G-Tutorialclass
813 subscribers
2.23K photos
29 videos
1.43K files
356 links
Impossible is possible with learning & reading.
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ይሰጣሉ‼️

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ነገ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እንደሚሰጡ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ ህዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚገኘው መሰብሰቢያ አደራሽ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ማካሄድ ይጀምራል፡፡

አጀንዳዎቹም
1. የም/ቤቱን 6ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣
2. የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን መልስ ማዳመጥ እንደሆነ ምክር ቤቱ አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ለነበሩ ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ ተገለጸ‼️

በ2012 ዓ.ም ተመራቂ የነበሩ ተማሪዎች ከነገ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ጥሪ እንደሚደረግ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሌሎች ቀሪ ተማሪዎች እንዲገቡ እና በዚህ የትምህርት ዘመን የሚጠበቅባቸውን ሦስት የትምህርት ሴሜስቴር እንዲያጠናቅቁ በቂ ድጋፍ እና ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል ሲል ገልጿል።

ተማራቂ ተማሪዎች በቀሪዎቹ አጭር ወራት ውስጥ ያልተጠናቀቁ የትምህርት እና ሥልጠና ተግባራትን በተቻለ ቅልጥፍና እና ዝግጁነት በማጠናቀቅ ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም እንዲትቀላቀሉ እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ አሳስቧል።

በ2013 ትምህርት እና ሥልጠና ዘመን ሙሉ ዓመቱን በተቋማት ቆይታ የሚደርጉት ተማሪዎች በሙሉ፣ ትምህርታቸውን በአግባቡ እየተማሩ ለአገራችን እና ለሕዝባችን አንድነት እና ኅብረት እንዲሁም ብልጽግና ጉዞ ፋይዳ ያላቸው ሰብአዊ እና ማኅበራዊ በጎ አድራጎት ተግባራት እና አገልግሎቶች በንቃት በመሳተፍ ወገንተኝነታቸውን እንዲገልጹ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አድርጓል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
ሦስተኛው ምዕራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መገባቱን ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ገለጹ፡፡‼️

“ብንማረክ እንኳን በእነርሱ አንማረክም፤ እኛን የሚማርከን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” ያሉት የራያ ግንባር የጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ ወቅታዊ የህግ ማስከበር ሥራን በተመለከተ በትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን ተራሮች ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸው ሦስተኛው ምእራፍ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ በድል መጠናቀቁን እና አሁን ላይ ወደ መልሶ ማደራጀት መሸጋገራቸውን ተናግረዋል፡፡
የጁንታው ርዝራዦች የጦር መሪዎችን ማርከናል እያሉ የሚነዙት የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ስለ ጦርነት አውድ ያላቸው እውቀት አናሳነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አንድን የጦር አዛዥ ለመማረክ ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት እንደሚጠይቅ በማብራራት፤ የትህነግ ጁንታ ቡድን ሀይል ሰራዊቱን ሰብሮ መግባት ቁመናም እንደሌለው አይተናል ብለዋል ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ፡፡ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ዘመቻውን አስመልክቶ እና በቀጣይ ሁኔታ ላይ ከጄኔራል አበባው ታደሰ ጋር በመቀሌ ከተማ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
Channel name was changed to «ወቅታዊ ሹክታዎች👀 👁👁»
Channel name was changed to «ወቅታዊ ሹክታዎች🎤 👁👁👂»
Channel name was changed to «ወቅታዊ ሹክታዎች🎤👁👁👂»
Forwarded from Fast promo
😭 ቴዲ አፍሮ በትግራይ ክልል እየተካሄደ የሚገኘው ጦርነት መቆም እንዳለበት እና የ ኤርትራ - ኢትዮጲያ እልቂት እንዳይደገም የሚያሳስብ አዲስ ልብ ሚሰብር ሙዚቃ ለቀቀ 😭 ይህን አሳዛኝ ሙዚቃ እኛጋ ያገኙታል 😭👇
https://t.me/joinchat/AAAAAFWIHCezSHLDF-_rgg
BREAKING G12‼️

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በትግራይ ክልል መረጋጋት እስኪፈጠር እና የኢንተርኔት አገልግሎት እስኪመለስ ይቆያል‼️

ሆኖም በሌሎች አካባቢዎች ያላችሁ ተማሪዎች ዝግጅታቹን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እናሳስባለን::
@Timhrtministers
@Timhrtministers
↘️ የዋቻሞ ዩንቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ከህዳር 21 እስከ ህዳር 23/13 ድረስ ወደ ግቢ እንድትገቡ ተብላቹሃል(ከግቢ ውጪ ላላቹህ)

ትምህርት ህዳር 24/13 ይጀመራል‼️

ማሳሰቢያ ፡ ተመራቂ ያልሆናቹህ ተማሪዎች በቅርቡ ስለምትጠሩ ቅድመ ዝግጅት አድርጉ ተብላቹሃል‼️
የመልስ ወረቀት አሞላልና አጠቋቆርን በሚመለከት ተማሪዎች ላደርጓቸዉ የሚገቡ ጥንቃቄዎች❗️

↘️ ተፈታኞች የመልስ ወረቀቱን ሲሞሉ የሚፈጽሙት ስህተት ያልተጠበቀ ውጤትን ለማግኘት መንስኤ ሊሆን ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

↘️ ተማሪዎች መልስ የሚሰጡበት የመልስ ወረቀት የሚነበበው በቅጽ ማንበቢያ መሣሪያ ወይም ማረሚያ መሣሪያ / 0pitical Mark Reader/ ነው፡፡ ስለዚህ ተፈታኞች በፈተና ወቅት መልስ ሲሠሩ ከሳጥኖቹ ሳያልፉ አድምቀው ማጥቆር አለባቸው፡፡

↘️በደማቁ ያልጠቆሩ ወይም በከፊል ብቻ የጠቆሩ የመልስ ወረቀቶች ለማረሚያ ማሽኑ ስለማይነበቡለት ጥራቱ በተጠበቀ እርሳስ ብቻ በመጠቀም አድምቆ ማጥቆር አስፈላጊ ነው፡፡ በብዕር ወይንም በእስክርብቶ የተጠቆረ የመልስ ወረቀት ማረሚያ ማሽኑ ስለማያነበው ከእርሳስ ውጪ መጠቀም አጥብቆ የተከለከለ ነው፡፡

↘️የተሻሸ፣የታጠፈ በእስክርብቶ የተጠቆረ ወይም መጻፍ የተከለከለባቸው ቦታዎች ላይ የተጻፈበት የመልስ ወረቀት የማረሚያ ማሽኑ ማረም ስለማይችል የተከለከለ ነው፡፡

የመልስ ወረቀት የሚያካትታቸው መረጃዎች

1. የእያንዳንዱ ተፈታኝ ስም፣ የአባት ስም እና የአያት ስም በጽሑፍ የሚገለጽበት ክፍት ቦታ /ከተፈቀደው ቦታ ውጭ አለመውጣት/

2. የትምህርት ቤቱ ስም የሚጻፍበት ክፍት ቦታ፣ የትምህርት ቤት ይዞታ

3. የምዝገባ ቁጥር ተሞልቶ ቁልቁል በትይዩ ያሉ ቁጥሮች የሚጠቆሩባቸው ቦታዎች

4. የትምህርት ቤቱ መለያ ቁጥር ተሞልቶ ቁልቁል በትይዩ ያሉ ቁጥሮች የሚጠቆሩባቸው ቦታዎች

5. በእለቱ የሚወሰድ የትምህርት አይነቶች መጥቆር አለባቸው

6. ለእያንዳንዱ ጥያቄ በተፈታኝ የተመረጡ መልሶች የሚጠቆሩባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡

↘️ ከላይ የተጠቀሱት መረጀዎች በሙሉ ከመግቢያ ካርድ ጋር የሚወሰዱ ናቸው፡፡

ከዚህ ቻናል በተጨማሪ ወቅታዊ እና ትክክለኛ መረጃዎች ብቻ የሚለቀቅበትን የ #ልዩ_መረጃ ቻናል ይቀላቀሉ👇
@Timhrtministers
@Timhrtministers
295 ዜጎች ከሳዑዲ ዓረቢያ ተመለሱ‼️

295 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ የኢትዮጵያ መንግስትና የሳዑዲ ዓረቢያ መንግስት በትብብር መስራታቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ ከስደት ተመላሽ ዜጎች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
አክሱም ተያዘና አውሮፕላን ተመታ መባሉን መንግሥት ሐሰት ነው አለ‼️

የህወሓት ኃይሎች ትላንት እሁድ ምሽት አክሱም ከተማ መልሰው እንደያዙና የፌዴራል መንግሥት ንብረት የሆነ ተዋጊ ጄት መትተው መጣላቸውን ገልጸው ነበር።ነገር ግን የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በህወሓት በኩል ተባሉት ነገሮችን "ነጭ ውሸት" ሲሉ አጣጥለውታል።ሚኒስትር ዛዲግ ጨምረውም "የህወሓት የመጨረሻ ይዞታ የነበረችው መቀሌ ናት፤ ይህንን ሊያደርጉ አይችሉም" ሲሉ ተናግረዋል።ከሦስት ሳምንት በላይ የኢትዮጵያ ሠራዊት በትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ ዋና ከተማዋን መቀለን መቆጣጠሩን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ መከላከያ "ሕግ የማስከበሩ ዘመቻ" መጠናቀቁን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

የህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከመቀለ መያዝ በኋላ ለሮይተርስ ዜና ወኪል በአጭር የጽሁፍ መልዕክት እንደገለጹት በውጊያው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።በተጨማሪም የቡድኑ ኃይል መቀለ ከተማ አቅራቢያ ውጊያ እያካሄደ ነው ሲሉ ተናግረዋል።ይህንን በተመለከተ ህወሓት የሽምቅ ውጊያ እያካሄደ እንደሆነ በቢቢሲ የተጠየቁት ሚኒስትሩ ዛዲግ አብረሃ ሲመልሱ "የህወሓት አመራሮች በአሁኑ ጊዜ ሕይወታቸውን ለማዳንና በሕግ ከመጠየቅ ለማምለጥ እየሸሹ ነው እንጂ ውጊያ ላይ አይደሉም" ሲሉ መልሰዋል።ትናንት ምሽት ከየት ቦታ እንደሆነ ካልታወቀ ስፍራ ከህወሓት በኩል ወጣ በተባለ መግለጫ ላይ የቡድኑ ተዋጊዎች ከሳምንት በፊት በፌደራሉ ኃይሎች የተያዘችውን የአክሱም ከተማን መልሰው እንደተቆጣጠሩና አንድ ተዋጊ አውሮፕላን መትተው መጣላቸውን ገልጸዋል።

አቶ ዛዲግ አብርሃ ግን ተመትቶ የወደቀ የጦር አውሮፕላን እንደሌለና የአክሱም ከተማ "መያዝም በፍፁም ከእውነት የራቀ ነው" ብለው፤ "ህወሓት በአሁኑ ወቅት ምንም ዓይነት ወታደራዊ አቅም የለውም፤ ሚሊሻውም ሆነ ልዩ ኃይሉ እጅ እየሰጠ ነው" ሲሉ ከቢቢሲ ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።ሚኒስትሩ አክለው በክልሉ ያለውን ሁኔታ ለጋዜጠኞች ክፍት ለማድረግ በትግራይ የተለያዩ ቦታዎች በርካታ መሠረተ ልማቶች በህወሓት ኃይል በመውደማቸው እነሱ ከተጠገኑ በኋላ ጋዜጠኞች ወደ ሥፍራው ሄደው ሁኔታውን ማጣራት ይችላሉ ሲሉ የመገናኛ መስመሮች አለመኖራቸውን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
በአሮጌው የብር ኖት መገበያየት ከነገ ጀምሮ ያበቃል‼️

በአሮጌው የብር ኖት መገበያየት ከነገ ኅዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ያበቃል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም በህዳር 10 ቀን 2013 ዓ.ም ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ከነገ ጀምሮ በአሮጌው የብር ኖት መገበያየት አይቻልም።
የአሮጌው ብር ኖት ቅያሬ ታኅሣሥ 6 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በወቅቱ መግለጹ ይታወሳል።ከመስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም አሮጌ የብር ኖቶች በአዲስ የብር ኖቶች እየተቀየሩ መሆኑ ይታወቃል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
በአ/አ የ8ኛ ክፍል የፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ

¤ ሐሙስ ህዳር 24/2013
ጠዋት 3፡00-5፡00 (አማርኛ አና እንግሊዘኛ )

ከሰዓት 8፡00-11፡ዐዐ ( ሂሳብና ባዮሎጂ)

¤ አርብ ህዳር 25,2013

ጠዋት 3፡00-5፡00 (ፊዚክስ እና ኬሚስትሪ )

ከሰዓት 8፡00-11፡00
(የህብረተሰብ ሳይንስ እና ስነ ዜጋ ስነ ምግባር)

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
በፈተና_ጊዜ_የሚፈጠርን_ጭንቀት_ወይም_ቴንሽንን_ልንቆጣጠር_የምንችልባቸው_ዘዴዎች!.docx
19.3 KB
በፈተና ጊዜ የሚፈጠርን ጭንቀት ወይም ቴንሽንን ልንቆጣጠር የምንችልባቸው ዘዴዎች!

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
Forwarded from ETHIO-MEREJAÂŽ
“እኛ ጁንታ አይደለንም፤ በኃላፊነት ነው የምንሰራው፤” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ትግራይ ክልል በተካሄደ የህግ ማስከበር ሂደት ንጹሓን እንዳይጎዱ ያላሰለሠ ጥረት ሲደረግ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ እናም የሃገር መከላከያ ሰራዊቱ በሰራው ህግ የማስከበር ሥራ ወቅት አንድም ሰው ላይ ችግር አልፈጠረም ነው ያሉት፡፡
ይህም መከላከያ ሠራዊቱ በቂ እና ጠንካራ ብቃት ያለው መሆኑን እንደሚያሳይ ነው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

አየር ሀይሉ ዒላማዎችን ለይቶ በእያንዳንዱ ዒላማ እየፈረመ፣ ኃላፊነት እየወሰደ እንደሚወሰን ተናግረዋል፡፡ ጁንታው ከታጠቀው ሮኬት ቁጥር በላይ መከላከያ ሀይሉ ቢኖረውም ህግ ወደ ማስከበሩ ሂደት ሲገባ አንድም ሮኬት ወደ ትግራይ ክልል አለመተኮሱን አረጋግጠዋል፡፡ “እኛ ጁንታ አይደለንም፤ በኃላፊነት ነው የምንሰራው፤” ሲሉ መቀሌ ከተማን ጭምር ስንቆጣጠር ንጹሓን ሳይጎዱ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ፡፡

SHARE | ሟር
⊰━━━━━━━━━━━━⊰
T.me/ethio_mereja
T.me/ethio_merejabot
⊰━━━━━━━━━━━━
Forwarded from Finance Today
የቀድሞው የሠሜን ዕዝ አዛዥ ሳይመረዙ እንዳልቀሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ!!

በሠሜን ዕዝ ላይ ጥቃቱ ከመፈጸሙ በፊት የዕዙ አዛዥ ሳይመረዙ እንዳልቀረ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስተሩ እንዳሉት፤ የሠሜን ዕዝ አዛዥ የነበሩት ጄነራል ድሪባ ግጭቱ ከመፈጠሩ ከሁለት ሳምንት በፊት "ስብሰባ ከእነሱ ጋር ውሎ፣ ምሳ ከበላ በኋላ ታሞ እራሱን ስቶ ጦር ኃይሎች ሆስፒታል ገብቷል" ብለዋል።

ጨምረውም ከጄነራሉ ጋር የነበሩ ሰዎች "አቅምሰውት ነው" የሚል መረጃ እንዳመጡና እንዲህ ያለው ጉዳይ በህክምና እስኪጣራ ድረስ እንዲቆይ "ብለን አፈንነው" ካሉ በኋላ፤ ጄነራል ድሪባ ባጋጠማቸው ችግር ምክንያት አስካሁን አገግመው ወደሥራቸው እንዳልተመለሱ ገልጸዋል።

ይህንንም ተከትሎ ጄነራሉን በመተካት የሠሜን ዕዝን የሚመራ ጄነራል ለመመደብ መገደዳቸውንና የህወሓት አመራሮች አዲሱን ተሿሚ አንቀበልም ማለታቸውን በመግለጽ "ለካ እሱን በማኮላሸትና የሚመጣውን እምቢ የማለት ፍላጎት ነበረ" ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህም በኋላ "የሠሜን ዕዝ አዛዥ ጄነራል ድሪባ ታመሙ፣ አዲስ የተመደበውን ጀነራል አንቀበልም አሉ ከዚያም ጥቃት ፈጽመው የዕዙን ምክትል አዛዥ ጀነራል አደምን አፈኑ" ሲሉ ለምክር ቤቱ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት አምስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባውን ባካሄደበት ወቅት ከምክር ቤቱ አባላት ስለወቅታዊ ጉዳዮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ላይ ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from Finance Today
“ወደ ሱዳን ከተሰደዱ ወጣቶች መካከል ማይካድራ ላይ በተካሄደው ጭፍጨፋ ላይ የተሳተፉ ይገኙበታል የሚል ጥርጣሬ አለን!!

አምባሳደር ሬድዋን ይህን ያስታወቁት የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ከሬውተርስ ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው።

በትግራይ ክልል ከተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ እስካሁን ከ40 እስከ 43 ሺህ የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ድንበር ተሻግረው ሱዳን መግባታቸውን አምባሳደሩ ተናግረዋል።

አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን ለስደት የበቁት በተለይ ወደ 700 ሰዎች ከተጨፈጨፉበት የማይካድራው ክስተት ጋር ተያይዞ መሆኑንም ገልጸዋል።

በግጭቶች ወቅት አብዛኛውን ጊዜ ለስደት የሚዳረጉት ሴቶች፣ ሕፃናት እና አረጋውያን ናቸው ያሉት አምባሳደር ሬድዋን፣ ከማይካድራው ክስተት ጋር በተያያዘ ግን የሴቶች እና የሕፃናት ቁጥር አነስተኛ መሆኑን፣ የወጣቶች ቁጥር በተቃራኒው እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በማይካድራው ጭፍጨፋ ከሕወሓት ልዩ ኃይል እና ሚሊሺያ በተጨማሪ መደበኛ ያልሆነ አደረጃጀት ውስጥ የነበሩ ወጣቶች የተሳተፉበት መሆኑን በዓለም አቀፍ እና በሀገር ውስጥ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት መረጋገጡን ገልጸዋል።

“ማይካድራ ለሱዳን ቅርብ በመሆኗ ወደ ሱዳን ከገቡት ስደተኞች መካከል በዚህ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ወጣቶች ይገኙበታል የሚል ጥርጣሬ አለን ብለዋል” አምባሳደሩ።

ስለዚህ የእነዚህን ስደተኞች ማንነት እና ምንነት በመለየት ሥራ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሱዳን ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from About education
#ለ2012 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት‼️

- የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ህዳር 24 እና 25

-የዋቻሞ ዩንቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ከህዳር 21 እስከ ህዳር 23/13 ድረስ እንዲገቡ

-የመቱ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎችን ከ
ህዳር 28 -29 እንዲገቡ

-የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ህደር 24 ና 25 ሪፖርት እንዲታደርጉ ተብሏችኋል።ህዳር 26 በሁሉም ካምፓሶች Orientation ይሰጣል።
ህዳር 28 ክላስ ይጀመራል።

- የዲላ ዩኒቨርስቲ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በግቢ ደረጃ የተማሪዎችን የመግቢያ ቀን በተመለከተ የተወሰነ ነገር የለም:: ዛሬ ወይም ነገ የሚወሰነውን ውሳኔ ቀድመን የምናሳውቅ ይሆናል።

-ለኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪዎች
የምዝገባ ቀን ህዳር 25 እና 26፣2013 ሲሆን ትምህርት የሚጀመረው ህዳር 28፣2013

@NEAEA_nea

for your comments 👇👇

@ministry_of_educationbot
"ዶክተር ደብረጽዮን ወደ ደቡብ ሱዳን ተሰደዋል"መባሉን አስተባበሉ።

የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል «ወደ ደቡብ ሱዳን ተሰደዋል» ተብሎ የተነገረዉ ዘገባ «ሐሰት ነው» በማለት መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ደብረጽዮን «አሁንም በመቀሌ ከተማ አቅራብያ ከመንግስት ኃይሎች ጋር እየተዋጋን ነው።» ብለዋል። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ባለፈው ቅዳሜ የመቀሌ ከተማን መቆጣጠሩን አስታውቋል።

በወቅቱ ደብረጽዮን የመቀሌ ከተማን ለቀው መውጣታቸውን ለሮይተርስ በላኩት አጭር የጽሁፍ መልዕክት አረጋግጠዋል። የሕወሓቱ መሪ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ወደ ደቡብ ሱዳን ሸሽተዋል የሚሉ ዘገባዎች መውጣታቸውን ተከትሎ በሰጡት መልስ« ከትግራይ ክልል አልወጣሁም» ሲሉ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ሚንስትሩ ቃል አቃባይ ቢለኔ ስዩም በበኩላቸው «የፌዴራል መንግሥት በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን በማረጋጋት ስራ ላይ ተጠምዷል፤ ተበታትኖ ላለ ወንጀለኛ ንግግር መልስ መስጠት ጉዳያችን አይደለም » ሲሉ ዶክተር ደብረጽዮን «በመቀሌ አቅራብያ ከመንግስት ኃይሎች ጋር ውግያ ቀጥለናል» ብለው መናገራቸውን ያጣጣሉበትን ሃሳብ ለሮይተርስ ነግረዋል።
---------------------------------------------------
ክቡራን ቤተሰቦች ሀሳብ አስተያየታችሁን የዜና የመረጃ ጥቆማችሁን ከሰር ባለው ሊንክ አድርሱኝ:: አመሰግናለሁ
አቤል ብርሀኑ (የወይኗ ልጅ)
👉@abel21bot
በትግራይ ክልል የባንክ እና ቴሌኮም አገልግሎቶች ወደ ቀድሞ አገልግሎታቸው እንዲመለሱ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አሳሰበ።

ኮሚሽኑ የመልሶ ማቋቋም ተግባራት በሰብአዊ መብቶች የሚመሩ መሆን አለባቸውም ብሏል።

ቀደም ሲል በኢሰመኮ የቀረቡ፣ በተለይም በሲቪል ሰዎች ላይ ማንኛውም አይነት ጉዳት እንዳይደርስ ጥንቃቄ እንዲደረግ አጽንዖት የሚሰጡት ምክረ ሃሳቦችንና ጥሪዎችን በማስታወስ፣ በቀጣይ የሚደረጉ የመልሶ ማቋቋምና መልሶ ግንባታ ተግባራት በፌዴራል መንግሥቱ ሰብአዊ መብቶችን የማክበርና የመጠበቅ ግዴታ የሚመራ እንዲሆን አሳስቧል።

የተጠፋፉ ቤተሰቦች እንዲገናኙና ተገቢው ሰብአዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆን የተቋረጡ የቴሌኮሙኒኬሽን፣ ውሃና ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ መሰል መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲሁም የሰብአዊ እርዳታ ሰጪ አካላት አገልግሎት ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ ማሳሰቡን ኮሚሽኑ ለኢትዮ ኤፍ ም በላከው መግለጫ ገልጿል።

እንዲሁም በግጭቱ የተፈናቀሉና የተሰደዱ ሰዎች ወደ መደበኛ መኖሪያቸው እንዲመለሱ እና የተጠፋፉ ቤተሰቦች እንዲገናኙ የሚያስችል አስፈላጊ የሆነው የሎጂስቲክስና የሰብአዊ እርዳታ መሰረተ ልማት እንዲደራጅም ጠይቋል።

ተጠያቂነትን ለማረጋገጥና ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም የሰብአዊ መብቶች ጥሰትና ያስከተለውን ሰብአዊ ቀውስ የሚመመረምር ገለልተኛና ግልጽ የሆነ አሰራር ከወዲሁ እንዲተገበር፣ ተዓማኒና አካታች የሆኑ የእርቅና የፍትሕ ሂደቶች በጊዜ ሊደራጁ ይገባልም ብሏል።

በተጨማሪም ኢሰመኮ በትግራይ ተወላጆች ላይ ብሔርን መሰረት ያደረገ መድሎዎና መገለል ስለመድረሱ የሚቀርቡለት ቅሬታዎች በከፍተኛ ደረጃ እያሳሰበውና እየተከታተለው መሆኑን ገልጿል።
(ኢትዮ ኤፍ ኤም)
---------------------------------------------------
ክቡራን ቤተሰቦች ሀሳብ አስተያየታችሁን የዜና የመረጃ ጥቆማችሁን ከሰር ባለው ሊንክ አድርሱኝ:: አመሰግናለሁ
አቤል ብርሀኑ (የወይኗ ልጅ)
👉@abel21bot