Debre markos preparatory school
1.06K subscribers
316 photos
5 videos
295 files
52 links
Download Telegram
Grade 12 physics unit 2 horizontal projectile motion https://youtu.be/o1jBMcjeZYM?si=7PO-dAgle7KyQZDb
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
" ተማሪዎች ምደባቸውን በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et እና
በቴሌግራም ቦት፦
@moestudentbot መመልከት ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር

የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ ተለቋል፡፡

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባቸው ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ተማሪዎች ምደባቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et
በቴሌግራም ቦት፦ @moestudentbot

Via @tikvahuniversity
Forwarded from Yamral Tadesse
#Hemorrhagic_Fever ምንድን ነው
‎ይህ በሽታ በቫይረስ የሚከሰት ከባድ የበሽታ ቡድን ነው ። በሽታው በመሰረቱ የደም መፍሰስን ወይም የደም መርጋትን በሰውነት ውስጥ የሚያመጣ ነው ። በርካታ የሰውነት አካላትን በማጥቃት እና በሰውነት ውስጥ ያሉ የደም ሥሮችን የሚጎዳ ፣ በተለያዩ ቫይረሶች የሚመጣ በሽታ ነው።

#‎የበሺታው_መንስኤ እና የቫይረስ ዓይነት

‎. Ebola and ,Rift Valley Fever (RVF) & Yellow Fever ተብሎ የሚከፈል ሲሆን እንደ #ኢቦላቫይረስ#ደንጉ እና #የለውፊቨር የተባሉ ቫይርሶች የበሺታው መንስኤ ሲሆኑ #በትንኝ ንክሻም የሚመጡ ናቸው ።

‎ በሽታው ስሙ እንደሚያመለክተው በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ደም እንዲፈስ በማድረግ ለሞት የሚዳርግ ህክምና አልባ አደገኛ በሺታ ነው።

‎በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ደም መድማት እና መፍስሥ ከተከሰተ የበሽታው ከባድ ደረጃ ምልክት ነው።

‎በሽታው እንዴት ይተላለፋል?

‎1· ከተያዙ እንስሳት ጋር በመነካካት፡ በእንስሳት (ለምሳሌ አይጥ) ፣ ሽንት፣ ምራቅ ፣ ወይም ሌሎች ከሰውነት የሚለቀቁ ፈሳሾች በሚነካኩበት ጊዜ።
‎2· በነፍሳት ንክሻ፡
‎3· ከሰው ወደ ሰው፡ ከተያዘ ሰው የሚገኘው ደም፣ ምራቅ፣ የሰውነት ፈሳሾች ወይም ሌሎች ክምችቶች በቀጥታ በሚነካኩበት ጊዜ። ይህ ለበሽታው ከባዱ እና ዋነኛው ዓይነት የመተላለፊያ መንገድ ነው።

#የበሽታው_ምልክቶች

‎ምልክቶቹ በድንገት ሊታዩ እና በፍጥነት ሊባባሱ ይችላሉ። አንድ ሰው በቫይረሱ በተጠቃ ከ 2-21 ቀናት ውስጥ ምልክቶቹ መታየት ይጀምራሉ

‎መጀመሪያ ላይ የሚታዩ ምልክቶች
‎ምልክቶቹን በሁለት ከፍሎ ማየት የሚቻል ሲሆን
‎የመጀመሪው ቀለል ያሉ ምልክቶች እና የመጨረሻው አደገኛ //አስጊ ደረጃ ላይ ሲደርስ የሚታዩ ናቸው

#የመጀመሪያ_ምልክቶች
‎· ከፍተኛ የሰውነት ሙቀት (ትኩሳት)
‎· ድካም እና የመዛል ስሜት
‎· የጡንቻ፣ የአጥንት ህመም እና ቁርጥማት
‎· ራስ ምታት
‎· የጉሮሮ ህመም

#ከባድ_ምልክቶች (በሽታው እየተባባሰ ሲሄድ)፡

‎· በቆዳ ስር ደም መውጣት
‎. ከአፍ፣ አፍንጫ፣ ከዓይን ወይም ከጆሮ ደም መፍሰስ።
‎· የጭንቅላት አዕምሮ መናጋት ፣ መደንገጥ፣
‎. ራስን መሳት ኮማ ውስጥ መግባት)
‎· የኩላሊት እና የጉበት መጎዳት እና ስራ ማቆም
‎· ከፍተኛ ድካም እና ሾክ/Shock
‎· የበርካታ አካላት አለመሥራት

‎እንዴት መከላከል ይቻላል ?

‎በሽታው በትንኝ ንክሻ አማካኝነት የሚተላለፍ በመሆኑ #የአልጋ_አጎበርን ነፍሶን ከሞት መታደግ ስለሆነ በአግባቡ ይጠቀሙት ። ከታማሚ ሰው ጋር ያልዎትን ንክክ መከላከል እና
‎አፋጣኝ አስፈላጊ የህክምና እርዳታ ማግኘት አስፈላጉ ሆኖ ፣በሺታውን ሙሉበሙሉ ማዳን የሚችል ህክምና የለም ፣
‎መከላከል ብቸኛው ቁልፍ መንገድ ነው !

‎ የሚከተሉትን ማድረግ ያስፈልግዎታል !!

‎1. እጆችዎን በንፅህና ይታጠቡ፡ በሳሙና እና በንጹህ ውሃ ዘወትር ማጠብ አስፈላጊ ነው።
‎2. ከሌሎች ሰዎች (ክምችቶች) ራስዎን ይጠብቁ፡ ከሰዎች ደም፣ ምራቅ ወይም ሌሎች ከሰውነት የሚለቀቁ ፈሳሾች ንክኪዎች ራስዎን ይጠብቁ። ይህ ለቤተሰብ አባላት እና በተለይም ለህክምና ባለሙያዎች እጂግ አስፈላጊ ነው።
‎ብዙ የህክምና/ጤ ና ባለሙያዎች ህይወታቸውን የሚያጡበት ወረርሺኝ ነው።
‎3. ከእንስሳት ይራቁ፣ አይጦችን እና ሌሎች እንስሳት ከቤትዎ አርቀው ያቆዩ። የሚታወቁ የእንስሳት ክምችቶች ባሉበት ስፍራ ጥንቃቄ አይለይዎት
‎4.ከ ነፍሳት ይጠበቁ ፣ አጎበር መጠቀም፡
ይህን በሽታ ለመግታት እና ለመቆጣጠር መከላከያ መንገዶቹ ላይ ማተኮሩ ይመከራል።
ውድ ተማሪዎቻችን በጣም ጠቃሚ ስለሆኑ ተጠቀሙባቸው።
የተማሪዎች_ስነ_ምግባር_መመሪያ_2018_@Ethiopian_Digital_Library.pdf
312.4 KB
የተማሪዎች ስነ ምግባር መመሪያ 2018

ሁሉም ተማሪዎች ሊያነቧቸው ይገባል::

@Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library
የደ/ማ/አጠ/2ኛ ደረጃ ት/ቤት የወላጅ ውይይት መድረክ በ26/04/2018ዓም ተካሄደ
አዲሱ የክፍል መሸጋገሪያ መመሪያ ምን ይላል?

​በአዲሱ የትምህርት ሥርዓት (6-2-4) መሠረት፣ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ለመሸጋገር "ዝም ብሎ አማካይ ውጤት" ማምጣት ብቻ በቂ አይደለም።

መመሪያው የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አካቷል፦
​1. የማለፊያ ነጥብ (Pass Mark):
👉​ማንኛውም ተማሪ ከክፍል ወደ ክፍል ለመሸጋገር በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ቢያንስ 50% እና ከዚያ በላይ ማምጣት አለበት።
👉​ከአንድ በላይ የትምህርት ዓይነት ላይ ከ50% በታች (Fail) ያመጣ ተማሪ እንደ ድሮው "በአማካይ" ማለፍ አይችልም፤ ክፍሉን እንዲደግም ይገደዳል።

​2. የ50/50 የውጤት አሰጣጥ ሥርዓት:
👉​50% ተከታታይ ምዘና (Formative Assessment): ይህ በክፍል ውስጥ የሚሰሩ ስራዎች፣ ፕሮጀክቶች፣ ተግባራዊ ሙከራዎችና አጫጭር ፈተናዎችን ያካትታል።
👉​50% የማጠቃለያ ፈተና (Summative Assessment): በሴሚስተር መጨረሻ የሚሰጥ አንድ ወጥ ፈተና።
👉​ትኩረት፦ ተማሪው በክፍል ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ካላደረገ የማጠቃለያ ፈተናው ብቻውን አያሳልፈውም።

​3. የብሔራዊ ፈተናዎች ለውጥ:
👉​6ኛ ክፍል: ተማሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ መካከለኛ ደረጃ (Middle School) ለመሸጋገር የክልል አቀፍ ፈተና ወስደው ማለፍ አለባቸው።
👉​8ኛ ክፍል: ወደ ሁለተኛ ደረጃ (High School) ለመግባት ክልላዊ ፈተና የግድ ነው።
👉​12ኛ ክፍል: ወደ ከፍተኛ ትምህርት ለመግባት የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በ10ኛ ክፍልም የመውጫ ፈተና ሊኖር ይችላል።

​4. የስነ-ምግባር እና የመገኘት መስፈርት:
👉​አንድ ተማሪ በዓመቱ ውስጥ ከ 80% በላይ በክፍል ውስጥ ካልተገኘ፣ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ወደ ቀጣዩ ክፍል አይሸጋገርም።

​5. ተግባር ተኮር ትምህርት:
👉​በአዲሱ ካሪኩለም፣ ተማሪዎች በንድፈ-ሀሳብ (Theory) ብቻ ሳይሆን በተግባር (Practical) ብቁ መሆናቸው ይገመገማል። በተለይ በሳይንስ ትምህርቶች የላብራቶሪ ስራዎች ውጤት ላይ ትልቅ ተጽዕኖ አላቸው።

💡 ወላጆች ምን ማድረግ ይኖርባቸዋል?
👉ልጅዎ በፈተና ሰሞን ብቻ እንዲያጠና ከመጠበቅ ይልቅ፣ በየቀኑ የሚሰጡ የቤት ስራዎችን እና የክፍል ስራዎችን (Portfolio) በትክክል መስራቱን መከታተል አለብዎት። ምክንያቱም 50% ውጤቱ የሚመዘገበው በየቀኑ ከሚሰራው ስራ ነው።

​#New_Curriculum#ትምህርት #አዲሱ_ካሪኩለም_የተማሪዎች_ውጤት!!

#Follow_Like_sher!!
ደ/ማ/አጠ/2ኛ/ደረጃ ትቤት የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ
ሰላም እንዴት ናቹህ የደ/ማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ የ2018ዓም ካርድ ለመውሰድ የዲጅታል ሊትሬሲ ሰርተፍኬት ማሳየት ስላለባቹህ ሁላችሁም በአትኩረት እንድትሰሩ እናሳስባለን::