የወላይታ ሶዶ የኮንቨርተር ጣቢያ የሙከራ (commissioning) ስራ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል
.........................///.........................
የወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራ ስራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
በፕሮጀክቱ የሰብስቴሽን ኢንቻርጅ ባለሙያው አቶ ሃብታሙ ግርማ እንደገለፁት የኮንቨርተር ጣቢያውን የግንባታ ስራ በማጠናቀቅ በአሁኑ ወቅት የሙከራ ስራው በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ከወላይታ ሶዶ ከተማ 7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እየተገነባ የሚገኘውን የኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራ ስራ በቅርቡ በማጠናቀቅ የፍተሻ ስራውን ለመጀመር እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ እንደሚገኝም አቶ ሃብታሙ ገልፀዋል፡፡
እንደ አቶ ሃብታሙ ገለፃ የሙከራ ስራው ከስራ ተቋራጩ፣ ከአማካሪ ድርጅቱ እንዲሁም ከተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በተውጣጡ ባለሙያዎች በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው ከወላይታ ሶዶ ነባሩ የማከፋፈያ ጣቢያ የወጡ አራት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመሮች እንዳሉት ነው ባለሙያዉ የጠቆሙት፡፡
ጣቢያው በዲዛይን፣ በቴክኖሎጂ እና በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሆነ ያነሱት አቶ ሃብታሙ ይህም ቀጥተኛ ዥረት (Directe current) መሆኑ እና 12 ኮንቨርተር ትራንስፎርመሮች የተገጠሙለት በመሆኑ ከሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
ይህ ባለ 500 ኪሎ ቮሎት የኮንቨርተር ጣቢያ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ማስተላለፊያ መስመር የማሻገር አቅም ያለው እንደሆነም ነው ባለሙያው ያብራሩት።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ኬንያን ጨምሮ ታንዛኒያን እና ሌሎች የአፍሪካ ሃገራትን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎም ይጠበቃል፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የኮንቨርተር ጣቢያ መገንባት የክፍለ-አህጉራዊ የኃይል ትስስርን ከማጠናከሩም ባሻገር የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ያግዛልም ተብሏል፡፡
የፕሮጀክቱን የግንባታ ስራ ሲመንስ የተሰኘ የጀርመን ኩባንያ በማከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ስራው ላይ ደግሞ ትራክ ቤል የተሰኘ ኩባንያ ተሳትፎበታል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል በመገንባት ላይ የሚገኘው የኢትዮ -ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር እና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ስራ ቢጠናቀቅም ወደ አገልግሎት ለማስገባት የዚህ ፕሮጀክት አካል የሆነውንና በኬኒያ መንግስት በኩል እየተገነባ የሚገኘውን ፕሮጀክት መጠናቀቅ ይጠብቃል ነው የተባለው፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት በብድር በተገኘ ከ285 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት በመከናወን ላይ የሚገኝ መሆኑን ከፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከዚህ ውስጥም 243 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላሩ በዓለም ባንክ እንዲሁም ቀሪው ከ42 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላዩ ደግሞ በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚሸፈን ነው ተብሏል፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው የግንባታ ስራ በ2009 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ይታወሳል፡፡
.........................///.........................
የወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራ ስራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
በፕሮጀክቱ የሰብስቴሽን ኢንቻርጅ ባለሙያው አቶ ሃብታሙ ግርማ እንደገለፁት የኮንቨርተር ጣቢያውን የግንባታ ስራ በማጠናቀቅ በአሁኑ ወቅት የሙከራ ስራው በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ከወላይታ ሶዶ ከተማ 7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እየተገነባ የሚገኘውን የኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራ ስራ በቅርቡ በማጠናቀቅ የፍተሻ ስራውን ለመጀመር እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ እንደሚገኝም አቶ ሃብታሙ ገልፀዋል፡፡
እንደ አቶ ሃብታሙ ገለፃ የሙከራ ስራው ከስራ ተቋራጩ፣ ከአማካሪ ድርጅቱ እንዲሁም ከተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በተውጣጡ ባለሙያዎች በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው ከወላይታ ሶዶ ነባሩ የማከፋፈያ ጣቢያ የወጡ አራት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመሮች እንዳሉት ነው ባለሙያዉ የጠቆሙት፡፡
ጣቢያው በዲዛይን፣ በቴክኖሎጂ እና በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሆነ ያነሱት አቶ ሃብታሙ ይህም ቀጥተኛ ዥረት (Directe current) መሆኑ እና 12 ኮንቨርተር ትራንስፎርመሮች የተገጠሙለት በመሆኑ ከሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
ይህ ባለ 500 ኪሎ ቮሎት የኮንቨርተር ጣቢያ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ማስተላለፊያ መስመር የማሻገር አቅም ያለው እንደሆነም ነው ባለሙያው ያብራሩት።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ኬንያን ጨምሮ ታንዛኒያን እና ሌሎች የአፍሪካ ሃገራትን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎም ይጠበቃል፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የኮንቨርተር ጣቢያ መገንባት የክፍለ-አህጉራዊ የኃይል ትስስርን ከማጠናከሩም ባሻገር የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ያግዛልም ተብሏል፡፡
የፕሮጀክቱን የግንባታ ስራ ሲመንስ የተሰኘ የጀርመን ኩባንያ በማከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ስራው ላይ ደግሞ ትራክ ቤል የተሰኘ ኩባንያ ተሳትፎበታል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል በመገንባት ላይ የሚገኘው የኢትዮ -ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር እና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ስራ ቢጠናቀቅም ወደ አገልግሎት ለማስገባት የዚህ ፕሮጀክት አካል የሆነውንና በኬኒያ መንግስት በኩል እየተገነባ የሚገኘውን ፕሮጀክት መጠናቀቅ ይጠብቃል ነው የተባለው፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት በብድር በተገኘ ከ285 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት በመከናወን ላይ የሚገኝ መሆኑን ከፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከዚህ ውስጥም 243 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላሩ በዓለም ባንክ እንዲሁም ቀሪው ከ42 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላዩ ደግሞ በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚሸፈን ነው ተብሏል፡፡
የኮንቨርተር ጣቢያው የግንባታ ስራ በ2009 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ይታወሳል፡፡
ሚኒስትሩ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ
***********************
የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ጸሃፊ ከቬራ ሶንግዌ ጋር በመሆን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታንና በሥራ ላይ የሚገኘውን ጊቤ ሶስት የውሃ ኃይል ማመንጫን ጎበኙ፡፡
ጉብኝቱ ኢትዮጵያ ያሏትን የውሃ ሃብቶች ለዘላቂ እድገትና ለዜጎች ህይወት መሻሻል እንዴት በአግባቡ እየተጠቀመች እንደሆነ ለማየት አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
“በኦሞ ወንዝ ላይ የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጋችን በተመሳሳይ ሌሎች ወንዞቻችንንም እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንደምንችል ማሳያ ነው ብለዋል” ሚኒስትሩ፡፡
ጊቤ ሶስት የውሃ ኃይል ማመንጫ በአሁኑ ሰዓት 1870 ሜጋ ዋት ሃይል የማመንጨት አቅም ያለው ላይ ሲሆን አሁን ግንባታው 39 በመቶ የደረሰው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ደግሞ ሲጠናቀቅ ደግሞ 2160 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል እንደሚያመነጭ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡
“የኮይሻና የሕዳሴ ግድቦች ሲጠናቀቁ አሁን ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል ምርት በ170% በማሳደግ በ2022 ሙሉ በሙሉ ለዜጎች ኃይል ለማቅረብ በምናደርገው ጥረት ላይ ትልቁን ሚና ይጫወታሉ” ማለታቸውን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬሽን ዘግቧል።
በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተገኝተዋል።
መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ/ም
***********************
የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ጸሃፊ ከቬራ ሶንግዌ ጋር በመሆን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታንና በሥራ ላይ የሚገኘውን ጊቤ ሶስት የውሃ ኃይል ማመንጫን ጎበኙ፡፡
ጉብኝቱ ኢትዮጵያ ያሏትን የውሃ ሃብቶች ለዘላቂ እድገትና ለዜጎች ህይወት መሻሻል እንዴት በአግባቡ እየተጠቀመች እንደሆነ ለማየት አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
“በኦሞ ወንዝ ላይ የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጋችን በተመሳሳይ ሌሎች ወንዞቻችንንም እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንደምንችል ማሳያ ነው ብለዋል” ሚኒስትሩ፡፡
ጊቤ ሶስት የውሃ ኃይል ማመንጫ በአሁኑ ሰዓት 1870 ሜጋ ዋት ሃይል የማመንጨት አቅም ያለው ላይ ሲሆን አሁን ግንባታው 39 በመቶ የደረሰው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ደግሞ ሲጠናቀቅ ደግሞ 2160 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል እንደሚያመነጭ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡
“የኮይሻና የሕዳሴ ግድቦች ሲጠናቀቁ አሁን ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል ምርት በ170% በማሳደግ በ2022 ሙሉ በሙሉ ለዜጎች ኃይል ለማቅረብ በምናደርገው ጥረት ላይ ትልቁን ሚና ይጫወታሉ” ማለታቸውን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬሽን ዘግቧል።
በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተገኝተዋል።
መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ/ም
ሚኒስትሩ የታላቁ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ
*******************
የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ፡፡
ኃላፊዎቹ ስለግድቡና ስለግንባታው ሂደት በሚኒስትሩ ገለፃ ተደርጎላቸው ግንባታውን እየተዘዋወሩ ተመልክተዋል።
ከጉብኝቱ በኋላም በግድቡ ግዝፈትና በግንባታው ሂደት ውስብስብነት መደነቃቸውን ኃላፊዎቹ ለሚኒስትሩ ገልፀውላቸዋል።
በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንዲሁም የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ንጉሴ ተገኝተዋል።
በኢትዮጵያውያን የገንዘብ ድጋፍ በመገንባት ላይ የሚገኘው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ አፈፃፀም 76 ነጥብ 3 በመቶ ላይ ደርሷል።
መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ/ም
*******************
የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ፡፡
ኃላፊዎቹ ስለግድቡና ስለግንባታው ሂደት በሚኒስትሩ ገለፃ ተደርጎላቸው ግንባታውን እየተዘዋወሩ ተመልክተዋል።
ከጉብኝቱ በኋላም በግድቡ ግዝፈትና በግንባታው ሂደት ውስብስብነት መደነቃቸውን ኃላፊዎቹ ለሚኒስትሩ ገልፀውላቸዋል።
በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንዲሁም የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ንጉሴ ተገኝተዋል።
በኢትዮጵያውያን የገንዘብ ድጋፍ በመገንባት ላይ የሚገኘው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ አፈፃፀም 76 ነጥብ 3 በመቶ ላይ ደርሷል።
መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ/ም
በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ሥራ በመከናወን ላይ ነው
……………///……………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ስራ በማከናወን ላይ መሆኑን በተቋሙ የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ቢሮ ስራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደገለጹት ተቋሙ 130 በሚሆኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የቆጣሪዎቹ መገጠም የተቋሙ ደንበኞች ለተጠቀሙት ኃይል ትክክለኛውን ክፍያ እንዲከፍሉ ለማድረግ እንደሚያግዝ ስራ አስኪያጇ አስታውቀዋል፡፡
ይህም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዚህ ቀደም በ40/60 የክፍፍል ስምምነት መሰረት የሚገኘውን ክፍያ በማስቀረት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወጣውን ኃይል ቆጥሮ በማስከፈል የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ ይጠቅማል ብለዋል፡፡
እንደ ወ/ሮ ሐይማኖት ገለፃ የቆጣሪ ገጠማ ስራው የኃይል ብክነትን ለመለየት እና አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምጃ ለመውሰድም ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡
በመገጠም ላይ የሚገኙት ቆጣሪዎች በእንግሊዝ ሀገር የተመረቱ “CEWE Prometer 100” የተባሉ ሲሆን የገጠማ ስራውንም “Siemens Proprietary Limited” የተባለ ድርጅት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ድርጅቱ 1 ሺ 476 ቆጣሪዎችን እንዲያቀርብ ስምምነት ላይ መደረሱን የጠቀሱት ወ/ሮ ሐይማኖት ከዚህ ውስጥ 1 ሺ 226 ቆጣሪዎች በጣቢዎች ላይ የሚገጠሙ ሲሆን ቀሪ 250 ቆጣሪዎች ደግሞ ለመጠባበቂያነት የሚያገለግሉ ናቸው ብለዋል፡፡
በጣቢያዎች ላይ ለመግጠም ከታሰቡ ቆጣሪዎች መካከል ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ድረስ በ42 ጣቢያዎች ላይ 353 ቆጣሪዎች ተገጥመው የሙከራና የፍተሻ ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡
እንደ ስራ አስኪያጇ ገለፃ በእያንዳንዱ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚገጠመው የቆጣሪ ብዛት እንደ ጣቢያው ወጪ መስመር ብዛት የሚወሰን ይሆናል፡፡
የቆጣሪዎች ተከላ የዲዛይን፣ የማምረት እና የማጓጓዝ ስራው በ2012 በጀት ዓመት የተገባደደ መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ሐይማኖት እስከ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የገጠማ ስራውን ለማጠናቀቅ እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡
በቆጣሪ ገጠማ ስራው ላይ ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ ባለሞያዎች እንዲሳተፉ መደረጉን የተናገሩት ስራ አስኪያጇ ይህም በቀጣይ ለሚከናወኑ የቆጣሪ ገጠማ ስራዎች በራስ አቅም ለመስራት የሚያስችል ልምድ ለማግኘት ታስቦ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
በ130 ጣቢያዎች ላይ ለሚከናወነው የቆጣሪ ገጠማ አጠቃላይ ስራ የአቅርቦት፣ የተከላ፣ የፍተሻና ሙከራ ስራዎች ለማከናወን በዓለም ባንክ የሚሸፈን ከ25 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ብር እና ከ2 ነጥብ 17 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር በጀት ተይዞለታል፡፡
……………///……………..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ስራ በማከናወን ላይ መሆኑን በተቋሙ የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ቢሮ ስራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደገለጹት ተቋሙ 130 በሚሆኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የቆጣሪዎቹ መገጠም የተቋሙ ደንበኞች ለተጠቀሙት ኃይል ትክክለኛውን ክፍያ እንዲከፍሉ ለማድረግ እንደሚያግዝ ስራ አስኪያጇ አስታውቀዋል፡፡
ይህም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዚህ ቀደም በ40/60 የክፍፍል ስምምነት መሰረት የሚገኘውን ክፍያ በማስቀረት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወጣውን ኃይል ቆጥሮ በማስከፈል የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ ይጠቅማል ብለዋል፡፡
እንደ ወ/ሮ ሐይማኖት ገለፃ የቆጣሪ ገጠማ ስራው የኃይል ብክነትን ለመለየት እና አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምጃ ለመውሰድም ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡
በመገጠም ላይ የሚገኙት ቆጣሪዎች በእንግሊዝ ሀገር የተመረቱ “CEWE Prometer 100” የተባሉ ሲሆን የገጠማ ስራውንም “Siemens Proprietary Limited” የተባለ ድርጅት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ድርጅቱ 1 ሺ 476 ቆጣሪዎችን እንዲያቀርብ ስምምነት ላይ መደረሱን የጠቀሱት ወ/ሮ ሐይማኖት ከዚህ ውስጥ 1 ሺ 226 ቆጣሪዎች በጣቢዎች ላይ የሚገጠሙ ሲሆን ቀሪ 250 ቆጣሪዎች ደግሞ ለመጠባበቂያነት የሚያገለግሉ ናቸው ብለዋል፡፡
በጣቢያዎች ላይ ለመግጠም ከታሰቡ ቆጣሪዎች መካከል ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ድረስ በ42 ጣቢያዎች ላይ 353 ቆጣሪዎች ተገጥመው የሙከራና የፍተሻ ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡
እንደ ስራ አስኪያጇ ገለፃ በእያንዳንዱ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚገጠመው የቆጣሪ ብዛት እንደ ጣቢያው ወጪ መስመር ብዛት የሚወሰን ይሆናል፡፡
የቆጣሪዎች ተከላ የዲዛይን፣ የማምረት እና የማጓጓዝ ስራው በ2012 በጀት ዓመት የተገባደደ መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ሐይማኖት እስከ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የገጠማ ስራውን ለማጠናቀቅ እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡
በቆጣሪ ገጠማ ስራው ላይ ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ ባለሞያዎች እንዲሳተፉ መደረጉን የተናገሩት ስራ አስኪያጇ ይህም በቀጣይ ለሚከናወኑ የቆጣሪ ገጠማ ስራዎች በራስ አቅም ለመስራት የሚያስችል ልምድ ለማግኘት ታስቦ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
በ130 ጣቢያዎች ላይ ለሚከናወነው የቆጣሪ ገጠማ አጠቃላይ ስራ የአቅርቦት፣ የተከላ፣ የፍተሻና ሙከራ ስራዎች ለማከናወን በዓለም ባንክ የሚሸፈን ከ25 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ብር እና ከ2 ነጥብ 17 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር በጀት ተይዞለታል፡፡
በፕሮጀክቱ ንብረቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ ዳርጎታል
……………..////………………….
የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀሙበት እንደሚገኝ የኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ አስተባባሪ ገለፁ፡፡
አስተባባሪው አቶ ሰይፉ ፈይሳ እንደገለፁት በኢትዮጵያ በኩል የሚገነባው የ433 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡
ይሁን እንጅ በወላይታ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች በማስተላለፊያ መስመሩ ሽቦዎች እና የምሰሶ ብረቶች ላይ በተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀመበት ይገኛል ብለዋል፡፡
ይህም ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ በመዳረግ ከ34 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራም እንዳደረሰበት ነው ያስታወቁት፡፡
ኪሳራው የደረሰው በስርቆቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰበትን የማስተላለፊያ መስመሩን አካላት በአዲስ ለመተካትና ለመቀየር፣ እንዲሁም ለመበየድ፣ ለዕቃ ግዥ እና ለምሶሶ (Tower) ቅየራ ተጨማሪ ወጪ በመውጣቱ ነው፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ 994 ምሶሶች ያሉት ሲሆን በተፈፀመው ስርቆት ጉዳት ከደረሰባቸው ምሶሶዎች መካከል አንዱን ሙሉ በሙሉ መቀየሩን አስተባባሪው ተናግረዋል፡፡
የግንባታ ሰራው በ2008 ዓ. ም የተጀመረው የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ183 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
መስከረም 27 2013 ዓ.ም.
……………..////………………….
የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀሙበት እንደሚገኝ የኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ አስተባባሪ ገለፁ፡፡
አስተባባሪው አቶ ሰይፉ ፈይሳ እንደገለፁት በኢትዮጵያ በኩል የሚገነባው የ433 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡
ይሁን እንጅ በወላይታ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች በማስተላለፊያ መስመሩ ሽቦዎች እና የምሰሶ ብረቶች ላይ በተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀመበት ይገኛል ብለዋል፡፡
ይህም ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ በመዳረግ ከ34 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራም እንዳደረሰበት ነው ያስታወቁት፡፡
ኪሳራው የደረሰው በስርቆቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰበትን የማስተላለፊያ መስመሩን አካላት በአዲስ ለመተካትና ለመቀየር፣ እንዲሁም ለመበየድ፣ ለዕቃ ግዥ እና ለምሶሶ (Tower) ቅየራ ተጨማሪ ወጪ በመውጣቱ ነው፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ 994 ምሶሶች ያሉት ሲሆን በተፈፀመው ስርቆት ጉዳት ከደረሰባቸው ምሶሶዎች መካከል አንዱን ሙሉ በሙሉ መቀየሩን አስተባባሪው ተናግረዋል፡፡
የግንባታ ሰራው በ2008 ዓ. ም የተጀመረው የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ183 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/
መስከረም 27 2013 ዓ.ም.