የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከኔዘርላንድስ ቀይ መስቀል ጋር በመተባበር ከአውሮፓ ህብረት የሰብአዊ እርዳታ (ECHO) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በሶማሌ ክልል፣ ሸበሌ ዞን፣ ጎዴ እና ኤሌሌ ወረዳዎች ለሚገኙ ለድርቅ አደጋ ተጋላጭ አባወራዎች ሁለገብ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ፡፡
በአካባቢው ካለፈው ጥቅምት እስከ ታህሣሥ ወር ይጠበቅ የነበረው ዝናብ ባለመጣሉ ሊከሰት የሚችልን የድርቅ አደጋ ለመከላከል በአጠቃላይ በሁለቱ ወረዳዎች 1,800 አባወራዎች የገንዘብ ድጋፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡
በኤሌሌ ወረዳ ቦቅ ቢላል ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ፈርዶሳ ኡስማን ድጋፉን አስመልክቶ እንደተናገሩት፣ "ቀይ መስቀል 11,300 ብር የሰጠን ሲሆን፣ ይህም ያለብንን የምግብና ውሃ ችግር ለመፍታት ይጠቅመናል፡፡ ከብቶቻችንም የሞቱብን በመሆኑ ድጋፉ ለኑሮአችን የሚያስፈልገንን ወጪ ለመሸፈን ይጠቅመናል፡፡ ለተደረገልን ድጋፍም እናመሰግናለን" ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በድርቅ እና በሌሎች አደጋዎች ለጉዳት የተጋለጡ ወገኖቻችንን ህይወት ለመታደግ ድጋፍ በማድረግ ላይ ሲሆን፣ በእነዚህ ሁለት ወረዳዎች ለሰጠው ምላሽ ድጋፍ ላደረጉለት ለአውሮፓ ህብረት የሰብአዊ እርዳታ እና ለኔዘርላንድ ቀይ መስቀል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
በአካባቢው ካለፈው ጥቅምት እስከ ታህሣሥ ወር ይጠበቅ የነበረው ዝናብ ባለመጣሉ ሊከሰት የሚችልን የድርቅ አደጋ ለመከላከል በአጠቃላይ በሁለቱ ወረዳዎች 1,800 አባወራዎች የገንዘብ ድጋፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡
በኤሌሌ ወረዳ ቦቅ ቢላል ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ፈርዶሳ ኡስማን ድጋፉን አስመልክቶ እንደተናገሩት፣ "ቀይ መስቀል 11,300 ብር የሰጠን ሲሆን፣ ይህም ያለብንን የምግብና ውሃ ችግር ለመፍታት ይጠቅመናል፡፡ ከብቶቻችንም የሞቱብን በመሆኑ ድጋፉ ለኑሮአችን የሚያስፈልገንን ወጪ ለመሸፈን ይጠቅመናል፡፡ ለተደረገልን ድጋፍም እናመሰግናለን" ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በድርቅ እና በሌሎች አደጋዎች ለጉዳት የተጋለጡ ወገኖቻችንን ህይወት ለመታደግ ድጋፍ በማድረግ ላይ ሲሆን፣ በእነዚህ ሁለት ወረዳዎች ለሰጠው ምላሽ ድጋፍ ላደረጉለት ለአውሮፓ ህብረት የሰብአዊ እርዳታ እና ለኔዘርላንድ ቀይ መስቀል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
👍14