ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት እጥረት የጣቢያው ስጋት እየሆኑ ነው ተባለ
--------------/////////----------------
የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት ስራውን እያስተጓጎለበት መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡
ኃላፊው አቶ ፍቃዱ ደምሴ እንደገለፁት ወደ ጣቢያው የውሃ መቀበያ እየተገመሰ የሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ለኃይል ማመንጫው የኦፕሬሽን ሥራ ከፍተኛ ስጋት እየሆነ ነው፡፡
ተንሳፋፊ ሳሩ ከሐምሌ 9-11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን እስከማስቆም ደርሶ እንደነበረ የገለፁት ኃላፊው ባለፈው ዓመትም በተንሳፋፊ ሳሩ ምክንያት ከ10 ቀን በላይ ጣቢያው መቆሙን አስታውሰዋል፡፡
ጣቢያውን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ኤክስካቬተር በመከራየትና ዋና በሚችሉ የጣቢያው ሠራተኞችን በመጠቀም የኃይል ማመንጫውን ውሃ መቀበያ የዘጋውን ተንሳፋፊው ሣር ለጊዜውም ቢሆን በማስወገድ ሥራ ማስጀመር መቻሉን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡
ጣቢያውን ከተንሳፋፊ ሳር ለመጠበቅ የሚያግዝ መከላከያ (Taff Boom) ያለው ቢሆንም በዘንድሮ ዓመት ከሃይቁ ዳር እየተገመሰ የሚመጣው የሳር ደሴት መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ ቀደም ሲል የተገጠመው መከላለያ ሊመልሰው አልቻለም፡፡
በመሆኑም በየጊዜው ወደ ኃይል ማመንጫው ለሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ዘላቂ መፍትሄ ካልተሰጠው በቀር ጣቢያውን እስከ መዘጋት ሊያደርሰው እንደሚችል አብራርተዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 27 ቀን 2012 ዓ.ም.
--------------/////////----------------
የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት ስራውን እያስተጓጎለበት መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡
ኃላፊው አቶ ፍቃዱ ደምሴ እንደገለፁት ወደ ጣቢያው የውሃ መቀበያ እየተገመሰ የሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ለኃይል ማመንጫው የኦፕሬሽን ሥራ ከፍተኛ ስጋት እየሆነ ነው፡፡
ተንሳፋፊ ሳሩ ከሐምሌ 9-11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን እስከማስቆም ደርሶ እንደነበረ የገለፁት ኃላፊው ባለፈው ዓመትም በተንሳፋፊ ሳሩ ምክንያት ከ10 ቀን በላይ ጣቢያው መቆሙን አስታውሰዋል፡፡
ጣቢያውን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ኤክስካቬተር በመከራየትና ዋና በሚችሉ የጣቢያው ሠራተኞችን በመጠቀም የኃይል ማመንጫውን ውሃ መቀበያ የዘጋውን ተንሳፋፊው ሣር ለጊዜውም ቢሆን በማስወገድ ሥራ ማስጀመር መቻሉን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡
ጣቢያውን ከተንሳፋፊ ሳር ለመጠበቅ የሚያግዝ መከላከያ (Taff Boom) ያለው ቢሆንም በዘንድሮ ዓመት ከሃይቁ ዳር እየተገመሰ የሚመጣው የሳር ደሴት መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ ቀደም ሲል የተገጠመው መከላለያ ሊመልሰው አልቻለም፡፡
በመሆኑም በየጊዜው ወደ ኃይል ማመንጫው ለሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ዘላቂ መፍትሄ ካልተሰጠው በቀር ጣቢያውን እስከ መዘጋት ሊያደርሰው እንደሚችል አብራርተዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ነሐሴ 27 ቀን 2012 ዓ.ም.
የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዓለምአቀፍ ትኩረት ስቧል
……………/////………..
የኤሌክትሪክ ዘርፍ ተሸላሚው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለሁሉም ለማዳረስ እገዛ እያደረገ መሆኑን ፓወር የተሰኘው በኃይል ላይ በማተኮር የሚዘጋጀው ዓለምአቀፍ መጽሔት ዘግቧል፡፡
ከህዝቦቿ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኤሌክትሪክ የማያገኙባት ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ አቅርቦት እየተሻሻለች መምጣቷን መጽሔቱ በዝርዝር አትቷል፡፡
መፅሔቱ ይፋ እንዳደረገው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት መንግስት እ.ኤ.አ እስከ 2025 በመላው ሀገሪቱ ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት የሚደረገውን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እገዛ ማድረግ ጀምሯል፡፡
በ3 ተርባይኖች 254 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ተመርቆ ስራ የጀመረው በተያዘው ዓመት አጋማሽ ላይ ነበር፡፡
ይህን ሊንክ በመጫን ዝርዝር ዘገባውን ማግኘት ይችላሉ፡፡
https://www.powermag.com/award-winning-hydropower-project-helps-electrify-ethiopia/
……………/////………..
የኤሌክትሪክ ዘርፍ ተሸላሚው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለሁሉም ለማዳረስ እገዛ እያደረገ መሆኑን ፓወር የተሰኘው በኃይል ላይ በማተኮር የሚዘጋጀው ዓለምአቀፍ መጽሔት ዘግቧል፡፡
ከህዝቦቿ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኤሌክትሪክ የማያገኙባት ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ አቅርቦት እየተሻሻለች መምጣቷን መጽሔቱ በዝርዝር አትቷል፡፡
መፅሔቱ ይፋ እንዳደረገው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት መንግስት እ.ኤ.አ እስከ 2025 በመላው ሀገሪቱ ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት የሚደረገውን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እገዛ ማድረግ ጀምሯል፡፡
በ3 ተርባይኖች 254 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ተመርቆ ስራ የጀመረው በተያዘው ዓመት አጋማሽ ላይ ነበር፡፡
ይህን ሊንክ በመጫን ዝርዝር ዘገባውን ማግኘት ይችላሉ፡፡
https://www.powermag.com/award-winning-hydropower-project-helps-electrify-ethiopia/
POWER
Award-Winning Hydropower Project Helps Electrify Ethiopia
The government of Ethiopia has set a goal of providing access to electricity to all its citizens by 2025. It still has a long way to go, but projects such as the Genale Dawa III hydropower station are helping
የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኑ
*****************//////*****************
የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኑ።
ሽልማቱ የተበረከተው የግድቡ መሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ከመጋቢት 24/2004 ዓ.ም ጀምሮ በጉባ በሥራ ላይ ለሚገኙ የግድቡ ሰራተኞችና ጸጥታውን ለሚቆጣጠሩ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፓሊስ አባላት ነው።
በጉባ የሚገኙ ሰራተኞችን ወክለው የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሽልማቱን ተረክበዋል፡፡
በአባይ ፖለቲካ ላይ የተለያዩ ጥንቶችን ያደረጉት ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የጤና ባለሙያዎችና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች እንዲሁም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአረብኛ የኢትዮጵያን አቋም በተለያዩ መድረኮች በማንፀባረቅ የሚታወቀው መሀመድ አል አሩሲ የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ጳጉሜ 02 ቀን 2012 ዓ.ም
*****************//////*****************
የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኑ።
ሽልማቱ የተበረከተው የግድቡ መሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ከመጋቢት 24/2004 ዓ.ም ጀምሮ በጉባ በሥራ ላይ ለሚገኙ የግድቡ ሰራተኞችና ጸጥታውን ለሚቆጣጠሩ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፓሊስ አባላት ነው።
በጉባ የሚገኙ ሰራተኞችን ወክለው የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሽልማቱን ተረክበዋል፡፡
በአባይ ፖለቲካ ላይ የተለያዩ ጥንቶችን ያደረጉት ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የጤና ባለሙያዎችና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች እንዲሁም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአረብኛ የኢትዮጵያን አቋም በተለያዩ መድረኮች በማንፀባረቅ የሚታወቀው መሀመድ አል አሩሲ የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ጳጉሜ 02 ቀን 2012 ዓ.ም
አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
…………./////………..
በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡
አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡
32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ጳጉሜ 02 ቀን 2012 ዓ.ም
…………./////………..
በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡
የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡
አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡
32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
ጳጉሜ 02 ቀን 2012 ዓ.ም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ስመ ጥር ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የሀገራችንን አቋም የሚያሳይ ቪድዮ ተለቀቀ።
EEP new year 2013.mpg
384.2 MB
እንኳን ለ2013 ዓ.ም. በሰላም አደረሳችሁ!!
አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይመኛል!!
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
🌻🌻 መልካም 🌻🌻
🌻🌻 አዲስ 🌻🌻
🌻🌻 ዓመት 🌻🌻
🌻🌹🌾🌻💐🌷🌻
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይመኛል!!
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
🌻🌻 መልካም 🌻🌻
🌻🌻 አዲስ 🌻🌻
🌻🌻 ዓመት 🌻🌻
🌻🌹🌾🌻💐🌷🌻
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
እንኳን ለ2013 ዓ.ም. በሰላም አደረሳችሁ!!
አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንልን ከልቤ እመኛለሁ!!
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
🌻🌻 መልካም 🌻🌻
🌻🌻 አዲስ 🌻🌻
🌻🌻 ዓመት 🌻🌻
🌻🌹🌾🌻💐🌷🌻
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንልን ከልቤ እመኛለሁ!!
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
🌻🌻 መልካም 🌻🌻
🌻🌻 አዲስ 🌻🌻
🌻🌻 ዓመት 🌻🌻
🌻🌹🌾🌻💐🌷🌻
🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊
25 ጊጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት ካለው ድርጅት ጋር ውይይት ተካሄደ
...................////............
ፎርቲስኪው የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት በ10 ቢሊዮን ዶላር 15 ጊጋ ዋት ከውሃና 10 ጊጋ ዋት ከጂኦ ተርማል ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡
የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በሸራተን አዲስ ሆቴል ከድርጅቱ ተወካዮች ጋር በተካሄደው ውይይት ላይ እንደገለፁት መንግስት 45 በመቶ ብቻ የሆነውን የኃይል ተደራሽነት ለማሻሻል የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ማከናወኑን ገልፀዋል።
በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የኃይል ተደራሽነት ለማሳደግ ንፁህና ታዳሽ ኃይል በማልማት ፣ ዘርፉንም ፋይናንስ በማድረግና የግሉን ባለሃብት በማሳተፍ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማትን የመገንባት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ለልዑካኑ አብራርተውላቸዋል፡፡
እ.አ.አ. በ2030 ኢትዮጵያ ለዜጎቿ መቶ በመቶ ኃይል ለማቅረብ የያዘችውን ዕቅድ ለማሳካት ድርጅቱ ያሳየው ተነሳሽነት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል እያቀረበች እንደሆነና 350 ሜጋ ዋት የደረሰው የኃይል ሽያጭ በጥቂት ዓመታት ወደ 700 ለማሳደግ መታቀዱንም ገልጸውላቸዋል፡፡
በተለይ በከተሞች አካባቢ እየጨመረ የመጣው የኢንዱስትሪዎች መስፋፋትና የኃይል ፍላጎት መጨመር ለግል ባለሀብቱ ትልቅ ዕድል እንደሆነም ጠቅሰውላቸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ንጹህና ታዳሽ ኃይል ማልማት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ምቹ እንደሆነችና ሰፊ አማራጮችም እንዳሏት ነግረዋቸዋል፡፡
በተለያዩ ዓለም ሀገራት ንጹህና ታዳሽ ኃይል በማመንጨት ግንባር ቀደም የሆነው ፎርቲስኪው የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ልዑካን ድርጅታቸው በኢትዮጵያ በ10 ቢሊዮን ዶላር 15 ጊጋ ዋት ከውሃና 10 ጊጋ ዋት ከጂኦ ተርማል ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት እንዳለው ለሚኒስትሩ ገልፀውላቸዋል።
ውይይቱም በኢትዮጵያ የኃይል ልማቱን ለመጀመር ያለንን ተነሳሽነት ለማሳየት ሲሆን ይህን ድርጅቱ በአውስትራሊያ በጊኒና በሌሎችም ሃገራት ተመሳሳይ ሥራ በመሥራት ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።
የሚሠሩትም የልማት ሥራ በርካታ ሥራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና በተለይም ሴቶችን ያሳተፈ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡
ሚኒስትሩም የድርጅቱ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን ማፍሰስ ዘርፈ ብዙ ትልቅ እድል ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ፎርቲስኪው በማዕድን ፣ በማዳበሪያ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የተሰማራ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው፡፡
መስከረም 07 ቀን 2013 ዓ/ም
...................////............
ፎርቲስኪው የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት በ10 ቢሊዮን ዶላር 15 ጊጋ ዋት ከውሃና 10 ጊጋ ዋት ከጂኦ ተርማል ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡
የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በሸራተን አዲስ ሆቴል ከድርጅቱ ተወካዮች ጋር በተካሄደው ውይይት ላይ እንደገለፁት መንግስት 45 በመቶ ብቻ የሆነውን የኃይል ተደራሽነት ለማሻሻል የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ማከናወኑን ገልፀዋል።
በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የኃይል ተደራሽነት ለማሳደግ ንፁህና ታዳሽ ኃይል በማልማት ፣ ዘርፉንም ፋይናንስ በማድረግና የግሉን ባለሃብት በማሳተፍ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማትን የመገንባት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ለልዑካኑ አብራርተውላቸዋል፡፡
እ.አ.አ. በ2030 ኢትዮጵያ ለዜጎቿ መቶ በመቶ ኃይል ለማቅረብ የያዘችውን ዕቅድ ለማሳካት ድርጅቱ ያሳየው ተነሳሽነት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል እያቀረበች እንደሆነና 350 ሜጋ ዋት የደረሰው የኃይል ሽያጭ በጥቂት ዓመታት ወደ 700 ለማሳደግ መታቀዱንም ገልጸውላቸዋል፡፡
በተለይ በከተሞች አካባቢ እየጨመረ የመጣው የኢንዱስትሪዎች መስፋፋትና የኃይል ፍላጎት መጨመር ለግል ባለሀብቱ ትልቅ ዕድል እንደሆነም ጠቅሰውላቸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ንጹህና ታዳሽ ኃይል ማልማት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ምቹ እንደሆነችና ሰፊ አማራጮችም እንዳሏት ነግረዋቸዋል፡፡
በተለያዩ ዓለም ሀገራት ንጹህና ታዳሽ ኃይል በማመንጨት ግንባር ቀደም የሆነው ፎርቲስኪው የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ልዑካን ድርጅታቸው በኢትዮጵያ በ10 ቢሊዮን ዶላር 15 ጊጋ ዋት ከውሃና 10 ጊጋ ዋት ከጂኦ ተርማል ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት እንዳለው ለሚኒስትሩ ገልፀውላቸዋል።
ውይይቱም በኢትዮጵያ የኃይል ልማቱን ለመጀመር ያለንን ተነሳሽነት ለማሳየት ሲሆን ይህን ድርጅቱ በአውስትራሊያ በጊኒና በሌሎችም ሃገራት ተመሳሳይ ሥራ በመሥራት ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።
የሚሠሩትም የልማት ሥራ በርካታ ሥራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና በተለይም ሴቶችን ያሳተፈ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡
ሚኒስትሩም የድርጅቱ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን ማፍሰስ ዘርፈ ብዙ ትልቅ እድል ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ፎርቲስኪው በማዕድን ፣ በማዳበሪያ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የተሰማራ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው፡፡
መስከረም 07 ቀን 2013 ዓ/ም
ፎርቲስኪው በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት አለው
……………../////………………..
በማዕድን ፣ በማዳበሪያ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በሃይድሮጂን ምርት እና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የተሰማራው ፎርቲስኪው በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ በማዕድን ልማት፣ በማዳበሪያ አቅርቦትና በሃይድሮጂን ምርት ሲሰማራ የሚያስፈልገውን ኃይል በራሱ ከማሟላት ባሻገር የሚያመርተውን ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የኃይል ቋት በመጠቀም እስከ 25 ጊጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት አለው፡፡
የፎርቲስኪው እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ በማሻሻል ኤሌክትሪክ ለሁሉም ለማዳረስ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ታምኖበታል፡፡
ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን በሀገሪቱ የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ በማሳካት በአህጉሪቱ በቀዳሚነት ለመሰለፍ ማለሙን ይፋ አድርጓል፡፡
መስከረም 08 ቀን 2013 ዓ/ም
……………../////………………..
በማዕድን ፣ በማዳበሪያ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በሃይድሮጂን ምርት እና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የተሰማራው ፎርቲስኪው በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ በማዕድን ልማት፣ በማዳበሪያ አቅርቦትና በሃይድሮጂን ምርት ሲሰማራ የሚያስፈልገውን ኃይል በራሱ ከማሟላት ባሻገር የሚያመርተውን ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የኃይል ቋት በመጠቀም እስከ 25 ጊጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት አለው፡፡
የፎርቲስኪው እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ በማሻሻል ኤሌክትሪክ ለሁሉም ለማዳረስ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ታምኖበታል፡፡
ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን በሀገሪቱ የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ በማሳካት በአህጉሪቱ በቀዳሚነት ለመሰለፍ ማለሙን ይፋ አድርጓል፡፡
መስከረም 08 ቀን 2013 ዓ/ም
ከ25 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የቢሾፍቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ
………………..///………………
ከአዲስ አበባ በ45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በቢሾፍቱ ከተማ የተገነባው ባለ 400/230/15 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑን የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ ዳዊት ገብረ እግዚአብሄር ገለጹ፡፡
አቶ ዳዊት እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ስራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል፡፡
ከነባሩ አቃቂ - ገላን ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ እስከ ቢሾፍቱ ማከፋፈያ ድረስ 46 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ጥንድ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታም ተከናውኗል፡፡
የፕሮጀከቱ የሳይት ተቆጣጣሪ መሃንዲስ አቶ ዘውዱ ለገሰ እንደገለፁት ማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 600 ሜጋ ቮልት አምፒር እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትንስፎርመሮች ተተክለውለታል፡፡
ጣቢያው ጥንድ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እና ሁለት ጥንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እንዲሁም 10 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡
የማከፋፋያ ጣቢያውን የገነባው ላርሰን ኤንድ ቱብሮ የተባለ የህንድ ኩባንያ ሲሆን ግንባታው ለመጨረስ ከ25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ ተደርጎበታል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በቢሾፍቱ ከተማ እና በዙሪዋ ለሚገኙ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎችና የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲሁም ለህብረተሰቡ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይታመናል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም.
………………..///………………
ከአዲስ አበባ በ45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በቢሾፍቱ ከተማ የተገነባው ባለ 400/230/15 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑን የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ ዳዊት ገብረ እግዚአብሄር ገለጹ፡፡
አቶ ዳዊት እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ስራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል፡፡
ከነባሩ አቃቂ - ገላን ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ እስከ ቢሾፍቱ ማከፋፈያ ድረስ 46 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ጥንድ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታም ተከናውኗል፡፡
የፕሮጀከቱ የሳይት ተቆጣጣሪ መሃንዲስ አቶ ዘውዱ ለገሰ እንደገለፁት ማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 600 ሜጋ ቮልት አምፒር እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትንስፎርመሮች ተተክለውለታል፡፡
ጣቢያው ጥንድ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እና ሁለት ጥንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እንዲሁም 10 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡
የማከፋፋያ ጣቢያውን የገነባው ላርሰን ኤንድ ቱብሮ የተባለ የህንድ ኩባንያ ሲሆን ግንባታው ለመጨረስ ከ25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ ተደርጎበታል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በቢሾፍቱ ከተማ እና በዙሪዋ ለሚገኙ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎችና የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲሁም ለህብረተሰቡ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይታመናል፡፡
የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour
መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም.