ጋዜጣዊ መግለጫ
የቡድን ስራ እና የመንገድ ደህንነት መልዕክቶች የጎሉበት 20ኛው አይ.ኤፍ.ኤች./አ.አ.መ.ባ. የዱላ ቅብብል ሩጫ ዛሬ ተካሔደ
20ኛው የአይ.ኤፍ.ኤች./አ.አ.መ.ባ. የዱላ ቅብብል ሩጫ ከቦሌ ቡልቡላ ወደ ኮዬ ፈቼ በሚወስደው መንገድ ላይ ዛሬ ተካሒዷል።
በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አማካኝነት የተዘጋጀው ይህ ልዩ ውድድር፣ ወደ አንድ ሺህ የሚጠጉ ተሳታፊዎችን አወዳድሯል። ዝግጅቱ የሁለት አስርት ዓመታትን የአካል ብቃት እና የኢትዮ-ቻይና ወዳጅነት የጠነከረበት እንዲሁም የመንገድ ደህንነት መልዕክቶች የተላለፉበት መድረክ ሆኗል።
የአዲስ አበባ የቀለበት መንገድ ምረቃን ተከትሎ የተጀመረው ይህ የዱላ ቅብብል ሩጫ፤ በአሁኑ ወቅት በብዙ ተቋማት ዘንድ የሚጠበቅ የሰራተኞች የጋራ ቀን ሆኗል።
የዘንድሮው ውድድር “የ6ታችን ቃልኪዳን” (Our Pact) በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን፣ ይህም በቡድን አባላት መካከል ያለውን ትስስር እና በመተባበር ማሸነፍን የሚያጎላ ነው።
አራት የቡድን አባላቶች እያንዳንዳቸው አራት ኪሎ ሜትሮችን በሮጡበት የአትሌቶች ምድብ ከፍተኛ ፉክክር ታይቷል። በዚህም መሰረት በሁለቱም ፆታ ከኢ.ኮ.ስ.ኮ. የተሰባሰቡ አትሌቶች በአንደኛ እና ሶስተኝነት ሲያጠናቅቁ የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌቶች ሁለተኛ ሆኘዋል።
ከአትሌቶች ውጭ እያንዳንዱ ቡድን ስድስት አባላትን የያዘ ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተወዳዳሪ 1 ኪሎ ሜትር በመሮጥ በድምሩ 6 ኪሎ ሜትር ርቀትን ሸፍነዋል። ውድድሩ በዘጠኝ የተለያዩ ዘርፎች አሸናፊዎችን የሸለመ ሲሆን፤ ይህም የመንግስት ተቋማትን፣ የንግድ ድርጅቶችን፣ ጂም እና የጤና ቡድኖችን፣ ኤምባሲዎችን፣ ባንክና ኢንሹራንስን፣ ሆቴሎችን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን (NGOs) እንዲሁም የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አባላትና ጓደኞችን ያካተተ ነበር።
ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የኤምባሲ ዘርፍ የቻይና ኤምባሲ ቡድን ልዩ ቅንጅት በማሳየት ውድድሩን ሲያሸንፍ፣ በሆቴሎች ዘርፍ አሸናፊዎቹ ኃይሌ ግራንድ ሆቴሎች ደግሞ ከምድባቸው ባሻገር የአጠቃላይ የውድድሩ አሸናፊ በመሆን ድልን ተቀዳጅተዋል።
ይህ የ20 ዓመታት የውድድር ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን የቻይና ኮሙኒኬሽን ፈርስት ሃይዌይ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ (CCFHEG/CCCC) የሚያበረክተው ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርጓል። የሲ.ሲ.ሲ.ሲ (CCCC) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ ዌይ ቺያንግዩ በመድረክ ላይ ሲናገሩ “ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን እና የስፖርታዊ ጨዋነትን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ የማህበራዊ ኃላፊነታችንን ለመወጣት በተለይም የመንገድ ደህንነት ግንዛቤን ለማስጨበጥ ይህንን ዝግጅት በቋሚነት ለማዘጋጀት ቁርጠኞች ነን” ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን (AACRA) የጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ተክለፃዲቅ በበኩላቸው የመንገድ ደህንነት የጋራ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸው፤ "ይህ ውድድር ስፖርትን ከማሳደጉም ባለፈ የአብሮነትና የትብብር ተምሳሌት ሆኖ ለሁለት አስርት ዓመታት ዘልቋል" ብለዋል። ወ/ሮ ትዕግስት አክለውም "የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የብዙ አካላትን ርብርብና የተጠቃሚዎችን ተሳትፎ ይፈልጋል፤ ስለዚህ የመንገድ መሰረተ ልማት ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት በመጠበቅ የራሳችንን እና የሌሎችን ህይወት እንድናድን አሳስባለሁ" ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የቡድን ስራ እና የመንገድ ደህንነት መልዕክቶች የጎሉበት 20ኛው አይ.ኤፍ.ኤች./አ.አ.መ.ባ. የዱላ ቅብብል ሩጫ ዛሬ ተካሔደ
20ኛው የአይ.ኤፍ.ኤች./አ.አ.መ.ባ. የዱላ ቅብብል ሩጫ ከቦሌ ቡልቡላ ወደ ኮዬ ፈቼ በሚወስደው መንገድ ላይ ዛሬ ተካሒዷል።
በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አማካኝነት የተዘጋጀው ይህ ልዩ ውድድር፣ ወደ አንድ ሺህ የሚጠጉ ተሳታፊዎችን አወዳድሯል። ዝግጅቱ የሁለት አስርት ዓመታትን የአካል ብቃት እና የኢትዮ-ቻይና ወዳጅነት የጠነከረበት እንዲሁም የመንገድ ደህንነት መልዕክቶች የተላለፉበት መድረክ ሆኗል።
የአዲስ አበባ የቀለበት መንገድ ምረቃን ተከትሎ የተጀመረው ይህ የዱላ ቅብብል ሩጫ፤ በአሁኑ ወቅት በብዙ ተቋማት ዘንድ የሚጠበቅ የሰራተኞች የጋራ ቀን ሆኗል።
የዘንድሮው ውድድር “የ6ታችን ቃልኪዳን” (Our Pact) በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን፣ ይህም በቡድን አባላት መካከል ያለውን ትስስር እና በመተባበር ማሸነፍን የሚያጎላ ነው።
አራት የቡድን አባላቶች እያንዳንዳቸው አራት ኪሎ ሜትሮችን በሮጡበት የአትሌቶች ምድብ ከፍተኛ ፉክክር ታይቷል። በዚህም መሰረት በሁለቱም ፆታ ከኢ.ኮ.ስ.ኮ. የተሰባሰቡ አትሌቶች በአንደኛ እና ሶስተኝነት ሲያጠናቅቁ የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌቶች ሁለተኛ ሆኘዋል።
ከአትሌቶች ውጭ እያንዳንዱ ቡድን ስድስት አባላትን የያዘ ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተወዳዳሪ 1 ኪሎ ሜትር በመሮጥ በድምሩ 6 ኪሎ ሜትር ርቀትን ሸፍነዋል። ውድድሩ በዘጠኝ የተለያዩ ዘርፎች አሸናፊዎችን የሸለመ ሲሆን፤ ይህም የመንግስት ተቋማትን፣ የንግድ ድርጅቶችን፣ ጂም እና የጤና ቡድኖችን፣ ኤምባሲዎችን፣ ባንክና ኢንሹራንስን፣ ሆቴሎችን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን (NGOs) እንዲሁም የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አባላትና ጓደኞችን ያካተተ ነበር።
ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የኤምባሲ ዘርፍ የቻይና ኤምባሲ ቡድን ልዩ ቅንጅት በማሳየት ውድድሩን ሲያሸንፍ፣ በሆቴሎች ዘርፍ አሸናፊዎቹ ኃይሌ ግራንድ ሆቴሎች ደግሞ ከምድባቸው ባሻገር የአጠቃላይ የውድድሩ አሸናፊ በመሆን ድልን ተቀዳጅተዋል።
ይህ የ20 ዓመታት የውድድር ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን የቻይና ኮሙኒኬሽን ፈርስት ሃይዌይ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ (CCFHEG/CCCC) የሚያበረክተው ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርጓል። የሲ.ሲ.ሲ.ሲ (CCCC) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ ዌይ ቺያንግዩ በመድረክ ላይ ሲናገሩ “ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን እና የስፖርታዊ ጨዋነትን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ የማህበራዊ ኃላፊነታችንን ለመወጣት በተለይም የመንገድ ደህንነት ግንዛቤን ለማስጨበጥ ይህንን ዝግጅት በቋሚነት ለማዘጋጀት ቁርጠኞች ነን” ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን (AACRA) የጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ተክለፃዲቅ በበኩላቸው የመንገድ ደህንነት የጋራ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸው፤ "ይህ ውድድር ስፖርትን ከማሳደጉም ባለፈ የአብሮነትና የትብብር ተምሳሌት ሆኖ ለሁለት አስርት ዓመታት ዘልቋል" ብለዋል። ወ/ሮ ትዕግስት አክለውም "የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የብዙ አካላትን ርብርብና የተጠቃሚዎችን ተሳትፎ ይፈልጋል፤ ስለዚህ የመንገድ መሰረተ ልማት ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት በመጠበቅ የራሳችንን እና የሌሎችን ህይወት እንድናድን አሳስባለሁ" ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
❤7👍4
ምዝገባ ተጀምሯል!
ሲቢኢ ብር ፕላስ ላይ ገብተው በነፃ ይመዝገቡ!
በድጋሚ የተመለሰው እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ - የመጀመሪያ ወር ውድድር✨
ቅዳሜ የካቲት 7 በእንጦጦ እንገናኝ ✨
#EntotoPark #CBE #GreatEthiopianRun
ሲቢኢ ብር ፕላስ ላይ ገብተው በነፃ ይመዝገቡ!
በድጋሚ የተመለሰው እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ - የመጀመሪያ ወር ውድድር✨
ቅዳሜ የካቲት 7 በእንጦጦ እንገናኝ ✨
#EntotoPark #CBE #GreatEthiopianRun
❤11
ጋዜጣዊ መግለጫ
የእንግሊዝ ሃገር አንጋፋ አትሌቶች ስብስብ የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ አካል የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ።
ሐሙስ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም.፦
ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በላይ የሆኑ አንጋፋ አትሌቶችን ያሰባሰበ ቡድን በዛሬው ዕለት ከእንግሊዝ ወደ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ እንግሊዛዊያኑ ተሳታፊዎች የፊታችን የካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም. በውቢቷ ሀዋሳ ከተማ በሚካሄደው 14ተኛው ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን ላይ ይወዳደራሉ፡፡
ከተሳታፊዎቹ ውስጥ ከ55 አመት በላይና ከ5000 ሜትር በላይ ውድድር የዓለም ሻምፒዮን እንዲሁም ከ65 ዓመት በላይ የማራቶን ሪከርድ ባለቤት የሆነው ቤን ሬይኖልድስን ይገኝበታል የሪከርዱ ሰዓትም 2 ሰዓት ከ47 ደቂቃ ነው። በተጨማሪም ቡድኑ በ5 ኪ.ሜ. ርቀት ውድድር በጣም ፈጣኑን የእንግሊዝ ከ60 ዓመት በላይ አንጋፋ አትሌት ሯጮች መሐከል ሁለቱን ያካትታል።
የእንግሊዛውያኑ ቡድን የመጀመሪያዎቹን ዘጠኝ ቀናት ቆይታውን በአዲስ አበባ በልምምድና በጉብኝት ያሳልፋል፡፡ አባላቱም በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ አንዳንዶቹ በመንገድ፣ በትራክ እና በሀገር አቋራጭ ውድድር ላይ በተለያየ የዕድሜ ክልል ባሉ የዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች ላይ ይሳተፋሉ።
በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሞብላይዜሽን አስተባባሪ ሃላፊ የሆኑት አብዱራዛቅ አሌዊ ስለ ቡድኑ ሲናገሩ "እነዚህ ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ አንጋፋ አትሌቶች ምን ያህል ፈጣን ሰዓት እንዳላቸው ማየት አስደናቂ ነው። ኢትዮጵያ ያሉ ሯጮችም ይህን ማየት እንደሚያበረታታቸውና የራሳቸውን የሩጫ ግቦች ማስቀመጥን እንዲቀጥሉ እንደሚያነሳሳቸው ተስፋ አደርጋለሁ። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያም በሀዋሳ በሚገኘው የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ከእንግሊዝ ከመጡት አንጋፋ አትሌቶች ጋር ለመወዳደር ኢትዮጵያዊ አንጋፋ አትሌቶችን ያቀፈ ቡድን አዘጋጅቷል" ብለዋል፡፡
የእንግሊዝ ቡድንን አስተባባሪ የሆነው ስቲቭ ዋትሞው እንደተናገረው "ይህ ጉዞ ለውጤት የበቃው የእኔን ወደ ኢትዮጵያ ስለመምጣት ከሪቻርድ ጋር ባደረግነው ውይይት ነው። ስለ ዕቅዶቼ ለጓደኞቼ መንገር እንደጀመርኩ ሌሎችም መቀላቀል ፈለጉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ስልጠና እና ውድድር ለመካፈል እንዲሁም የዚህን አስደናቂ ሀገር ባህልና ታሪክ ለማየት በጣም ጓጉተናል።" ብለዋል፡፡
የ2018 የኢትዮ ቴሌኮም የሀዋሳ ሃይቅ ዓለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን በቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ቴሌብር ፣ ዳሽን ባንክ፣ ፔፕሲ፣ ፋብ የውበት ሳሙና፣ ቶፕ ውሃ፣ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት እንዲሁም በአፍራን ሆስፒታል ድጋፍ የተዘጋጀ ነው።
የ2018ቱ ኢትዮ ቴሌኮም የሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን በሀዋሳ ሃይቅ ዳርቻ ላይ በሚገኝ መንገድ ላይ የካቲት 1 ቀን 2018ዓ.ም. በድምቀት ይካሔዳል።
የእንግሊዝ ሃገር አንጋፋ አትሌቶች ስብስብ የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ አካል የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ።
ሐሙስ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም.፦
ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በላይ የሆኑ አንጋፋ አትሌቶችን ያሰባሰበ ቡድን በዛሬው ዕለት ከእንግሊዝ ወደ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ እንግሊዛዊያኑ ተሳታፊዎች የፊታችን የካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም. በውቢቷ ሀዋሳ ከተማ በሚካሄደው 14ተኛው ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን ላይ ይወዳደራሉ፡፡
ከተሳታፊዎቹ ውስጥ ከ55 አመት በላይና ከ5000 ሜትር በላይ ውድድር የዓለም ሻምፒዮን እንዲሁም ከ65 ዓመት በላይ የማራቶን ሪከርድ ባለቤት የሆነው ቤን ሬይኖልድስን ይገኝበታል የሪከርዱ ሰዓትም 2 ሰዓት ከ47 ደቂቃ ነው። በተጨማሪም ቡድኑ በ5 ኪ.ሜ. ርቀት ውድድር በጣም ፈጣኑን የእንግሊዝ ከ60 ዓመት በላይ አንጋፋ አትሌት ሯጮች መሐከል ሁለቱን ያካትታል።
የእንግሊዛውያኑ ቡድን የመጀመሪያዎቹን ዘጠኝ ቀናት ቆይታውን በአዲስ አበባ በልምምድና በጉብኝት ያሳልፋል፡፡ አባላቱም በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ አንዳንዶቹ በመንገድ፣ በትራክ እና በሀገር አቋራጭ ውድድር ላይ በተለያየ የዕድሜ ክልል ባሉ የዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች ላይ ይሳተፋሉ።
በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሞብላይዜሽን አስተባባሪ ሃላፊ የሆኑት አብዱራዛቅ አሌዊ ስለ ቡድኑ ሲናገሩ "እነዚህ ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ አንጋፋ አትሌቶች ምን ያህል ፈጣን ሰዓት እንዳላቸው ማየት አስደናቂ ነው። ኢትዮጵያ ያሉ ሯጮችም ይህን ማየት እንደሚያበረታታቸውና የራሳቸውን የሩጫ ግቦች ማስቀመጥን እንዲቀጥሉ እንደሚያነሳሳቸው ተስፋ አደርጋለሁ። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያም በሀዋሳ በሚገኘው የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ከእንግሊዝ ከመጡት አንጋፋ አትሌቶች ጋር ለመወዳደር ኢትዮጵያዊ አንጋፋ አትሌቶችን ያቀፈ ቡድን አዘጋጅቷል" ብለዋል፡፡
የእንግሊዝ ቡድንን አስተባባሪ የሆነው ስቲቭ ዋትሞው እንደተናገረው "ይህ ጉዞ ለውጤት የበቃው የእኔን ወደ ኢትዮጵያ ስለመምጣት ከሪቻርድ ጋር ባደረግነው ውይይት ነው። ስለ ዕቅዶቼ ለጓደኞቼ መንገር እንደጀመርኩ ሌሎችም መቀላቀል ፈለጉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ስልጠና እና ውድድር ለመካፈል እንዲሁም የዚህን አስደናቂ ሀገር ባህልና ታሪክ ለማየት በጣም ጓጉተናል።" ብለዋል፡፡
የ2018 የኢትዮ ቴሌኮም የሀዋሳ ሃይቅ ዓለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን በቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ቴሌብር ፣ ዳሽን ባንክ፣ ፔፕሲ፣ ፋብ የውበት ሳሙና፣ ቶፕ ውሃ፣ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት እንዲሁም በአፍራን ሆስፒታል ድጋፍ የተዘጋጀ ነው።
የ2018ቱ ኢትዮ ቴሌኮም የሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን በሀዋሳ ሃይቅ ዳርቻ ላይ በሚገኝ መንገድ ላይ የካቲት 1 ቀን 2018ዓ.ም. በድምቀት ይካሔዳል።
❤5
🤩 የልወቅሽ ኢትዮዽያ ክላሲክስ 2ኛ መዳረሻችን በነበረችው ሀዋሳ ውብ የእረፍት ቀናት እና ሩጫ ውድድር ነበረን ✨
2018 ኢትዮ ቴሌኮም ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን✨
ቀጣይ መዳረሻችን - ጅማ - ሚያዝያ 18 ቀን 2018ዓ.ም.
✨ይጎብኙ፣ ይሩጡ፣ ሀገርዎን ይወቁ ✨
#GreatEthiopianRun #DiscoverEthiopiaClassics #2026Registration #6CitiesSeries #LHHM
2018 ኢትዮ ቴሌኮም ሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን✨
ቀጣይ መዳረሻችን - ጅማ - ሚያዝያ 18 ቀን 2018ዓ.ም.
✨ይጎብኙ፣ ይሩጡ፣ ሀገርዎን ይወቁ ✨
#GreatEthiopianRun #DiscoverEthiopiaClassics #2026Registration #6CitiesSeries #LHHM
❤18👍2
በየወሩ የሚካሄደው የእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ከየካቲት ወር ጀምሮ ተመልሷል።
የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም.
በጉጉት የሚጠበቀውና በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ወርሃዊው 'እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ' የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር ዳግም ተጀመረ። የፊታችን የካቲት 7 ቀን 2018ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ ውድድር፣ ከተለመደው የስፖርት እንቅስቃሴ እና ውድድር ባለፈ የፍቅረኛሞች ቀንን (Valentine's Day) ታሳቢ ያደረጉ ልዩ ዝግጅቶች ተካተዋል።
ሩጫ ወዳጆች ሁሉ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፉ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ባሉበት ቦታ ሆነው በሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ አማካኝነት በነፃ እና በቀላሉ መመዝገብ እንዲችሉ አድርጓል።
በተጨማሪም ወደ እንጦጦ ፓርክ የሚደረገውን ጉዞ ምቹ እና ቀላል ለማድረግ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ለተሳታፊዎች በመሄጃ መንገዳቸው ላይ ያሉትን የአዲስ አበባን አዳዲስ መዳረሻዎች እየጎበኙ ወደ ፓርኩ አድርሶ የሚመልስ የትራንስፖርት አገልግሎት በነፃ አዘጋጅቷል።
የወሩ የሩጫ መርሃ-ግብር «የእኔ አጋር ይሮጣል» (My Valentine is Running) በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ጥንዶች በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን መንገድ ታሳቢ አድርጎ ተዘጋጅተል። ይህንንም ለማበረታታት ጥንዶች የሚፎካከሩበትና አሸናፊዎች የሚሸለሙበት ልዩ ፉክክር አንዱ የውድድሩ ድምቀት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ ጥንዶች በኩሪፍቱ ሪዞርት ልዩ ሽልማቶች ይበረከቱላቸዋል።
ስለ ውድድሩ መግለጫ
የእንጦጦ ፖርክ ሲቢኢ ሩጫ በየወሩ የተለያየ ጭብጥ በመያዝ የሚዘጋጅ የ5ኪ.ሜ. የፓርክ ሩጫ ነው። ውድድሩ ማህበረሰቡ በስፖርት እንዲነቃቃ፣ ተፈጥሮን እንዲያደንቅ እና ሩጫን ቋሚ ልምምዱ እንዲያደርግ ዓላማ ያደረገ ወርሀዊ ውድድር ነው።
የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም.
በጉጉት የሚጠበቀውና በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚዘጋጀው ወርሃዊው 'እንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ' የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር ዳግም ተጀመረ። የፊታችን የካቲት 7 ቀን 2018ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ ውድድር፣ ከተለመደው የስፖርት እንቅስቃሴ እና ውድድር ባለፈ የፍቅረኛሞች ቀንን (Valentine's Day) ታሳቢ ያደረጉ ልዩ ዝግጅቶች ተካተዋል።
ሩጫ ወዳጆች ሁሉ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፉ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ባሉበት ቦታ ሆነው በሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ አማካኝነት በነፃ እና በቀላሉ መመዝገብ እንዲችሉ አድርጓል።
በተጨማሪም ወደ እንጦጦ ፓርክ የሚደረገውን ጉዞ ምቹ እና ቀላል ለማድረግ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ለተሳታፊዎች በመሄጃ መንገዳቸው ላይ ያሉትን የአዲስ አበባን አዳዲስ መዳረሻዎች እየጎበኙ ወደ ፓርኩ አድርሶ የሚመልስ የትራንስፖርት አገልግሎት በነፃ አዘጋጅቷል።
የወሩ የሩጫ መርሃ-ግብር «የእኔ አጋር ይሮጣል» (My Valentine is Running) በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ጥንዶች በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበትን መንገድ ታሳቢ አድርጎ ተዘጋጅተል። ይህንንም ለማበረታታት ጥንዶች የሚፎካከሩበትና አሸናፊዎች የሚሸለሙበት ልዩ ፉክክር አንዱ የውድድሩ ድምቀት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ ጥንዶች በኩሪፍቱ ሪዞርት ልዩ ሽልማቶች ይበረከቱላቸዋል።
ስለ ውድድሩ መግለጫ
የእንጦጦ ፖርክ ሲቢኢ ሩጫ በየወሩ የተለያየ ጭብጥ በመያዝ የሚዘጋጅ የ5ኪ.ሜ. የፓርክ ሩጫ ነው። ውድድሩ ማህበረሰቡ በስፖርት እንዲነቃቃ፣ ተፈጥሮን እንዲያደንቅ እና ሩጫን ቋሚ ልምምዱ እንዲያደርግ ዓላማ ያደረገ ወርሀዊ ውድድር ነው።
❤7👍1