HaqCheck
428 subscribers
324 photos
39 videos
541 links
HaqCheck is an Ethiopia based fact-checking project that verifies media content from social to the mainstream. We fact-check in English and on local languages widely spoken in the Horn of Africa.

https://haqcheck.org
Download Telegram
UNESCO, in collaboration with Inform Africa, organized a training session on combating hate speech and disinformation for community radio journalists under the theme "Strengthening the capacity of community radio in peace building, countering hate speech and disinformation." 
1
#የጥንቃቄመልዕክት

በምስሉ ላይ ያለው አጭር የፅሁፍ መልዕክት ቁጥር በአሁኑ ሰዓት ለቦረና እርዳታ ማሰባብሰቢያ የሚውል አይደለም

በመጋቢት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ላይ ከ12 ሺ በላይ ተከታዮች ያሉት አንድ የፌስቡክ ገፅ በቦረና አካባቢ ለተከሰተው ድርቅ የገቢ ማሰባሰቢያ እናድርግ በማለት በኦሮሞ አርቲስቶች ስም ከኢትዮ-ቴሌኮም 655 የሚል አጭር የፅሁፍ መልዕክት ቁጥር አንደተፈቀደ እና በተጨማሪም እሱ 100 ብር ያስገባበትንና የምስጋና መልዕክት እንደደረሰው የሚያሳይ ስክሪን ሾት አብሮ አጋርቶ ነበር። እንዲሁም ሌሎች ይህን ዘመቻ እንዲቀላቀሉት ጠይቋል።

በተጨማሪም Oromoo fi Oromiyaa በሚባል እና ወደ 213ሺህ አባላት ያሉት የፌስቡክ ግሩፕ ላይ መልዕክቱን ተጋርቷል። ይህ የተጋራው ፖስት ብዙ ግብረመልሶችን ማግኘት ችሏል።

ሀቅቼክ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል የደወለ ሲሆን ፤ በአሁኑ ሰዓት በዚህ ቁጥር ምንም አይነት እርዳታ እየተሰባሰበ እንዳልሆነ ኢትዮ ቴሌኮን አሳውቆናል። የተባለው ቁጥር መልዕክት ሲላክበት ‘በኋላ ላይ ይሞክሩ’ የሚል መልስ እንደሚሰጥም ሀቅቼክ አረጋግጧል።

በመሆኑም በእንደዚህ አይነት መልዕክቶች ምክንያት ብዙ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች እርዳታውን ሳያገኙ ሊቀሩ ስለሚችሉ ለዕርዳታ የሚዘጋጁ አጭር የመልዕክት መላኪያ ቁጥሮችን ጠንቅቀን ማወቅ፣ ማጣራት እና እራስንም ሆነ ሌሎችን ከተሳሳተ መረጃ መጠበቅ ይኖርብናል።

ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች የዕርዳታ አማራጮችን በመጠቀም ለተቸገሩ ወገኖች መድረስ ይቻላል።

ባጣራነው መረጃ መሠረት በአሁኑ ሰዓት በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች እርዳታ ለማድረግ በቀይ መስቀል አጭር የፅሁፍ መልዕክት 9400 ላይ እርዳታ እየተሰባሰበ መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል።
ምስሉ ወ/ሮ በረከት አደራ የ ጠ/ሚ አብይ አህመድን ሶስተኛ መፅሀፍ ገልብጠው ሲያነቡ ኣያሳይም

ከሰሞኑ በተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ ገፆች ላይ ወ/ሮ በረከት አደራ ወይም በረከት ገበሬዋ በሚባል ስም የምትታወቀው ባለሀብት ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ “የመደመር ትውልድ” የተሰኘውን መፅሀፋቸውን ማስመረቃቸውን ተከትሎ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ለተለያዩ ባለሀብቶች ግብዣ በማድረግ “የመደመር ትውልድ” ሽያጭ እና የማስተዋወቅ መርሃ ግብር አዘጋጅቶ ነበር ። በመረሀ ግብሩም ባለሀብቶች እና ተቋማት ከ609 ሚልዮን ብር በላይ ግዢ ፈፅመዋል።

በፕሮግራሙ ላይም ወ/ሮ በረከት አደራ (በረከት ገበሬዋ) በግብዣው ላይ በመገኘት ሶስተኛው እና “የመደመር ትውልድ” የተሰኘውን መፅሀፍ በ50ሺህ ዩሮ እንደገዛች የሚገልፁ የተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ መረጃዎች ሲዘዋወሩ ቆይተዋል።


ከነዚህም መካከል አንድ የፌስቡክ ገፅ ፦

50ሺህ ዮሮ ከፍላ የገዛችውን መፅሃፍ በፈለገችው አቅጣጫ ብታነበው ምን አገባችሁ ፈጣሪ ሆይ ፎቶሾፕ ነው በለኝ ፣ ምንም ሆነ ምን በረከት ገበሬዋ እንወድሻለን ፣ አንቺ ጀግና ሴት

የሚል ፅሁፍን በመጠቀም አንድ ምስል አጋርቷል።

ሀቅቼክ መረጃውን ለማጣራት ባደረገው ጥረት ትክክለኛውን ምስል ለሽያጭ በሚቀርቡ የማስታወቂያ ድረገፆች ላይ አግኝቶታል።
በምስሉ ላይ መረዳት እንደሚቻለው ከሆነ ፊቷ አካባቢ በቅንብር የተለወጠ ሲሆን ከዚያም ባለፈ አዲሱ የአብይ አህመድ “የመደመር ትውልድ” የተሰኘው መፅሀፍ የፊት ሽፋን ተጨምሮበታል።

ይህ የሀሰተኛ መረጃ አይነት በቅንብር የተለወጠ እና ስላቅ/ሹፈት የሚባል ሲሆን መረጃው ለቀልድ የተጋራ ቢመስልም ብዙዎችን የማሳሳት ትልቅ አዝማሚያ ይኖረዋል።
#Alert

የባንክ ቁጥሩ የአቶ ክርስትያን ታደለ ንግድ ባንክ አካውንት ኣይደለም

ከ136 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ በመጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ላይ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) የህዝብ ግንኙነት ሀላፊና የኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑት 'አቶ ክርስትያን ታደለ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ በተከፈተ የባንክ አካውንታቸው 74 ሚልዮን ብር እንደገባላቸው' የሚገልጽ ፅሁፍን በማጋራት የአንድ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥርን ከኮምፕዩተር ላይ በማንሳት አጋርቶ ነበር።

ይህ የፌስቡክ ፖስት ከ300 በላይ ግብረመልስን ሲያገኝ ከ50 ጊዜ በላይ መጋራት ችሏል።

የፌስቡክ ፖስቱ ላይ ያለው ምስል የተለወጠ መሆኑን ከሚያሳዩ ነገሮች አንዱ Currency በሚለው የመግለጫ ቦታ ላይ “ETB Kristian Tadele” የሚል ፅሁፍ ይታያል።


የአቶ ክርስትያን ታደለ ነው ተብሎ የተቀመጠው የንግድ ባንክ ቁጥር “10003355830378” ሲሆን ሀቅቼክ በቀላል መንገድ የአካውንት ቁጥሩን ለማጣራት ባደረገው ጥረት አካውንቱ “The Memory of Artist Hachalu Hundesa” በሚል ስም የተከፈተ እንደሆነ ማረጋገጥ ተችሏል።
👍4
አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን ሰባተኛ ዓመት

የመጀመሪያው አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን (International Fact-Checking Day) መከበር የጀመረው በአውሮፓውያን አቆጣጠር የካቲት 2 2017 ነው።

ይሁን እንጂ ለመጀመሪያ ጊዜ የታሰበው እ.ኤ.አ በ2014 በለንደን የኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ክፍል ለጋዜጠኞች እና ባለሙያ የሆኑ የመረጃ አጣሪ ባለሙያዎች በተገኙበት ነበር።

ይህ ሀሳብ የተነሳው በወቅቱ ከፖሊቲካ ጋር ተያይዘው ሲሰራጩ የነበሩ ሀሰተኛ መረጃዎች አደገኝነት ግንዛቤ ውስጥ ገብቶ ሲሆን በተለይም ከ2016 የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ጋር ተያይዞ የነበሩት አወዛጋቢ እና ሀሰተኛ መረጃዎች ለዚህ አለም አቀፍ ቀን መከበር እንደ ምክንያት የሆኑ ሲሆን በአመቱ ማለትም የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም. መከበር ተጀምሯል።   

አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን የካቲት 2 የሆነበት ምክንያት የካቲት 1 በተለምዶው አፕሪል ዘ ፉል (April the fool) እየተባለ በሚጠራው ቀን ማግስት እንዲሆን ታስቦ ነው።
👍2
#odeffannooofeeggannoo

Lakkoofsi ergaa barreeffamaa gabaabaan suuraa irratti mul'atu yeroo ammaa gargaarsa Borena walitti qabuuf hin tajaajilu.

Sadaasa 14, 2015 fuula Feesbuukii hordoftoota kuma kudha lama ol qabu, gogiinsa naannoo Booreenaatti mudateef maallaqa walitti qabuuf gaafachuun, maqaa artistoota Oromootiin ergaa barreeffamaa gabaabaa lakoofssa 655 aka Hayyama argette, akkasumas suuraa iskiriinii iiraa akka inni maallaqa dhibba galchee fi ergaan galateeffannaa argate qoodee jiirraa, Namoonni biroos duula kana irratti akka isa waliin hirmaatan gaafateera.

Akkasumas Garee Feesbuukii Oromoo fi Oromiyaa jedhamu kan miseensota gara kuma 213 qabu irrattis ergaa isaa qoodeera.

Haqcheck dhimma kana qorachuuf gara tajaajila maamiltootaa Itiyoo Telekoomitti bilbilee; Yeroo ammaa lakkoofsa kanaan gargaarsi sassaabamaa akka hin jirre Ethio Telecom nuuf beeksiseera. Haqcheck lakkoofsi jedhame kun yeroo ergaan ergamu 'booda yaalaa' jedhee deebii akka kennus mirkaneesseera.
እዚ ናይ ሓጺር ጽሑፍ መልኣኺ ቁጽሪ ኣብ ቦሮና ብድርቂ ንዝተጠቕዑ መኣከቢ ሓገዝ ዝተዳለወ አይኮነን

ብ14 መጋቢት 2015 ዓ.ም ሓደ ልዕሊ ዓሰርተ ክልተ ሽሕ ተኸተልቲ ዘለዉዎ ናይ ፌስቡክ ገጽ ብስም ናይ ኦሮሞ ስነጥበባውያን ኣብ ቦሮና ብድርቂ ንዝተጠቕዑ ዝውዕል ሓገዝ መኣከቢ ተባሂሉ ብኢትዮ ቴሌኮም ዝተዳለወ ሓጺር ናይ ጽሑፍ መልካኺ ቁጽሪ 655 እዩ ክብል ሓንቲ ስእሊ ጠቂዑ ነይሩ፡፡ ኢሉ እዉን ናብታ ቁጽሪ ሚኢቲ ብር ከምዘእተወ እሞ ሓጺር ናይ ምስጋና መልእኽቲ ከምዝተላእኸሉ ወሲኹ ሓቢሩ ነይሩ፡፡

ብምቕጻል እዚ ሓበሬታ እዚ Oromoo fi Oromiyaa ኣብ ዝብል ልዕሊ ክልተ ሚኢቲን ዓሰርተ ሰለስተን ሽሕ ኣባላት ዘለዉዎ ናይ ፌስቡክ ጉጅለ ተጠቂዑ ነይሩ፡፡ ኮይኑ እዉን ብዙሕ ግብረመልሲ ረኺቡ ነይሩ፡፡

ሃቂቸክ ነቲ ጉዳይ ንኸጻሪ ኢሉ ናብ ማእከል መቐበሊ ጻውዒት ዓማዊል ዝደወለ እንትኸዉን፡ አብዚ እዋን እዚ በዚ ቑጽሪ እዚ ዝኾነ ዓይነት ንሓገዝ ዝኸዉን ገንዘብ ይእከብ ከምዘየሎ አረጋጊጹ አሎ፡፡ እዚ ቁጽሪ እዚ ዋላ መልእኽቲ እንተለኣኽካሉ 'ደጊሞም ዳሕራይ ይፈትኑ' ዝብል ግብረመልሲ ከምዝህብ ሓቂቸክ አረጋጊጹ አሎ፡፡

ናብ ከምዚኦም ዓይነት ንሓገዝ ተባሂሎም ዝዳለዉ ናይ ሓጺር መልእኽቲ መስደዲ ቑጽርታት ነቲ ሓገዝ ቅድሚምልኣኽ ብምስትውዓል፣ ምጽራይ፣ ንባዕልኻን ካልኦትን ካብ ዝተሓሓተ ሓበሬታ ምጥንቃቕ የድሊ እዩ፡፡ ብተወሳኺ ካልኦት ዝተጸገሙ ሰባት ክሕገዝሉ ዝኽእሉ ዝተፈላለዩ መንገድታት ብምንዳይ ደገፍና ክነበርክት ንኽእል ኢና፡፡

ብመሰረት ዘጻረናዮ ሓበሬታ፡ አብ ቦሮና ብድርቂ ንዝተጠቕዑ ወገናት ሓገዝ ዝውዕል ብናይ ቀይሕ-መስቀል ዝተዳለወ 9400 ብዝብል ቁጽሪ ሓገዝ ይእከብ ከምዘሎ አረጋጊጽና አለና፡፡
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ከማጋራት እንቆጠብ

አለም አቀፍ ሀቅን የማጣራት ቀን በማስመልከት ሀቅቼክ ባለፉት ጊዜያቶች ካጣራቸው ሀሰተኛ መረጃዎች መካከል፦
👍2🔥1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አለምን ያወዛገቡ አስር የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች እና ጉዳታቸው

በታሪክ አጋጣሚዎች ውዝግብ ለመፍጠር፣ የህብረተሰቡን አስተሳሰብ ለመቀየር፣ እንዲሁም ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋትን ለመፍጠር በማሰብ ሀሰተኛ መረጃዎች ሆን ተብለው ይሰራጫሉ።
👍3