የማይነድ እሳት !!!!!
የማይነድ ቁስቋስ ፤ ማገዶ አምጥታችሁ ፤
ማለዳ ጀምሬ ፤
እፍ ብል እፍ ብል ፤
አልሰማም ጀበናው ፤አልፈላም ቡናችሁ ።
የለመደባችሁ ፤
ደረቅ ትእዛዛችሁ ፤
ቆስቁሺው ነው አንጅ፤
አንድጅው ነው እንጅ፤ አጭሺ እንደገና ፤
እኔም እርም አያርመኝ ፤
ደግሞ እንደ በቀደም እንደ ትናንትና ፤
ዛሬም እፍ....... እላለሁ
እንዳይፈላ እያወቅኩ ፤ የእናንተ ጀበና ።
ቆስቁሽበት ብለው ፤
ጤዛ የጠገበ ፤
የለዘዘ ቁስቋስ ፤ ይዘው እየመጡ ፤
ዛሬም እንደገና ፤
እሳቱ አልነደደም ፤ እነርሱም አልጠጡ ።
ምድጃ ዳር ቆሞ ፤
የማይነድን ቁስቋስ ፤
አቃጥሉ ቆስቁሱ ፤
አንድዱበት ብሎ ፤ በእፍ ባይ መከበብ ከጧት እስከ ማታ ፤
አየዋ ልንገርህ ፤
ያበሻ ግብር ነው ፤ የጦቢያ በሽታ ።
(((( ጃ ኖ )))💚💛❤
@getem0
@getem0
የማይነድ ቁስቋስ ፤ ማገዶ አምጥታችሁ ፤
ማለዳ ጀምሬ ፤
እፍ ብል እፍ ብል ፤
አልሰማም ጀበናው ፤አልፈላም ቡናችሁ ።
የለመደባችሁ ፤
ደረቅ ትእዛዛችሁ ፤
ቆስቁሺው ነው አንጅ፤
አንድጅው ነው እንጅ፤ አጭሺ እንደገና ፤
እኔም እርም አያርመኝ ፤
ደግሞ እንደ በቀደም እንደ ትናንትና ፤
ዛሬም እፍ....... እላለሁ
እንዳይፈላ እያወቅኩ ፤ የእናንተ ጀበና ።
ቆስቁሽበት ብለው ፤
ጤዛ የጠገበ ፤
የለዘዘ ቁስቋስ ፤ ይዘው እየመጡ ፤
ዛሬም እንደገና ፤
እሳቱ አልነደደም ፤ እነርሱም አልጠጡ ።
ምድጃ ዳር ቆሞ ፤
የማይነድን ቁስቋስ ፤
አቃጥሉ ቆስቁሱ ፤
አንድዱበት ብሎ ፤ በእፍ ባይ መከበብ ከጧት እስከ ማታ ፤
አየዋ ልንገርህ ፤
ያበሻ ግብር ነው ፤ የጦቢያ በሽታ ።
(((( ጃ ኖ )))💚💛❤
@getem0
@getem0
#ፍቅር_ፈራን_ጠላን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
@getem0
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
@getem0
አላሳዝንሽም?
እኔ አንቺን አፍቅሬ
ከሰውነት ተርታ ወዲያ ተሸቀንጥሬ
የምኖርበትን እይወቴን ረስቼ
እስከማልታወቅ ጠቍሬ ከስቼ
አንቺ የኔ ካልሆንሽ ህይወቴ ይረሳ መኖሬ አይታወስ
እያልኩ እስካነባ ከጸባሆት ድረስ
ከጸባሆት ደርሶ መልሶ እስኪዘንብ
ድንገት ክረምትሆኖ ልብስሽ ልብሴ ሲረጥብ
ዝናብ ይመስልሻል ይኀው አሁን እንዄን ከላይ የሚዘንበው የኔው እምባኮ ነው
አላሳዝንሸም?
በኔ ፍቅር ጉዳይ እግዜር ጣልቃ ገብቶ
ዶፉን የሚያወርደዉ መብረቁን አብርቶ
ደግሞም ሳያባራ ጨረቃ በግርጌ ፀሀይ በቀኝ በኩል ድንገት የምትወጣው
ጠብ ጠብ እያለ ኮከቡ እሚረገፈው ለምን ይመስልሻል የሀዘኔን ጥልቀት አይተው ተመልክተው
የእምባኤን ብዛት መላዕክት ለክተው ቢነግሩት እኮነው
አላሳዝንሽም?
አለሽበት ካሉት አለሸ ካልኩት ቦታ ይኀው ቁጭ ብያለው
አንቺን በመጠበቅ አንቺን መስያለው
የአይኖችሽ ጥላ አይኔላይ ስላሉ
አይኖቼን ብታዪ ያንቺን ይመስላሉ
በሩ በተነካ ሰዉ ባለፈ ቁጥር
መጣች ቅረች የሚል ጎዶሎ ስቆጥር
አመሸው እንደዚ ቆየሁኝ እንደዛ ዝቅ አልኩ ወደምድር አሻቀብኩ ወደዚያ
ከፍብዬ አየሁት ተንሳፈፍኩ ወደላይ እንደማያይ ገባኝ ሰው ከራሱ በላይ
አላሳዝንሽም?
ምድር ተፈርክሷል ሰማይ ተሰንጥቋል
በስንጥቁ መሃል እግዚሃር ይታያል
በስንጥቁ መሃል አግዚሃር እንዲ ይላል
አያሳዝንሽም?
ጨረቃንም እንኪ ፀሀይን ውሰጃት ብቻ አንድ ሂጂለት
ይልሻል እግዜሩ ገብቶታል ነገሩ
አላሳዝንሽም?አሳዝንሻለዉ ጨካኝ አይደለሽም አዛኝ ነሽ አዉቃለዉ
ይህ ሁሉ ሲሆን ይህ ሁሉ ሲፈጠር ባትሰሚ ባታይ ነዉ !!!
(ትልቅ ይቅርታ ለምዕልቲ ኪሮስ🙏🙏🙏)
@getem0
@getem0
እኔ አንቺን አፍቅሬ
ከሰውነት ተርታ ወዲያ ተሸቀንጥሬ
የምኖርበትን እይወቴን ረስቼ
እስከማልታወቅ ጠቍሬ ከስቼ
አንቺ የኔ ካልሆንሽ ህይወቴ ይረሳ መኖሬ አይታወስ
እያልኩ እስካነባ ከጸባሆት ድረስ
ከጸባሆት ደርሶ መልሶ እስኪዘንብ
ድንገት ክረምትሆኖ ልብስሽ ልብሴ ሲረጥብ
ዝናብ ይመስልሻል ይኀው አሁን እንዄን ከላይ የሚዘንበው የኔው እምባኮ ነው
አላሳዝንሸም?
በኔ ፍቅር ጉዳይ እግዜር ጣልቃ ገብቶ
ዶፉን የሚያወርደዉ መብረቁን አብርቶ
ደግሞም ሳያባራ ጨረቃ በግርጌ ፀሀይ በቀኝ በኩል ድንገት የምትወጣው
ጠብ ጠብ እያለ ኮከቡ እሚረገፈው ለምን ይመስልሻል የሀዘኔን ጥልቀት አይተው ተመልክተው
የእምባኤን ብዛት መላዕክት ለክተው ቢነግሩት እኮነው
አላሳዝንሽም?
አለሽበት ካሉት አለሸ ካልኩት ቦታ ይኀው ቁጭ ብያለው
አንቺን በመጠበቅ አንቺን መስያለው
የአይኖችሽ ጥላ አይኔላይ ስላሉ
አይኖቼን ብታዪ ያንቺን ይመስላሉ
በሩ በተነካ ሰዉ ባለፈ ቁጥር
መጣች ቅረች የሚል ጎዶሎ ስቆጥር
አመሸው እንደዚ ቆየሁኝ እንደዛ ዝቅ አልኩ ወደምድር አሻቀብኩ ወደዚያ
ከፍብዬ አየሁት ተንሳፈፍኩ ወደላይ እንደማያይ ገባኝ ሰው ከራሱ በላይ
አላሳዝንሽም?
ምድር ተፈርክሷል ሰማይ ተሰንጥቋል
በስንጥቁ መሃል እግዚሃር ይታያል
በስንጥቁ መሃል አግዚሃር እንዲ ይላል
አያሳዝንሽም?
ጨረቃንም እንኪ ፀሀይን ውሰጃት ብቻ አንድ ሂጂለት
ይልሻል እግዜሩ ገብቶታል ነገሩ
አላሳዝንሽም?አሳዝንሻለዉ ጨካኝ አይደለሽም አዛኝ ነሽ አዉቃለዉ
ይህ ሁሉ ሲሆን ይህ ሁሉ ሲፈጠር ባትሰሚ ባታይ ነዉ !!!
(ትልቅ ይቅርታ ለምዕልቲ ኪሮስ🙏🙏🙏)
@getem0
@getem0
እሳት ወይ አበባ
..........
ይቅር ብቻ አንናገርም፥
እኔና አንቺ አንወያይም፥
ለውይይት አልታደልንም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም.....ዝም፡፡
አበባ አንሆን ወይም እሳት
ተጠምደን በምኞት ቅጣት
ሰመመን ባጫረው መአት
እድሜአችንን እንዳማጥናት....
እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ -እንቅ ስንባባ
ባከነች ልጅነታችን ፥ እየቃተትን ስናነባ፡፡......
ፈራን፤ አዎን ፍቅር ፈራን፥
የነፍስን አንደበት ዘጋን፥
የእድሜ ጠብታችንን ምጥ፥ የጣር ፅንሳችንን ልሣን፥
ልጅነት የለገሠንን
በመለኮት የቀባንን
በእሳቱ ያጠመቀንን
የፍቅር አምላክ በጥበቡ፥ በሥልጣን ያላበሰንን
ፈራን፥ አዎን እውነት ፈራን
የስሜት እስትንፋስ ነሳን፡፡ ....
( ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን)
@getem0
..........
ይቅር ብቻ አንናገርም፥
እኔና አንቺ አንወያይም፥
ለውይይት አልታደልንም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም.....ዝም፡፡
አበባ አንሆን ወይም እሳት
ተጠምደን በምኞት ቅጣት
ሰመመን ባጫረው መአት
እድሜአችንን እንዳማጥናት....
እሳት አንሆን ወይ አበባ
በሕቅ -እንቅ ስንባባ
ባከነች ልጅነታችን ፥ እየቃተትን ስናነባ፡፡......
ፈራን፤ አዎን ፍቅር ፈራን፥
የነፍስን አንደበት ዘጋን፥
የእድሜ ጠብታችንን ምጥ፥ የጣር ፅንሳችንን ልሣን፥
ልጅነት የለገሠንን
በመለኮት የቀባንን
በእሳቱ ያጠመቀንን
የፍቅር አምላክ በጥበቡ፥ በሥልጣን ያላበሰንን
ፈራን፥ አዎን እውነት ፈራን
የስሜት እስትንፋስ ነሳን፡፡ ....
( ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን)
@getem0
አንቺ እውነትም ሴት ነሽ
ግላዊ ሂወትሽ ደስታሽ ሣያጓጓሽ
ለሰው የምትኖሪ የራስሽን ትተሽ
ዘመንሽን ምትገፊ ስለሰው እያሰብሽ
ለሰው እየለፋሽ
ስለሰው እየኖርሽ፡
ይሄን አወቄአለው
አንቺ እውነትም ሴት ነሽ፡፡
ሴት ነሽ ማለቴ ግን
አላዋቂ ሁሉ ደካማን ሲነቅፋ
አቅም የሌለውን ሴት ብሎ እንደሚያልፋ
ወይ ደሞ
ያቀለለ መስሎት ሴት ብሎ ሚሳደብ
ማክበሩን ሳያቀው የሚናገር ደደብ
የሴትነት ትርጉም ለኔ ይህ አደለም
ባዶ መረዳት ነው በሰነፎች አለም
እኔ ሴት የምላት
ለራስ ብቻደለም በዙርያዋ ላሉት
መናኖር እንደቻለች ምንም ቢታክታት
ደስታን ከፈጠረች የራሷም ቢያርባት
መስዋት ከከፈለች ልክ እንደ እናት
ሌላ ቃል የለኝም የኔ ሴት ይቺ ናት፡፡
አንቺም ለሰው የኖርሽ
ደስታን ልሰጥ ስትይ ደስታሽም ላጣሽ
ከራስሽም በላይ ስለ ምትወጂው ሠው መኖሩንም ከቻልሽ
አረጋግጫለው ዮሪ እውነትም ሴት ነሽ፡፡
28/06/2011
@getem0
@getem0
ግላዊ ሂወትሽ ደስታሽ ሣያጓጓሽ
ለሰው የምትኖሪ የራስሽን ትተሽ
ዘመንሽን ምትገፊ ስለሰው እያሰብሽ
ለሰው እየለፋሽ
ስለሰው እየኖርሽ፡
ይሄን አወቄአለው
አንቺ እውነትም ሴት ነሽ፡፡
ሴት ነሽ ማለቴ ግን
አላዋቂ ሁሉ ደካማን ሲነቅፋ
አቅም የሌለውን ሴት ብሎ እንደሚያልፋ
ወይ ደሞ
ያቀለለ መስሎት ሴት ብሎ ሚሳደብ
ማክበሩን ሳያቀው የሚናገር ደደብ
የሴትነት ትርጉም ለኔ ይህ አደለም
ባዶ መረዳት ነው በሰነፎች አለም
እኔ ሴት የምላት
ለራስ ብቻደለም በዙርያዋ ላሉት
መናኖር እንደቻለች ምንም ቢታክታት
ደስታን ከፈጠረች የራሷም ቢያርባት
መስዋት ከከፈለች ልክ እንደ እናት
ሌላ ቃል የለኝም የኔ ሴት ይቺ ናት፡፡
አንቺም ለሰው የኖርሽ
ደስታን ልሰጥ ስትይ ደስታሽም ላጣሽ
ከራስሽም በላይ ስለ ምትወጂው ሠው መኖሩንም ከቻልሽ
አረጋግጫለው ዮሪ እውነትም ሴት ነሽ፡፡
28/06/2011
@getem0
@getem0
በዚህ ጊዜ
ያለ ጥርጣሬ አብረን እንድንሆን እያመነሽ ልቤ የለመድነው ቀርቶ
አየሁ ንፁህ ፍቅርሽ ጠፍቶ እኔ አላውቅም
ዛሬ ያቆራረጠን ምን ተገኝቶ ነው
ያንቺ የኔ የኔ ያንቺ እኮ ነው
እንድንከፋፈል አሰብሽ ምነው
ሰላም ነበር የሚሻለው
ምን ይሆን መሃላችን ጣልቃ እየገባ
የሚያረባብሸን ሚያጋጨን በየ ዕለት ሰርሥሮ እያደባ
መደራደር ሳለ መደላደል
መተራረም መገላገል
እንድንተሳሠብ ይገባ ነበር
ያወራነው መና እንዳይቀር
ለምን ፍቅራችን ላላ
ምን አለ ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ
እንቺ ትብሽ አንተ እየተባባልን ነገር አበላሽተን ኋላ እንዳይፀፅተን ተዳፍረን እየተፎካከርን እኔ አላምንም
እየተቀናናን በገዛ እጃችን
አላምር አለ ሁኔታችን
ተነጣጥለን ልንቀር ለማን ብለን ?
በዚህ ዘመን ምን ሞኝ ነን ?
አንገት የሚያስደፋ የሚያሳፍረንን ድርጊት እየፈፀምን ዋጋ እንዳናሳጣው ክብራችን በሰዎች አፍ ገብተን እኔ አላምንም
መከባበር ሳለ መመካከር
በሁለታችን ሁሉ እንዲቀር
እንድንጠባበቅ ይገባ ነበር
እቅዳችን እንዲሰምር
እንዴት ፍቅራችን ላላ
ምን ነበር ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ መቀየጣችን አትዘንጊ ተዋደን
አሄ እያልን በየፊናችን
አሄ አጠፋፋን መራራቃችን
አሄ ተለያይተን እንዳንቀር
አሄ ፀብ ትተን እንኑር ተይ አንቃቃር
እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን
እንደ ድር እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው እንደውም እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድር እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው..........ትዕግሥት ያስከብራል !!!
አዲስ ሥራዬን ወደ እናንተ ለማድረስ ዝግጅቴን እያጠናቀኩ ነው ። የሰራዋቸውን ሥራዎች የዋህ ፣ ያም ሆነ ይህ ፣ ብር አምባር እና የሌለ ነው እንዲሁም በኦዲዮ ያሉ ሥራዎቼን ስለወደዳችሁልኝ እያ @getem0
ያለ ጥርጣሬ አብረን እንድንሆን እያመነሽ ልቤ የለመድነው ቀርቶ
አየሁ ንፁህ ፍቅርሽ ጠፍቶ እኔ አላውቅም
ዛሬ ያቆራረጠን ምን ተገኝቶ ነው
ያንቺ የኔ የኔ ያንቺ እኮ ነው
እንድንከፋፈል አሰብሽ ምነው
ሰላም ነበር የሚሻለው
ምን ይሆን መሃላችን ጣልቃ እየገባ
የሚያረባብሸን ሚያጋጨን በየ ዕለት ሰርሥሮ እያደባ
መደራደር ሳለ መደላደል
መተራረም መገላገል
እንድንተሳሠብ ይገባ ነበር
ያወራነው መና እንዳይቀር
ለምን ፍቅራችን ላላ
ምን አለ ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ
እንቺ ትብሽ አንተ እየተባባልን ነገር አበላሽተን ኋላ እንዳይፀፅተን ተዳፍረን እየተፎካከርን እኔ አላምንም
እየተቀናናን በገዛ እጃችን
አላምር አለ ሁኔታችን
ተነጣጥለን ልንቀር ለማን ብለን ?
በዚህ ዘመን ምን ሞኝ ነን ?
አንገት የሚያስደፋ የሚያሳፍረንን ድርጊት እየፈፀምን ዋጋ እንዳናሳጣው ክብራችን በሰዎች አፍ ገብተን እኔ አላምንም
መከባበር ሳለ መመካከር
በሁለታችን ሁሉ እንዲቀር
እንድንጠባበቅ ይገባ ነበር
እቅዳችን እንዲሰምር
እንዴት ፍቅራችን ላላ
ምን ነበር ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ መቀየጣችን አትዘንጊ ተዋደን
አሄ እያልን በየፊናችን
አሄ አጠፋፋን መራራቃችን
አሄ ተለያይተን እንዳንቀር
አሄ ፀብ ትተን እንኑር ተይ አንቃቃር
እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን
እንደ ድር እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው እንደውም እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድር እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው..........ትዕግሥት ያስከብራል !!!
አዲስ ሥራዬን ወደ እናንተ ለማድረስ ዝግጅቴን እያጠናቀኩ ነው ። የሰራዋቸውን ሥራዎች የዋህ ፣ ያም ሆነ ይህ ፣ ብር አምባር እና የሌለ ነው እንዲሁም በኦዲዮ ያሉ ሥራዎቼን ስለወደዳችሁልኝ እያ @getem0
~ስወድሽ~ ♡
ዉዴ አንችን ስወድሽ
እንዲህ ያደርገኛል.. ፣
አንደበቴ ታስሮ በፍቅርሽ ምትሀት
በቁም ያቃዠኛል፣
የዉበትሽ ግርማ የማማርሽ ፀዳል
ገዝፎ ይታየኛል፣
ብቻ አንችን ሳስብሽ
እንዲህ ያደርገኛል..፣
የድምፅሽ ዉብ ቃላት በጀሮየ ታቡር
ደምቆ ይሰማኛል፣
ደሞ እንዳየዉሽ
መአዛ.. ጠረንሽ.. ወዝሽ.. ያፈዘኛል፣
ብቻ አንችን.. አንችን.. አንችን እላለሁኝ፣
ደስታየን መልሰሽ በፍቅርሽ ታከምኩኝ፣
በፍቅርሽ ጥበብ ዉስጥ
እራሴን አወኩት፣
ባይኖችሽ ዉብ ጨረር
ነፍሴንም አስዋብኩት፣
በወዝሽ ወዝቸ
በጥርስሽ ስቂያለሁ፣
ከልብሽ እምነትን
ፍቅርን ቀስሚያለሁ፣
ሰናይ ባህሪሽን ካንች ተዉሻለሁ፣
መጥፎ ትዝታየን ሁሉን ትቸዋለሁ፣
....
እናልሽ አካሌ :-
ለዚህ እንድበቃ
ያረግሽኝ አንች ነሽ፣
ተከፍሎ የማያልቅ
አለብኝ ዉለታሽ፣
°°°°°°°°°°°°°°
እናም የኔ ፍቅር•••
በቀሪዉ ዘመኔ በተሰጠኝ ቀናት፣
ካንች ጋራ ልኑር ነፍሴን ላስደስታት፣
የመኖሬን ትርጉም
ባንች አይቻለሁ፣
የልቤ ንግስት ነሽ
ዉዴ እ ወ ድ ሻ ለ ሁ !!
💞💞💞 @getem0 💞💞💞
ዉዴ አንችን ስወድሽ
እንዲህ ያደርገኛል.. ፣
አንደበቴ ታስሮ በፍቅርሽ ምትሀት
በቁም ያቃዠኛል፣
የዉበትሽ ግርማ የማማርሽ ፀዳል
ገዝፎ ይታየኛል፣
ብቻ አንችን ሳስብሽ
እንዲህ ያደርገኛል..፣
የድምፅሽ ዉብ ቃላት በጀሮየ ታቡር
ደምቆ ይሰማኛል፣
ደሞ እንዳየዉሽ
መአዛ.. ጠረንሽ.. ወዝሽ.. ያፈዘኛል፣
ብቻ አንችን.. አንችን.. አንችን እላለሁኝ፣
ደስታየን መልሰሽ በፍቅርሽ ታከምኩኝ፣
በፍቅርሽ ጥበብ ዉስጥ
እራሴን አወኩት፣
ባይኖችሽ ዉብ ጨረር
ነፍሴንም አስዋብኩት፣
በወዝሽ ወዝቸ
በጥርስሽ ስቂያለሁ፣
ከልብሽ እምነትን
ፍቅርን ቀስሚያለሁ፣
ሰናይ ባህሪሽን ካንች ተዉሻለሁ፣
መጥፎ ትዝታየን ሁሉን ትቸዋለሁ፣
....
እናልሽ አካሌ :-
ለዚህ እንድበቃ
ያረግሽኝ አንች ነሽ፣
ተከፍሎ የማያልቅ
አለብኝ ዉለታሽ፣
°°°°°°°°°°°°°°
እናም የኔ ፍቅር•••
በቀሪዉ ዘመኔ በተሰጠኝ ቀናት፣
ካንች ጋራ ልኑር ነፍሴን ላስደስታት፣
የመኖሬን ትርጉም
ባንች አይቻለሁ፣
የልቤ ንግስት ነሽ
ዉዴ እ ወ ድ ሻ ለ ሁ !!
💞💞💞 @getem0 💞💞💞
✍ቤተል
*ግመሽ ጨረቃዋ🌒*
የዛሬ ወር ነበር የዛሬ ሁለት ወር፤
ውዴ ተማምለን የጀመርነው ፍቅር💏፤
ከጨረቃዋ ፊት ከክበቧ ቆመን🌕፤
እሷ ለኛ ስቃ እኛ እሷን እያየን😍፤
ትዝ ይልሀል ውዴ ጨረቃ ውበቷ፤
አቤት ሙሉነቷ በዛ ላይ ፍካቷ፤
ዳሩ ምን ያደረጋል ፍቅራችን ተረስተዋል፤
በኔ ልብ ውዴ ከጥልቁ ተቀብሯል😪፤
.
.
.
ታዲያ እንዲምልህ ናፍቄ እንዳይመስልህ፤
ወይም ሌላ ሌላ እንዳያስብ ልብህ፤
አልያም ልላት አይደለም ጨረቃ ፍረጂ፤
የጨረቃ ምልአት ተደግሞ ነው እንጂ፤
.
.
.
እንዳለቀ ባውቅም የፍቅራችን ፀዋ ፤
ቀኗን ግን ጠብቃ መላች ጨረቃዋ🌕፤
እንደ ድሮም ባይሆን .....
እንደ አሁንም ብንሆን......
ለእርሷግድ ሳይላት ዛሬም ሙሉ ሆናለች፥
ደስታዬን እረስታ ሀዘኔን ጭራለች😕፤
ታዲያ ጨረቃዋ ሀዘኔን እዘኚ ፤v
ደስታዬ እንደነበርሽ ዛሬም ከእኔ ሁኚ፤
አልይሽ መሉ ሆነሽ በድጋሚ፤
ግመሽ ጨረቃዋ🌛 በይ ሁኚ
የፍቅሬ ፈፃሚ💔።
11-06-2011 ዓ.ም
@getem0
*ግመሽ ጨረቃዋ🌒*
የዛሬ ወር ነበር የዛሬ ሁለት ወር፤
ውዴ ተማምለን የጀመርነው ፍቅር💏፤
ከጨረቃዋ ፊት ከክበቧ ቆመን🌕፤
እሷ ለኛ ስቃ እኛ እሷን እያየን😍፤
ትዝ ይልሀል ውዴ ጨረቃ ውበቷ፤
አቤት ሙሉነቷ በዛ ላይ ፍካቷ፤
ዳሩ ምን ያደረጋል ፍቅራችን ተረስተዋል፤
በኔ ልብ ውዴ ከጥልቁ ተቀብሯል😪፤
.
.
.
ታዲያ እንዲምልህ ናፍቄ እንዳይመስልህ፤
ወይም ሌላ ሌላ እንዳያስብ ልብህ፤
አልያም ልላት አይደለም ጨረቃ ፍረጂ፤
የጨረቃ ምልአት ተደግሞ ነው እንጂ፤
.
.
.
እንዳለቀ ባውቅም የፍቅራችን ፀዋ ፤
ቀኗን ግን ጠብቃ መላች ጨረቃዋ🌕፤
እንደ ድሮም ባይሆን .....
እንደ አሁንም ብንሆን......
ለእርሷግድ ሳይላት ዛሬም ሙሉ ሆናለች፥
ደስታዬን እረስታ ሀዘኔን ጭራለች😕፤
ታዲያ ጨረቃዋ ሀዘኔን እዘኚ ፤v
ደስታዬ እንደነበርሽ ዛሬም ከእኔ ሁኚ፤
አልይሽ መሉ ሆነሽ በድጋሚ፤
ግመሽ ጨረቃዋ🌛 በይ ሁኚ
የፍቅሬ ፈፃሚ💔።
11-06-2011 ዓ.ም
@getem0
ዕድለ-ዕድል(ልዑል ሀይሌ)
ሰው ይታመማል ወይ
ስለት አስገብቶ፤
እግሩን ይሰብራል ወይ
ምርኩዝ ዱላን አይቶ፤
.
ዓይኑን ያጠፋል ወይ
ጠላት ላለማየት፤
አይገናኝም ወይ
ላለመለያየት።
.
ያፍሳል ወይ ውሃውን
ከቁጭት ለመዳን፤
ከአውሬው ለመሸሽ
ያንሳል ወይ ከጉንዳን፤
.
ያነጥፋል ወይ እሾህ
ከገደል ሳር ፍርሃት ርቆ ሊገላገል፤
እጁን ይቆርጣል ወይ
አንበሣ ለመግደል፤
.
ቤቱን ያፈርሳል ወይ
ዛፍ ላይ የተሰራ
የወፍ ጎጆ እያየ፤
አይፈቀርም ወይ
የተፋቀረ ሰው ሲለያይ ስላየ።
.
ለዚህ ነው የምልሽ!..
ዓይንሽን አትመኝ
ጆሮሽን አትመኝ
ልብሽን አትመኝ፤
ልቤ ፈርሷልና
ጨረቃ ምድር ላይ ቆማ ስትገጥመኝ።
.
ለዚህ ነው የምልሽ!..
እንዳትታበዪ እንዳትኮሪበት፤
ምንም ትላንት ባይኖር
ለነገው ትንፋሼ
ትንፋሽሽ አለበት።
.
ስለዚህ!..
ክፈቺው ልብሽን
ክፈች ዓይኖችሽን ነገሽን አልሚ፤
ትላንት የወጋሽ ጦር
ነገ እንዳይገድልሽ ዛሬ አትታመሚ።
.
የምልሽን ስሚ!
ጆሮሽን ክፈቺ ኮርኩሪው ይሰማሽ፤
ያለፈው ሲቃ ድምፅ
ሊሽር ቆሞልሻል በፍቅር የተጠማሽ።
.
፳፱-፪-፳፻፲፩ ዓ.ም.
@getem0
@getem0
ሰው ይታመማል ወይ
ስለት አስገብቶ፤
እግሩን ይሰብራል ወይ
ምርኩዝ ዱላን አይቶ፤
.
ዓይኑን ያጠፋል ወይ
ጠላት ላለማየት፤
አይገናኝም ወይ
ላለመለያየት።
.
ያፍሳል ወይ ውሃውን
ከቁጭት ለመዳን፤
ከአውሬው ለመሸሽ
ያንሳል ወይ ከጉንዳን፤
.
ያነጥፋል ወይ እሾህ
ከገደል ሳር ፍርሃት ርቆ ሊገላገል፤
እጁን ይቆርጣል ወይ
አንበሣ ለመግደል፤
.
ቤቱን ያፈርሳል ወይ
ዛፍ ላይ የተሰራ
የወፍ ጎጆ እያየ፤
አይፈቀርም ወይ
የተፋቀረ ሰው ሲለያይ ስላየ።
.
ለዚህ ነው የምልሽ!..
ዓይንሽን አትመኝ
ጆሮሽን አትመኝ
ልብሽን አትመኝ፤
ልቤ ፈርሷልና
ጨረቃ ምድር ላይ ቆማ ስትገጥመኝ።
.
ለዚህ ነው የምልሽ!..
እንዳትታበዪ እንዳትኮሪበት፤
ምንም ትላንት ባይኖር
ለነገው ትንፋሼ
ትንፋሽሽ አለበት።
.
ስለዚህ!..
ክፈቺው ልብሽን
ክፈች ዓይኖችሽን ነገሽን አልሚ፤
ትላንት የወጋሽ ጦር
ነገ እንዳይገድልሽ ዛሬ አትታመሚ።
.
የምልሽን ስሚ!
ጆሮሽን ክፈቺ ኮርኩሪው ይሰማሽ፤
ያለፈው ሲቃ ድምፅ
ሊሽር ቆሞልሻል በፍቅር የተጠማሽ።
.
፳፱-፪-፳፻፲፩ ዓ.ም.
@getem0
@getem0
Ethiopian.Airlines.crash victims:
32 Kenyan
18 Canadian
9 Ethiopian
8 Chinese
8 Italian
8 American
7 French
7 British
6 Egyptian
5 Dutch
4 UN passports
4 Indian
3 Russian
2 Moroccan
2 Israeli
1 Belgian
1 Ugandan
1 Yemeni
1 Sudanese
1 Togolese
1 Mozambican
1 Norwegian
ነብስ ይማር ምንጭ Ethiopian.Airlines
32 Kenyan
18 Canadian
9 Ethiopian
8 Chinese
8 Italian
8 American
7 French
7 British
6 Egyptian
5 Dutch
4 UN passports
4 Indian
3 Russian
2 Moroccan
2 Israeli
1 Belgian
1 Ugandan
1 Yemeni
1 Sudanese
1 Togolese
1 Mozambican
1 Norwegian
ነብስ ይማር ምንጭ Ethiopian.Airlines
--ከተማሪዋ ለጉልቤው የተላከ--
ጭሱም የእናቴ ነው ከማድቤቱ ማውቀው
ቅጠሉም ባገሬ ከዛፉ ላይ ሆኖ የሚወዛወዘው
ፍየል አይደለሁኝ ቅጠል ባፌ ይዤ የማመነዠከው
ምድጃም አይደለሁ ጭሱን ከአፌ በራፍ የማንቦለቡለው
መማሬ መልፋቴ ካልቀረ መድከሜ
ፍየል መሆን ሳይሆን ሰው መሆን ነው ህልሜ።
እናምልህ ጓዴ፡ ጓዴ ጉልበተኛው አትበለኝ እንቃም
የምኖረው እድሜ እንኳንስ ለመቃም ለመኖር አትበቃም
አስታውሳለሁኝ ያኔ...
ሀገር ማለት ላንተ ምንድነው ያልኩህ ለት
"ሀገር ማለትማ 'country'ማለት ናት የምንኖርባት''
ብለህ ስትመልስ ከአይምሮዬ አይጠፋም የቋንቋክም ለዛ
አልተጠራጠርኩም ሀገርህን ሸጠህ ጫት እንደምትገዛ።
ጉልቤው በጉልበትህ ትምህርትህ ተሳክቶ
አንደማይህ አውቃለሁ ይሄ ስብዕናህ ለኀላፊነት በቅቶ
ታድያ እንደለመድከው በዙሪያህ ያሉትን በጉልበትህ ገዝተህ
ስትኖር ይታየኛል በሀብት ተትረፍርፈህ
በየዋሀን እንባ አንተ ተደስተህ
ደግሞም ይታየኛል
ድሀው ገንዘብ አቶ ሳይበላ አንባሻ
በጀርባክ ተኝተህ ስትጠባ ሺሻ
ይታየኛል አዎ በአይኔ ድቅን ይላል
የሚደበደብ ህዝብ ጩሀት ይሰማኛል
የህፃን ልጆች እንባ ከሩቅ ይታየኛል
አዛውንቱ ቆሞ አንተን ይለምናል።
ከዚ ሀሉ መሀል
ያንተ የጭካኔ ሳቅ በጆሮዬ ይመጣል
ከምትቅምበት ቤት የሚወጣው እጣን በአፍንጫዬ ያልፋል
በምናቤ እያሰብኩ እኔኑ ያመኛል
ስለዚህም ጓዴ፡ጓዴ ጉልበተኛው አትበለኝ እንቃም
የምኖረው እድሜ እንኳንስ ለመቃም ለመኖር አትበቃም
ህዝብ እያለቀሰ ካንተ ቤት አልመጣም
ወገኔ ውሀ ጠምቶት እኔ ውስኪ አልጠጣም።
ይልቅ ባንተ ኑሮ በወደፊት ምናብ እኔው ከምታመም
በተስፋ ገስግሼ ወደ ነገዋ እኔ በሀሳቤ ልትመም
ብዙ በጎ አላማ ትልቅ ህልም አንግቤ
የህዝብ ኀላፊነት አደራን ደርቤ
ልታገል መጣሁኝ ያንተ አይነቱን ጉልቤ
ሀገሬና ህዝቤን ማገልገል ተርቤ
አይደለም ጉልቤነት ኩራትና ልብሴ
ለፍትህ መሞት ነው የማንነት ውርሴ
የሀገሬን ችግር ሸክም ልቀበላት
የህዝቤን አደራ የተረከብኩ ሰአት
ልጅዋን ለማስተማር የምትጓጓ እናት
ዘመዴ መሆኗ መስፈርቷ አይሆንም
ልጅዋ እንዲማርላት
የተጎዳ ደሀ የእውነት ፈራጅ ያጣ
100ብር መያዙ አያሳስበውም ወደኔ ሲመጣ
የስራ ሀሳብ ይዘሽ ወደኔ ስትመጪ
በሀሳብሽ እንጂ በመልክሽ አይደለም ምትስተናገጂ፡፡
የሚደበደብ ህዝብ የሚያለቅስ ህፃን
እግዚኦታን ሚያሰማ የአዛውንት እርግማን
ዳግም ላይመለስ ከሀገሬ ምሎ
በኔ ጊዜ ይወጣል ከቀዬው ኮብልሎ
አንተ ግን
ለፈፀምከው ስህተት ላፈሰስከው እንባ
የፀፀት አለንጋ ቅጣት ነው ሚገባህ
እንዲህ ያለ አላማ ስላለኝ ትልቅ ህልም
እውቀትን ነው እንጂ እኔ ጫት አልቅምም
ስለዚህም ጓዴ አትበለኝ እንቃም
የምኖረው እድሜ እንኳንስ ለመቃም
ለመኖር አትበቃም።
(( ንፁህ ግርማ))
@getem0
@getem0
ጭሱም የእናቴ ነው ከማድቤቱ ማውቀው
ቅጠሉም ባገሬ ከዛፉ ላይ ሆኖ የሚወዛወዘው
ፍየል አይደለሁኝ ቅጠል ባፌ ይዤ የማመነዠከው
ምድጃም አይደለሁ ጭሱን ከአፌ በራፍ የማንቦለቡለው
መማሬ መልፋቴ ካልቀረ መድከሜ
ፍየል መሆን ሳይሆን ሰው መሆን ነው ህልሜ።
እናምልህ ጓዴ፡ ጓዴ ጉልበተኛው አትበለኝ እንቃም
የምኖረው እድሜ እንኳንስ ለመቃም ለመኖር አትበቃም
አስታውሳለሁኝ ያኔ...
ሀገር ማለት ላንተ ምንድነው ያልኩህ ለት
"ሀገር ማለትማ 'country'ማለት ናት የምንኖርባት''
ብለህ ስትመልስ ከአይምሮዬ አይጠፋም የቋንቋክም ለዛ
አልተጠራጠርኩም ሀገርህን ሸጠህ ጫት እንደምትገዛ።
ጉልቤው በጉልበትህ ትምህርትህ ተሳክቶ
አንደማይህ አውቃለሁ ይሄ ስብዕናህ ለኀላፊነት በቅቶ
ታድያ እንደለመድከው በዙሪያህ ያሉትን በጉልበትህ ገዝተህ
ስትኖር ይታየኛል በሀብት ተትረፍርፈህ
በየዋሀን እንባ አንተ ተደስተህ
ደግሞም ይታየኛል
ድሀው ገንዘብ አቶ ሳይበላ አንባሻ
በጀርባክ ተኝተህ ስትጠባ ሺሻ
ይታየኛል አዎ በአይኔ ድቅን ይላል
የሚደበደብ ህዝብ ጩሀት ይሰማኛል
የህፃን ልጆች እንባ ከሩቅ ይታየኛል
አዛውንቱ ቆሞ አንተን ይለምናል።
ከዚ ሀሉ መሀል
ያንተ የጭካኔ ሳቅ በጆሮዬ ይመጣል
ከምትቅምበት ቤት የሚወጣው እጣን በአፍንጫዬ ያልፋል
በምናቤ እያሰብኩ እኔኑ ያመኛል
ስለዚህም ጓዴ፡ጓዴ ጉልበተኛው አትበለኝ እንቃም
የምኖረው እድሜ እንኳንስ ለመቃም ለመኖር አትበቃም
ህዝብ እያለቀሰ ካንተ ቤት አልመጣም
ወገኔ ውሀ ጠምቶት እኔ ውስኪ አልጠጣም።
ይልቅ ባንተ ኑሮ በወደፊት ምናብ እኔው ከምታመም
በተስፋ ገስግሼ ወደ ነገዋ እኔ በሀሳቤ ልትመም
ብዙ በጎ አላማ ትልቅ ህልም አንግቤ
የህዝብ ኀላፊነት አደራን ደርቤ
ልታገል መጣሁኝ ያንተ አይነቱን ጉልቤ
ሀገሬና ህዝቤን ማገልገል ተርቤ
አይደለም ጉልቤነት ኩራትና ልብሴ
ለፍትህ መሞት ነው የማንነት ውርሴ
የሀገሬን ችግር ሸክም ልቀበላት
የህዝቤን አደራ የተረከብኩ ሰአት
ልጅዋን ለማስተማር የምትጓጓ እናት
ዘመዴ መሆኗ መስፈርቷ አይሆንም
ልጅዋ እንዲማርላት
የተጎዳ ደሀ የእውነት ፈራጅ ያጣ
100ብር መያዙ አያሳስበውም ወደኔ ሲመጣ
የስራ ሀሳብ ይዘሽ ወደኔ ስትመጪ
በሀሳብሽ እንጂ በመልክሽ አይደለም ምትስተናገጂ፡፡
የሚደበደብ ህዝብ የሚያለቅስ ህፃን
እግዚኦታን ሚያሰማ የአዛውንት እርግማን
ዳግም ላይመለስ ከሀገሬ ምሎ
በኔ ጊዜ ይወጣል ከቀዬው ኮብልሎ
አንተ ግን
ለፈፀምከው ስህተት ላፈሰስከው እንባ
የፀፀት አለንጋ ቅጣት ነው ሚገባህ
እንዲህ ያለ አላማ ስላለኝ ትልቅ ህልም
እውቀትን ነው እንጂ እኔ ጫት አልቅምም
ስለዚህም ጓዴ አትበለኝ እንቃም
የምኖረው እድሜ እንኳንስ ለመቃም
ለመኖር አትበቃም።
(( ንፁህ ግርማ))
@getem0
@getem0
"ይድረስ ለሄዋኔ "
ኑሮ እንዴት ይዞሻል እንዴት ነሽ ሄዋኔ
ይመስገን ደህና ነኝ አታስቢ ለእኔ
..................ይልቅስ ሄዋኔ
ወጣትነት አልፎ እርጅና ሳይመጣ
ከቻልሽ ነይልኝ ፡ካልሆነ እኔ ልምጣ
ግን ልትመጪ ከሆነ ፡መንገድ
ሳትጀምሪ
ማንነቴን ሰምተሽ ፡ከቀረሽም ቅሪ
ወደ እኔ ለመምጣት ሀሳብ ስትሰንቂ
የሞላ ቪላ ቤት ፎቅ እንዳትጠብቂ
ጥሪትም የለኝም ወርሼ የማወርስሽ
ቤት ማጀቴ ፡ባዶ ጮማ እንዳላጎርስሽ
ልብሴም ድሪቶ ነው ፡ፊቴም ውበት
የለው
ልቤም የእንባ ናዳ ክህደት ፡ያቆሰለው
ግን ይህን ሁሉ አይተሽ መፀየፍ
ሳይረታሽ
ንፁህ ፍቅሬ ገዝቶሽ ፡ወደ እኔ
ከመጣሽ
እ.ጠ.ብ.ቅ.ሻ.ለ.ሁ........በደስታ
ፈንጥዤ
በሰባራው ልቤ ንፁህ ፍቅርን ይዤ፡፡
@getem0
@getem0
ኑሮ እንዴት ይዞሻል እንዴት ነሽ ሄዋኔ
ይመስገን ደህና ነኝ አታስቢ ለእኔ
..................ይልቅስ ሄዋኔ
ወጣትነት አልፎ እርጅና ሳይመጣ
ከቻልሽ ነይልኝ ፡ካልሆነ እኔ ልምጣ
ግን ልትመጪ ከሆነ ፡መንገድ
ሳትጀምሪ
ማንነቴን ሰምተሽ ፡ከቀረሽም ቅሪ
ወደ እኔ ለመምጣት ሀሳብ ስትሰንቂ
የሞላ ቪላ ቤት ፎቅ እንዳትጠብቂ
ጥሪትም የለኝም ወርሼ የማወርስሽ
ቤት ማጀቴ ፡ባዶ ጮማ እንዳላጎርስሽ
ልብሴም ድሪቶ ነው ፡ፊቴም ውበት
የለው
ልቤም የእንባ ናዳ ክህደት ፡ያቆሰለው
ግን ይህን ሁሉ አይተሽ መፀየፍ
ሳይረታሽ
ንፁህ ፍቅሬ ገዝቶሽ ፡ወደ እኔ
ከመጣሽ
እ.ጠ.ብ.ቅ.ሻ.ለ.ሁ........በደስታ
ፈንጥዤ
በሰባራው ልቤ ንፁህ ፍቅርን ይዤ፡፡
@getem0
@getem0
+++++
ካንተ ቤት...
ቋንጣ ተሰቀለ
ሻኛ ተቆረጠ፣ ወይን እየተጠጣ፣
...
ያ’ዳም ዘር ወንድምህ
ያለ ሁዳዴ ፆም በ’ራብ የ’ተቀጣ፡፡
ይገርማል
አንተ ማለትኮ...
አንተ ማለት ጠጋብ ያለልክ ሠልቃጭ፣
እሱ ማለት ደግሞ...
እሱ ማለት ሚስኪን ካንተ ቤት ቀላዋጭ፣
...
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
...
በተራበች ነፍሱ
...........................ቀልቡ እየዋለለ፣
ድህነት ሰቅዞት
...........................ሳይበላ እየዋለ፣
ሂወት ጨክናበት
ቆዳ ምላሽ ሊያገኝ
..........በጌቶቹ ቅዬ ፍሪዳ እየጣለ፣
ለሁዳዴው ፆም ፍቺ
በግ ሲጠባ ያድራል ቢለዋ እየሳለ፣
...
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
...
ትቀምሰው ያጣች ነፍስ ቁራሽ ንጣይ ቅምሻ፣
በጣር ሲቃ ታንቃ ስታጣ መድረሻ፣
ፍርድ አጥተን ከሰማይ የ'ግዜር እጅ መንሻ፣
ሠው የሠው አገልጋይ ሠው የመንደር ውሻ፣
ሲ ጎ መ ጅ ይኖራል - በ በ ሊ ቶ ች ጉርሻ፡፡
@getem0
@getem0
ካንተ ቤት...
ቋንጣ ተሰቀለ
ሻኛ ተቆረጠ፣ ወይን እየተጠጣ፣
...
ያ’ዳም ዘር ወንድምህ
ያለ ሁዳዴ ፆም በ’ራብ የ’ተቀጣ፡፡
ይገርማል
አንተ ማለትኮ...
አንተ ማለት ጠጋብ ያለልክ ሠልቃጭ፣
እሱ ማለት ደግሞ...
እሱ ማለት ሚስኪን ካንተ ቤት ቀላዋጭ፣
...
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
...
በተራበች ነፍሱ
...........................ቀልቡ እየዋለለ፣
ድህነት ሰቅዞት
...........................ሳይበላ እየዋለ፣
ሂወት ጨክናበት
ቆዳ ምላሽ ሊያገኝ
..........በጌቶቹ ቅዬ ፍሪዳ እየጣለ፣
ለሁዳዴው ፆም ፍቺ
በግ ሲጠባ ያድራል ቢለዋ እየሳለ፣
...
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
...
ትቀምሰው ያጣች ነፍስ ቁራሽ ንጣይ ቅምሻ፣
በጣር ሲቃ ታንቃ ስታጣ መድረሻ፣
ፍርድ አጥተን ከሰማይ የ'ግዜር እጅ መንሻ፣
ሠው የሠው አገልጋይ ሠው የመንደር ውሻ፣
ሲ ጎ መ ጅ ይኖራል - በ በ ሊ ቶ ች ጉርሻ፡፡
@getem0
@getem0
በዚህ ጊዜ
ያለ ጥርጣሬ አብረን እንድንሆን እያመነሽ ልቤ የለመድነው ቀርቶ
አየሁ ንፁህ ፍቅርሽ ጠፍቶ እኔ አላውቅም
ዛሬ ያቆራረጠን ምን ተገኝቶ ነው
ያንቺ የኔ የኔ ያንቺ እኮ ነው
እንድንከፋፈል አሰብሽ ምነው
ሰላም ነበር የሚሻለው
ምን ይሆን መሃላችን ጣልቃ እየገባ
የሚያረባብሸን ሚያጋጨን በየ ዕለት ሰርሥሮ እያደባ
መደራደር ሳለ መደላደል
መተራረም መገላገል
እንድንተሳሠብ ይገባ ነበር
ያወራነው መና እንዳይቀር
ለምን ፍቅራችን ላላ
ምን አለ ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ
እንቺ ትብሽ አንተ እየተባባልን ነገር አበላሽተን ኋላ እንዳይፀፅተን ተዳፍረን እየተፎካከርን እኔ አላምንም
እየተቀናናን በገዛ እጃችን
አላምር አለ ሁኔታችን
ተነጣጥለን ልንቀር ለማን ብለን ?
በዚህ ዘመን ምን ሞኝ ነን ?
አንገት የሚያስደፋ የሚያሳፍረንን ድርጊት እየፈፀምን ዋጋ እንዳናሳጣው ክብራችን በሰዎች አፍ ገብተን እኔ አላምንም
መከባበር ሳለ መመካከር
በሁለታችን ሁሉ እንዲቀር
እንድንጠባበቅ ይገባ ነበር
እቅዳችን እንዲሰምር
እንዴት ፍቅራችን ላላ
ምን ነበር ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ መቀየጣችን አትዘንጊ ተዋደን
አሄ እያልን በየፊናችን
አሄ አጠፋፋን መራራቃችን
አሄ ተለያይተን እንዳንቀር
አሄ ፀብ ትተን እንኑር ተይ አንቃቃር
እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን
እንደ ድር እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው እንደውም እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድር እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው..........ትዕግሥት ያስከብራል !!!
አዲስ ሥራዬን ወደ እናንተ ለማድረስ ዝግጅቴን እያጠናቀኩ ነው ። የሰራዋቸውን ሥራዎች የዋህ ፣ ያም ሆነ ይህ ፣ ብር አምባር እና የሌለ ነው እንዲሁም በኦዲዮ ያሉ ሥራዎቼን ስለወደዳችሁልኝ እያ
@getem0
ያለ ጥርጣሬ አብረን እንድንሆን እያመነሽ ልቤ የለመድነው ቀርቶ
አየሁ ንፁህ ፍቅርሽ ጠፍቶ እኔ አላውቅም
ዛሬ ያቆራረጠን ምን ተገኝቶ ነው
ያንቺ የኔ የኔ ያንቺ እኮ ነው
እንድንከፋፈል አሰብሽ ምነው
ሰላም ነበር የሚሻለው
ምን ይሆን መሃላችን ጣልቃ እየገባ
የሚያረባብሸን ሚያጋጨን በየ ዕለት ሰርሥሮ እያደባ
መደራደር ሳለ መደላደል
መተራረም መገላገል
እንድንተሳሠብ ይገባ ነበር
ያወራነው መና እንዳይቀር
ለምን ፍቅራችን ላላ
ምን አለ ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ
እንቺ ትብሽ አንተ እየተባባልን ነገር አበላሽተን ኋላ እንዳይፀፅተን ተዳፍረን እየተፎካከርን እኔ አላምንም
እየተቀናናን በገዛ እጃችን
አላምር አለ ሁኔታችን
ተነጣጥለን ልንቀር ለማን ብለን ?
በዚህ ዘመን ምን ሞኝ ነን ?
አንገት የሚያስደፋ የሚያሳፍረንን ድርጊት እየፈፀምን ዋጋ እንዳናሳጣው ክብራችን በሰዎች አፍ ገብተን እኔ አላምንም
መከባበር ሳለ መመካከር
በሁለታችን ሁሉ እንዲቀር
እንድንጠባበቅ ይገባ ነበር
እቅዳችን እንዲሰምር
እንዴት ፍቅራችን ላላ
ምን ነበር ባንጣላ
እኛው እርስ በእርሳችን
ተኳርፈን ምን አመጣን
ከጠላት አይን ያውጣን
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ ነው
ፍቅር መሆን ያለብን
እንደድሮው
በዚህ ጊዜ (2x)
በዚህ ጊዜ እንደሁ
ፍቅር መሆን አለብን
እንደድሮው !!!
አንተዛዘንም ወይ ሃኤ
አንቀራረብም ወይ ኦዎ ኦኦዎ
አንጠያየቅም ወይ
አንፈላለግም ወይ መቀየጣችን አትዘንጊ ተዋደን
አሄ እያልን በየፊናችን
አሄ አጠፋፋን መራራቃችን
አሄ ተለያይተን እንዳንቀር
አሄ ፀብ ትተን እንኑር ተይ አንቃቃር
እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን
እንደ ድር እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው እንደውም እንደ ድሮው ነው ፍቅር መሆን ያለብን እንደ ድሮው ልክ እንደ ድር እንደ ድሮው ፍቅር መሆን አለብን እንደ ድሮው..........ትዕግሥት ያስከብራል !!!
አዲስ ሥራዬን ወደ እናንተ ለማድረስ ዝግጅቴን እያጠናቀኩ ነው ። የሰራዋቸውን ሥራዎች የዋህ ፣ ያም ሆነ ይህ ፣ ብር አምባር እና የሌለ ነው እንዲሁም በኦዲዮ ያሉ ሥራዎቼን ስለወደዳችሁልኝ እያ
@getem0
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
.
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን ትዝታ እንጂ
ዉስጡ ህይወት የለም እያልሽ ላገሩ
ታወሪያለሽ አሉ
.
.
እኔ ግን ልንገርሽ
የሁለታችን ፍቅር
ምን እንደሚመስል. . .
እንዴት እንደነበር
በሶስት ምስክር
1
አሁን በቀደም ለት
የሆነ ቦታ ላይ
ድምጻችን ከፍ አርገን የሳቅንበት ቦታ
ፒያሳ አደባባይ
ድንገት
በቀደም ለት
በዛ ቦታ ስሄድ
ከሰባት ወር በፊት
ስቀሽ የነበረዉ
ያንቺ ሳቅ ተሰማኝ
መራመድ አቃተኝ
የሚገርምሽ ነገር
ያለፈ ነዉ ያልሺዉ
ትዝታ ነዉ ያልሽዉ
ፍቅርሽና ሳቅሽ
ከሰባት ወር ኋላ እንደ ወንዝ ፍሳሽ
ይሰማል ልንገርሽ
.
ታዲያ ለምንድን ነዉ
የወንዝ ዉሀ ሳቅሽ
ያለፈ ትዝታ ምናምን ነዉ ብሎ
ማንም ተራ ዘፋኝ የሚሸነግልሽ
ይልቅ እኔን ስሚኝ
.
ወደየትም ሳይሆን
ወዴትም ተመለሽ
የትም ሳትደርሺ
ጊዜን እንዳቆምነዉ
እንኳን ጊዜ ቀርቶ ሰዓት እንዳልሄደ
ደቂቃ እንዳልሄደ
አስረጂ ሊሆንሽ
ምስክር ሊሆንሽ
ከምንም አቅጣጫ. . . የትም ሳትመለሽ
አደባባይ መሀል
ከቡና ጠረን ጋር
እንደወንዝ የሚፈስ
ሳቅሽን ትሰሚያለሽ
.
2
ትዝ ይልሽ እንደሆን
ካንቺ መኖሪያ ቤት
የመጣሁኝ ጊዜ
የመራራቅ ናፍቆት
አስክሮን ቸኩለን
ሰማያት ለመዝለቅ
ከመሬት ላይ ወድቀን
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ከሴት ወዝሽ ጋራ
የጡትሽ ስር ሽቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ምወደዉን ሸሚዝ
ለመልበስ እርም አልኩኝ
ለብሼዉ እንዳልሄድ
ከበደኝ ጨነቀኝ
ያንቺን ጠረን ማጠብ. . .
ነፍስ የማጥፋት ያህል
ሀጥያት መስሎ ታየኝ
የሚገርምሽ ነገር
እስከ ዛሬ ድረስ
በመስኮቱ ዘልቆ. . .በበሬ
የሚወጣዉ የማለዳዉ ነፋስ
በሽቶሽ ጠረን ነዉ መንደሩን የሚብስ
.
3
ታስታዉሽ እንደሆን
የሆነ ቅዳሜ
የሆነ ዉብ ሆቴል
ደግሞም አትረሺዉም. . .ፍጻሜ ምሳ ነዉ
ይኼ እንኳን ትዝ ይላል
እና. . .
እኔና አንቺ ብቻ
የተቀመጥንበት ወንበር ጠረጴዛዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ. . .
እዛዉ ቤት ዳግመኛ ተመልሼ ባየዉ
የሚገርምሽ ነገር
ጻፊዉን ባላዉቅም
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
የሚል ጽሁፍ ሰቅለዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ
አንድ ለብቻዬ ካንድ አንቺ ናፍቆት ጋር
ነበር ለምትይዉ ለሁለታችን ፍቅር
ምስክር ሊሆኑን
ያኔ ሁለታችን የጠጣነዉ ወይን
ከወይንም. . . Two Ocean
እኔ የጨለጥኩት
አንቺ ያጋመስሽዉ
እኛ ያስተረፍነዉ
እስከዛሬ ድረስ
ያተረፍነዉ ማዕድ. . .
ጠርሙስና ጽዋዉ
በክብር ተቀምጧል
ማንም ሳያነሳዉ. . .ያኔ እንደነበረዉ
ታዲያ ምን ማለት ነዉ?
.
.
ፒያሳ አደባባይ
የወንዝ ዉሃ ሳቅሽ
ከቡና ጠረን ጋ
ከኔ መኖሪያ ቤት. . .
የምወደዉ ሸሚዝ ላይ
የሽቶ መአዛሽ
ከሴት ላቦትሽ ጋር
ደግሞም
እዚያ ዉብ ሆቴል ስር
ያስተረፍነዉ . . .
ማዕድ ጠርሙስና ጽዋ
አንጀት ከሚበላ
ከቆንጆ ጥቅስ ጋር
‘’#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር::’’
.
ነበርን እስካሁን
በመሆን እያየሽ
ሳቅሽ ፈሶ ሳያልቅ
ከምወደዉ ሸሚዝ
የሽቶ መዓዛሽ ዉብ ጠረኑ ሳይለቅ
ማዕድ ሳይነሳ ጽዋዉ ሳይታጠብ
ሦሥቱን ምስክሮች በዓይንሽ ፊት እያየሽ
ታዲያ ለምንድን ነዉ?
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን_ትዝታ_እንጂ .....
ዉስጡ_ህይወት_የለም
ብለሽ ለመንደሩ
ላገሩ ማዉራትሽ
እዉነት ለምንድን ነዉ?
.
.
.
@getem0
.
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን ትዝታ እንጂ
ዉስጡ ህይወት የለም እያልሽ ላገሩ
ታወሪያለሽ አሉ
.
.
እኔ ግን ልንገርሽ
የሁለታችን ፍቅር
ምን እንደሚመስል. . .
እንዴት እንደነበር
በሶስት ምስክር
1
አሁን በቀደም ለት
የሆነ ቦታ ላይ
ድምጻችን ከፍ አርገን የሳቅንበት ቦታ
ፒያሳ አደባባይ
ድንገት
በቀደም ለት
በዛ ቦታ ስሄድ
ከሰባት ወር በፊት
ስቀሽ የነበረዉ
ያንቺ ሳቅ ተሰማኝ
መራመድ አቃተኝ
የሚገርምሽ ነገር
ያለፈ ነዉ ያልሺዉ
ትዝታ ነዉ ያልሽዉ
ፍቅርሽና ሳቅሽ
ከሰባት ወር ኋላ እንደ ወንዝ ፍሳሽ
ይሰማል ልንገርሽ
.
ታዲያ ለምንድን ነዉ
የወንዝ ዉሀ ሳቅሽ
ያለፈ ትዝታ ምናምን ነዉ ብሎ
ማንም ተራ ዘፋኝ የሚሸነግልሽ
ይልቅ እኔን ስሚኝ
.
ወደየትም ሳይሆን
ወዴትም ተመለሽ
የትም ሳትደርሺ
ጊዜን እንዳቆምነዉ
እንኳን ጊዜ ቀርቶ ሰዓት እንዳልሄደ
ደቂቃ እንዳልሄደ
አስረጂ ሊሆንሽ
ምስክር ሊሆንሽ
ከምንም አቅጣጫ. . . የትም ሳትመለሽ
አደባባይ መሀል
ከቡና ጠረን ጋር
እንደወንዝ የሚፈስ
ሳቅሽን ትሰሚያለሽ
.
2
ትዝ ይልሽ እንደሆን
ካንቺ መኖሪያ ቤት
የመጣሁኝ ጊዜ
የመራራቅ ናፍቆት
አስክሮን ቸኩለን
ሰማያት ለመዝለቅ
ከመሬት ላይ ወድቀን
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ከሴት ወዝሽ ጋራ
የጡትሽ ስር ሽቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ምወደዉን ሸሚዝ
ለመልበስ እርም አልኩኝ
ለብሼዉ እንዳልሄድ
ከበደኝ ጨነቀኝ
ያንቺን ጠረን ማጠብ. . .
ነፍስ የማጥፋት ያህል
ሀጥያት መስሎ ታየኝ
የሚገርምሽ ነገር
እስከ ዛሬ ድረስ
በመስኮቱ ዘልቆ. . .በበሬ
የሚወጣዉ የማለዳዉ ነፋስ
በሽቶሽ ጠረን ነዉ መንደሩን የሚብስ
.
3
ታስታዉሽ እንደሆን
የሆነ ቅዳሜ
የሆነ ዉብ ሆቴል
ደግሞም አትረሺዉም. . .ፍጻሜ ምሳ ነዉ
ይኼ እንኳን ትዝ ይላል
እና. . .
እኔና አንቺ ብቻ
የተቀመጥንበት ወንበር ጠረጴዛዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ. . .
እዛዉ ቤት ዳግመኛ ተመልሼ ባየዉ
የሚገርምሽ ነገር
ጻፊዉን ባላዉቅም
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
የሚል ጽሁፍ ሰቅለዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ
አንድ ለብቻዬ ካንድ አንቺ ናፍቆት ጋር
ነበር ለምትይዉ ለሁለታችን ፍቅር
ምስክር ሊሆኑን
ያኔ ሁለታችን የጠጣነዉ ወይን
ከወይንም. . . Two Ocean
እኔ የጨለጥኩት
አንቺ ያጋመስሽዉ
እኛ ያስተረፍነዉ
እስከዛሬ ድረስ
ያተረፍነዉ ማዕድ. . .
ጠርሙስና ጽዋዉ
በክብር ተቀምጧል
ማንም ሳያነሳዉ. . .ያኔ እንደነበረዉ
ታዲያ ምን ማለት ነዉ?
.
.
ፒያሳ አደባባይ
የወንዝ ዉሃ ሳቅሽ
ከቡና ጠረን ጋ
ከኔ መኖሪያ ቤት. . .
የምወደዉ ሸሚዝ ላይ
የሽቶ መአዛሽ
ከሴት ላቦትሽ ጋር
ደግሞም
እዚያ ዉብ ሆቴል ስር
ያስተረፍነዉ . . .
ማዕድ ጠርሙስና ጽዋ
አንጀት ከሚበላ
ከቆንጆ ጥቅስ ጋር
‘’#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር::’’
.
ነበርን እስካሁን
በመሆን እያየሽ
ሳቅሽ ፈሶ ሳያልቅ
ከምወደዉ ሸሚዝ
የሽቶ መዓዛሽ ዉብ ጠረኑ ሳይለቅ
ማዕድ ሳይነሳ ጽዋዉ ሳይታጠብ
ሦሥቱን ምስክሮች በዓይንሽ ፊት እያየሽ
ታዲያ ለምንድን ነዉ?
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን_ትዝታ_እንጂ .....
ዉስጡ_ህይወት_የለም
ብለሽ ለመንደሩ
ላገሩ ማዉራትሽ
እዉነት ለምንድን ነዉ?
.
.
.
@getem0