G-Tutorialclass
811 subscribers
2.23K photos
29 videos
1.43K files
356 links
Impossible is possible with learning & reading.
Download Telegram
Forwarded from ETHIO-MEREJA®
ሰበርዜና!

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ውቅሮን፣ ሀውዜን፣ አልነጃሺ፣ አዲቀየህ እና ማይመሳኖን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አሳውቋል።

በመቀሌ ያለውን የወንጀለኛ ቡድን የመቆጣጠር ተግባር በማጠቃላይ ምዕራፍነት የተያዘ ሲሆን ሰራዊቱ ግዳጁን በምን አኳኋን መፈጸም እንዳለበት በቂ ዝግጅት አድርጎ የወንጀለኛውን ቡድን በቁጥጥር ስር ለማዋል መዘጋጀቱን ተገልጿል።

የጁንታው ቡድንም በፕሮፓጋንዳ ጭምር እያፈገፈገ መሄዱ ሽንፈቱን እያረጋገጠ መሆኑን አመልክተዋል። በማጠቃለያው ምዕራፍ መቀሌን ለመቆጣጠር የሚያስሉ ስትራቴጂክ ቦታዎች መያዙን አስታወቀ። በራያ በኩልም አድቀይህ ፣ አዲመሳኖን እና ሂዋናን ከታጣቂ ሃይሉ ነፃ ማድረጉን ገልጸዋል። በጉላን በኩል መንገድ ለመዝጋት ቢሞክርም እንዳልተሳካለትና ወደ ኋላ ማፈግፈጉን ተናግረዋል።

አሁን ላይ መቀሌ ብቻ መቅረቱን የገለጹት ሌተናል ጀነራል ሀሰን በጥቂት ቀናት ወስጥ ተጠናቆ ጁንታው ለሀግ እነደሚቀርብ አረጋግጠዋል። የጁንታው ሃይል በራያ በኩል ያለ የሌለ ሃይሉን በመጠቀም የሰራዊቱን ጥቃት ለመቋቋም ቢሞክርም በመመታቱ ለመልቀቅ ተገዷል ነው ያሉት። የህወሃት ጁንታ ሽንፈቱን እያረጋገጠ በመምጣቱ በሀሰት ወሬ ላይ ተጠምዶ ህዝብን በማደናገር ላይ ነው ብለዋል። ዘገባው የኢዜአ ነው፡፡
⊰━━━━━━━━━━━━⊰
T.me/ethio_mereja
T.me/ethio_merejabot
⊰━━━━━━━━━━━━⊰
Forwarded from About education
አየር ኃይል የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለተለያየ የስራ ጉዳዮች በትግራይ ክልል የሚገኙ ሰራተኞችን ወደየአካባቢያቸው የማመላለስ ስራ መጀመሩን አሳወቀ።

አየር ኃይል ወደመጡበት አካባቢያቸው እየመለሳቸው ከሚገኙት ውስጥ ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ የሄዱ ፣ በአካባቢው የደረሱና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች ይገኙበታል።

አየር ኃይል ከሽሬ አውሮፕላን ማረፊያ ነው ተማሪዎችን የማመላለስ ስራ የጀመረው።

ተማሪዎቹ የመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ሲያደርግላቸው እንደነበር ተናግረዋል።

ሰራዊቱ ላለፉት ቀናት ለተማሪዎች ምግብና መጠጥ ፣ መጠለያ ሲያቀርብ እንደነበር ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ገልፀዋል።

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሄዱ ተማሪዎችን ወደየቤተሰቦቻቸው የመመለሱን ስራ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

@NEAEA_nea
Forwarded from About education
#Eritrea

ከ45 ደቂቃዎች በፊት ኤርትራ ላይ የሮኬት ጥቃት መሰንዘሩን የሚገልፁ ሪፖርቶች ወጥተዋል።

የአስመራ ከተማ ነዋሪዎችም ዛሬ ምሽቱን የፍንዳታ ድምፅ እንደሰሙ አሳውቀዋል።

ከአስመራ ውጭም በደቂመኸር ፣ በአዲሃሎ አካባቢ ጥቃት ሳይሰነዘር እንዳልቀረ ተገልጿል።

እስካሁን በጥቃቱ ስለደረሰ ጉዳት የታወቀ ነገር የለም።


@NEAEA_nea
በኦሮሚያ የ8ኛ ክፍል ፈተና ከኅዳር 30 እስከ ታኅሣሥ 2 እንደሚሰጥ ተገለጸ❗️

በክልል ደረጃ የሚሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና በኦሮሚያ ከኅዳር 30 እስከ ታኅሣሥ 2 የሚሰጥ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ።

በክልሉ ከመዋዕለ ሕፃናት ውጪ ያለው የመማር ማስተማር ሂደት ከመጪው ማክሰኞ አንስቶ እንደሚጀምርም ተገልጿል።

የመዋዕለ ሕፃናት ትምህርት መጀመሪያ ጊዜ ለሁለት ሳምንታት መራዘሙ ነው የተገለጸው።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
Forwarded from ETHIO-MEREJA®
ሰበር ዜና!

የህወሀት ቡድን በርካታ ሮኬቶችን ወደ ኤርትራ ከተሞች ማስወንጨፉን ኤርትራ ፕሬስ ዘገቧል።

ኤርትራ ፕረስ በአስመራ የወደቁ ሮኬቶች በተጨናነቁ የመኖሪያ መንደር አቅራቢያ ባለ አቅራቢያ እንደወደቁ ማረጋገጥ ችሏል። ይሁን እንጂ በሰው ላይ የደረሰ ምንም ጉዳት የለም ብሏል። ከአስመራ ውጭም በደቂመኸር ፣ በአዲሃሎ አካባቢ ጥቃት ሳይሰነዘር እንዳልቀረ ተገልጿል። ተጨማሪ መረጃ ካገኘን የምናቀርብ ይሆናል። (ኢትዮ-መረጃ)

⊰━━━━━━━━━━━━⊰
T.me/ethio_mereja
T.me/ethio_merejabot
⊰━━━━━━━━━━━━⊰
Forwarded from ETHIO-MEREJA®
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🎬VIDEO : ሰራዊቱ መቐለን እና የወንጀለኛው ጁንታ ቡድን አባላትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስትራቴጂክ ቦታዎችን ስለመያዙ ከሀገር መከላከያ ዛሬ ምሽት የተሰጠውን መግለጫ በቪዲዮ ይመልከቱ! (ኢትዮመረጃ)

T.me/ethio_mereja
T.me/ethio_merejabot
ድምፂ ወያነ ኢንተርናሽናል (DW International) እና ትግራይ ቴሌቪዥን (Tigray TV) ስርጭታቸው ተቋርጧል‼️

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ዛሬም የኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ በሮኬት ተመታለች‼️

ከምሽቱ አራት ሰዓት አከባቢ ላይ አስመራ በሮኬት መመቷቷን ከኤርትሪያ ፕረስ የፌስቡክ ገፅ ተመልክተናል።
©ኤርትሪያ ፕረስ

@Esat_tv1
@Esat_tv1
Forwarded from About education
የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ለነበሩ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ ተገለጸ
***************************
በ2012 ዓ.ም ተመራቂ የነበሩ ተማሪዎች ከነገ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሌሎች ቀሪ ተማሪዎች እንዲገቡ እና በዚህ የትምህርት ዘመን የሚጠበቅባቸውን ሦስት የትምህርት ሴሜስቴር እንዲያጠናቅቁ በቂ ድጋፍ እና ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል ሲል ገልጿል።

ተማራቂ ተማሪዎች በቀሪዎቹ አጭር ወራት ውስጥ ያልተጠናቀቁ የትምህርት እና ሥልጠና ተግባራትን በተቻለ ቅልጥፍና እና ዝግጁነት በማጠናቀቅ ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም እንዲትቀላቀሉ እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ አሳስቧል።

ሚኒስቴሌሎች በ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን ሙሉ ዓመቱን በተቋማት ቆይታ የሚደርጉት ተማሪዎች በሙሉ፣ ትምህርታቸውን በአግባቡ እየተማሩ ለአገራችን እና ለሕዝባችን አንድነት እና ኅብረት እንዲሁም ብልጽግና ጉዞ ፋይዳ ያላቸው ሰብአዊ እና ማኅበራዊ በጎ አድራጎት ተግባራት እና አገልግሎቶች በንቃት በመሳተፍ ወገንተኝነታቸውን እንዲገልጹ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አድርጓል።

@NEAEA_nea
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ይሰጣሉ‼️

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እንደሚሰጡ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ ህዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚገኘው መሰብሰቢያ አደራሽ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል፡፡

አጀንዳዎቹም
1. የም/ቤቱን 6ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣
2. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን መልስ ማዳመጥ እንደሆነ ምክር ቤቱ አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ለነበሩ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ ተገለጸ‼️

በ2012 ዓ.ም ተመራቂ የነበሩ ተማሪዎች ከነገ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሌሎች ቀሪ ተማሪዎች እንዲገቡ እና በዚህ የትምህርት ዘመን የሚጠበቅባቸውን ሦስት የትምህርት ሴሜስቴር እንዲያጠናቅቁ በቂ ድጋፍ እና ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል ሲል ገልጿል።

ተማራቂ ተማሪዎች በቀሪዎቹ አጭር ወራት ውስጥ ያልተጠናቀቁ የትምህርት እና ሥልጠና ተግባራትን በተቻለ ቅልጥፍና እና ዝግጁነት በማጠናቀቅ ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም እንዲትቀላቀሉ እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ አሳስቧል።

በ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን ሙሉ ዓመቱን በተቋማት ቆይታ የሚደርጉት ተማሪዎች በሙሉ፣ ትምህርታቸውን በአግባቡ እየተማሩ ለአገራችን እና ለሕዝባችን አንድነት እና ኅብረት እንዲሁም ብልጽግና ጉዞ ፋይዳ ያላቸው ሰብአዊ እና ማኅበራዊ በጎ አድራጎት ተግባራት እና አገልግሎቶች በንቃት በመሳተፍ ወገንተኝነታቸውን እንዲገልጹ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አድርጓል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ሦስተኛው ምዕራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መገባቱን ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ገለጹ፡፡‼️

“ብንማረክ እንኳን በእነርሱ አንማረክም፤ እኛን የሚማርከን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” ያሉት የራያ ግንባር የጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ወቅታዊ የህግ ማስከበር ሥራን በተመለከተ በትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን ተራሮች ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸው ሦስተኛው ምእራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መሸጋገራቸውን ተናግረዋል፡፡
የጁንታው ርዝራዦች የጦር መሪዎችን ማርከናል እያሉ የሚነዙት የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ስለ ጦርነት አውድ ያላቸው እውቀት አናሳነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አንድን የጦር አዛዥ ለመማረክ ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት እንደሚጠይቅ በማብራራት፤ የትህነግ ጁንታ ቡድን ሀይል ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት ቁመናም እንደሌለው አይተናል ብለዋል ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ፡፡ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ዘመቻውን አስመልክቶ እና በቀጣይ ሁኔታ ላይ ከጄኔራል አበባው ታደሰ ጋር በመቀሌ ከተማ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
Channel name was changed to «ወቅታዊ ሹክታዎች👀 👁👁»
Channel name was changed to «ወቅታዊ ሹክታዎች🎤 👁👁👂»
Channel name was changed to «ወቅታዊ ሹክታዎች🎤👁👁👂»
Forwarded from Fast promo
😭 ቴዲ አፍሮ በትግራይ ክልል እየተካሄደ የሚገኘው ጦርነት መቆም እንዳለበት እና የ ኤርትራ - ኢትዮጲያ እልቂት እንዳይደገም የሚያሳስብ አዲስ ልብ ሚሰብር ሙዚቃ ለቀቀ 😭 ይህን አሳዛኝ ሙዚቃ እኛጋ ያገኙታል 😭👇
https://t.me/joinchat/AAAAAFWIHCezSHLDF-_rgg
BREAKING G12‼️

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በትግራይ ክልል መረጋጋት እስኪፈጠር እና የኢንተርኔት አገልግሎት እስኪመለስ ይቆያል‼️

ሆኖም በሌሎች አካባቢዎች ያላችሁ ተማሪዎች ዝግጅታቹን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እናሳስባለን::
@Timhrtministers
@Timhrtministers
↘️ የዋቻሞ ዩንቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ከህዳር 21 እስከ ህዳር 23/13 ድረስ ወደ ግቢ እንድትገቡ ተብላቹሃል(ከግቢ ውጪ ላላቹህ)

ትምህርት ህዳር 24/13 ይጀመራል‼️

ማሳሰቢያ ፡ ተመራቂ ያልሆናቹህ ተማሪዎች በቅርቡ ስለምትጠሩ ቅድመ ዝግጅት አድርጉ ተብላቹሃል‼️
የመልስ ወረቀት አሞላልና አጠቋቆርን በሚመለከት ተማሪዎች ላደርጓቸዉ የሚገቡ ጥንቃቄዎች❗️

↘️ ተፈታኞች የመልስ ወረቀቱን ሲሞሉ የሚፈጽሙት ስህተት ያልተጠበቀ ውጤትን ለማግኘት መንስኤ ሊሆን ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

↘️ ተማሪዎች መልስ የሚሰጡበት የመልስ ወረቀት የሚነበበው በቅጽ ማንበቢያ መሣሪያ ወይም ማረሚያ መሣሪያ / 0pitical Mark Reader/ ነው፡፡ ስለዚህ ተፈታኞች በፈተና ወቅት መልስ ሲሠሩ ከሳጥኖቹ ሳያልፉ አድምቀው ማጥቆር አለባቸው፡፡

↘️በደማቁ ያልጠቆሩ ወይም በከፊል ብቻ የጠቆሩ የመልስ ወረቀቶች ለማረሚያ ማሽኑ ስለማይነበቡለት ጥራቱ በተጠበቀ እርሳስ ብቻ በመጠቀም አድምቆ ማጥቆር አስፈላጊ ነው፡፡ በብዕር ወይንም በእስክርብቶ የተጠቆረ የመልስ ወረቀት ማረሚያ ማሽኑ ስለማያነበው ከእርሳስ ውጪ መጠቀም አጥብቆ የተከለከለ ነው፡፡

↘️የተሻሸ፣የታጠፈ በእስክርብቶ የተጠቆረ ወይም መጻፍ የተከለከለባቸው ቦታዎች ላይ የተጻፈበት የመልስ ወረቀት የማረሚያ ማሽኑ ማረም ስለማይችል የተከለከለ ነው፡፡

የመልስ ወረቀት የሚያካትታቸው መረጃዎች

1. የእያንዳንዱ ተፈታኝ ስም፣ የአባት ስም እና የአያት ስም በጽሑፍ የሚገለጽበት ክፍት ቦታ /ከተፈቀደው ቦታ ውጭ አለመውጣት/

2. የትምህርት ቤቱ ስም የሚጻፍበት ክፍት ቦታ፣ የትምህርት ቤት ይዞታ

3. የምዝገባ ቁጥር ተሞልቶ ቁልቁል በትይዩ ያሉ ቁጥሮች የሚጠቆሩባቸው ቦታዎች

4. የትምህርት ቤቱ መለያ ቁጥር ተሞልቶ ቁልቁል በትይዩ ያሉ ቁጥሮች የሚጠቆሩባቸው ቦታዎች

5. በእለቱ የሚወሰድ የትምህርት አይነቶች መጥቆር አለባቸው

6. ለእያንዳንዱ ጥያቄ በተፈታኝ የተመረጡ መልሶች የሚጠቆሩባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡

↘️ ከላይ የተጠቀሱት መረጀዎች በሙሉ ከመግቢያ ካርድ ጋር የሚወሰዱ ናቸው፡፡

ከዚህ ቻናል በተጨማሪ ወቅታዊ እና ትክክለኛ መረጃዎች ብቻ የሚለቀቅበትን የ #ልዩ_መረጃ ቻናል ይቀላቀሉ👇
@Timhrtministers
@Timhrtministers
295 ዜጎች ከሳዑዲ ዓረቢያ ተመለሱ‼️

295 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ የኢትዮጵያ መንግስትና የሳዑዲ ዓረቢያ መንግስት በትብብር መስራታቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ ከስደት ተመላሽ ዜጎች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1