Eotc Task Force
7.23K subscribers
1.56K photos
349 videos
12 files
397 links
ወቅታዊ ጉዳይ
Download Telegram
📝የገዳማውያኑ ጥቃት ሥርዓታዊና ጥላቻን ያዘለው ስልት ቀጣይ ምዕራፍ ነው!


©በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ የአቋም መግለጫ

👉ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ 4:00 ላይ በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ የሚገኘው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጽሞ 2(ኹለት) መነኮሳይያት እናቶች ወዲያው ሲገደሉ፣ 14(አሥራ አራቱ) እናቶች ደግሞ ክፉኛ ቆስለው መካነ ሰላምና ደሴ ሆስፒታል ተወስደዋል። በጥላቻና ኾነ ተብሎ በሚመስል መልኩ በተፈጸመው ጥቃት የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲኾን፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሐ ማጠራቀሚያ የኮንክሪት ታንከር፣ የውሐ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ሙሉ በሙሉ ወድማል። "በገዳሙ ሥርዓት የጠዋት 3:00 ፀሎት አድርሰን ኹሉም ወደተመደበበት ሥራ ሲሠማራ ድሮን የምትባለው ስትዞርና ድምጿን ሰምተናል፣ አይተናታል። እኛ ገዳማውያን ነን መቸም ቴክኖሎጂ ነው ያዩናል ምንም የሚያጠራጥርና የሚያስፈራን ነገር የለም ብለን ሥራችንን ቀጠልን" የሚሉት እማኝ "ነገር ግን እኛ እንዳስብነው አልነበረም ቆይተው ለሥራ በተሰበሰብንበት መዓት አወረዱብን፣ ያን የመሰለ ጭካኔ ለምን ማድረግ እንዳስፈለጋቸው ማሰብም ማለምም ይከብዳል። በተለይ የቆሰሉት ሲታዩ የሞቱት ይሻላል ያስብላል" ይላሉ።

👉ገዳሙ እጅግ ከባድ በረሃ ላይ ያለ ነው። በዙሪያው የሚገኝ ታጣቂም ይኹን ወታደር አናውቅም። እንግዲኽ ገዳሙ የቆመውም በእነዚኹ ወጣት መነኮሳይያት እናቶችች ድካም ነበር። ሠሪው ከተገደለ፣ አካሉ ከጎደለና የዓመት ቀለቡ ከወደመ ቀሪውንም የመግደል ያኽል ነው። ተጠንቶ የተደረገ ይመስላል ይላሉ ሌላው እማኝ።

👉እናት ፓርቲ ይኽ እብሪት የተላበሰ ድርጊት ከድግግሞሹ፣ እያስከተለ ከሚገኘው ጉዳትና በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ በታጣቂዎች ሽፋን በእምነቱ ተከታዮች፣ አገልጋዮችና ገዳማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት ተራ ስህተት ሳይኾን ሥርዓታዊና ከጥላቻ የመነጨ ብሎም የአጥፍቶ መጥፋት ተግባር እንደኾነ በጽኑ ያምናል፤ ድርጊቱንም በጽኑ ያወግዛል። ለሞቱት ገዳማውያንም ሐዘኑን እንገልጻለን።

ስለኾነም፣
1. መላው ኢትዮጵያውያን ይኽን የአጥፍቶ ጠፊ የሽብር ድርጊት በአንድነት እንዲያወግዝ እንጠይቃለን።

2. መንግሥት ለድርጊቱ ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድና ድርጊቱ ሲፈጸም የሚያሳይ የፎቶና የቪዲዮ መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡

3. ሀገርን ከጥቃት ለመጠበቅ የተቋቋሙ ተቋሟት ሕዝብን ጅምላ ጨረሽ ወደመኾን መሸጋገራቸው መላው ሕዝባችንና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያውቀው እና አጥፊው አካል ተጠያቂ እንዲደረግ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡

4. መላው ኢትዮጵያውያን በዚያ ሐሩር ለሀገርና ሕዝብ የሚፀልዩ ገዳማውያን ቀለባቸው እና የመጠጥ ውሐ በጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ቀሪዎቹ በረሃብና ጥም ከማለቃቸው በፊት እንዲደርስላቸው እንጠይቃለን።

ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝባን ይጠብቅ!

©እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

         
12👍4🥱2
👍9
ወሀቢዝም እንዴት እና መቼ ወደ ኢትዮጵያ ገባ?

ከወሀቢዝም በፊት የነበረው ሁኔታ
የእስልምና አመራሮች በአካባቢ ሸህዎች እና ታላላቅ መምህራን ነበሩ
መስጊዶች እና ዛውያዎች (Sufi lodges) ዋና የሃይማኖት ማዕከላት ነበሩ
ከክርስቲያን ማህበረሰብ ጋር ብዙ ጊዜ ሰላማዊ መኖር ነበር

ከወሀቢዝም በፊት የኢትዮጵያ እስልምና:
በሱፊ ትምህርት የተመሠረተ
ከአካባቢ ባህል ጋር የተዋሃደ
የመቃብር ክብርን የሚቀበል
በረጅም ታሪክ የተገነባ

ወሀቢዝም ወደ ኢትዮጵያ በቀጥታ አልገባም፤ በኔትወርክ(ትስስር) መንገዶች ቀስ በቀስ ተስፋፋ።

(ከ1920-1950 ዓ.ም)
በቀይ ባህር በኩል ባለው  የንግድ ትስስር ወደ ኢትዮጵያ ገባ
ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለሐጅ እና ለትምህርት  ወደ መካ ይጓዙ ነበር።
ትምህርቱን የተማሩ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ  ከነባሩ እስልምና የተለየ "አዲሱን እስልምና(የወሀቢዝምን አስተምህሮ) "ይዘው ገቡ
የወሀቢ ተቋማት በዚያ ዘመን አልነበሩም።
እስልምና በሱፊ ትምህርት ተመስርቶ ነበር።
የኢትዮጵያ  ሙስሊሞች ሙሉ በሙሉ የሱፊ ተከታዮች ነበሩ

     19560-1970 ዓ.ም
  በተቋም ደረጃ መግባት
     በትምህርት ዕድሎች (Scholarships)ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ የሚሄዱ የሙስሊሞች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ
የሳዑዲ የወሀቢዝም  መጽሐፍት በኢትዮጵያ ውስጥ  ተሰራጩ።
አዲሱ ሳዑዲ ዓረቢያን እስልምና የሚያስተምሩ መምህራን አዲስ አበባ ገቡ
ነባር ሙስሊሞች(ሱፊዎች) ላይ ትች ተጀመረ
ደርግ የሃይማኖት እንቅስቃሴን ገድቦት ስለነበር ወሀቢዝም ለጊዜው ቀስቀስ ብሎ ነበር

            ከ1980-2000ዓ.ም
ወያኔ Dismantle Orthodox Strengthening Islam(ኦርቶዶክስን ማክሰም እስልምናን ማጠንከር)የሚል መርሕ ይዞ በመምጣቱ ያሻቸውን ያደርጉ ዘንድ በሩ ክፍት ሆነላቸው
የገልፍ  የግል እርዳታ ድርጅቶች መስጊዶችን  እና ትምህርት ቤቶችን ገነቡ
በአዲስ አበባ፣ ባሌ፣ አርሲ እና ወሎ ተስፋፋ
የሶማሊያ መንግሥት መውደቅ ምቹ ሁኔታ ፈጠረላቸው
በሚዲያ(በካሴት፣በቲቪ እና በ ኢንተርኔት )መስፋፋት ጀመረ
ይኽን እሳቤ የሚያራምዱ ሰዎች ወደ ፖለቲካው ከመግባት አልፈው ኢስላማዊ ፓርቲዎችን እስከመመሥረት ደረሱ
ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥቃት መሰንዘር በአርሲ፣በባሌ፣በሐረርጌ፣በወሎ፣በሀላባ፣በሥልጤ ወዘተ...
ዋና የመግቢያ መንገዶች ጠቅለል ተደርገው ሲቀርቡ
ሐጅ እና ኡምራ
በሳዑዲ የተማሪዎች ስኮላርሺፕ
የገልፍ ኤንጂኦዎች(NGOs)  መስጊዶች እና ትምህርት ቤቶች ግንባታ
የሃይማኖት መጽሐፍት እና ሚዲያ
የሃርጦስ የአፍሪካ(Horn Of Africa) እና ኢትዮጵያ አካባቢ አውድ ኔትወርክ

ይቀጥላል...
https://t.me/EotcTaskForce
ወሀቢያ ከ2000ዓ .ም በኋላ በኢትዮጵያ የተስፋፋባቸው መንገዶች
1) የገልፍ(Saudi ,UAE,Oman ,Qatar etc..) ፋይናንስና የኤንጂኦ አውታረ መረብ
2000 በኋላ ዓለም አቀፍ ሳላፊ/ ወሀቢዝም ተጽእኖ በተለይ በየግልፍ ፋይናንስ የተደገፉ ሃይማኖታዊ ተቋማት እየተስፋፋ መጣ፡
👉ወደ ሳውዲ አረቢያ ለትምህርት የሚሰጥ የተማሪዎች ድጋፍ (ለምሳሌ በመዲና እና በራዲያድ ዩኒቨርሲቲዎች).
በኦሮሚያ፣ ሶማሌ ክልል፣በአማራ ክልል  ደቡብ ወሎና ከሚሴ፣በደቡብ፣ አፋርና በአዲስ አበባ አካባቢ ለመስጊድ  ሕንፃዎችና ኢስላማዊ ማዕከላት ለማስፋት የተደረገ  የፋይናንስ ድጋፍ.
ከገልፍ ወጣቶች ጋር የተያያዙ ኢስላማዊ በጎ አድራጎት ድርጅቶች
2) ዲያስፖራ እና የሥራ ፍለጋ ስደት
ከ2000 ዓ.ም በኋላ ወደ ሳውዲ አረቢያና ገልፍ ሀገራት ለሥራ ፍለጋ የሚወጡ የሙስሊሞች ቁጥር እጅጉን እየጨመ መጣ።
ከሳውዲ አረቢያ የሚመለሱ ኢትዮጵያዊ ሰራተኞች አዲሱን የሳላፊ እምነትን(ወሀቢዝምን) አስተምህሮዎችን ያንጸባርቃሉ
ሀጅና ኡምራ ሄደው የጅሃዲስት እሳቤን ይዘው ይመለሳሉ

3 ሚዲያና ሳተላይት
የዓረቢኛ ቋንቋ  በሳተላይቶች መሰራጨት
ዩቲዩብ፣ቲክቶክና ፌስቡክን ለጅሃድ ቀስቃሽነት ፣ለሥልጠና መጠቀም
የነባሩን የሱፊን እምነት ለመወጣ ትምህርቶቻቸውን በOnline ማስተማር(fatiwaመስጠት)
4) መጅሊሱን መቆጣጠር
5) በሶማሊያ እና በፑንትላንድ  የአልሸባብ እና የአይኤስአይስ እየተጠናከረ መምጣት
የኢትዮጵያ ወጣት ሙስሊሞችን ለውትድርና መመልመልና አሠልጥኖ ወደ ሀገር መላክ
ወደ ኢትዮጵያ ድንበሮች ዘልቆ መግባት ወታደራዊ የሥልጠና ማዕከላትን መገንባት(ምሳሌ :-አልሸባብ በ ባሌ በረሃ)
በሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር በቀል ወሀቢዮች የ ፋይናንስ፣የ ጦር መሳሪያና የርዕዮተዓለም ድጋፍ ማድረግ

ይቀጥላል...
https://t.me/EotcTaskForce
6😁2
እነዚህ ሰዎች እንዲህ ዓይነት አጀንዳዎችን የሚያመርቱት ለእነርሱ ምላሽ በመስጠት ጊዜያችንን እንድናባክን ከዋናው አጀንዳችንም እንድንወጣ ነው።ንቁባቸው።
👍166🔥2
መግለጫ ለምን ይወጣል?

፩ በቤተ ክርስቲያንቱና በአማኞቿ ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን ለማሳወቅ
፪ መንግሥት ሀላፊነቱን እንዲወጣ ማሳሰብ እና ማስጠንቀቅ
፫ መንግሥት ሀላፊነቱን የማይወጣ ከሆነ እርምጃ ለመውሰድ ኦርቶዶክሳውያንን ከጥፋት ለመታደግ
የእኛዎቹ ግን ስምንት ዓመት ሙሉ መግለጫ ያወጣሉ አንድም ጥቅም አላስገኘም ።ሲኖዶሱ የሚሰጣቸው መግለጫዎች ፦
👉 እናዝናለን፣አዝነናል ሲሉ እንኳን ቅዱሱ የሰው ልጅ  ከብት እንኳ የሞተባቸው ያክል አይሰማቸውም
👉እልቂታችንን የሚሸፍንና ቀጣይነት እንዲኖረው ያደርጋል
👉ለገዳዮች ሳይቀር ጥብቅና ይቆማል
👉ሕዝቡ ራሱን እንዲከላከል ወይም ሸሽቶ ራሱን እንዲያተርፍ አቅጣጫ አያሳይም
👉እየተነጋገርን ነው እየተወያየን ነው፣አጣሪ ኮሚቴ አቋቋመናል ወዘተ...እያለ  የመንግሥትን አጀንዳ ያስፈጽማል

  መፍትሔው ምንድን ነው?

👉ኦርቶዶክሱ ከአጥፊዎች የሚታደገው እረኛም ሆነ  መዋቅር እንደሌለው  አውቆ ራሱን በራሱ ይጠብቅ
እንዴት አድርገን ራሳችንን በራሳችን እንጠብቅ የሚለውን ከቤተሰቦቻችን ፣ከጓደኞቻችን፣ከሰን/ቤት፣ከማኅበራት ጋር መምከር።ቅር ብንለው እንኳን የማይቀር ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ መከራ ከፊትታችን ተደቅኗልና ከድንዛዜ ነጻ አዉጪ ከመጠበቅ እንውጣ ።

   አንባቢው ይኽን ያስተውል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሰው ሁለተናዊ ጥቃት በመንግሥት እውቅና ተሰጥቶት የሚፈጸም ነው
በእረኞቻችን ተክደናል ገንዘባችንን እንጂ እኛን አይፈልጉንም
የራሳችንን ድርሻ ካልተወጣንና ካልሠራን አሁን ባለንበት ሁኔታ ከቀጠልን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ሆና እንዳትቀር ያሰጋል
👍134👏3
ይድረስ ለቅዱስ ፓትርያርክ አባ ማቲያስ

ቅዱስ አባታችን ሆይ፤

በመጀመሪያ በልዑል እግዚአብሔር ስም ሰላምታችንን እያቀረብን፤ ይህን መልእክት ለመላክ የተገደድነው በቤተ ክርስቲያናችን እና በልጆችዋ ላይ እየወረደ ያለው የመከራ ዶፍ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት መሆኑን እንገልጻለን።

ለ ስምንት ዓመታት  በየጊዜው የሚወጡ የ"እናዝናለን" መግለጫዎችን መስማትና ማንበብ ሰልችቶናል። እነዚህ መግለጫዎች የሕዝባችንን ሞት፣ ስደት እና የቤተ ክርስቲያናችንን ውድመት ሊያስቆሙልን አልቻሉም። ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግሥት ያሉትን ተፅዕኖዎች የምንረዳ ቢሆንም፣ ቅዱስነትዎ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት እውነትን መስክረው ቤተ ክርስቲያንን የማስቀጠል እና ልጆችዎን ከጥፋት የመታደግ መንፈሳዊና አባታዊ ሀላፊነት አለብዎት።

ሥርዐቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እያደረሰ ያለው ተፅዕኖ በመግለጫ እና በልምምጫ ሊቆም እንደማይችል ከእኛ ከልጆችዎ በላይ ጠንቅቀው ያውቃሉ ይረዳሉ።

ስለሆነም የልጆችዎ የጅምላ ፍጅት እና የቤተ ክርስቲያን ውድመት በእውነት የሚያሳስብዎ ከሆነ፤ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን አማራጮች ተግባራዊ እንዲያደርጉልን በትሕትና እንጠይቃለን፦

1. ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጉዳዩን ማሳወቅ፦
   ሥርዐቱ በቤተ ክርስቲያናችን እና በልጆችዋ ላይ እያደረሰ ያለውን ፍጅት እና በደል በይፋ ለሚከተሉት አካላት በደብዳቤ እንዲያሳውቁልን፦
   👉ለአኃት አቢያተ ክርስቲያናት
   ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) እና ለሰብአዊ መብት ምክር ቤት
   👉ለዓለም አቀፍ ሃይማኖቶች ፓርላማ እና ለምክር ቤቶች
    👉ለዓለም ሃይማኖትና እምነት ነጻነት ሲቪል ማኅበራት ኮሚቴ
    👉ለዩኔስኮ (UNESCO)
    👉ለዓለም አቀፍ ፍትሕ ፍርድ ቤት (ICJ)
👉ለአፍሪካ ኅብረት
   👉ለዓለም ሀገራት መሪዎች እና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ
2. መንፈሳዊ ውሳኔ መስጠት፦
   ይህን ማድረግ የማይቻል ከሆነ፤ "ልጆቼን መጠበቅም ሆነ መታደግ አልቻልሁም" በማለት መንፈሳዊ ኃላፊነትዎን በመወጣት ወደ ገዳም (ለምሳሌ አቅራቢያ ወደሚገኘው ደብረ ሊባኖስ ገዳም) በመግባት በጸሎት እንዲወሰኑ።
እነዚህን እርምጃዎች መውሰድ ከኅሊና፣ ከታሪክ እና ከእግዚአብሔር ፍርድ ነጻ የሚያወጣ እርምጃ ነው ብለን እናምናለን።

ቅዱስ አባታችን ሆይ፥አሁን ባለው ሁኔታ  የ"እናዝናለን" መግለጫ ብቻ እያወጣን እንቀጥላለን ብለው የሚያስቡ ከሆነ ግን እርስዎም  ኦርቶዶክሳውያንን የማጥፋት መንግሥታዊ ፕሮጄክቱን ይደግፋሉ ወደ ሚለው ድምዳሜ ለመድረስ እንገደዳለን። አዎ  የ"እናዝናለን"መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣
አጥፊን የማይከስስ እና ተጎጂዎችን የማያስክስ የማጭበርበርና ከገዳዮች ጋር የመተባበር ተምሳሌት የሆነ ልፍስፍስ መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣፣ ገዳዩን ሥርዐት የማይከስና ፍትሕን የማያሰፍን  መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣እልቂታችንን የማያቆም መግለጫ መስማት ሰልችቶናል


ለሁለም ይደርስ ዘንድ ሼር በማድረግ እንተባበር
https://t.me/Eyo21e
25😁2
11
ይኽን መልእክቱ የፌስቡክም በቲክቶኩም በማጋራት እንተባበር
17
10
#ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19)

ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው። 

ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው። 

ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ። 

መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ። 

በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። 

ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው። 

ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና። 

ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው። 

ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ ➛ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ)
🥰132
የእኛ ትልቁ ችግር ወይ አንሠራም ወይ ደግሞ የሚሠሩትን አናግዝም።እርግጠኛ ሆኜ የምናግራችሁ ሁላችንም በአንድ ቃል ቅዱስ ፓትርያርኩ ላይ ጫና ብናሳድርባቸው ለውጥ ማምጣት እንችላለን ።አንፍራ አናስመስል እውነትን በፍቅር እንናገር ።መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ እናጋራው።
ሳር አምባ፣ፍኖተ አበው፣ፍኖተ ርቱዓን ሬድዮ እና ሞዐ ተዋሕዶ እናመሰግናለን።እንደነዚህ ዓይነት ሚዲያዎችን ማበረታታት ማሳደግ ያስፈልጋል።
33
"ሃይማኖትህን ስትቀይር መጤ ትሆናለህ! "
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በ Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል

አምስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ጓደኞሞች ነበሩ።በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት በአንድ ትምህርት ቤት አብረው ተምረዋል።ሆኖም ወደ ተለያዩ ዩኒቪርሲቲዎች ተመደቡና ተለያዩ።ከረጅም ዓመታት ተጠፋፍተው በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ተገናኙ። ተነፋፍቀው ነበርና በአካል ሊገናኙ ተቀጣጥረው ተገናኙ።

በቆይታቸው በህይወታቸው የተለያዩ ለውጦች ተስናግደዋል። አራቱ እምነታቸው ቀይረዋል።አንዱ ሙስሊም፣ ሌላው ካቶሊክ፣ሌላኛው ፕሮቴስታንት ሲሆን አንዱ ደግሞ የጆቫ እምነት ተከታይ ሆነዋል። እምነቱን ከኦርቶዶክስ ያልቀየተው ጓደኛቸው የኦርቶዶክስን እምነትን በመቀየራቸው ክፉኛ አዘነ። ዉስጡንም ንዴት ሞላው።

ሻይቡና ካሉ በኋላ ስለኢትዮጵያና ስለእኩልነት ሲወያዩ የኦርቶዶክሱ ጋር የሀሳብ ልዩነት ተፈጠረ።
በአንድ ሀገር ተወልደው አድገው፣ከአንድ ህዝብ ወጥተው፣ አንድ የኦርቶዶክስ እምነትን ሲከተሉ እንዳልነበር ዛሬ ላይ እምነታቸው ቀይረው ስላገኛቸው በቁጣ ተሞልቶ "እናንተ መጤዎች! ከኛ ከነባሩ ሕዝብ ጋር ሀገርን በእኩልነት እንጋራ ለማለት ደረሳችሁ? ይህ ድፍረት ነው! ኦርቶዶክስ ሀገር ያቆመች።ፊደል ቀርጻ ትውልድ ያስተማረች። እናንተ ተሰዳችሁ ስትመጡ የተቀበለች ነች።" እያለ ተናገራቸው። በሁኔታው አዘኑ። አንደኛው "እምነት መቀየር መጤ የሚያደርግ ከሆነ፣ሁላችንም መጤ ነና?"።

የካቶሊክ እምነት ተካዩ ደግሞ "እምነትን ከኦርቶዶክስ ወደ ሌላ መቀየር መጤ የሚያደርግ ከሆነ፣እናንተ ኦርቶዶክስን የኢትዮጵያዊነት ብያኔ ማዕከል አደርጋችኋል ማለት ነው።

ኦርቶዶክስ ከሌላው በተለየ የሀገር ባለውለታ ከሆናች ያንን ዉለታ ማን ላይ የምትቆጥረው? እኛም ዉለታ የተባለው ነገርን ኦርቶዶክስ እያለን አብረን ያበረከት ነው።" አለ።

ሙስሊሙ ወንድም አከለ"ኦርቶዶክስ በ7ኛ ክፍለ ዘመን የነቢዩ ሙሐመድ(ሰ. ዐ. ወ) ተከታዮች ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት አለኝ ብላ በምትቆጠረው ታሪክና ስልጣኔ ሁሉ የብቻዋ አይደለም። ኦርቶዶክስ የነበሩና እምነታቸውን ወደ ኢስላም የቀየሩ ኢትዮጵያውያን ጭምር ነው።" አሉ።

ፕሮቴስታንቱም ቀጠለ "ለእኛ የወንጌላውያንም እንደዚሁ ነው።ከ19ኛ ክፍለ ዘመን ወንጌላውያን እምነቱን ወደ ኢትዮጵያ ከማምጣታቸው በፊት ኦርቶዶክስም፣ሙስሊሞችም ሆኑ ካቶሊካውያን በኢትዮጵያ የሠሩት ታሪክ፣ገድል፣ስልጣኔና አሻራ ሁሉ እኛ ወንጌላውያን እነዚያን እምነቶችን በምንከተልበት ጊዜ አብረን የሠራናቸው ናቸው። እንደ ግል ደግሞ የዛሬ 5 ዓመት ወንጌላዊ ከመሆኔ በፊት ኦርቶዶክስ አለኝ በምትለው ነገር ሁሉ አለሁበት።ያኔ የነበረኝ አስተዋፅኦና ስፍራ እምነቴን ስለቀየርኩ ብቻ የትናንት ድርሻዬ አይሻርም።" አለ።

ሙስሊም በማስከተል እንዲህ በማለት ሀሳቡን ማብራራት ቀጠለ "ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን መስሊሞች በመሆናቸው ብቻ መጤ አድርጎ የሚፈርጀው ይህ የደናቁርት ርዕዮተ ዓለም እያለ ያለው ዐማራ ሙስሊሞች እምነታቸው ኢስላም ስለሆነ ብቻ መጤ ናቸው፥ ክርስቲያን አማሮች ግን ኢትዮጵያዊ ናቸው፤

ትግራዋይ ክርስቲያኖች ኢትዮጵያዊ ናቸው፤ ሙስሊም ትግራዋይ ግን መጤ ናቸው፤ ሲዳማ ክርስቲያኖች ኢትዮጵያዊ ናቸው፤ ሙስሊም ሲዳማዎች ግን መጤ ናቸው፤ ክርስቲያን ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ነው፤ ሙስሊም ኦሮሞ ግን መጤ ነው፤ እያላችሁ መሆኑን አስተውላችኋልን?"

የጆቫ እምነት ተከታዩም ቀጠለ "አንድ የትግሬ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ ወይም የሌላ ብሔር አባል የሆነ ሰው ሃይማኖቱን ሲቀይር የዉስጥ ማንነቱ መገለጫ «ዲ ኤን ኤው» (DNA) ወይም የዘር ግንዱ አይቀየርም። ሃይማኖቱ ተቀየረ እንጂ የብሄር ወይም የዘር ማንነቱ አይቀየርም።" በማለት አብራራ።

ማጠቃለያ
🌺🌺🌺🌺

ሀ) ኢትዮጵያዊነት የጋራ ቤት እንጂ የአንድ ክፍለ ዘመን ዉርስ አይደለም።
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥

አንድ ሰው እምነቱን ሲቀይር የቀደሙ አባቶቹ (እርሱ) ከጥንት ጀምሮ የገነቡትን ሀገር አያጣም።አይሁድ፣ኦርቶዶክስ አልያም ሌላ እምነት ተከታይ እያለ የከፈለው መስዋዕትነት፣ የሠራው ታሪክ እና ያቆየው ቅርስ እምነቱን ሥለቀየረ ብቻ ባለቤትነቱ አይነፈግም። "የኔ አይደለም" ብሎም አይጥለውም።ሌላውም ሊገፋበት አይችልም።

ለ) ታሪክን በሃይማኖት ብቻ መመዘን ታሪካዊ ስህተት ነው!
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

የኢትዮጵያ ታሪክ የሃይማኖት ታሪክ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ፣የግብርና፣የቋንቋ፣የክነ ሕንጻ፣የእውቀት ስርጭት፣የሀገር ግንባታ፣የሥልጣኔ፣የሉዓላዊነት፣ የንግድ፣የባህል፣ወዘተ ታሪክ ድምር ነው። በነዚህ ሁሉ የተሳተፊት ከሁሉም ኢትዮጵያውያን የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን እንጂ የአንድ ሃይማኖት ተከታዮች ብቻ አይደሉም።

ሐ)ዜግነት በሕግ፣ሃይማኖት በነጻነት!
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
ዜግነትና ሀገራዊ መብት የሚወረሱት ወይም የሚገኙት በደም(በወላጆች) እና በሕግ እንጂ በሃይማኖት ምዝገባ አይደለም። ሃይማኖት የምርጫ ጉዳይ እንጂ የሀገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ አይደለም።

መ)መጤነት በሃይማኖት ከሆነ ኦርቶዶክሶችም መጤዎች ናቸው።

.
.
#የአህመዲን ጀበል ማደንዘዣ እና እስልምናን የሀገር ባለውለታ ማድረግ እና ኦርቶዶክስን ጨቋኝ ለማለት እንዲሁም ቤተክርስቲያን ምንም የኢትዮጵያ አሻራ እንደሌላት የማሳየት ዘዴ
👍84