሬዲዮ ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ሰላም ግንባታ ላይ በጎ ተጽእኖ ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ 

ተጨማሪ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ለተጨማሪ መረጃ: የሀቅቼክ ድህረ ገጽ እና ማህበራዊ ሚድያ ገጾችን ይጎብኙ👇

Telegram|Facebook|website|Twitter
👍21👌1
HaqCheck pinned «ሐሰተኛ መረጃ በየትኛው የማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት የሚሰራጭ ይመስሎታል?»