HaqCheck
428 subscribers
324 photos
39 videos
541 links
HaqCheck is an Ethiopia based fact-checking project that verifies media content from social to the mainstream. We fact-check in English and on local languages widely spoken in the Horn of Africa.

https://haqcheck.org
Download Telegram
አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን ሰባተኛ ዓመት

የመጀመሪያው አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን (International Fact-Checking Day) መከበር የጀመረው በአውሮፓውያን አቆጣጠር የካቲት 2 2017 ነው።

ይሁን እንጂ ለመጀመሪያ ጊዜ የታሰበው እ.ኤ.አ በ2014 በለንደን የኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ክፍል ለጋዜጠኞች እና ባለሙያ የሆኑ የመረጃ አጣሪ ባለሙያዎች በተገኙበት ነበር።

ይህ ሀሳብ የተነሳው በወቅቱ ከፖሊቲካ ጋር ተያይዘው ሲሰራጩ የነበሩ ሀሰተኛ መረጃዎች አደገኝነት ግንዛቤ ውስጥ ገብቶ ሲሆን በተለይም ከ2016 የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ጋር ተያይዞ የነበሩት አወዛጋቢ እና ሀሰተኛ መረጃዎች ለዚህ አለም አቀፍ ቀን መከበር እንደ ምክንያት የሆኑ ሲሆን በአመቱ ማለትም የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም. መከበር ተጀምሯል።   

አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን የካቲት 2 የሆነበት ምክንያት የካቲት 1 በተለምዶው አፕሪል ዘ ፉል (April the fool) እየተባለ በሚጠራው ቀን ማግስት እንዲሆን ታስቦ ነው።
👍2
#odeffannooofeeggannoo

Lakkoofsi ergaa barreeffamaa gabaabaan suuraa irratti mul'atu yeroo ammaa gargaarsa Borena walitti qabuuf hin tajaajilu.

Sadaasa 14, 2015 fuula Feesbuukii hordoftoota kuma kudha lama ol qabu, gogiinsa naannoo Booreenaatti mudateef maallaqa walitti qabuuf gaafachuun, maqaa artistoota Oromootiin ergaa barreeffamaa gabaabaa lakoofssa 655 aka Hayyama argette, akkasumas suuraa iskiriinii iiraa akka inni maallaqa dhibba galchee fi ergaan galateeffannaa argate qoodee jiirraa, Namoonni biroos duula kana irratti akka isa waliin hirmaatan gaafateera.

Akkasumas Garee Feesbuukii Oromoo fi Oromiyaa jedhamu kan miseensota gara kuma 213 qabu irrattis ergaa isaa qoodeera.

Haqcheck dhimma kana qorachuuf gara tajaajila maamiltootaa Itiyoo Telekoomitti bilbilee; Yeroo ammaa lakkoofsa kanaan gargaarsi sassaabamaa akka hin jirre Ethio Telecom nuuf beeksiseera. Haqcheck lakkoofsi jedhame kun yeroo ergaan ergamu 'booda yaalaa' jedhee deebii akka kennus mirkaneesseera.
እዚ ናይ ሓጺር ጽሑፍ መልኣኺ ቁጽሪ ኣብ ቦሮና ብድርቂ ንዝተጠቕዑ መኣከቢ ሓገዝ ዝተዳለወ አይኮነን

ብ14 መጋቢት 2015 ዓ.ም ሓደ ልዕሊ ዓሰርተ ክልተ ሽሕ ተኸተልቲ ዘለዉዎ ናይ ፌስቡክ ገጽ ብስም ናይ ኦሮሞ ስነጥበባውያን ኣብ ቦሮና ብድርቂ ንዝተጠቕዑ ዝውዕል ሓገዝ መኣከቢ ተባሂሉ ብኢትዮ ቴሌኮም ዝተዳለወ ሓጺር ናይ ጽሑፍ መልካኺ ቁጽሪ 655 እዩ ክብል ሓንቲ ስእሊ ጠቂዑ ነይሩ፡፡ ኢሉ እዉን ናብታ ቁጽሪ ሚኢቲ ብር ከምዘእተወ እሞ ሓጺር ናይ ምስጋና መልእኽቲ ከምዝተላእኸሉ ወሲኹ ሓቢሩ ነይሩ፡፡

ብምቕጻል እዚ ሓበሬታ እዚ Oromoo fi Oromiyaa ኣብ ዝብል ልዕሊ ክልተ ሚኢቲን ዓሰርተ ሰለስተን ሽሕ ኣባላት ዘለዉዎ ናይ ፌስቡክ ጉጅለ ተጠቂዑ ነይሩ፡፡ ኮይኑ እዉን ብዙሕ ግብረመልሲ ረኺቡ ነይሩ፡፡

ሃቂቸክ ነቲ ጉዳይ ንኸጻሪ ኢሉ ናብ ማእከል መቐበሊ ጻውዒት ዓማዊል ዝደወለ እንትኸዉን፡ አብዚ እዋን እዚ በዚ ቑጽሪ እዚ ዝኾነ ዓይነት ንሓገዝ ዝኸዉን ገንዘብ ይእከብ ከምዘየሎ አረጋጊጹ አሎ፡፡ እዚ ቁጽሪ እዚ ዋላ መልእኽቲ እንተለኣኽካሉ 'ደጊሞም ዳሕራይ ይፈትኑ' ዝብል ግብረመልሲ ከምዝህብ ሓቂቸክ አረጋጊጹ አሎ፡፡

ናብ ከምዚኦም ዓይነት ንሓገዝ ተባሂሎም ዝዳለዉ ናይ ሓጺር መልእኽቲ መስደዲ ቑጽርታት ነቲ ሓገዝ ቅድሚምልኣኽ ብምስትውዓል፣ ምጽራይ፣ ንባዕልኻን ካልኦትን ካብ ዝተሓሓተ ሓበሬታ ምጥንቃቕ የድሊ እዩ፡፡ ብተወሳኺ ካልኦት ዝተጸገሙ ሰባት ክሕገዝሉ ዝኽእሉ ዝተፈላለዩ መንገድታት ብምንዳይ ደገፍና ክነበርክት ንኽእል ኢና፡፡

ብመሰረት ዘጻረናዮ ሓበሬታ፡ አብ ቦሮና ብድርቂ ንዝተጠቕዑ ወገናት ሓገዝ ዝውዕል ብናይ ቀይሕ-መስቀል ዝተዳለወ 9400 ብዝብል ቁጽሪ ሓገዝ ይእከብ ከምዘሎ አረጋጊጽና አለና፡፡
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ከማጋራት እንቆጠብ

አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን በማስመልከት ሀቅቼክ ባለፉት ጊዜያቶች ካጣራቸው ሀሰተኛ መረጃዎች መካከል፦
👍2🔥1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አለምን ያወዛገቡ አስር የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች እና ጉዳታቸው

በታሪክ አጋጣሚዎች ውዝግብ ለመፍጠር፣ የህብረተሰቡን አስተሳሰብ ለመቀየር፣ እንዲሁም ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋትን ለመፍጠር በማሰብ ሀሰተኛ መረጃዎች ሆን ተብለው ይሰራጫሉ።
👍3
አሳሳች ፡ የደቡብ አፍሪካ ነፃነት ታጋዮች ንግግር ተብሎ በማህበራዊ ሚድያ የተሰራጨው የሀሰት መረጃ

በደቡብ አፍሪካ በአንድ የፌስቡክ ግሩፕ ላይ የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፖለቲከኞች የሆኑት ክሪስ ሃኒ ፤ ኦሊቨር ታምቦ እና ኔልሰን ማንዴላ የተናገሩት ንግግር በማለት ፅሁፎችን ተጋርቶ ነበር።

ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ቅኝ አገዛዝ ነፃ ከወጣች በኋላ በፈረንጆቹ ሚያዝያ 27 ቀን 1994 ብሄራዊ ምርጫ አካሂዳ ነበር። ይህ ቀንም በደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ የነፃነት ቀን ተብሎ በየአመቱ ይከበራል። ይህ የፌስቡክ ገፅም የዚህን አመታዊ ክብረ በዓል ተከትሎ ይህን መረጃ አጋርቶ ነበር።

ይህ የፌስቡክ ፖስት በእነዚህ ሦስት ጥቅሶች ውስጥ የፀረ-አፓርታይድ አክቲቪስቶች የነበሩት የፖለቲካ መሪዎች የደቡብ አፍሪካን አሁናዊ የፖለቲካ ሁኔታ አስቀድመው እንደተነበዩት ለማሳየት ሞክሯል።
ይህ የፌስቡክ ፖስት “ስለ ንግግራቸው ብዙ ጊዜ አስብ ነበር ... ምን አይተው ነበር?” የሚል የመግለጫ ፅሁፍን ከምስሎቹ ጋር አያይዞ አጋርቶ ነበር።

ከነዚያ መካከል የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ገዢ ፓርቲ 'የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ’ ፕሬዝደንት የነበሩት ኦሊቨር ታምቦ “በሙስና የተዘፈቀ የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ ከአፓርታይድ አገዛዝ ይልቅ የከፋ ነው።” ብለው ተናግረዋል የሚለው ንግግር ቀድሞም በማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት ሲዘዋወር የነበረ ነው።

በደቡብ አፍሪካ የሚገኝ አፍሪካ ቼክ የተባለ የመረጃ አጣሪ ተቋም በፈረንጆቹ 2019 በዚህ የኦሊቨር ታምቦ ነው ተብሎ በተሰራጨው ንግግር ላይ ምርመራ አድርጎ፡ ታምቦ ይህን እንደተናገሩ የሚያሳይ ምንም ፍንጭ ማግኘት አልቻለም።
የቀጠለ.......

ሌላኛው ደግሞ ከቀድሞ የነፃነት ታጋይ እና ፖለቲከኛ ኔልሰን ማንዴላ የተናገሩት ተብሎ የተሰራጨ ነው።
“የአፓርታይድ አገዛዝ እና መንግስት ላይ ያደረጋችሁትን በአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ላይ አርጉ” የሚል ሲሆን አፍሪካ ቼክ በዚህ አባባል ላይ ጥልቅ የሆነ ጥናትን ያካሄዱ ሲሆን ንግግሩ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንጆቹ 1994 5ተኛው የደቡብ አፍሪካ የንግድ ህብረት ብሄራዊ ኮንግረስ ስብሰባ ላይ ኔልሰን ማንዴላ ካደረጉት ንግግር ላይ የተወሰደ ነው።

ከዚያ በኋላ ግን ንግግሩ እየተነካካ እና እየተቀየረ እዚህ ላይ መድረሱ ተረጋግጧል። ነገር ግን ኔልሰን ማንዴላ ደጋፊዎቻቸውን “የአፓርታይድ አገዛዝ እና መንግስት ላይ ያደረጋችሁትን በአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ላይ አርጉ” ለማለታቸው ምንም አይነት ተጨባጭ የሆነ መረጃ መገኘት አልተቻለም።

ሶስተኛው በክሪስ ሃኒ የተነገረ የተባለው አባባል “እኔ የምፈራው ደቡብ አፍሪካን ነፃ ያወጡ ሰዎች በከተማው መሀል ማርቼዲስ እና ቤንዝ እየነዱ እና የሀገሪቱን ሀብት እየበዘበዙ በቅንጡ ቤተ-መንግስት ውስጥ እየኖሩ ሀብትን እንዳያካብቱ ነው።” የሚል ነበር።

ይህ ንግግር ትክክለኛው መሆኑ ተረጋግጧል። ይህም በፖለቲከኛው በፈረንጆቹ ጥቅምት 29 ቀን 1992 ዓ.ም የተነገረ እንደሆነ ሲረጋገጥ፡ የደቡብ አፍሪካው ኮሙኒስት ፓርቲ አመራር የሆኑት ክሪስ ሃኒ ከመገደላቸው ከ6 ወር በፊት የተናገሩት እንደሆነ ተረጋግጧል።
#የተለወጠ_ምስል
ምስሎች የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ፣ ስሜትን ለመኮርኮር እንዲሁም ሀሳብን ለማስቀየር ይውላሉ። ከዚህ ባለፈ ሰዎችን የማሳመን እና የማደናገር ሚናቸው ከፍተኛ ነው። ይህን ተከትሎ አውዳቸውን የሳቱ፣ የተቀናበሩ እና የተቀየሩ ምስሎች ሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎችን ለማሰራጨት በስፋት ጥቅም ላይ ይውላሉ።

መረጃዎችን ከማጋራታችን በፊት እውነት መሆናቸውን እናረጋግጥ!
👍1
#የጥንቃቄ_መልዕክት
#Alert

ከትላንት ሚያዝያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በማህበራዊ ሚድያ በተለይም በፌስቡክ ላይ “የፌደራል መንግስት በአማራ ክልል ላይ በፈፀመው የአየር ድብደባ እንስሳት በዚህ መልኩ ተቃጥለዋል” በሚል ፅሁፍ ስር ይህ ምስል በስፋት ሲዘዋወር ቆይቷል።

ነገር ግን ምስሉ ሚያዝያ 24 ቀን 2015 ዓ.ም “በጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በዶኮ ካሌ ቀበሌ በልዩ ስሙ ኤተሎ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቀን 23/08/2015 ዓ/ም ከምሽቱ ሦስት ሠዓት አካባቢ የተከሰተ የእሳት አደጋ በእንሰሳትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።" በሚል ፅሁፍ ስር ከሌሎች ምስሎች ጋር ተጋርቶ ነበር።

ስለዚህ በአማራ ክልል ግጭት እንዳለ ቢነገርም ይሄንን ምስል በክልሉ የአየር ድብደባ እየተደረገ እንደሆነ አያሳይም።
👍1