EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
134K subscribers
42.1K photos
483 videos
80 files
13.5K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
8ቱ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አከባበር ልማዶች በዓለም ዙሪያ
************************

ቱሪዝም ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራው ሎንሊ ፕላኔት የተባለው ድረገጽ “8 የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል አከባበር ልማዶች ከዓለም ዙሪያ” በሚል ርዕስ ስር ባስነበበው ጽሁፉ ኢትዮጵያን ጨምሮ በገና ሰሞን ለየት ያለ የአከባበር ባሕል ያላቸውን አገራት ልምዶች አካፍሏል።

ኢትዮጵያ የተካተተችበት ይህ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አከባበር ባህል ምን ይመስላል?

1. ታኅሣሥ 29 ቀን (በጃንዋሪ 7) የሚከበረው የኢትዮጵያ ገና
“መጽሐፍ ቅዱስም ሆነ ታሪክ እንደሚነግረን ሦስት ጠቢባን ለተወለደው ሕጻን እጅ መንሻ ለማቅረብ በኮከብ እየተመሩ ከምስራቅ ወደ ቤተልሄም ሄዱ፡፡” እናም እነዚህ ሦስት ጠቢባን ከእስያ፣ አውሮፓ እና ኢትዮጵያ የሄዱ እንደነበሩም ይነሳል። ብዙ ኢትዮጵያውያን ግን ሦስቱ ጠቢባን (12 ናቸው የሚሉም አሉ) በሙሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው ብለውም ያምናሉ ይላል ድረ-ገጹ በጽሁፉ።

የኢትዮጵያ ቀን አቆጣጠር ከጁሊያን የዘመን ቀመር ጋር የሚስማማ ነው የሚለው የዚህ ድረ ገጽ ዘገባ ይህም በመሆኑ የክርስቶስ ልደትን በታኅሣሥ 29 (January 7) እንዲያከብሩ አስችሏቸዋል ብሏል፡፡ እናም ኢትዮጵያውያን በዓሉን በሚያከብሩበት ጊዜ ነገሥታት የሚያስመስላቸውን ነጭ በነጭ ለብሰው፣ ጥለት ያለበት ነጠላ አጣፍተው፣ ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ እንደሚያከብሩት ነው ያተተው፡፡

ሙሉ ፅሁፉን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://ebc.et/newsdetails.aspx?newsid=9167
👍113
የበዓል ዋዜማን ከእኛ ጋር ያሳልፉ
***********

ዛሬ በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል ምሽት ከ12፡00 እስከ 4፡30 ሰዓት

የአዕላፋት ዝማሬ፣ ከቦሌ መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን

የሰላም ልዑል የኳየር ኮንሰርት ከጊዮን ሆቴል

ዝማሬ ከቅዱስ ዮሴፍ ካቶሊካዊት ቤ/ክርስቲያን የዋዜማችን ድምቀቶች ናቸው፡፡

ሸጎሌ ከሚገኘው ዋናው የኢቢሲ ስቱዲዮ ጨምሮ ከአራቱ የክልል ስቱዲዮዎቻችን ባሕርዳር፣ ወላይታ፣ አሶሳ እና ጅማ የተለያዩ በዓል በዓል የሚሸቱ መረጃዎችን በቀጥታ ስርጭት ወደ እናንተ እናደርሳችኋለን፡፡

የዋዜማውን የምሽት ድባብ ከተለያዩ አዲስ አበባ አካባቢዎች እንቃኛለን፡፡

ዋዜማውን ከእኛ ጋር ብታሳልፉ ታተርፋላችሁ፡፡

በቴሌቪዥን መስኮት የመዝናኛ ቻናላችሁን ክፍት አድርጋችሁ ጠብቁን እንዲሁም በዶትስትሪም የመዝናኛ ፌስቡክ ገፃችን የዋዜማ ዝግጅቱን በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ፡፡

መልካም በዓል!
👍116
ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
***************

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው፣ የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን ሲያከብሩ በኃይማኖታዊ አስተምህሮው መሠረት በልደቱ ያገኙትን በረከትና መዳን፣ ትህትናና ፍቅር በተግባር በማሳየት ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ለሀገራችን ሠላም በአብሮነት መቆም አለብን ያሉት አቶ አሻድሊ፤ የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ ጥረቶችን በተባበረ ክንድ ዕውን ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በክልሉ ሠላምን ለማረጋገጥ በተሰሩ ሥራዎች አመርቂ ውጤት መገኘቱን ጠቅሰው፤ ሰላሙን ዘላቂ ከማድረግ ጎን ለጎን እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል በጋራ መትጋት ይጠበቃል ብለዋል።

የእምነቱ ተከታዮች የልደት በዓልን ሲያከብሩ አብሮነትን በማጠናከር፣ ፍቅርና ይቅርታን በማጎልበት፣ የተቸገሩትን በመርዳት ሊሆን እንደሚገባም መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለበዓሉ አደረሣችሁ ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እንዲሆንም ተመኝተዋል።
👍124👎3
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
**************

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሰው ልጆች እና በአምላክ መካከል የነበረውን የጥል ግድግዳ አፍርሶ በምህረት፣ በይቅርታ እና በታላቅ ፍቅር ወደ ምድር መምጣቱ ሰላምን እና ፍቅርን ለምድር እንዲሁም አብሮነት እንዲጎለብት ምሳሌ ለመሆን ነው ብለዋል::

ስለዚህ በዓሉን ስናከብር የኢየሱስ ክርስቶስን ምሳሌነትን በመከተል የሰላም እሴቶችን እየገነባን፣ ፍቅራችንን ይበልጥ እያጎለበትን እንዲሁም አብሮነታችንን እያጠናከርን ሊሆን ይገባል ሲሉም አስፍረዋል::

በዓሉን ስናከብር ያላቸው ለሌላቸው ማዕድ በማጋራት ፍቅር፣ መተሳሰብና አብሮነት በሚገለጽበት መልክ እንዲሆን ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከንቲባዋ በዓሉ የሰላም እና የደስታ በዓል እንዲሆንም ተመኝተዋል፡፡
17👍6👎2
ከንቲባ ከድር ጁሀር ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
********************

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከንቲባው በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረው የገና በዓል የስጦታ እና የልግስና በዓል መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በዓሉን ስናከብር በተለያዩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ ወገኖችን በተለይም ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው አቅመ ደካማ አረጋውያንን ፣ ወላጆቻቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ያጡ ህጻናትን ፣ ታምመው አልጋ ላይ የዋሉ ሕሙማንን በማሰብና የበዓሉ ደስታ የእነሱም እንዲሆን በማድረግ ልናሳልፍ ይገባል ብለዋል።

ከንቲባው በዓሉ የሰላም የፍቅር ፣ የጤና ፣ የብልጽግና የመደጋገፍና የመተጋገዝ ይሁንልን ሲሉም መልካም ምኞታቸውን መግለጻቸውን የአስተዳደሩ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመልክታል።
👍228👏5
የገና በዓል ገበያ ድባብ በአዲስ አበባ
*************

በአዲስ አበባ በጉለሌ እና ሾላ ገበያ አካባቢዎች የቁም እንስሳትና የተለያዩ የምግብ ፍጆታዎች ግብይት በፎቶ፡-

📷 ኢቢሲ ዶትስትሪም
👍132
የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ የአደራ መልእክት

"ከዚህ ምርጫ በኋላ ለአገሬ የምመኘው ሰላም፣ አንድነት እና ብልፅግና ነው፡፡ እኔም በ91 ዓመቴ በምርጫው የተሳተፍኩኝ ሲሆን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የማስተላልፈው መልእክት የአገሪቱን ሰላምና አንድነት እንድትጠብቁ አደራ እላለሁ፡፡ አገር ከፖለቲካ ፓርቲዎች በላይ ናት፡፡"

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በተካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስተላለፉት መልእክት
41👍24👎4