G-Tutorialclass
814 subscribers
2.23K photos
29 videos
1.43K files
351 links
Impossible is possible with learning & reading.
Download Telegram
የRemedial ፕሮግራም ምደባ‼️
በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን መከታተል ትችላላችሁ።
የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች
1. Website:  https://student.ethernet.edu.et
2. Telegram bot: @moestudentbot
==========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
4
አንዲት ሴት ምስጢር የምትይዝበት አማካይ ጊዜ ለ47 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ነው ይለናል በብሪታኒያ የተሰራ የቆየ ጥናት‼️
ከ16 አመት በፊት የብሪታኒያ ተመራማሪዎች ከ18 እስከ 65 ዓመት የሆኑ 3,000 ሴቶችን ዳሰሳ ያደረጉ ሲሆን፣ ከ10 አራት የሚሆኑት ምስጢሩ ምን ያህል የግል ወይም የሚያሳፍር ቢሆንም እንኳ ሚስጥር መያዝ እንዳልቻሉ ተናግረዋል።

ወደ 45 ከመቶ የሚሆኑት ምስጢሩን ከውስጣቸው ለማውጣት ሲሉ ብቻ እንደሚናገሩ ተናግረዋል፣ ነገር ግን አብዛኛዎቹ በኋላ የጥፋተኝነት ስሜት ይሰማቸዋል።

ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ምስጢርን በመግለጣቸው አልኮልን መጠጥን ወቅሰዋል። ሴቶቹ ምስጢሩን ለባላቸው፣ ለፍቅረኛቸው፣ ለእናታቸው  ወይም ለቅርብ ጓደኛቸው ሊነግሩ እንደቻሉ ተናግረዋል።

ቢሆንም፣ 83 ከመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሙሉ በሙሉ ታማኝ እንደሆኑ ያምናሉ፣ እና ከ10 ሦስት የሚሆኑት የጓደኛቸውን እምነት ፈጽሞ እንደማይከዱ ይናገራሉ። ጥናቱ በተጨማሪም ሴቶች በሳምንት ቢያንስ ሦስት ወሬ/ሐሜት እንደሚሰሙ አሳይቷል። ይሁን እንጂ ጥናቱን ያካሄደው የዊንስ ኦፍ ቺሊ የዩኬ ዳይሬክተር የሆኑት ሚካኤል ኮክስ እንዳሉት፣ የተጋሩት ምስጢራት ብዛት ሴቶቹ ከያዙበት ጊዜ ያህል አስገራሚ አልነበረም። "በዚህ ዳሰሳ ምን ያህል ምስጢራት ለሰዎች እንደሚነገሩ ለማወቅ በጣም ጓጉተን ነበር" ይላሉ። "ያላሰብነው ግን እነዚህ ምስጢራት በምንተማመንባቸው ሰዎች ምን ያህል በፍጥነት እንደሚተላለፉ ነበር።"

በዚህ ጥናት ላይ ተመስርቶ ሴቶች ሚስጥር አይጠብቁም ብሎ መደምደም የተሳሳተ መረጃ ነው የሚል ትችትም ጥናቱ  ቀርቦበት ነበር።
fidel post
==========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
2
#Updated

🗣 የተለያዩ ዩንቨርስቲዎች Mid ፈተናዎች


➡️ Addis Ababa University Exams
▪️AAU- Entrepreneurship mid exam
▪️AAU-Economics Mid Exam
▪️AAU-Psychology Mid Exam
▪️AAU-Physics Mid Exam
▪️AAU-Maths Mid Exam
▪️AAU-Logic Mid Exam
▪️AAU-Emerging mid Exam
▪️AAU-Global trends mid exam

➡️ Arbaminch University Exams
▪️AMU-Logic mid exam
▪️AMU- Psychology Mid Exam

➡️ Addis Ababa Science and Technology University
▪️AASTU-Maths Mid Exam
▪️AASTU-Physics mid exam
▪️AASTU-Logic mid exam

➡️ Arsi University
▪️Arsi-Psychology Mid Exam
▪️Arsi-Maths mid exam

➡️ Bahirdar University Mid Exam
▪️BDU- Global trends mid exam
▪️BDU-Anthropology mid Exam
▪️BDU-Emerging mid exam
▪️BDU-Geography mid exam
▪️BDU-Emerging mid exam

➡️ Debrebirhan University
▪️DBU-Emerging mid exam

➡️ Debre Markos University
▪️DMU-History mid Exam
▪️DMU-Physics mid exam
▪️DMU- Civics mid exam
▪️DMU- Anthropology mid exam

➡️vDilla university
▪️DU-English mid Exam

➡️ Gonder University
▪️Gonder-History mid exam
▪️Gonder-Emerging mid exam
▪️Gonder-Global trends mid exam
▪️Gonder-Emerging mid exam

➡️ Haremaya University
▪️HU-Psychology mid exam
▪️HU-Geography mid exam

➡️ Hawassa University
▪️Hwu-logic mid exam
▪️Hwu-Civics mid exam
▪️Hwu-Anthropology mid exam
▪️Hwu-Physics mid exam
▪️Hwu-Global trends mid Exam
▪️Hwu-Logic Mid Exam
▪️Hwu-maths mid exam

➡️ Jimma University Mid Exam
▪️Jimma-Emerging mid Exam
▪️Jimma-Logic mid exam
▪️Jimma-Civics mid exam
▪️Jimma-Psychology mid exam
▪️Jimma-Global trends mid exam
▪️Jimma-Anthropology Mid Exam

➡️Jigjiga university
▪️JJU-Geography mid exam
▪️JJU-Inclusiveness mid exam

➡️ Mekele University
▪️Mekele- Psychology mid exam

➡️ Mettu University
▪️MU-Geography mid exam
▪️MU-Maths mid Exam

➡️ Wachemo University
▪️Wache-Logic Mid Exam
▪️Wache-English mid exam
▪️Wache-Maths mid exam
▪️Wache-Logic mid exam
▪️Wache-Geography mid exam

➡️ Welayta Sodo University
▪️WSU-Logic mid exam
▪️WSU-Maths mid exam

➡️ Welkite university
▪️Welkite-Civics mid exam
▪️Welkite-Maths mid exam
▪️Welkite-Psychology mid exam

➡️ Wollo University
▪️WU-Emerging mid exam

JOIN: 📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :
@GTutorialclass
3👍1
የተማሪዎች ተቃውሞ‼️
ትምህርት ሚንስትር ከመጭው አመት ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ ያቀደው አስገዳጅ መመሪያ ተቃውሞ ገጠመው
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስትር ከመጭው አመት ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ  ለማድረግ ያቀደው አስገዳጅ መመሪያ ተቃውሞ እንደገጠመው ተገልጿል።

የትምህርት ሚንስትር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የ3ኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ፣ ለአንድ ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ ከመጭው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ እንዳለው አሳውቆ ነበር።

መመሪያውን የተቋወሙ የተለያዩ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከትላንት ጀምሮ በሀገሪቱ በተለያዩ ትምህርት ተቋማት የተቃውሞ ድምፃቸውን ማሰማት ላይ መሆናቸውን ታውቋል።

ተማሪዎቹ  ሚንስተር መስሪያ ቤቱ  ያወጣው አስገዳጅ መመሪያ ያለመምህርነት ሙያ ስልጠና ተግባራዊ ማድረግ ተገቢ እንዳልሆነ አንስተዋል።

የትምህርት ሚንስቴር በበኩሉ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ተመራቂ ተማሪዎች የአንድ ዓመት የማስተማር ስነ ዘዴ ኮርስ በመውሰድ ለመምህርነት ብቁ መሆን እንደሚችሉ በቅርቡ አስታውቋል።
ማለዳ ሚዲያ
==========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
2
አዲስ የትምህርት ደንብ‼️ እስከ 150,000 ብር የሚደርስ ቅጣት እና የባህል ጥበቃ‼️

የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ተቋማትና አካባቢያቸው የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ማውጣቱን አስታወቀ።

ይህ ደንብ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና ብቁ ዜጎችን ለመፍጠር ያለመ ነው።

ዋና ዋና ነጥቦች እና ዓላማዎች:
* የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 150,000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ተመላክቷል።

ደንቡ እየጨመሩ የመጡትን አዋኪ ጉዳዮች ከመግታት ባሻገር፣ ከኢትዮጵያውያን ወግና ልማድ ጋር ይቃረናሉ ተብለው የተለዩ የውጭ ባህላዊ ልማዶችን በትምህርት ተቋማት አካባቢ መፈጸም ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።

ዋንኛው ዓላማ በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ጉዳዮችን በመከላከል፣ ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ፣ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀና ግብረ-ገብነትን የተላበሰ ብቁ ትውልድ እንዲፈጠር ማስቻል ነው።

የተከለከሉ የውጭ ባህላዊ ድርጊቶች ምሳሌዎች:
አዲሱ ደንብ የሀገሪቷን ባህልና ወግ ይቃረናሉ ተብለው በግልጽ የዘረዘራቸውን አሉታዊ መጤ ድርጊቶችንና ክብረ በዓላትን ይከለክላል።

ከእነዚህም መካከል:
* Crazy Day
* Gentle Day
* Olds Day
* Valentine Day
* Color Day
* Pyjama Day የሚሉት ይገኙበታል።

Via Capital
==========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
2
Learn English With Us!

Daily phrases

✔️ I can't wait to see you.
አስከማይህ ቸኩያለሁ/አስከማይሽ ጓጉቻለሁ

✔️ I am so glad you came.
በመምጣትሽ/ህ ደስ ብሎኛል።

✔️ What took you so long?
ምንድነው ያቆየህ?

✔️ You made my day.
ቀኔን አሳመርክልኝ።

📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
4
💎 Never say never.
አይሆንም አትበል።

💎 First thing is first.
መጀመሪያ አስፈላጊውን ነገር አድርግ።

💎 Same old same old.
አዲስ ነገር የለም።

💎 What's in it for me.
ለኔ ምን ይጠቅመኛል።

💎 Any thing is possible.
ማንኛውም ነገር ይቻላል።

👇👇👇👇👇
@GT12192123

#ለፈጣን እና ታማኝ መረጃ

👇👇👇👇👇👇

#share
#share

🙏🙏🙏🙏🙏

🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝
JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝🔝
4
ምልከታ‼️
#እየሸለምን ያለነው ሀገር ገንቢዎችን ወይስ ጊዜ ገዳዮችን? 👉??«#TikTok_Creative_Award»
ከሰሞኑ የተከናወነው የ«TikTok Creative Award» ደማቅ አልባሳት ቅንጦት ና አፍራሽ ተግባራት የታዩበት ሊያሳየን ያልቻለው አንድ አስፈሪ እውነት የሀገራችንን የወደፊት አቅጣጫ የሚወስን ነው።

ጥያቄው፡- እየሸለምን ያለነው ሀገር ገንቢዎችን ወይስ ጊዜ ገዳዮችን? የሚለው ነው።ከበለፀጉት ሀገራት ተሞክሮ አንፃር ሲታይ፣ የዘንድሮው ሽልማት ለወጣቱ ያስተላለፈው መልእክት እጅግ አደገኛ ነው።

Has to be banned!!

ለምን?

1. የቻይናን ጥበብ ወይስ የቻይናን ቆሻሻ? (The Double Standard) የቲክቶክ ባለቤት የሆነችው ቻይና፣ ዓለምን በቴክኖሎጂ የተቆጣጠረችው በመጨፈር አይደለም።

ቻይና ለገዛ ወጣቶቿ የምትፈቅደው የቲክቶክ ቅጂ (Douyin)፣ ከ14 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚያሳየው የሳይንስ ሙከራዎችን፣ የሮቦቲክስ ፈጠራዎችን እና የአገር ፍቅር ታሪኮችን ብቻ ነው።

ለምን? ምክንያቱም «ነገን የሚረከበው ትውልድ ጭንቅላት በዕውቀት እንጂ መደንዘዝ የለበትም» ብለው ስለሚያምኑ ወደኛ ሲመጣ ግን ነገሩ ተገላቢጦሽ ነው።

ሽልማታችን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የመፅሀፍ እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ወደ ዳር ገፍቶ «ቀልድን» የጀግንነት ማማ ላይ ሰቀለ። ቻይና ለልጆቿ የዕውቀት ወተት ስትግት፣ እኛ ለልጆቻችን በመዝናኛ የተለወሰ መርዝ እየሰጠን ይሆን? ይህንን ቆም ብለን ልንጠይቅ ልንመረምር ይገባል።

2. «Creative» (ፈጠራ) ወይስ «Viral» (ማነጋገሪያ)? ቃላትን በትክክል እንጠቀም። «ፈጠራ» (Creativity) ማለት የህዝብን ችግር የሚፈታ፣ አዲስ እሴት የሚጨምር እና ትውልድን የሚያሻግር ስራ ነው።

ስልክን አገላብጦ በመቅረጽ በሺዎች የሚቆጠሩ «ላይክ» ማግኘት ታዋቂነት (Popularity) እንጂ ፈጠራ (Creativity) ሊሆን አይችልም።
ባደጉት ሀገራት ሽልማት የሚሰጠው ለይዘት ጥራት እና ለሚያመጣው ለውጥ ነው።

እኛ ጋር ግን መስፈርቱ  የቁጥር ጨዋታ ሆነ። ሳይንስን፣ ህክምናን እና ትምህርትን የሚያስተላልፉ ቻናሎች እንደ ሁለተኛ  ሲታዩ፣ ቀላል መዝናኛዎች የክብር ዙፋን ላይ ተቀምጠዋል። እውቀት በ «ላይክ» ብዛት አይለካም፤ እውነትም በ «ሼር» ብዛት አይረጋገጥም።

3. ለወጣቱ የተላለፈው አደገኛ መልእክት (The Wrong Role Models) አንድ ወጣት ይህንን ሽልማት ሲመለከት አእምሮው ውስጥ የሚቀረፀው ምንድን ነው?

• "ለካ ክብር ለማግኘት ተምሮ ዲግሪ መያዝ፣ ሌሊት ተቀን ለሀገር የሚጠቅም ምርምር ማድረግ ወይም መፅሀፍ መጻፍ አይጠበቅብኝም።"
• "ለካ አቋራጭ መንገድ አለ! ስልኬ ላይ ብጨፍር፣ በቅጽበት 'የዓመቱ ምርጥ' ተብዬ እሸለማለሁ።"

ይህ አስተሳሰብ የስራ ባህልን (Work ethic) የሚገድል መርዝ ነው። አሜሪካን፣ ጃፓንን እና ጀርመንን የገነቡት ፊታቸው በላብ የረጠበ ኢንጂነሮች ሐኪሞች ሙህራኖች ና ገበሬዎች እንጂ፣ ካሜራ ፊት የሚሽሞነሞኑ አይደሉም።

ወጣቱን ትምህርት እና የሥራ ጎዳና አውጥተን፣ ወደ አቋራጭ መንገድ እየገፋነው ነዉ አገርንም ጭምር!

4. የባህል ወረራ በሽልማት ስም
ሽልማቱ ላይ የታየው የአለባበስ እና የቅንጦት ትርኢት፣ የኢትዮጵያን ወጣት ማንነት የሚወክል ነበር? ወይስ የሆሊውድን "Red Carpet" ለመኮረጅ ? 
Via:- Dr BEREKET EMMANUEL
MD, Author Founder influential youth Ethiopia CEO
==========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
6
ትክክለኛ ሊንኮች‼️
ብሄራዊ ባንክ ሁሉም የባንክ ደንበኞች የፋይዳ መታወቂያ ቁጥራቸውን ማስተሳሰር እንዳለባቸው መመሪያ ማውጣቱ ይታወሳል።
ባንክ መሄድ ሳይጠበቅባችሁ የባንክ ሒሳብን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር  ከታች ያሉትን ሊንኮች መጠቀም ትችላላችሁ።
ፋይዳ ለማስተሳሰር ትክክለኛ ሊንኮች የሚከተሉት ናቸው።
ሲስተም ላይ በነበረ መጨናነቅ ለቀናት ቆይቶ የነበረውም የመዘግየት ችግር በመፈታቱ ፣ ደንበኛ የሆኑበትን ባንክ ከታች በተዘረዘሩት ዝርዝር በመምረጥ ባለ 16 አኃዝ የፋይዳ ቁጥርዎን (FAN/FCN) በመጠቀም ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ማጣመር ይችላሉ።
💸 አቢሲኒያ ባንክ: cs.bankofabyssinia.com/fayda_connect 

💸 አዋሽ ባንክ : fayda.awashbank.com

የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ:
my.coopbankoromiasc.com/harmonization 

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
cbefayda.cbe.com.et
ኦሮሚያ ባንክ
bfayda.oromiabank.com

ወጋገን ባንክ
fayda.wegagenbanksc.com.et/harmonization

ንብ ባንክ
fayda.nibbank.com.et

ፀሀይ ባንክ
fayda.tsehaybank.com.et/FAYDA/home

ስንቄ ባንክ :
fayda.siinqeebank.com:7443

💸  ዘምዘም ባንክ :
fayda.zamzambank.com.et

💸  አማራ ባንክ :
fayda.amharabank.com.et

​=========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
4
የተቀማጭ ገንዘብ ወለድ‼️
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አዲስ ባወጣው መመሪያ ቁጥር NBE/INT/13/2026 መሠረት፣ ባንኮች የሚሰጡት የቁጠባ እና የብድር ወለድ ተመን ከዚህ በኋላ በገበያ ፍላጎት እና አቅርቦት ላይ ተመስርቶ በየባንኮቹ እንዲወሰን አዝዟል።


📌 ዋና ዋና ነጥቦች፦
የቁጠባ ወለድ ተመን (Saving Rate): ከዚህ ቀደም ብሄራዊ ባንክ ያስቀምጠው የነበረው ዝቅተኛ የቁጠባ ወለድ ተመን ቀርቶ፣ እያንዳንዱ ባንክ እንደ ፍላጎቱ የራሱን የቁጠባ ወለድ ተመን ይወስናል።

የጊዜ ገደብ ተቀማጭ (Time Deposit): ባንኮች ለጊዜ ገደብ ተቀማጭ የሚከፍሉትን የወለድ መጠን ራሳቸው በነፃነት ይወስናሉ።

የዳይሬክተሮች ቦርድ ኃላፊነት: የእያንዳንዱ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ የወለድ መጠኑን በጽሁፍ የመወሰን እና ግልጽ የሆነ አሰራር የመዘርጋት ኃላፊነት ተጥሎበታል።

አድልዎ መከልከሉ: ባንኮች ለተመሳሳይ የቁጠባ ዘርፍ ደንበኞች እኩል የሆነ የወለድ ተመን መተግበር አለባቸው፤ አድልዎ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

💡 ይህ ምን ማለት ነው?
ባንኮች ደንበኞችን ለመሳብ የተሻለ የወለድ መጠን በማቅረብ እርስ በርሳቸው እንዲወዳደሩ በር ይከፍታል። ይህም የሀገሪቱን የፋይናንስ መረጋጋት እና የኢኮኖሚ እድገት ለማፋጠን የታለመ መሆኑ ተገልጿል።

​መመሪያው በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ሁሉም ባንኮች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል።
#አዩዘሀበሻ
​=========≠============
💎⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
          JOIN :@GTutorialclass
😍4
ከባዱ ወደ ጨረቃ መውጣቱ ሳይሆን መመለሱ ነው‼️
አራቱ የናሳ ተመራማሪዎች የ13 ደቂቃ ከህዋ ወደመሬት የመመለስ (Reentry) ስህተት ፍርሃት፤ መሞት ወይም በህይወት የመገኘት ታሪክ ሊፈፀም:- ጥቂት ሰዓት ብቻ ቀርቷል
=======================================
ዛሬ እኤአ ኤፕሪል 10፣ 7:53 ምሽት ET ወይም በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ከሌሊቱ 9 ሰአት፣ በፓሲፊክ ውቅያኖስ ላይ  የሆነ ቦታ፣ አራት ሰዎች ከዚህ በፊት ማንም ሰው በሕይወት ባልተረፈበት ፍጥነት  አንድ ነገር ሊያደርጉ ተዘጋጅተዋል። ከ ዛሬ ዘጠኝ ቀን በፊት 4 የናሳ ተመራማሪዎችን ይዛ ወደ ህዋ የመጠቀችው አርጤምስ ሁለት የተባለችው መንኩራኩር ለዘጠኝ ቀን በመሬትና በጨረቃ መካከል ስትዞር ቆይታ ዛሬ ወደምድር ሊመለሱ ተዘጋጅተዋል። የመንኮራኩሩ አብዛኛው አካል በህዋ ላይ ቀርቶ ወደምድር መመለሻ  ኦሪዮን የሚባለው መንኮራኩር የመሬት ከባቢ አየር የላይኛው ጫፍ ሲገባ፣ ፍጥነቱ  በሰዓት 38,000 ኪሎሜትር በሰአት እየተምዘገዘገ ወደ መሬት  ፍጥነት እየተጓዘ ይመጣል።
እንደገና አንብቡት።
38,000 ኪሎሜትር በሰዓት።
ለምሳሌ፣ የመደበኛ አየር መንገድ አውሮፕላን በሰዓት 900 ኪሎሜትር ይበርራል። የወታደር ስናይፐር ጥይት በሰዓት 3,500 ኪሎሜትር ያህል ይጓዛል። ኦሪዮን ግን በMach 32 ፍጥነት ይንቀሳቀሳል፣ ከጥይት 11 እጥፍ ይፈጥናል ማለት ነው። ይህ በታሪክ ውስጥ በሰው ተሸካሚ መንኮራኩር የሚደረግ ፈጣን ወደ መሬት ለመመለስ የሚደረግ ጉዞ ይሆናል ማለት ነው።
መንኮራኩሩ ውስጥ አራት ሰዎች በመቀመጫቸው ተጠግተው  በre cycling የተመረተ  አየር እየተነፈሱ፣ ልባቸው በፍርሃት እተመታ፣ ፊዚክስ ሕይወታቸውን ወይም ሞታቸውን ሊወስን እየተጠባበቁ ነው።

🔥 የእሳት ግድግዳ (The Wall of Fire)
ኦሪዮን ከአየር ጋር ሲገጥም፣ ከፊቱ ያለው አየር ለመንቀሳቀስ ጊዜ የለውም። ወዲያውኑ ይጨመቃል። የተጨመቀ አየር ይሞቃል። በ38,000 ኪሎሜትር ፍጥነት ደግሞ እጅግ ከፍ ያለ ሙቀት ይፈጠራል። በመንኮራኩሩ ውስጥ ያለ ሁሉ እስከ 5,000°C ሙቀት ድረስ ይግላል አለያም ሊቀልጥ ይችላል ማለት ነው። ። ይህ ከእሳተገሞራ  ሁለት እጥፍ የሚሞቅ ሙቀት ነው። ብረትን ሊያተን የሚችል፣ መንኮራኩሩን እና ውስጥ ያሉትን ሰዎች ወደ አመድነት ሊያስቀይር የሚችል ሙቀት ነው።
ታዲያ ኦሪዮንን ከዚህ እሳት የሚከላከለው 16.5 ጫማ ዲያሜትር ያለው AVCOAT የተባለ ቁሳቁስ ነው። ይህ የሙቀት መከላከያ በቀስ በቀስ ይቃጠላል፣ ይሰነጠቃል፣ እና እየተበላሸ ሙቀቱን ከመንኮራኩሩ ይወስዳል ወይም ያስወግዳል። እሳቱን አያቆምም—ለሰዎቹ ሕይወት እራሱን ይሰዋል።

⚠️ ይህም ሙከራ  የተሳካ የሆነው  አንድ ጊዜ ቢሆንም  የተሳሳተ የሙቀት መከላከያ ነበር ። በፈረንጆቹ 2022 በArtemis I ጊዜ፣ ኦሪዮን ያለ ሰው ከጨረቃ ሲመለስ፣ የሙቀት መከላከያው በ100 በላይ ቦታዎች ተሰነጠቀ እና ተበታተነ።
ምክንያቱ የተጠመዱ ጋዞች ነበሩ። በመመለስ ሙቀት ጊዜ ግፊት ተፈጠረ፣ እና ክፍሎቹ ተበታተኑ።
Artemis I ላይ ሰው ስለሌለ ችግር አልነበረም።
Artemis II ግን አራት ሰዎች አሉ።
NASA መፍትሄ አልቀየረም—የመመለስ አንግልን ቀየረ። ሙሉ አዲስ መከላከያ አልሰራም።

አሁን የ⏱️ 13 ደቂቃ ዝምታ ተቃርቧል
የመመለስ ሂደቱ ከ13 ደቂቃ ይሆናል።በዚህ ጉዞ ላይ በሙቀቱ ምክንያት በሚፈጠር ከፍተኛ የፕላዝማ ነፀብራቅ መገናኛ ሬድዎችና የሲግና ዘዴዎች ከመቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ጋር ይቋረጣል
ያኔ NASA ምንም አይሰማም መልዕክት አይደርሰው ታድያ ፍርሃት ጭንቀት ሰአት ይሆናል ። ሰዎቹ አይነጋገሩም።
አራት ሰዎች በእሳት ውስጥ በሙሉ ዝምታ ይወርዳሉ።
🌊 ማረፊያቸው ውቅያኖስ ላይ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል
መንኮራኩሩ በፓሲፊክ ውቅያኖስ 100 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ያርፋል ተብሎ ይጠበቃል ።
ለዚህም ሂደት 11 ፓራሹቶች በትክክል መከፈት አለባቸው ምክንያቱም
ፍጥነቱን ከ38,000 ኪሎሜትር በሰአት ወደ 27 ኪሎሜትር በሰአት ዝቅ እንዲል ያደርገዋል።
አንድ ፓራሹት እንኳ ቢሳሳት ውጤቱ ከባድ ይሆናል።
👨‍🚀 አሁን ያሉበት ስሜት
አራቱ አባላት ዛሬ የመጨረሻ ቀናቸውን በስፔስ አሳልፈዋል። ምግብ ተዘጋጅቷል፣ ስርዓቶች ተፈትሸዋል። አሁን የ13 ቷን ደቂቃዎች የሰቀቀን ጉዞ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።
የፊዚክስ ምስጢር ህይወት ወይ ሞት
እሳት እና ሕይወት ፍት ለፊት  ተገናኝተዋል።
የ13 ደቂቃ ረጅም ጊዜ
7:53 PM — መግቢያ
የ13 ደቂቃ — ዝምታ
ከዚያ — እሳት
ከዚያ — ፓራሹቶች
ከዚያ — ፓስፊክ ውቅያኖስ
Girum Tekle
@Gtutorialclass
2
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ!።

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ድረስ ይሰጣል

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 የትምህርት ዘመን የሚካሄዱ ፈተናዎች የሚሰጡባቸውን ቀናት ይፋ አደረገ።

በዚህም መሰረት የሪሚዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ 20፣ የቅደመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ 12 እንዲሁም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

በተመሳሳይ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከሐምሌ 29 እና 30 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሰጥ፤ የመሰረታዊ የንብባና የስሌት ክህሎት ምዘና ፈተና ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ውስጥ ይሰጣል፡፡የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር )÷ እስከ ተጠቀሱት ጊዜያት ድረስ ተፈታኞች አስፈላጊውን የይዘትና የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲደርጉ አስገንዝበዋል።ወላጆች፣ መምህራንና በየደረጃው ያለው የትምህርት አመራር ተፈታኞቻቸው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል  ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡
2
ወደ ካናዳ ምዝገባ አልተጀመረም‼️
ለካናዳ የስራ ስምሪት ምንም አይነት ይፋዊ ምዝገባ አለመጀመሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዳስታወቀው የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ወይም AI/Deepfake በመጠቀም የተፈበረኩና አሳሳች ምስሎችንና በቪዲዮዎችን በማሰራጨት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ወደ ካናዳ "ምዝገባ ጀምሯል" የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎችን በመልቀቅ ማህበረሰቡን በማደናገር የሚገኙ አካላት መኖራቸውን አስታውቋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል እና ከካናዳ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ካናዳ ለመላክ የሚያስችል ስምምነት ሚያዝያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም መፈራረሙ ይታወሳል።ይህንኑ ተከትሎ፣ አንዳንድ ሕገ-ወጥ አካላት  የፈጠራ ወሬዎች በማህበራዊ ሚዲያ እያሰራጩ የሚገኙ ሲሆን በሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI/Deepfake) በመጠቀም የተፈበረኩና አሳሳች ምስሎችንና በቪዲዮ በማሰራጨት  "ምዝገባ ተጀምሯል" የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎችን በመልቀቅ ማህበረሰቡን ማደናገር ላይ ይገኛሉ።

በግል ስልክ ቁጥሮች ደውሉ በማለት ዜጎችን ለኢኮኖሚያዊ ብዝበዛ መጋበዝ ላይ ሲሆኑ እነዚህ ማስታወቂያዎች ሙሉ በሙሉ የማጭበርበር ተግባራት መሆናቸውን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማስጠንቀቁን አዩዘሀበሻ ሰምቷል፡፡በአሁኑ ወቅት ለካናዳ የሥራ ስምሪት ምንም አይነት ይፋዊ ምዝገባ አልተጀመረም፡፡

በግል ስልክ ቁጥሮች የሚደረጉ ጥሪዎችም ሆኑ የሚላኩ አጫጭር መልዕክቶች ሚኒስቴሩን መስሪያ ቤቱን እንደማይወክሉ ያስታወቀው ቢሮው የምዝገባ ጥሪ የሚደረገው በብሔራዊ ቴሌቪዥንና የሬዲዮ ጣቢያዎች፤ የሚኒስቴሩን ይፋዊ የማረጋገጫ ምልክት ባላቸው ማህበራዊ ትስስር ገጾች ብቻ በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል፡፡
=====================
💎👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ
@Gtutorialclass
2
ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች መለቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል 📢📝

አገልግሎት መ/ቤቱ ፦

1. እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የትምህርት  ቤቱን ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ መያዝ እንዳለበት አሳስቧል 🎓

2. በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ ፣ የጾታ ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በግድግዳ ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጿል 🔄📅

3. እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከል ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዝ አሳስቧል ⚠️🛡️

4. ተፈታኞች ፈተና ላይ ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸው ገልጿል 🆔📋
1
ውጤትዎን ይመልከቱ! 📄

ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም ከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት 

ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et

ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። 📝🔍
2
1
#በአማራ ክልል የ2018 #የትምህርት ዘመን #የ8ኛ ክፍል #ክልላዊ ፈተና #ውጤት ይፋ ሆነ።
በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል #አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

ከሰኔ 3-5/2018ዓ.ም ለተከታታይ ሶስት ቀናት  ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት በቴክኖሎጅ ታርሞ ይፋ የተደረገ ሲሆን በክልሉ 173699 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸው ይታወቃል። ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135003(77.72%)ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።

ተማሪዎችም ውጤታቸውን   በሁለት  አማራጮች ማየት የሚችሉ ሲሆን:-
🔴 በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1) ለ8ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2) በሚመጣው ቅጽ (form) ላይ  የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት
3) ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡

🔴 በተጨማሪም  @emacs_ministry_result_qmt_bot  በሚለው የቴሌግራም ቦት ላይ በመግባት ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ ሲሆን መጀመሪያ
     1) start የሚለውን ይጫኑ!
      2) በመቀጠልም ክፍልዎን ይምረጡ
      3) ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ
       4) በመቀጠል የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት  ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።

ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው ቅሬታ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን ይችላሉ። ቅሬታቸውንም ለማቅረብ
🔴 በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ላይ ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1)  ለ8ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara.ministry.et/#/complaint የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2)  በሚመጣው ቅጽ(form) ላይ የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና  የተማሪውን  የመጀመሪያ ስም (First Name)በማስገባት
3) የትምህርት ዓይነት አሳይ(Fetch course) የሚለውን ቁልፍ በመጫን
4) ቅሬታ ማቅረብ የሚፈልጉበትን ይምረጡ
5) በመጨረሻም ሪፖርት (Add Complaint) የሚለውን  ቁልፍ በመጫን ቅሬታቸውን  ማቅረብ ይችላሉ።

🔵ማስታወሻ ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡

2018ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል።
=====================
💎👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
2
የመሬት መንቀጥቀጥ‼️
በዛሬዉ እለት በመተሃራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

በዛሬዉ እለት ምሽት 2 ሰዓት ከ 11 ደቂቃ ላይ በመተሃራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.6 የተለካ መሆኑን ቮልካኖ ዲስከቨሪ የተሰኘዉ የመሬት መንቀጥቀጥ እና የእሳተገሞራ ፍንዳታዎችን የሚከታተል ተቋም በገጹ አሳዉቋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በአዲስአበባም አንዳንድ ቦታዎች ላይ ተሰምቷል።
=====================
💎👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
@Gtutorialclass
3
የኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ ኃይል ማስገቢያ የዱቤ ክፍያ ወለድ ሙሉ በሙሉ ተነሳ።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዲስ ኃይል ማስገቢያ ክፍያን በዱቤ ለሚከፍሉ ደንበኞች ይጠየቅ የነበረውን ከ3 እስከ 9 በመቶ የወለድ ክፍያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጅነር ጌቱ ገረመው አስታወቁ።

ቀደም ሲል የዱቤ ክፍያ ጊዜው እስከ 24 ወራት ሲሆን፣ ከ6 ወራት በላይ ለሚቆይ ክፍያ ወለድ ይጣል ነበር።

አሁን ወለዱ መነሳቱ ክፍያውን በአንድ ጊዜ መፈጸም ለማይችሉ ዜጎች የምስራች መሆኑንና አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከሰኔ 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በተጀመረው የአዲስ ቆጣሪ የዱቤ አሰራር በሁለት ሳምንታት ብቻ 19,231 አዳዲስ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ማግኘት ችለዋል።

ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት 664,505 አዳዲስ ደንበኞችን ያገናኘ ሲሆን፣ በ2019 ዓ.ም. ደግሞ 1.1 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞችን ለማገናኘት አቅዷል።

ኢንጅነር ጌቱ እንደገለጹት፣ አገልግሎቱ በ70 ዓመታት ታሪኩ 5.88 ሚሊዮን ደንበኞችን ማገናኘት ችሏል፤ አሁን ግን በዓመት እስከ 1 ሚሊዮን ደንበኞችን የማገናኘት አቅም ላይ ደርሷል።

ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ/ም

@Gtutorialclass
2
ተጨማሪ መረጃ‼️
ዛሬ ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት አካባቢ በራያ አላማጣ ወረዳ በመረዋ ንዑስ ወረዳ የተፈፀመው የድሮን ጥቃት በአራት ዙር መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ገልፀውልናል።
እንደ የአካባቢው ምንጮች ገለጻ፣ ጥቃቱ:-
📌በመረዋ 2ኛ ደረጃ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተሰበሰቡ ታጣቂዎች ላይ
▪️📌በችግኝ ጣቢያው አካባቢ በተሰበሰቡ ታጣቂዎች ላይ
📌ከቤተ-ክርስቲያን አለፍ ብሎ ባለው ዋርካ (ዳዕሮ) ዛፍ ስር በተሰበሰቡ ታጣቂዎች ላይ
📌ሚይ ሓርማዝ በሚገኙ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው የተፈፀመው።
ጥቃቱ በአራት ዙር የተፈፀመ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ታጣቂዎች ተሰውተዋል።
የተጎዱ ታጣቂዎች ደግሞ ወደ አላማጣ ለህክምና ተወስደዋል። መረዋ አካባቢ በሚገኝ በአንድ የቤተክርስቲያን ዋሻ ውስጥ የህክምና አገልግሎት መስጫ አዘጋጅተው ነበር ተብሏል።
Please
Strive for👉🕊🕊🕊🕊🕊
=====================
💎👇👇👇👇👇👇👇
@Gtutorialclass
@Gtutorialclass
1👏1