Eotc Task Force
7.25K subscribers
1.55K photos
348 videos
12 files
394 links
ወቅታዊ ጉዳይ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዘመናዊ የዘረፋ ስልት
🥰14👍5😁5
የከተማ መነኩሴ ሲነካ የሚንጫጩት እነ ማን ናቸው?
፩ ራሳቸው የከተማ መነኮሳት
፪ የምንኩስና መስፈርቱ ምን እንደሆነ የማያውቁ የግሪክ ልብስ የለበሰውን ሁሉ አባ የሚሉ ምዕመናን
፫ ፍትፍት ይዘው ወደ ከተማ መነኮሳት ቤት የሚንጦለጦሉ ሴቶች
፬ ከመነኮሳቱ ጋር ጥቅም የሚጋሩ
፭ የከተማ መነኮሳቱ ቤተ ክርስቲያንቱን እያዳከሙ መሆኑን የተረዱ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን
16👍6💯2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሁን ደግሞ "የወንጌል" ሰዓት ነው።መነኮሳቱና ካህናቱ እየተሰበኩ ነው። ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጳጳሳቱን ሰብስበው ከመጽሐፍ ቅዱስ እየጠቀሰ ሲሰብካቸው ነበር።ቤተ ክርስቲያናችን ከባድ ፈተና ውስጥ ናት።
😭269🔥3
የዚህ ስብስብ ዓላማው፦
👉ሕዝብን ከሕዝብ፣ሃይማኖትን ከሃይማኖት ማጣላት ፣የሕዝቡን አብሮ የመኖር እሴት መሸርሸርና ሀገርን ማፈራረስ ነው
28
ከቀሲስ ዶ/ር መንግሥቱ ጎበዜ

«ሞዐ ተዋሕዶ» የማነው?

ከወቅታዊ የሀገርና የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ጎልተው ከሚነሱ አጀንዳዎች መካከል አንዱ «ሞዐ ተዋሕዶ» ነው። ስለ ንቅናቄው ግልጽና የጠራ ግንዛቤ ይኖረን ዘንድ በተረዳሁት መጠን የሚከተለውን ምልከታ ማጋራት ወደድሁ።

«ሞዐ ተዋሕዶን» በተመለከተ ብዙ ግራ መጋባቶች ይስተዋላሉ። አንዳንዶች ሆን ብለው በሚመስል ሁኔታ ከዐውዱና ከዓላማው ውጭ የሆነ መረጃ በማሰራጨት፣ ንቅናቄው የፖለቲካ ዓላማ እንዳለው አድርገው በመሳል ብዙዎችን ያሳስታሉ። እንዲያውም «ሞዐ ተዋሕዶ» በአንዳንድ የመንግሥት አካላትም ሆነ በሌሎች የቤተ ክርስቲያን ተቃዋሚዎች በኩል የሚለጠፍበት አሉታዊ ስም፣ በተግባር ከሚሠራው በጎ ሥራ ጋር በፍጹም የሚገናኝ አይደለም። ከዚያም አልፎ ስሙን የመምቻ ዱላ በማድረግ፣ ኦርቶዶክሳውያንን ለማሳቀቅ፣ ለማሰር፣ ለማሳደድና ለማጥቃት እንደ ምክንያት ሲጠቀሙበት ይስተዋላል።

ሆኖም «ሞዐ ተዋሕዶ» ምንም ዓይነት የፖለቲካ ወገንተኝነት የሌለውና ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ሊጋሩት የሚችሉትን ዓላማ ሰንቆ የሚጓዝ ግብረ-ኃይል ነው። ዋና ግቡም ቤተ ክርስቲያንን ከጥቃት፣ ከስደትና ከጥፋት መከላከል ብቻ ነው። አንዳንዶች ሞዐ ተዋሕዶን ከ«ሞአ አንበሳ» ጋር በማመሳሰል ንቅናቄውን ከንጉሣዊ ሥርዓት መመለስ ጋር ለማያያዝ የሚያደርጉት ጥረት ፈጽሞ መሠረት የለውም። የግብረ-ኃይሉን ርእይ፣ ተልዕኮ፣ ግብና ተግባር ከግለሰቦች ማንነት ጋር ማያያዝም ትክክል እንዳልሆነ ተገንዝቤአለሁ።

የ«ሞዐ ተዋሕዶ» መነሻ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምት 2013 ዓ.ም. የምልዓተ ጉባኤው ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ያደረገውን ጥሪ መሠረት ያደረገ ነው። ሲኖዶሱ በምእመናንና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በመመልከት፣ ምእመናን ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የካቲት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በይፋ ተመሠረተ።

ሞዐ ተዋሕዶ በቤተ ክርስቲያኗ ላይ የሚሰነዘሩ መዋቅራዊ፣ አስተዳደራዊና ርዕዮተ-ዓለማዊ ጥቃቶችን ለመመከት የሚሠራ የጥብቅና ንቅናቄ (Advocacy Movement) ነው ማለት ይቻላል። ግብረ-ኃይሉ ለዘመናት የነበረውን «የዝምታ ስልት» በመስበር፣ የቤተ ክርስቲያኗን መብትና ድምፅ በግልጽ የሚያሰማበትን ሰላማዊ መንገድ ቀይሷል። ይህም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከዝምተኛ ተከታይነት ወደ «ንቁ ተሟጋችነት» የተሸጋገሩበትን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ያመላክታል።

«ሞዐ ተዋሕዶ» ከምሥረታው ዕለት ጀምሮ ለኢትዮጵያ መንግሥትና ለሚመለከታቸው አካላት ያቀረባቸው ሰባት ዋና ዋና ጥያቄዎችን በማስተጋባት ላይ ይገኛል። እነዚህም በትምህርት፣ በሚዲያና በልማት ስም የሚሰራጩ ጸረ-ኦርቶዶክስ ትረካዎች እንዲቆሙ፣ በመንግሥት መዋቅርና በኢኮኖሚ ላይ የሚፈጸም መዋቅራዊ ማግለል እንዲያበቃ፣ ቤተ ክርስቲያንን በብሔርና በቋንቋ የመከፋፈል ፖለቲካዊ ሴራዎች እንዲገቱ፣ በምእመናን ላይ የሚፈጸሙ አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ ጥቃቶች እንዲቆሙ፣ በጥፋተኞች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ተወስዶ ለተጎጂዎች ካሳ እንዲሰጥ፣ የተፈናቀሉ ምእመናን ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ፣ እንዲሁም «አዲሲቷን ኢትዮጵያ» በመገንባት ሰበብ የሚካሄዱ ኦርቶዶክሳዊ አሻራዎችን የማጥፋት ዘመቻዎች እንዲቆሙና መንግሥት ይፋዊ የይቅርታ መግለጫ እንዲሰጥ የሚጠይቁ ናቸው።

በአጠቃላይ፣ መገንዘብ እንደቻልሁት ሞዐ ተዋሕዶ በየትኛውም ዓይነት የፖለቲካ አሰላለፍ ያልወገነ፣ ዋና ዓላማውና ትኩረቱ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻና ብቻ የሆነ ንቅናቄ ነው። ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ የታሪክ እውነታ ሀገርና ቤተ ክርስቲያን ተነጣጥለው ስለማይቆሙ፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አወንታዊ አስተዋጽኦ ከማበርከት ወደ ኋላ አይልም። ሁሉም ኢትዮጵያውያን በፍቅርና በመከባበር የሚኖሩባት፣ ፍትሕ፣ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነባት ሀገር እንድትገነባ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።

እንደ እኔ መረዳት፣ በቤተ ክርስቲያኗ ላይ እየደረሰ ያለውን ዘርፈ-ብዙ ጥቃት ለመከላከል ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ የሚያበረክቱበት የትብብር መረብ በመሆኑ «ሞዐ ተዋሕዶ» የማንም ሳይሆን የሁሉም ነው። በአሁኑ ወቅት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በህልውና አደጋ ውስጥ የምትገኝ በመሆኗና ይህንን ሰፊና መዋቅራዊ ፈተና ለመመከት ይመጥናል ተብሎ የሚታመን ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት ባለመኖሩ፣ የጎደለውን ሞልቶና የጎበጠውን አቃንቶ እንደ «ሞዐ ተዋሕዶ» ያሉ ንቅናቄዎችን መደገፍ፣ ማበረታትና ማሳደግ ከመላው ኦርቶዶክሳውያን የሚጠበቅ ኃላፊነት ነው የሚል ጽኑ እምነት አለኝ።
20👍8
10🫡3
አርሲ ላይ እየሆነ ያለውን በትኩረት እየተከታተልሁ ነው። ወለጋ ላይ እነ ቄስ ዱጉማ ኡፋና ቄስ ደሲለኝ ነሞምሳን በኦነግ ሸኔ ያስገደለው ፣ቢሾፍቱ ላይ የወልዳ ዳንዲ አቦቲ(ፍኖተ አበው ማኅበር) ሰብሳቢ አቶ ንጉሤን አሳግቶ ደብዛው እንዲጠፋ ያደረገው ማፊያ ቡድን በአርሲም ያንኑ ታሪክ እንዳይደግም ያሰጋል።አሳቦቻችንና አይደግፉም የሚሉአቸውን ካህናትና ዲያቆናት ላይ በየሚዲያው "የግደለው ፍለጠው ቁርጠው" ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ናቸው።ቁጥራቸው ቀላል አይደለም ይኽን የጥፋት አጀንዳ የሚመራ ቡድን አለ።አርሲ ላይ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ላይ የሆነ ችግር ቢደርስ እነዚህም ልጆች ተጠያቂዎች ናቸው።በአዳማና በአሰላ ሆነው ይኽን የጥፋት ሴራ የሚመሩ ግለሰቦችን ከእነ ፎቶአቸው አጋልጣለሁ።
6👍63
እኔ የምለው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት "የጠለታ ቅዱስ ገብርኤልን እንሠራለን" እያለ ጥሩምባ ሲነፋ አልነበረም ወይ? "ከቁልቡ ገብርኤል ለጠለታ ገብርኤል" እየተባለ የሕዝቡ ኪስ ሲታጠብ አልነበረም ወይ?
19🤔2
"የባሰ አታምጣ" እያሉ ሃይማኖታዊ ጭቆናዎችን መታገስ መንፈሳዊነት ነው?
እርስዎስ መቼ ነው ከሥራዎ የሚታገዱት?ቀድሶ የሚያቆርብ እጅዎ በደም ቆሽሿልና።
😢28💯14🙈53😱2
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሰን አደረሳችሁ!!!
👏2726
የቤተ ክርስቲያን ችግር የሚስተካከለው መዋቅሩ ከላይ እስከታች ሲታከም ብቻ ነው።ጳጳሳቱና የከተማ መነኮሳቱ ቤተ ክርስቲያንቱን እያስተዳደሯት ሳይሆን እየጠቧት ነው።ቢቆጠሩ አምስት እንኳ የማይሞሉ ጳጳሳት ካልሆኑ በቀር አራት አምስት ፎቅ ያለሠራ የቤተ ክርስስቲያንቱን ካዝና ያላራቆተ ጳጳስ የለም።በቃ እውነት እውነቱን እንነጋገር ሌባ ሌባን ማገድ አይችልም።እነ አቡን ሳዊሮስ እነ አቡን ዲዮስቆሮስ በሌሎች ላይ እርምጃ መውሰዳቸው የሚበረታታ ቢሆንም እነርሱም ግን ከሁሉ የከፋ ጥፋት በ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲያደርሱ ኖረዋል አሁንም እያደረሱባት ነው።አቡነ ሳዊሮስ ከወሀቢያ ጋር ተሰልፈው ኦርቶዶክሳውያንን አስጨፍጭፈዋል እጃቸው በደም ተጨማልቋል ለብዙዎች አካል መጉደል ምክንያት ሆነዋል ከፖለቲከኞች በከፋ መልኩ በኦርቶዶክሳውያን መካከል ልዩነትን ተክለዋል ቤተ ክርስቲያንቱ የሥርዐቱ ሁለተኛው ጽ/ቤት አድርገውታል።አቡን ዲዮስቆሮስ በዘመነ ኢሕአዴግ የኢሕዴግ ሰው የነበሩ አሁን ደግሞ ተገልብጠው አሁን ያለውን ኦርቶዶክስ ጠል ብቻ ሳይሆን ኦርቶዶክስ በል ሥርዐት በካድሬነት በማገልገል ላይ ናቸው ይኽ ብቻ አይደለም ሀገረ ስብከታቸው ራያን ዘወር ብለው እንኳ አላዩትም ።አዎ ! ለውጥ እንዲመጣ ከተፈለገ ጳጳሳቱ በአደባባይ የበደሏትን ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ ይቅርታ ይጠይቁ።ሳዊሮስም እስከ ጥቅምት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን ይዘርፉታል የራሳቸውን ሰው በየመዋቅሩ ይሰገስጋሉ ከጥቅምት በኋላ ደግሞ እንደ እርሳቸው ቤተ ክርስቲያንቱን ለሥርዐቱ የሚያስገብር ጳጳስ ያስቀምጣሉ።እንደውም ከወዲሁ "ማርያ ቤዛ አትባልም፣የቤተ ክርስቲያን አዋልድ መጽሐፍት ተረትተረት ናቸው"በሚል የምንፍቅና ትምህርት የሚታወቁት አባ ገብርኤል እንዲሾሙ የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ተጀምሯል።
😭2013👍6
የገጽታ ግንባታ አገልግሎት መሆኑ ነው። የምንገደለው በ ቤተ መንግሥትና ቤተ ክህነትና ትብብር ነው የምንለው ለዚህ ነው።በአጭር ቃል ቤተ ክህነቱ በልጽጓል ።
24😁5👍2😭2