TIKVAH-ETHIO
663 subscribers
661 photos
27 videos
7 files
74 links
Download Telegram
#US #EU #USEmbassyAA

አሜሪካ በድጋሚ ተኩስ እንዲቆምና ድርድር እንዲጀመር ጠየቀች (ይህን ስትል በዚህ ሳምንት ብቻ ሁለተኛዋ ነው)

የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን በሰሜን ኢትዮጵያ የቀጠለው ጦርነት አሜሪካን እጅግ እንዳሳሰባት አሳውቀዋል።

ብሊንከን ጦርነቱ በስፋት መዛመቱ ሰብዓዊ ቀውሱን እንደሚያከፋው ጠቁመዋል።

ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በድርድር ላይ የተመሠረተ ተኩስ አቁም እንዲያደርጉም በመግለጫቸው ላይ አሳስበዋል።

ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተጨማሪ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኙነር ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል ሁሉም ወገኖች ያለ ቅድመ ሁኔታ ተኩስ እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቱን እንዲያቀላጥፉ እና የጥላቻ ንግግሮችን እንዲያቆሙም አሳስበዋል።

የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ በአፍሪካ ቀንድ የአፍሪካ ኅብረት ልዩ ልዑክ ኦሌሴጎን ኦባሳንጆ ቁልፍ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ ህብረቱ እምነቱን ገልጿል።

በሌላ መረጃ ፦

አዲስ አበባ ያለው የአሜሪካ ኤምባሲ በሰሜን ኢትዬጵያ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ እንደሚገኝ ገልጿል።

በአማራ ክልል፤ ደሴና ኮምቦልቻን ጨምሮ ግጭት ተባብሷል ብሏል። በሚፈጠርባቸው አካባቢዎች ካሉም ለመጠለል መዘጋጀት እንዳለባቸውና እነዚህን አካባቢዎች መልቀቅ ሊያስቡበት እንደሚገባ አብቆ አሳስቧል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ዕለታዊ የኮቪድ-19 ሪፖርት #Ethiopia

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 8 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 5,296 የላብራቶሪ ምርመራ 205 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 414 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ደሴ እና ኮምቦልቻ ?

የራሷን ነዋሪዎች ጨምራ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የጦርነት ሰለባ የሆኑ ተፈናቃዮችን አቅፋ በያዘችው ደሴ የስልክ ግንኙነት ከተቋረጠ ቀናት ተቆጥሯል፤ ይህም በአካባቢው ስላለው ውቅታዊ ሁኔታ ለመረዳት አዳጋች አድርጎታል።

ከአካባቢ ለቀው የወጡ አባላት መጠነኛ መረጃን ያካፈሉ ሲሆን በከተማው ወንጀል በከፍተኛ ደረጃ መበራከቱን፣ ኃይለኛ የንብረት ዘረፋም እንዳለ ጠቁመዋል።

የከተማው ነዋሪዎች ሁኔታ እጅጉን እንዳሳሰባቸው የገለፁ ሲሆን በተለይ ደግሞ ከፍተኛ ተፈናቃዮች በመጠለላቸው በፊትም እጥረት የነበረበት የመሰረታዊ አቅርቦት ችግር አሁን ላይ ተባብሶ የከፋ ሰብዓዊ ቀውስ ሊፈጥር እንደሚችል በብርቱ አሳስበዋል።

ደሴ በጦርነት የተፈናቀሉ ወላዶች፣ ህፃትናት፣ ነፍሰጡሮችን፣ አቅመ ደካሞችን አቅፋ አስጠልላላች።

በተጨማሪ በርካቶች በኔትዎርክ መቋረጥ የቤተሰቦቻቸውን ደህንነት ለማወቅ አልቻሉም።

በኮምቦልቻ በተመሳሳይ ዝርፊያ እየተፈፀመ መሆን ለመረዳት ተችሏል፤ ሁለቱ ከተሞች ያሉበት ቀጠና አሁንም በግጭት ውስጥ መሆኑን ለማውቅ ተችሏል፤ እንደከዚህ ቀደሞቹ አካባቢዎች በግንኙነት መቋረጥ ምክንያት መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አሁንም ለመረዳት አስቸጋሪ እንደሆነ ቀጥሏል።

በጦርነት ቀጠና ውስጥ ያሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ግን ለበርካታ ወራት እጅግ የከፋ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
በዛሬው ዕለት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 1ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ስብሰባ ይካሄዳል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 5/2014 ለማጽደቅ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ያፀድቃል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ አባላት ለመሰየም የሚቀርበውን የውሳኔ ሃሳብ በመመርመር ያፀድቃል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
" ... ከ5 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስገልገዋል " - የአማራ ክልል መንግስት

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስታና ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ፥ በክልሉ ህወሓት ወረራ በፈፀመባቸው ዞኖች ማለትም ፦
- ሰሜን ወሎ
- ደቡብ ወሎ
- ከፊል ደቡብ ጎንደር
- ዋግኽምራ ውስጥ የሚኖሩ እና ተፈናቅለው ያሉትን ጨምሮ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ሲል አሳውቋል።

ህወሓት በከፈተው ጦርነት ከ991 ሺ በላይ ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን በወረራ በተያዙ አካባቢዎች ደግሞ ከ5 ሚሊዮን ህዝብ በላይ አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል፤ እነዚህ ነዋሪዎች ለምግብ እጦት ፣ የመጠጥ ውሃ እና የመድሃኒት እጦት ችግር ተጋልጠዋል።

በሰሜን ወሎ ሜቄት አካባቢ ብቻ በህክምና እጦት 90 ሰዎች የሞቱ ሲሆን፤ በተመሳሳይ የወለሊድ አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት 13 እናቶች ሞተዋል።

በጋዝጊብላና በዝቋላ አካባቢ በመድሃኒት እጥረት ፣ በምግብ እጦት 13 ሰዎች ሞተዋል።

በአጠቃላይ በወረራ ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች ቤታቸውን እንደዘጉ በምግብ እና በመድሃኒት እጦት ሞተው የሚገኙበት ሁኔታ ነው እየተፈጠረ ያለው።

ከላይ የተገለፀው ቁጥር ሙሉ አይደለም ፤ ከዚህ በጣም ሊጨምር ይችላል፤ በየአካባቢው የመንግስት መዋቅር በመፍረሱ በምግብ እና በህክምና እጦት የሞቱ አጠቃላይ ሰዎችን ቁጥር ማወቅ አልተቻለም።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
አድሎ ፈፃሚዎቹ የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች !

አማራ ክልል በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ችግር ላይ በወደቁበት በዚህ ወቅት አንዳንዱ አይቶ እንዳላየ ሰምቶ እንዳልሰማ ሲያልፍ አንዳንዶቹ ደግሞ ቃል ከመግባት የዘለለ መሬት የወረደ ስራ ሲሰሩ አይታይም።

5 ሚሊዮን ህዝብ ችግር ላይ ይገኛል፤ የዓለም አቀፍ ረጂ ተቋማት ሆኑ የውጭ ሚዲያዎች ይህን ጉዳይ አላስጨነቃቸውም ፤ ምክንያቱን ጊዜ ይፈታዋል።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስታና እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ ኮሚሽን ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተቋቋሙበት ዓለም አቀፋዋ ህግጋትን ወደጎን ትተው አድሎ ሲፈፅሙ መመልከቱ እንዳሳዘነው ገልጿል።

በተደጋጋሚ የዩኒሴፍ ፣ የWFP ፣ የUNOCHA ካንትሪ ዳይሬክተሮች ወደ አማራ ክልል ሄደው ውይይት አድርገዋል፤ ክልሉ ያለውን ችግር እና ስፋት በአግባቡ እንዲያዩት ተደርገዋል።

እስካሁን ግን አንድም ምላሽ አልተደረገም።

የክልሉ መንግስት መሰረታዊ የገለልተኝነት ችግር አለ ብሎ ያምናል።

ሰብዓዊነት ዘርን፣ ቀለምን፣ ሃይማኖትን፣ የፖለቲካ ልዩነትን የሚጠይቅ ጉዳይ አይደለም፤ ተቋማቱም ሲቋቋሙ ዘርን ሃይማኖትን ፣ ብሄርን፣ የፖለቲካ አመለካከትን ማዕከል አድርገው ድጋፍ ለማድረግ አይደለም የተቋቋሙት፤ ሰብዓዊነት ሁሉም ሰው በመሆኑ ብቻ የሚደረግ ድጋፍ ነው።

ተቋማቱ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ አይደለም።

የሰብዓዊ ድርጅቶቹ በዓለም አቀፍ ድንጋጌ መሰረት ችግር ላይ ያሉ 5 ሚሊዮን ዜጎችን የመታደግ ኃላፊነት አለባቸው።

የአማራ ክልል አሁንም ተቋማቱ ከተቋቋሙበት ዓላማ አንፃር ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ እንዲወጡና ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን ስቃይ እንዲታደጉ ጥሪ አቅርቧል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ : በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት የጤና መሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡

በአማራ ክልል የደብረ ዘቢጥ ጤና ጣቢያ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁሟል፡፡ በዚህም ህሙማን በህክምና እና መድኃኒት እጥረት #እየሞቱ ይገኛሉ፡፡

የህክምና መሰረተ ልማቶች እና ባለሞያዎች የጦርነት ኢላማ መሆን የለባቸውም፡፡

#ICRCEthiopia

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በህ/ተ/ም/ቤት ፀደቀ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ6 ወራት ተፈጻሚ የሚሆን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርምሮ አፅድቋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በአንድ ድምጽ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።

#ተጨማሪ_መረጃ ፦ ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ አባላት ለመሰየም የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ አፅድቋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድን ፤ አቶ ለማ ተሰማ - በሰብሳቢነት ፤ ወ/ሮ ወርቀሰሙ ማሞ- በም/ሰብሳቢነት ይመሩታል።

መርማሪ ቦርዱ ሌሎች አምስት አባላት አሉት።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ፎቶ ፦ ፌልትማን ኢትዮጵያ ገብተዋል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ጄፍሪ ፌልትማን ዛሬ ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) ገብተዋል፤ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኃላም ከሙሳ ፋኪ ማሃመት ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ፌልትማንን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ጄፍሪ ፌልትማንን በቢሯቸው ተቀብለው በ #ኢትዮጵያ እና #ሱዳን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን አሳውቀዋል።

Credit : Moussa Faki Mahamat (Twitter)

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#ማስጠንቀቂያ

በሀረሪ ክልል የህክምና ቁሳቁሶችን ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ የሚሸጡ መድሃኒት መደብሮችን ከእኩይ ተግባራቸድ እንዲቆጠቡ የክልሉ ጤና ቢሮ አሥጠንቅቋል።

ቢሮው ፥ በጤና ባለሞያዎች የታዘዙ የመድሃኒት ምርቱ እያለ የለም በማለት እና ለህብረተሰቡ በተጋነነ ዋጋ በማቅረብ የግል ጥቅማቸውን የሚያሯሩጡ መድሀኒት መደብሮች ከዚህ እኩይ ተግባር ሊቆጠቡ ይገባል ብሏል።

በተያያዘ በጤና ባለሞያዎች ያልታዘዙ መድሃኒቶችን በግድ የለሽነት የሚሸጡ የግል መድሃኒት መደብሮች ህጋዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ቢሮው አሳውቋል።

መድሀኒት ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ የሚሸጡ መድሃኒት መደብሮችን ህብረተሰቡ በማጋለጥ የበኩሉን እንዲወጣ ሲል የክልሉ ጤና ቢሮ መልዕክት አስተላልፏል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#HappeningNow

ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ማብራሪያ እየተሰጠ ነው።

በአሁን ሰዓት መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላይ ላደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ እየተሰጠ ይገኛል።

ማብራሪያው በኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና በፍትህ ሚንስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ነው እየተሰጠ የሚገኘው።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ማብራሪያው የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ብዥታውን ለማጥራት ይረዳል ብለዋል። በሃገሪቱ ላይ የተጋረጠውን ፈተና ለመከላከል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ እንዳስፈለገም ተናግረዋል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ላይ የፍትህ ሚንስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።

Credit : ኤፍቢሲ

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
የተማሪዎች ምደባ ይፋ ሆኗል።

በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጊዚያዊ ምደባ ይፋ ሆኗል።

ተማሪዎች ተከታዩን ሊንክ በመከተል የዩኒቨርሲቲ መለያ ቁጥር እና ሙሉ ስም በማስገባት ጊዚያዊ ምደባቸውን መመልከት ይችላሉ፦ http://Placement.ethernet.edu.et

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
የዩኒቨርሲቲ ምደባ !

በመቐለ ፣ አክሱም ፣ ዓዲግራት ፤ ራያ እንዲሁም ወልዲያ ዩኒቨርስቲ ሲማሩ የነበሩና በፀጥታ ችግር ትምህርታቸውን መቀጠል ላልቻሉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ጊዜያዊ ምደባ ዛሬ ይፋ ሆኗል።

ምደባውን በዚህ http://Placement.ethernet.edu.et መመልከት ይቻላል።

• ምደባዉ እስከ ሰኔ 2013 ዓ.ም. የነበረዉን የትምህርት ጊዜ ሰሌዳን ጨርሰው የወጡት ተማሪዎችን ብቻ ይመለከታል፡፡

• ምደባዉ የተካሄደዉ መረጃዎችን በትክክል ላሰገቡ ተማሪዎች ሲሆን፣ በተጠየቀዉ መሰረት መረጃዎችን በትክክል ያላስገቡ ተማሪዎችና የኦን ላይን ፎርሙን በተለያየ ምክንያት በወቅቱ መሙላት ያልቻሉ ተማሪዎች ስማቸውን ኦንላይን ምደባ በሚረጋገጥበት ሶፍትዌር ላያገኙ ስለሚችሉ፣ በነበሩበት የትምህርት ክፍልና ዩኒቨርሲቲን መነሻ በማድረግ በዲፓርትመንት ስለተመደቡ፤ የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ በአካል በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ተብሏል።

• ተመዝግበው ሳይመደቡ የቀሩ ተማሪዎች በቂና ግልፅ መረጃ ያላቀረቡ መሆኑን በመገንዘብ ትምህርት ክፍላቸው የተመደበበትን ዩነቨርስቲ በአካል በመገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ተብሏል።

• ያልተመዘገቡ እንዲሁም ቅሬታ ወይም አቤቱታ ያላቸው ተማሪዎች በቴሌግራም ቦት (@moeplacementbot) አቤቱታቸውን ማቅረብ ይችላሉ። ትምህርት ሚኒስቴር አቤቱታዎችን በአካል እንደማያስተናግድ በጥብቅ አሳስቧል።

• በዩኒቨርስቲዎች ተፈቅዶላቸው እረፍት (Withdrawal) ላይ የነበሩ ተማሪዎች የትምህርት ክፍላቸው ለተመደበበት ዩኒቨርስቲ ማስረጃቸውን አቅርበው የሚታይላቸዉ ይሆናል ተብሏል።

NB : ተማሪዎች የተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ጥሪ ሲያደርግ ብቻ ነው በአካል ቀርበው ሪፖርት የሚያደርጉት።

#MoE

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
animation.gif
7.9 KB
" ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር አልዘጋችም " - የኬንያ ፖሊስ አገልግሎት

‘Citizen TV’ የተባለው የኬንያ ቴሌቪዝን ጣቢያ በትናንትናው ዕለት “ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ዘጋች” የሚል መረጃ አስረጭቶ ነበር። የቴሌቪዥን ጣቢያው ኬንያ ከ800 ኪሎሜትር በላይ የሚረዝመውን የሁለቱን ሀገራት ድንበር ላልተወሰነ ጊዜ መዝጋቷን ለዘገበበት ዜና ምንጭ አልጠቀሰም።

የኬንያ ፖሊስ አገልግሎት (Kenya Police Service) ዛሬ እንዳስታወቀው የኬንያ-ኢትዮጵያ ድንበር መዝጋቱን በተመለከተ በሚዲያ የተሰራጨው መልዕክት #የተሳሳተ መሆኑን አስታውቋል።

“አንዳንድ ሚዲያዎች በተሳሳተ መንገድ እንደዘገቡት ሳይሆን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስነው ድንበር አልተዘጋም” ያለው የኬንያ ፖሊስ “ያደረግነው በድንበር አካባቢ ያለውን የጸጥታ ቁመናችንን ማጠናከር ነው” ሲል አብራርቷል። የኬንያ ፖሊስ በተጨማሪም በድንበር አካባቢ ያለው ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን ገልጿል።

የኬኒያ ፖሊስ በትናንትናው ዕለት “አጎራባች” ባላቸው ሀገሮች እየታዩ ነው ካላቸው የጸጥታ ሁኔታዎች አኳያ አምስት ነጥቦችን የያዘ መግለጫ አውጥቶ የነበረ ሲሆን ከነጥቦቹ መካከል በድንበር አካባቢ የጸጥታ ቁጥጥርን ማጠናከር የሚል ይገኝበታል።

Credit : ኢትዮጵያ ቼክ

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
" በአማራ ክልል 33 ሺህ ተማሪዎች የ12 ክፍል መልቀቂያ አይፈተኑም " - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

በጦርነት ምክንያት በአማራ ክልል ከሚገኙ 357 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በ112ቱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እንደማይሰጥ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ይህ ያሳወቀው ለጀርመን ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።

በአማራ ክልል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 164 ሺህ ተማሪዎች መካከል ጦርነቱ በፈጠረው ችግር ምክንያት 33 ሺህ ተማሪዎች መፈተን አይችሉም።

የአማራ ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ሙላው አበበ እንደተናገሩት ፦
• በሰሜን ወሎ 42፣
• በዋግኽምራ 16፣
• በደቡብ ወሎ 48
• በደሴ ከተማ አስተዳደር 3፣
• በሰሜን ጎንደር 3 ሁለተኛ ት/ቤቶች ተማሪዎቻቸውን አያስፈትኑም፡፡

በክልሉ ለፈተናው የሚቀመጡት 131 ሺህ 167 ተማሪዎች ብቻ ሲሆኑ 123 ሺህ 159 በመደበኛ፣ 8 ሺህ 8 ደግሞ የግል ተፈታኞች መሆናቸውን ቢሮው ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከፊታችን ጥቅምት 29 እስከ ህዳር 2/2014 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ ይሰጣል፡፡

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተራዘመ !

ህዳር 5 በቀጣይ ሳምንት እሁድ ሊያኬድ የነበረው የ 2014 ቶታል ኢነርጂስ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መራዘሙ ተገልጿል ።

" በ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሰረት ህዳር 5 ቀን ሊካሄድ የነበረውን የ2014 ቶታልኢነርጂስ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ላልተወሰነ ጊዜ ለማራዘም መወሰናችንን እናሳውቃለን " ሲል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አስነብቧል ።

የ ውድድሩን ተለዋጭ ቀን በቅርብ ሳምንታት ውስጥ እንደሚያሳውቁ አዘጋጆቹ ገልፀዋል ።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
" በአማራ ክልል 33 ሺህ ተማሪዎች የ12 ክፍል መልቀቂያ አይፈተኑም " - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

በጦርነት ምክንያት በአማራ ክልል ከሚገኙ 357 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በ112ቱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እንደማይሰጥ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ይህ ያሳወቀው ለጀርመን ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።

በአማራ ክልል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 164 ሺህ ተማሪዎች መካከል ጦርነቱ በፈጠረው ችግር ምክንያት 33 ሺህ ተማሪዎች መፈተን አይችሉም።

የአማራ ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ሙላው አበበ እንደተናገሩት ፦
• በሰሜን ወሎ 42፣
• በዋግኽምራ 16፣
• በደቡብ ወሎ 48
• በደሴ ከተማ አስተዳደር 3፣
• በሰሜን ጎንደር 3 ሁለተኛ ት/ቤቶች ተማሪዎቻቸውን አያስፈትኑም፡፡

በክልሉ ለፈተናው የሚቀመጡት 131 ሺህ 167 ተማሪዎች ብቻ ሲሆኑ 123 ሺህ 159 በመደበኛ፣ 8 ሺህ 8 ደግሞ የግል ተፈታኞች መሆናቸውን ቢሮው ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከፊታችን ጥቅምት 29 እስከ ህዳር 2/2014 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ ይሰጣል፡፡

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
👆የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ (5 /2014) መምሪያ ዕዝ መዋቅር እና አደረጃጀት መመሪያ ቁጥር 1/2014

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
" የጦር መሳሪያ የጫነ ተሽከርካሪ ወደ ሆሳዕና ከተማ ገብቷል ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው " - የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ

የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጥቅምት 24/2014 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት አካባቢ መነሻውን ከአዲስ አበባ ያደረገ ኮድ 3 ሰሌዳ ቁጥር 19331 ደ.ህ የሆነ ተሽከርካሪ የጦር መሳሪያ ጭኖ በወልቂጤ ከተማ በኩል ወደ በሆሳዕና ገብቷል ተብሎ የሚሰራጨው ወሬ ሀሰት መሆኑን ገልጿል።

ይሁንና ተሽከርካሪው በፍጥነት እያሽከረከረ ስለነበረ ሆሳዕና ከተማ ናረሞ አከባቢ በስራ ላይ የነበሩ ትራፊክ ፖሊሶች ለማስቆም ሲሞክሩ ጥሶ በማለፍ በ2 ሞተረኞች ላይ የአካል ጉዳት አድርሷል።

አሽከርካሪው ጉዳት አድርሶ ለማምለጥ ጥረት ቢያደርግም በአከባቢው ህበረተሰብና በፀጥታ አካላት ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገልጿል።

በተጎጂዎቹም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት በመድረሱ በንግስት እሌኒ መህመድ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።

ጉዳቱን ባደረሰው አሽከርካሪ ምርመራ በማድረግ የማጣራት ስራ እያከናወነ ይገኛል።

ጉዳዩ ይህ ቢሆንም የጦር መሳሪያ የጫነ ተሽከርካሪ ወደ ሆሳዕና ገብቷል ተብሎ የሀሰት መረጃ የተሰራጨ ሲሆን ፖሊስ መረጃው ሀሰተኛ ነው ብሏል።

ህብረተሰቡ ትክክለኛነቱ ባልተረጋገጠ ወሬ ሳይረበሽ አካባቢውን ከፀጥታ አካለት ጋር በመተባበር በመጠበቅ ወንጀልን በጋራ እንዲከላከል ጥሪ ቀርቧል።

ነዋሪዎች ማንኛውም ጥርጣሬ ውስጥ የሚያስገባ ነገር ካጋጠማቸው 046550330 በመደወል ለፖሊስ መረጃ እንዲሰጡ ተጠይቋል።

(የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ)

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#የመንግስት_ማስጠንቀቂያ

የኢትዮጵያ መንግስት ሀገርን ለማፍረስ የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀ።

ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ያወጣው የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሀገርን ለማፍረስ የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ሲል አስጠንቅቋል።

መንግስት በመግለጫው "የሽብር ቡድኑ ማሽኖችና በሽርክና የሚሰሩ ሚዲያዎች የሽብር ወሬ እያሰራጩ ናቸው" ብሏል። ቁልፍ ኢላማቸው ደግሞ በአመራሩና ፣ በህዝቡና በወገን ጦር መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ፍርሃትም እንዲነግስ ማሸበር ነው ሲል ገልጿል።

በተለያየ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ያሉ ተላላኪዎቻቸው የፀጥታ ችግር እንዳለ በማስመሰል የግል ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ የማግባባት ስራ እየሰሩ ይገኛሉም ብሏል።

በህዝቡና በወገኑ ጦር ውስጥ ጥርጣሪዎችን ለመፍጠር የመንግስት ባለስልጣናት ቪዛ እየጠየቁ ነው በሚል የውሸት ፕሮፓጋንዳ እየነዙ ናቸውም ሲል ገልጿል።

የመንግስት ኮሚኒኬሽን በመግለጫው ከዲፕሎማሲ መርህ ውጪ የአንዳንድ ሃገር ኤምባሲዎች አዲስ አበባ እንደ ተከበበች በማስመሰልና ያሰቡት ውጥን እንዲሳካ በኤምባሲያቸው የሚሰሩ ዜጎቻቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እያሳሰቡ ይገኛሉ ብሏል።

በእንዲህ አይነት መንገድ ሀገርን ለማፍረስ የተጠመዱ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ያሳሰበው መንግስት በሀገር ጉዳይ ቀልድ የለምና ከድርጊቱ ባልተቆጠቡት ላይ የማያዳግም ርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል።

* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ዕለታዊ የኮቪድ-19 ሪፖርት #Ethiopia

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 15 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 7,341 የላብራቶሪ ምርመራ 327 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 420 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

#ጥንቃቄ 😷 #TikvahFamily

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA