#ሁለት በሬዎች ጋጣ ላይ እያሉ አንዱ ሰነፍ በሬ ለጓደኛው ዛሬ ገበሬው ሊጠምደን ሲመጣ አመመኝ ብዬ ዝርር እላለሁ ይለዋይ
ይገርማል....
ኤጭ አሁንስ መጠመድ ሰለቸኝ ቀንበር እላዬ ላይ ተሸክሜ እስከመቼ...ዛሬ ገበሬው ሊጠምደን ሲመጣ አመመኝ ብዬ ዝርርእላለሁ ይለዋል። ጓደኛውም ቀንዱን አዘቅዝቆ በሹክሹክታ ተው ግዴለክም እንረስ በኋላ መተኛት መዘዙ ብዙ ነው አትለግም ተነስ…ይለዋል።አንደኛው በሬ ግን በሀሳቡ ፀንቶ ልክ ገበሬው ሲመጣ መሬት ላይ ፍንግል ብሎ አልነሳም አለ።በበሬው ሁኔታ የደነገጠው ገበሬ ታድያ የቀዬውን ሰወች ጮኾ "ድረሱልኝ"ሲል መጣራት ጀመረ....ይሄኔ አጅሬው በሬ ገበሬው አዘነልኝ ብሎ በውስጡ ደስ መሰኘት ጀመረ...ከደቂቃወች በኋላ ግን የተጠሩት ሰወች ሲደርሱ ሁሉም በእጃቸው ካራ(ቢላ )እንደያዙ
በሉ ቶሎ እንባርከው... ከሞተ ጥንብ ይሆናል...በሉ እግሩን እሰሩት...ያዙ ያዙ እያሉ መጯጯህ ጀመሩ
የገዛ አሳዳጊው እግሩን ለመያዝ ሲተባበር አየ።ሊያድኑት የተጠሩ የመሰለው ጭንቅላቱን በሀይል እያቃኑ አንገቱን ሊቆርጡት መሆኑን አወቀ።ይሄኔ ውሸታሙ በሬ ቢፈራገጥ ቢጮህ ቢያለቅስ መታረዱ ግድ ሆነና በራሱ እጅ ሞቱን አፈጠነ። ይሄኔ ጓደኛው በሬ ቆሞ እያየ
ሞኙ በሬ ሆይ ሞኙ በሬ ሆይ
"ከካራ"መጠመድ አይሻልም ወይ ....አለው
ወንድሜ....እንግዲህ ስንፍና ሚያስከትለው ሞት መሆኑን አይተካል።አለም ደከመው አመመው ደበረው ብላ አትረዳንም!! የውሸት ስትተኛ የእውነት መሞቻ ቀንህን እያቀረብክ መሆኑን አትርሳ!!ካልታመምክ በቀር በቻልካት በአቂሚቲ ተነስተህ የሆነች ነገር አድርገህ ዋል፡፡ባትሰራ ቤተክርስትያን ሄደህ ፀልየህ ተመለስ።ተኝተህ ከቆየህ ጎረቤቶቹን እንደጠራው ገበሬ ሰይጣንም ድህነት፤ ድባቴ፤ ጭንቀት፤ስንፍና፤ የበታችነት፤ሲልም ደሞ ሞትን ጠርቶ እጅህ እና እግርህን አስሮ ያሰናብትሐል....
ይገርማል....
ኤጭ አሁንስ መጠመድ ሰለቸኝ ቀንበር እላዬ ላይ ተሸክሜ እስከመቼ...ዛሬ ገበሬው ሊጠምደን ሲመጣ አመመኝ ብዬ ዝርርእላለሁ ይለዋል። ጓደኛውም ቀንዱን አዘቅዝቆ በሹክሹክታ ተው ግዴለክም እንረስ በኋላ መተኛት መዘዙ ብዙ ነው አትለግም ተነስ…ይለዋል።አንደኛው በሬ ግን በሀሳቡ ፀንቶ ልክ ገበሬው ሲመጣ መሬት ላይ ፍንግል ብሎ አልነሳም አለ።በበሬው ሁኔታ የደነገጠው ገበሬ ታድያ የቀዬውን ሰወች ጮኾ "ድረሱልኝ"ሲል መጣራት ጀመረ....ይሄኔ አጅሬው በሬ ገበሬው አዘነልኝ ብሎ በውስጡ ደስ መሰኘት ጀመረ...ከደቂቃወች በኋላ ግን የተጠሩት ሰወች ሲደርሱ ሁሉም በእጃቸው ካራ(ቢላ )እንደያዙ
በሉ ቶሎ እንባርከው... ከሞተ ጥንብ ይሆናል...በሉ እግሩን እሰሩት...ያዙ ያዙ እያሉ መጯጯህ ጀመሩ
የገዛ አሳዳጊው እግሩን ለመያዝ ሲተባበር አየ።ሊያድኑት የተጠሩ የመሰለው ጭንቅላቱን በሀይል እያቃኑ አንገቱን ሊቆርጡት መሆኑን አወቀ።ይሄኔ ውሸታሙ በሬ ቢፈራገጥ ቢጮህ ቢያለቅስ መታረዱ ግድ ሆነና በራሱ እጅ ሞቱን አፈጠነ። ይሄኔ ጓደኛው በሬ ቆሞ እያየ
ሞኙ በሬ ሆይ ሞኙ በሬ ሆይ
"ከካራ"መጠመድ አይሻልም ወይ ....አለው
ወንድሜ....እንግዲህ ስንፍና ሚያስከትለው ሞት መሆኑን አይተካል።አለም ደከመው አመመው ደበረው ብላ አትረዳንም!! የውሸት ስትተኛ የእውነት መሞቻ ቀንህን እያቀረብክ መሆኑን አትርሳ!!ካልታመምክ በቀር በቻልካት በአቂሚቲ ተነስተህ የሆነች ነገር አድርገህ ዋል፡፡ባትሰራ ቤተክርስትያን ሄደህ ፀልየህ ተመለስ።ተኝተህ ከቆየህ ጎረቤቶቹን እንደጠራው ገበሬ ሰይጣንም ድህነት፤ ድባቴ፤ ጭንቀት፤ስንፍና፤ የበታችነት፤ሲልም ደሞ ሞትን ጠርቶ እጅህ እና እግርህን አስሮ ያሰናብትሐል....
🤝3