G-Tutorialclass
813 subscribers
2.23K photos
29 videos
1.43K files
356 links
Impossible is possible with learning & reading.
Download Telegram
Forwarded from Free Education Ethiopia ︎ (π)
#Update

የግል ተፈታኞችን በተመለከተ የመቁረጫ ነጥብ ፦

- በተፈጥሮ ሳይንስ በግል የተፈተኑ ተማሪዎች (በሁሉም ፆታዎች) 385 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ።

- በማህበራዊ ሳይንስ በግል የተፈተኑ ተማሪዎች (በሁሉም ፆታዎች) 385 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ።

ከኢፌድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር (@MinistryoSHE) የመቁረጫ ነጥብን በተመለከተ የተላከልንን ዝርዝር መግለጫ ከላይ ያንብቡ ፤ ለሌሎችም ያጋሩ።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
ትናንት ሌሊት በአዲስ አበባ በ4 የተለያዩ አካባቢዎች የእሳት አደጋ ደርሷል።

በመዲናዋ ትናንት ሌሊት በአራት የተለያዩ አካባቢዎች በደረሰ የእሳት አደጋ ከ7 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ንብረት ወደመ!

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ ለኢዜአ እንደገለጹት የእሳት አደጋው የተከሰተው በአቃቂ ቃሊቲ፣ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለከተሞች እንዲሁም በየካ ክፍለ ከተማ በሁለት የተለያዩ አካባቢዎች ነው።

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው መልካ ሸኔ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ከምሽቱ 12:50 ገደማ በከብቶች በረትና በ7 አባወራ ቤቶች ላይ ቃጠሎ ደርሶ ውድመት አስከትሏል።

በአደጋው 9 ላሞችና ሁለት ጥጆች መሞታቸውን ተናግረዋል፡፡ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ወይራ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጀመስጂድ ቅጥር ግቢ በሚገኝ መጋዘን ላይ የእሳት አደጋ ተከስቷል።

በተጨማሪም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው "ስኩል ኦፍ ቱሞሮው" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሌሊት 6 ሰዓት ገደማ የመኖሪያ ቤት ላይ ቃጠሎ ተከስቷል።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 "መለስ ፋውንዴሽን" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሌሊቱ 4 ሰዓት ገደማ በአንድ ማተሚያ ቤት በደረሰው የእሳት አደጋ ጉዳት ደርሷል።

እንደ አቶ ጉልላት ገለፃ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ ወረዳ 8 የተከሰተው አደጋ መንስኤው አባወራዎቹ የወይራ ጭስ ለማጠን በተያያዘ እሳት መሆኑ ታውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
#ማስተካከያ‼️

ትላንት ይፋ በተደረገው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመቁረጫ ነጥብ ላይ የተደረገ ማስተካከያ (መስማት ለተሳናቸው እና ለአይነስውራን) እንደሚከተለው ቀርቧል።

ተፈጥሮ ሳይንስ ፦

- መስማት ለተሳናቸው ወንድ ተማሪዎች 275 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ

- መስማት ለተሳናቸው ሴት ተማሪዎች 270 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ

ማህበራዊ ሳይንስ ፦

- መስማት ለተሳናቸው ወንድ ተማሪዎች 270 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ

- መስማት ለተሳናቸው ሴት ተማሪዎች 265 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ

- ለአይነስውራን ወንድ ተማሪዎች 240 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ

- ለአይነስውራን ሴት ተማሪዎች 235 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ

መረጀውን ያገኘነው ከMoSHE ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ባለፈው ወር በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እና በኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን በተቀሰቀሰው ግጭት ከ300 በላይ ሰዎች እንደሞቱ እና 369 ደሞ እንደቆሰሉ የፌደራሉ እንባ ጠባቂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር እንዳለ ኃይሌ መናገራቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።

የኦሮሞ አስተዳደር ዞን አንድ ሃላፊ ደሞ በዞኑ ብቻ 68 ሰዎች እንደተገደሉ እና 114 እንደቆሰሉ ተናግረዋል።

ለግጭቱ መንግሥት የሰጠው ምላሽ የዘገየ እንደነበር የጠቀሱት የፌደራሉ እንባ ጠባቂ፣ አሁንም ፌደራል መንግሥቱ ችግሩን ለመፍታት ጣልቃ እንዲገባ መጠየቃቸውን ዘገባው አመልክታል።

ዋዜማ - ራዲዮ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
🔝 ምርጥ 11 ተማሪዋች (2012) 👏👏👏

1️⃣ 669 BROOK BALKACHEW NIGATU
ST.JOSEPH A-A(R) 361757
2️⃣ 665 NAOL BELETE ADUGNA
EXCEL(R) 342175
3️⃣ 657 AEMIRO DEMEMEW YILAKU
QUARIT(R) 40895
3️⃣ 657 BILEN MEHALEK DANA
WOLAYTA LIQA(R) 350501
5️⃣ 656 ABENEZER TADESSE AMANUEL
SCHOOL OF TOMORROW(YE)(R) 369782
6️⃣ 655 BINIYAM GETACHW MENA
WOLAYTA LIQA(R) 350502
6️⃣ 655 TADIWOS YEHUALASHET KEBEDE
KIDUS RAGUEL(R) 353940
8️⃣ 653 LEUL WUJIRA BERHE
ETHIO BIHERAWI(R) 354931
8️⃣ 653 NAOL SAMUEL EREGA
ODA-SPECIAL BOARDING(R) 342015
🔟 652 MILLION TOLESSA SEDI
WOMBERA(R) 277313
🔟 652 ISRAEL WOLDEGIORGIS WANGORE
WACHAMO(R) 292519

#SHARE
"...ግብፅ 2ኛው ዙር የሕዳሴ ግድብ ሙሌት ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ ለመጋፈጥ ዝግጁ ናት" - ኢንጂነር ሞሐመድ ጋኔም

[አል ዓይን ኒውስ]

የግብፅ ባለሥልጣናት በመጪው የክረምት ወቅት ሊሞላ ለታቀደው ሁለተኛ ዙር የሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ሀገሪቱ በመዘጋጀት ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡

የግብፅ መስኖ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢንጂነር ሞሐመድ ጋኔም ትላንት ለ “አል-አረቢያ” ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ፥ ግብፅ ሁለተኛው ዙር የሕዳሴ ግድብ ሙሌት ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡

ቃል አቀባዩ የግድቡን 2ኛ ዙር የውሃ ሙሌት ተጽዕኖ ለመቀነስ በመስኖ መስክ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ወደ ትግበራ መግባታቸውን አንስተዋል፡፡

“ይሁን እና በዓባይ ውሃ ላይ ያለንን ታሪካዊ መብት እንዳልተውን እናረጋግጣለን” በማለት በውሃ ክፍፍል ረገድ ግብፅ ያላት አቋም የጸና መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ቃል አቀባዩ አክለውም ፥ “በሕዳሴ ግድብ ጉዳይ የሁሉም ወገኖች ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የምንጥር በመሆኑ ኢትዮጵያ ከግብፅና ከሱዳን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ የተወሰነ የአቋም ለውጥ ማሳየት አለባት” ብለዋል፡፡

“መረጃ ከመለዋወጥ በፊት በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ላይ መድረስ እንፈልጋለን” ሲሉም ነው ኢንጂነር ሞሐመድ የሀገራቸውን አቋም የገለጹት፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በጎንደር ከተማ 168 ህገወጥ ቱርክ ሰራሽ  ሽጉጦች መያዙን የጎንደር ከተማው ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡

በመምሪያው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር እየሩስ አስማረ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት÷ ህገወጥ የጦር መሳሪያው የተገኘው በተለምዶ ህዳሴ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በግለሰብ ቤት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ነው፡፡

የመኖሪያ ቤቱ  ባለቤት ለጊዜው የተሰወሩ ሲሆን ግለሰቧን ለመያዝና የህገወጥ የጦርመሳሪያውን  ምንጭ ለማወቅ ፖሊስ እየሰራ መሆኑን ዋና ኢንስፔክተር እየሩስ አስማረ  ገልጸዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from Finance Today
በትግራይ ስምንት አካባቢዎች የነበሩ የጁንታው ወታደሮች እና ጠባቂዎች ተደመሰሱ - ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ
በትግራይ ስምንት አካባቢዎች የነበሩ የጁንታው ወታደሮች እና ጠባቂዎች መደምሰሳቸውን የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሠራዊት የሠራዊት ግንባታ ዘርፍ ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ አስታውቀዋል፡፡

የጁንታው ቡድን ወታደሮች እና ጠባቂዎች በትግራይ ሲያደርግ የነበረው የሽፍታ እንቅሰቃሴ በመከላከያ ሠራዊቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ውጊያ በማድረግ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ህገ ወጥ ቡድኑ ወደ መቐለ እርዳታ እና ሌሎች ነገሮችን ለማጓጓዝ የሚያስችሉ ወሳኝ ቦታዎችን በመያዝ ሲዋጋ የነበረ ቢሆንም በመከላከያ ሰራዊቱ ተደምስሷል ነው የተባለው፡፡

አሁን ላይ የጁንታው ወታደሮች እና ጠባቂዎች በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን እየሰጡ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
Forwarded from Free Education Ethiopia ︎ (BÊŽÂ)
❗️አዲሱ የዩንቨርስቲ ምርጫን በተመለከተ

📚 የሳይንስ እና የከፍተኛ ትምህርተ ሚኒስተር የሆነው ዌብሳይት ላይ Www.moshe.gov.et አዲስ መረጃ ወጥቷል ።መረጃውም ምደባ እንደቀድሞ እንዳልሆነ ተነግሯል ተጨማሪ 4 ዮኒቨርስቲዎች መጨመራቸው እና የዮኒቨርስቲ ምርጫችሁን በፊልድ ምርጫቹሁ መሰረት ነው የምትሞሉት...ማለትም ለምሳሌ አንድ ተማሪ አርክቴክት መማር ቢፈልግ አርክቴክት የሚሰጡ ግቢዎች የመጀመርያው ምርጫው ያደርገል ....ከዛም ሁለተኛው ምርጫው mechanical enegernig ቢሆን በምርጫው መሰረት ይህ ፊልድ የሚሰጡ ግቢዎች አስከትሎ ይሞላል ...እስከ ሮብ የዮኒቨርስቲ ምርጫችሁን እንደ አዲስ መሙላት እንዳለባችሁ አሳስበዋል ።


ዮኒቨርስቲዎች ምን ፊልድ እንደሚሰጡ በምን እናውቃለን

📚 እንደድሮ ሁሉም ካንፓሶች አንድ አይነት ፊልድ አይሰጡም ዮኒቨርስቲዎች በ4 ምድብ ተከፋፍለዋል ... ከታች በለቀቅንላችሁ pdf የትኛው ግቢ የትኛውን ፊልድ እንደሚሰጥ ማየት ትችላላችሁ ....ከፊልዶቹ ፊትለፊት ካሉ ዮኒቨርስቲዎች የ * ምልክት ካለ ፊልዱ ይሰጣል ማለት ነው ባዶ ከሆነ ፊልዱ አይሰጥም .... ስለዚህ ምርጫችሁ የሆነው ፊልድ የሚሰጥባቸውን ግቢዎች ብቻ የመጀመርያ ምርጫችሁ ታረጋላችሁ ማለት ነው....።


📚 በpdfኡ መጨረሻ ላይ የምትፈልጉት ፊልድ የሚሰጡ ካንፓሶች (ዮኒቨርስቲዎች ) ብዛት ይናገራል ለምሳሌ ለ software engenerig የሚሰጡ ዮኒቨርስቲዎች ብዛት 14 ነው ስለሆነም የእናንተ የመደመርያ ፊልድ ምርጫ ሶፍትዌር ኢንጂነሪግ ከሆነ በዛ መሰረት 14 ቱን አስቀድማተችሀ ትመርጣላችሁ ( ከ14ቱ ደሞ እናንተ እንዲደርሳችሁ በፈለጋችሁ ቅደም ተከተል መሰረት ትሞላላችሁ ..) ...ከዛም ቀጣዮን የፊልድ ምርጫችሁን የሚሰጡትን ዮኒቨርስቲዎች ትሞላላችሁ ማለት ነው ።

@Free_Education_Ethiopia

Stay safe 😷
Forwarded from Free Education Ethiopia ︎ (BÊŽÂ)
1618424833639.xlsx
309 KB
📚 ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጡትን filed የያዛ ዶክሜንት ..!

💾Excel file

@Free_Education_Ethiopia
Stay safe 😷
Forwarded from www.ayerlay.et
በመኖሪያ ቤቱ የተገደለው የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ መምህር!

ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ በራሱ ቤት የተገደለው የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪ ቀጄላ ታሲሳ ጉዳይ እያወዛገበ ነው፡፡

መምህር ቀጄላ ታሲሳ ትምህርታቸውን ከሚከታተሉበት አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ ወደ ደምቢዶሎ ያቀኑት ባለፈው ቅዳሜ መሆኑንና እሁድ ማታ በገዛ ቤታቸው በፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ቤተሰቦቻቸው ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡

የመመህሩ ወላጅ እናት ወ/ሮ አጊቱ ቡልቻ እንዳሉት ልጃቸው የዘጠኝ ወር እርጉዝ የሆነችውን ባለቤቱን ለመጠየቅና በዓልን አብሯት ለማሳለፍ ከሚማርበት አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቅዳሜ እለት መምጣቱን ይናገራሉ፡፡ እሁድ ማምሻውን 1 ሰዓት ከ 30 ገደማ “ቁጥራቸው በርከት ያለ ነው” ባሉት የመንግስት የጸጥታ ኃይል ልብስ የለበሱ የመኖሪያ ቤት አጥሩን ከበው ግድያ መፈጸማቸውንም ተናግረዋል፡፡

ይህንኑን ድርጊት ለመንግስት አሳውቃችኋል ወይ? ከዚህ በፊትስ መምህር ቀጄላ በፀጥታ ኃይሎቹ ተፈልገው ያውቃሉን? ሲል ዶይቼ ቬሌ ለወ/ሮ አጊቱ ቡልቻ ላቀረበው ጥያቄ ግድያውን ለማንም አለማመልከታቸውንና መምህሩ ከዚህ ቀደም ለሦስት ዓመታት ሲያስተምርበት የነበረው ደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲን የፀጥታ አካላት የት እንዳለ መጠየቃቸውን ብቻ በጭምጭምታ መስማታቸውን ተናግረዋል፡፡

መምህር ቀጄላ በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል በማግኘት ከሚያስተምርበት ደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ስፍራው ያቀናው ባለፈው መስከረም ነበር፡፡ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የቄለም ወለጋ ዞን የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተሰማ ዋሪዮ ጉዳዩ እንደሚባለው አይደለም ይላሉ፡፡ በጫካ የሚንቀሳቀስ ሸማቂ ቡድን “አባቶርቤ” በሚል የመለመላቸው ግድያውን ሳይፈጽሙት እንዳልቀረም ተናግረዋል፡፡

ከመመህር ቀጄላ ታሲሳ በተጨማሪ ሰሞኑን ብቻ በአከባቢው አራት ሰዎች ላይ ተመሳሳይ ጥቃት መፈጸሙንም በመግለጽ፤ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው ሁለቱ የመንግስት የጸጥታ አባላት ናቸው ብለዋል፡፡

የቄለም ወለጋ ዞን የጸጥታ አስተዳዳሪው በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች ታጣቂዎች እንደሚንቀሳቀሱና ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ግድያ መፈጸማቸውንም አብራርተዋል፡፡ ግድያውን ይፈጽማሉ ያሏቸው ታጣቂዎች የመንግስት የፀጥታ ልብስ ጭምር እንደሚጠቀሙም አክለዋል፡፡

©ጀርመን ድምፅ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from ANATSI FURNITURE
#Wolkite

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ "ሰላም እና አንድነት ለኢትዮጵያ ህዝብ " በሚል መሪ ቃል በወልቂጤ ከተማ አዘጋጅነት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ መነሻ አደርጎ የ15 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በመካሔድ ላይ ይገኛል።

ውድድሩን አትሌት ሻለቃ ዶ/ር ኃይሌ ገ/ስላሴ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ እንዲሁም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ፋሪስ ደሊል የመክፈቻ ንግግር በማድረግ አስጀምረውታል።

Via የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት

@ethio_mereja_university
@ethio_mereja_university
Forwarded from ANATSI FURNITURE
የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ግንቦት 29/2013 ዓ.ም እንደሚሰጥ በአንዳንድ የማህበራዊ ትስስር ገፆች እየተሰራጨ ያለው መረጃ ትክክለኛ አይደለም ተባለ።

ፈተናው መቼ እንደሚሰጥ ገና #አለመወሰኑን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።

የኤጀንሲው የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ረዲ ሽፋ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን አሁንም ገና እንዳልተወሰነ ገልፀዋል።

ኤጀንሲው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ሲደረስ በይፋ መግለጫ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።(tikvahuniversity)

@ethio_mereja_university
@ethio_mereja_university
Forwarded from ቦላሌ ቦንዳ via @like
መሃል ላይ ቀረን እኮ 😢

ፍትህ ለ 12+1 ተማሪዎች‼️‼️
#ምርጫ2013

የስድስተኛው አገራዊ ምርጫ ውጤት መቼ ይታወቃል?

አንዲት መራጭ ድምጽ ስትሰጥ
በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ ስድስተኛው ብሔራዊ ምርጫ እየተካሄደ ነው።

በዚህ ምርጫ ላይ በክልሎችና በፌደራል ምክር ቤቶች ውስጥ ላሉ መቀመጫዎች የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ተወዳዳሪዎች ይፎካከራሉ።

ዛሬ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ማለዳ ላይ የጀመረው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ቀን ሙሉ ሲካሄድ ውሎ፤ ምሽት 3:00 ሰዓት ላይ ይጠናቀቃል።

የድምጽ መስጠት ሂደቱ እንዳበቃ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የሕዝብ ታዛቢዎች የዕጩ ታዛቢዎች በሚገኙበት የድምጽ ቆጠራው ይጀመራል።

በቅድሚያ ደምጽ በየምርጫ ጣቢያው ይቆጠራል። ነገር ግን በጸጥታ መደፍረስ ወይም ተመሳሳይ አስገዳጅ ምክንያት ሲከሰት የምርጫ ጣቢያው የምርጫ አስፈፃሚ ለምርጫ ክልሉ ጥያቄ አቅርቦ ሲፈቀድ ወይም የምርጫ ክልሉ የምርጫ አስፈፃሚ ሲወስን የድምጽ ቆጠራው በምርጫ ክልሉ ጽህፈት ቤት ይካሄዳል።

ድምጽ አሰጣጡ እንደተጠናቀቀ የምርጫ ጣቢያው ኃላፊ የሚከተሉትን ተግባራት የድምፅ ቆጠራ ሳይጀመር በፊት ያከናውናል

ቆጠራ ለመጀመር የዕጩ ወኪሎች፣ ከሕዝብ የተመረጡ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት እና የምርጫ ታዛቢዎች እና ሌሎች ምርጫ አስፈጻሚዎች እንዲገኙ ያደርጋል፡፡

👉በቂ የተፈጥሮ ወይም ሰው ሰራሽ ብርሃን መኖሩን ያረጋግጣል

👉ለምርጫ ጣቢያው የደረሰውን የድምጽ መስጫ ወረቀት ብዛት ይመዘግባል

👉በዕለቱ ድምጽ የሰጡ መራጮችን ብዛት ይመዘግባል

👉የተበላሹና ሥራ ላይ ያልዋሉ የድምጽ መስጫ ወረቀቶችን ብዛት ይመዘግባል

👉ድምጽ ቆጠራ ከመጀመሩ በፊት የድምጽ መስጫው ሳጥን እሽጉ ያልተከፈተ፣ ሳጥኑም ያልተቀደደ፣ ወይም ብልሽት ያልደረሰበት መሆኑን መጀመሪያ የጠቀስናቸው አካላት በተገኙበት አረጋግጦ ቃለ ጉባኤ ይይዛል

👉ቀጥሎም ሳጥኑ ተከፍቶ ድምጽ የተሰጠባቸው ወረቀቶች በሙሉ ይወጣሉ

👉የድምጽ መስጫ ሳጥኑም ባዶ መሆኑ ይረጋገጣል፡፡

👉በመቀጠልም ምርጫው የተካሄደው ለተለያዩ ምክር ቤቶች ከሆነ ቆጠራው ለየብቻ ይካሄዳል። ለምሳሌ ለፌደራል እና ለክልል ምክር ቤቶች የተደረገ ምርጫ ከሆነ የሁለቱም ምክር ቤቶች ድምጽ ለየብቻ በየተራ ይቆጠራል እንዲሁም ወረቀቶቹ ይለያሉ።

የአንዱ ምክር ቤት ተቆጥሮ እና ለእያንዳንዱ ዕጩ የተሰጠው የድምጽ ቁጥር ተመዝግቦ እንዳለቀ የሌላው ምክር ቤት ቆጠራ በተመሳሳይ ይካሄዳል
በቂ ብርሃን የሌለ እንደሆነ የዕጩ ወኪሎች፣ ከሕዝብ የተመረጡ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት እና የምርጫ ጣቢያው ኃላፊ ይህንኑ በመግለጽ ቃለጉባኤ ይፈራረማሉ፤ ድምፆቹም ሳይቆጠሩ በጥበቃ ስር ይቆያሉ
የተቋረጠ የድምጽ ቆጠራ ሂደት በሚቀጥለው ቀን እጅግ ቢዘገይ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል
ከተጠቀሱት ሰዎች አንዱ በሂደቱ ላይ ቅሬታ ያቀረበ እንደሆነ የምርጫ ጣቢያው ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ጉዳዩን መርምሮ ወዲያውኑ ወይም ቢዘገይ ከ12 ሰዓት በማይበልጥ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል
ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴው የድምጽ ቆጠራው ሁኔታዎች እስኪጣሩ እንዲቋረጥ ወይም እንዲቆም እንዲሁም እንደ አስፈላጊነቱ ዳግም ቆጠራ እንዲካሄድ ሊወስን ይችላል

ይቀጥላል👇

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Forwarded from Free Education Ethiopia ︎ (BÊŽÂ)
#UPDATE_NEWS

እስከአሁን ለፍሬሾች ጥሪ ያደረጉ ዩንቨርሲቲ👇👇👇👇


ሰኔ
1. ደብረታቦር ..........26-29

2. ጎንደር .......... 23-24

3 .ሰመራ .......... 26-27

4. ወላይታ ሶዶ .......... 26-27

5 . ወሎ ..........29_30

6. ደብረብርሃን .......... 25-30

7. አሶሳ .......... 26-30

8. አዲስ አበባ ..........19-20

9. አምቦ .......... 24-25

10.ሐዋሳ .......... 21-22

11. ባህር ዳር ..........22-23

12.ደባርቅ ..........26-30

13. ወለጋ .......... 28-30

14. AASU ..........24-25

15. ዋቻሞ .......... 29-30

16. ወልቂጤ .......... 28 እና 29

17.መቅደላ አምባ .......... 27-29

18. ድሬደዋ .......... 27- 29

19. ዲላ ..........22-23

20.ጅማ .......... 24-25

21. ASTU .......... 24-25

22. ጋምቤላ ..........28-29

23. እንጅባራ ..........28-29

24. ወልድያ ..........29-30

25. ሰላሌ ..........24-25

26.ጂጂጋ ..........28-30

@Free_Education_Ethiopia

Stay safe
Forwarded from ANATSI FURNITURE
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ምዝገባ ከሰኔ 22 እስከ 23/2013 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደዩኒቨርሲቲው ሲሄዱ ሊይዟቸው የሚገቡ፦

• የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች
ዋናውና ኮፒው
• 3×4 ፎቶግራፍ (6)
• የመኝታ አልባሳት
• የስፖርት ትጥቅ

በ2012 ዓ.ም የአንደኛ ዓመት ተማሪ የነበራችሁ እና በመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርታችሁን ያቋረጣችሁ ተማሪዎችም በተገለፁት ቀናት ማመልከት ትችላላችሁ ብሏል ዩኒቨርሲቲው።
የምርጫ 2013 ዉጤት!

እስካሁን ይፋ የሆኑ ዉጤቶች እንደሚያመለክቱት ገዢዉ ፓርቲ ብልፅግና ተቃዋሚዎቹን በሰፊ ልዩነት እየመራ ነዉ።

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀዉ በየድምፅ መስጪያ ጣቢያዎች የተቆጠሩት ድምፆች እየተደመሩ በየደረጃዉ ወደሚገኙ የምርጫ ማስፈፀሚያ መዋቅሮች እየተላለፉና ዉጤቱም በይፋ እየተነገረ ወይም እየተለጠፈ ነዉ። አጠቃላዩ ዉጤት ግን አልታወቀም።

ከምርጫዉ በፊት የገዢዉ ፓርቲ ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናል ተብሎ ይጠበቅ የነበረዉ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የድምፅ አሰጣጡን «የከፋ» በማለት ቅሬታዉን አሰምቷል።

ኢዜማ ከ460 በላይ ስሕተቶች መመዝገቡን ገልጿልም።

ኢዜማ በምርጫው ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ ተብሎ ቢጠበቅም እንደተጠበቀው ሳይሆን መቅረቱን ተሰምቷል።

በሌላዜና አብን በአማራ ክልል በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ጠንካራ ፉክክር እያደረገ መሆኑን ከምርጫ ጣቢያዎቹ በሚወጡ ውጤቶች ለመረዳት ተችሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news