የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሾሙ። ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች የምትገኘውን የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው።
በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ የሚከተለው ሰፍሯል፦ “የተከበሩ የእርስዎ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል። ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።”
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አመራር፣ ኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች ያስመዘገበችው እድገት ከፍተኛ አፈጻጸም ያሳየ ነው። የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኢ-መንግሥት (e-government) አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል፣ በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩትን ማቋቋም እንዲሁም ሀገራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ መንደፍ ለለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት ናቸው። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የታቀደው ዕቅድ፤ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክር ይጠበቃል።
Prime Minister Abiy Ahmed has been appointed as the African Union Champion for Artificial Intelligence and Digital Health. The announcement recognises his leadership and Ethiopia’s growing role in advancing artificial intelligence and innovation across the continent.
The appointment letter noted: “Your Excellency’s leadership in promoting digital transformation and emerging technologies has helped position artificial intelligence as a key tool for sovereignty, efficiency, and inclusive growth in Africa. Your continued advocacy for strategic autonomy and technological empowerment will be instrumental in positioning the continent as a global leader in responsible and equitable AI adoption.”
Ethiopia’s progress in digitization and artificial intelligence launched and accelerated significantly under the Prime Minister’s active engagement over the last few years. Initiatives such as the expansion of digital infrastructure, the rollout of e-government services, investments in innovation ecosystems, and the establishment of an AI institute and development of a national AI strategy have laid a strong foundation for transformation. In addition, plans to establish a dedicated AI university are expected to strengthen research, talent development, and continental collaboration in emerging technologies.
#AIforAfrica
#PMOEthiopia
በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ የሚከተለው ሰፍሯል፦ “የተከበሩ የእርስዎ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል። ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።”
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አመራር፣ ኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች ያስመዘገበችው እድገት ከፍተኛ አፈጻጸም ያሳየ ነው። የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኢ-መንግሥት (e-government) አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል፣ በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩትን ማቋቋም እንዲሁም ሀገራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ መንደፍ ለለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት ናቸው። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የታቀደው ዕቅድ፤ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክር ይጠበቃል።
Prime Minister Abiy Ahmed has been appointed as the African Union Champion for Artificial Intelligence and Digital Health. The announcement recognises his leadership and Ethiopia’s growing role in advancing artificial intelligence and innovation across the continent.
The appointment letter noted: “Your Excellency’s leadership in promoting digital transformation and emerging technologies has helped position artificial intelligence as a key tool for sovereignty, efficiency, and inclusive growth in Africa. Your continued advocacy for strategic autonomy and technological empowerment will be instrumental in positioning the continent as a global leader in responsible and equitable AI adoption.”
Ethiopia’s progress in digitization and artificial intelligence launched and accelerated significantly under the Prime Minister’s active engagement over the last few years. Initiatives such as the expansion of digital infrastructure, the rollout of e-government services, investments in innovation ecosystems, and the establishment of an AI institute and development of a national AI strategy have laid a strong foundation for transformation. In addition, plans to establish a dedicated AI university are expected to strengthen research, talent development, and continental collaboration in emerging technologies.
#AIforAfrica
#PMOEthiopia
❤3👍1
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እንኳን ደስ አለዎት!
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው በመሾምዎ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን የጥረታቸው ፍሬ በአፍሪካ ደረጃ እውቅና አግኝቶ ለዚህ ሹመት መብቃታቸው ለኢትዮጵያን ሁሉ ኩራት ነው ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ !
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው በመሾምዎ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን የጥረታቸው ፍሬ በአፍሪካ ደረጃ እውቅና አግኝቶ ለዚህ ሹመት መብቃታቸው ለኢትዮጵያን ሁሉ ኩራት ነው ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ !
❤3👍1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ከሰአት በኋላ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የመሪዎቹ ግንኙነት ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር በኢትዮጵያ የሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት አካል ነው። የመሪዎቹ ውይይት በሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና የወል የትብብር መስኮችን በማጠናከር ላይ እንደሚያጠነጥን ይጠበቃል።
Prime Minister Abiy Ahmed receives H.E. Salva Kiir Mayardit, President of the Republic of South Sudan, at the National Palace this afternoon. The meeting takes place as part of President Kiir’s two-day official visit to Ethiopia. Discussions are expected to focus on bilateral relations and advancing areas of mutual cooperation.
#PMOEthiopia
Prime Minister Abiy Ahmed receives H.E. Salva Kiir Mayardit, President of the Republic of South Sudan, at the National Palace this afternoon. The meeting takes place as part of President Kiir’s two-day official visit to Ethiopia. Discussions are expected to focus on bilateral relations and advancing areas of mutual cooperation.
#PMOEthiopia
❤2
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ቅጠል ተራን ወደ ውብ መኖሪያ ሥፍራ!
ለመኖር እጅግ ምቹ ያልሆነ፤ ለሰው ልጅ ክብር በማይመጥን፤ በጣም የቆሸሸ፣ የተፋፈገ እና የተጨናነቀ እንዲሁም ከተማ እምብርት ላይ ሆነው በተተበተበ ለአደጋ አጋላጭ የሆነ የኤሌክትሪክ መስመር ብሎም በኩራዝና በሻማ የሚጠቀሙ ነዋሪዎች ይኖሩበት የነበረውን የቅጠል ተራ ሰፈርን፣ ወደ ውብ መኖሪያ አካባቢነት ለመቀየር ዛሬ ባለ 8 ወለል የሆኑ ብዛታቸው 9 ህንጻዎች ከ500 በላይ ቤቶችን ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠናል።
ይህ ፕሮጀክት አካባቢው መንገድ ያልነበረው፣ እንደ ሸረሪት ድር የተጠላለፉ ገመዶች የበዙበት፣ ነዎሪዎች በድህነት ምክንያት ኑሯቸውን ለመደጎም ቤታቸው ውስጥ ቆጥ ሰርተው አልጋ የሚያከራዩበትና ሰዎች ላይ ቆልፈው በሚሄዱበት ጊዜ በሚፈጠር የእሳት አደጋ የሰዎች ህይወት የሚጠፋበት፣ ንብረት የሚወድምበት፣ እጅግ ብዙ ገመናዎችን የያዘ አስከፊ የሰው ህይወትን የሚቀይር ፕሮጀክት ነው።
አካባቢው የከተማ እምብርት ሆኖ ሳለ፣ ነገር ግን በብዙዎቹ የገጠር አካባቢዎች እንኳን የቀረውን ሻማ እና ኩራዝ የሚጠቀም ነዋሪ ያለበት አካባቢ ነው።
መርካቶ አካባቢ ብዙ “ተራ” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው - ቅጠል ተራ፣ ጭድ ተራ፣ ገብስ ተራ፣ ሳር ተራ፣ ቦንብ ተራ … ጠጋ ብለን ስናያቸው የነዋሪዎቻችን የአኗኗር ሁኔታ እና ገፅታውን የሚያሳዩ ናቸው። እንደዚህ ዓይነት ችግሮችን ደጋግመን በማውራት ነዋሪው ሆድ እንዲብሰው ማድረግ ሳይሆን፣ መፍትሄው ሰርተን ህይወቱ እንዲቀየር እና ለሰው ልጆች የሚመጥን የክብር ኑሮ እንዲኖር እዚያው የመኖሪያ ቤት እና የንግድ ቦታዎች እንዲያገኝ ማድረግ ነው ።
በከተማችን ዋነኛ የስራዎቻችንን ማዕከል ሰው ተኮር ስራዎች አድርገን እየሰራን እንገኛለን ።
በቅጠል ተራ ያስጀመርነው የቤት ግንባታ 10ሺህ ካሬ ላይ ያረፈ፤ ተገንብቶ ሲጠናቀቅም ከ20,000 በላይ ሰዎችን ንፁህ፤ ለሰው ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗር ያለው መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጅክት ነው ።
ፕሮጀክቱ ልጆች ቦርቀው እንዲያድጉ የስፖርት ሜዳ እንዲሁም የንግድ ሱቆች እና ሊሎች አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ ተሟልተውለት በጥራት እና በፍጥነት ተገንብቶ ይጠናቀቃል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለመኖር እጅግ ምቹ ያልሆነ፤ ለሰው ልጅ ክብር በማይመጥን፤ በጣም የቆሸሸ፣ የተፋፈገ እና የተጨናነቀ እንዲሁም ከተማ እምብርት ላይ ሆነው በተተበተበ ለአደጋ አጋላጭ የሆነ የኤሌክትሪክ መስመር ብሎም በኩራዝና በሻማ የሚጠቀሙ ነዋሪዎች ይኖሩበት የነበረውን የቅጠል ተራ ሰፈርን፣ ወደ ውብ መኖሪያ አካባቢነት ለመቀየር ዛሬ ባለ 8 ወለል የሆኑ ብዛታቸው 9 ህንጻዎች ከ500 በላይ ቤቶችን ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠናል።
ይህ ፕሮጀክት አካባቢው መንገድ ያልነበረው፣ እንደ ሸረሪት ድር የተጠላለፉ ገመዶች የበዙበት፣ ነዎሪዎች በድህነት ምክንያት ኑሯቸውን ለመደጎም ቤታቸው ውስጥ ቆጥ ሰርተው አልጋ የሚያከራዩበትና ሰዎች ላይ ቆልፈው በሚሄዱበት ጊዜ በሚፈጠር የእሳት አደጋ የሰዎች ህይወት የሚጠፋበት፣ ንብረት የሚወድምበት፣ እጅግ ብዙ ገመናዎችን የያዘ አስከፊ የሰው ህይወትን የሚቀይር ፕሮጀክት ነው።
አካባቢው የከተማ እምብርት ሆኖ ሳለ፣ ነገር ግን በብዙዎቹ የገጠር አካባቢዎች እንኳን የቀረውን ሻማ እና ኩራዝ የሚጠቀም ነዋሪ ያለበት አካባቢ ነው።
መርካቶ አካባቢ ብዙ “ተራ” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው - ቅጠል ተራ፣ ጭድ ተራ፣ ገብስ ተራ፣ ሳር ተራ፣ ቦንብ ተራ … ጠጋ ብለን ስናያቸው የነዋሪዎቻችን የአኗኗር ሁኔታ እና ገፅታውን የሚያሳዩ ናቸው። እንደዚህ ዓይነት ችግሮችን ደጋግመን በማውራት ነዋሪው ሆድ እንዲብሰው ማድረግ ሳይሆን፣ መፍትሄው ሰርተን ህይወቱ እንዲቀየር እና ለሰው ልጆች የሚመጥን የክብር ኑሮ እንዲኖር እዚያው የመኖሪያ ቤት እና የንግድ ቦታዎች እንዲያገኝ ማድረግ ነው ።
በከተማችን ዋነኛ የስራዎቻችንን ማዕከል ሰው ተኮር ስራዎች አድርገን እየሰራን እንገኛለን ።
በቅጠል ተራ ያስጀመርነው የቤት ግንባታ 10ሺህ ካሬ ላይ ያረፈ፤ ተገንብቶ ሲጠናቀቅም ከ20,000 በላይ ሰዎችን ንፁህ፤ ለሰው ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗር ያለው መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጅክት ነው ።
ፕሮጀክቱ ልጆች ቦርቀው እንዲያድጉ የስፖርት ሜዳ እንዲሁም የንግድ ሱቆች እና ሊሎች አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ ተሟልተውለት በጥራት እና በፍጥነት ተገንብቶ ይጠናቀቃል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤1
የከተማ አስተዳደራችንን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀምረናል።
በበጀት ዓመቱ በእቅድ ከያዝናቸው ተግባራት 96 በመቶ መፈፀም ችለናል።
ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው የግምገማ መድረክ በበጅት ዓመቱ ለመፈፀም ካቀድናቸው ውስጥ በ9 ወራት በጥብቅ ክትትል የተከናወኑትን የምንገመግምበት እና በቀሪ ወራት የትኩረት ማዕከል አድርገን የምንፈፅማቸው በመልካም አስተዳደር ተለይተው ያልተመለሱትን ምላሽ በመስጠት ማጠናቀቅ፣ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ችግሮችን በመቀነስ የዋጋ ንረትን መከላከል፣ የገበያ ማዛባት ችግሮችን መከላከል፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በመሶብ ዲጅታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት የጀመርነውን ውጤታማ ስራ በቀሪ ወራት በተሟላ ሁኔታ በማጠናቀቅና ወደ ስራ ማስገባት እንዲሁም ቀሪ አገልግሎቶችን ዲጅታላይዝ አድርጎ ወደ መሶብ ማስገባት፣ ተጀምረው በዚህ ዓመት መጠናቀቅ ያለባቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ የአፈፃፀም ግምገማ ማዕከላችን ይሆናሉ።
ባለፋት አምስት ዓመታት የእቅድ አፈፃፀማችን ከ90 በመቶ በላይ እያደገ መጥቶ በ2018 ደግሞ 96 በመቶ የደረሰበት ውጤታማ አፈፃፀም መኖሩን በመገምገም፣ ይህንን እያደገ የመጣ የመፈፀም ልምድ አጠናክረን መቀጠል እንድንችል በትኩረት እንገመግማለን ።
በተጨማሪም 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ነፃ፣ ተዓማኒና ገለልተኛ ሆኖ እንዲከናወን ሁሉም አመራራችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ትልቅ ሃላፊነት መወጣት እንዲችሉ የግምገማ አቅጣጫን አስቀምጠናል።
የነበሩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፣ ጉድለቶችን በመሙላት በቀሪዎች ወራት በላቀ መፈፀም የግምግማችን ማዕከል ይሆናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በበጀት ዓመቱ በእቅድ ከያዝናቸው ተግባራት 96 በመቶ መፈፀም ችለናል።
ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው የግምገማ መድረክ በበጅት ዓመቱ ለመፈፀም ካቀድናቸው ውስጥ በ9 ወራት በጥብቅ ክትትል የተከናወኑትን የምንገመግምበት እና በቀሪ ወራት የትኩረት ማዕከል አድርገን የምንፈፅማቸው በመልካም አስተዳደር ተለይተው ያልተመለሱትን ምላሽ በመስጠት ማጠናቀቅ፣ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ችግሮችን በመቀነስ የዋጋ ንረትን መከላከል፣ የገበያ ማዛባት ችግሮችን መከላከል፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በመሶብ ዲጅታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት የጀመርነውን ውጤታማ ስራ በቀሪ ወራት በተሟላ ሁኔታ በማጠናቀቅና ወደ ስራ ማስገባት እንዲሁም ቀሪ አገልግሎቶችን ዲጅታላይዝ አድርጎ ወደ መሶብ ማስገባት፣ ተጀምረው በዚህ ዓመት መጠናቀቅ ያለባቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ የአፈፃፀም ግምገማ ማዕከላችን ይሆናሉ።
ባለፋት አምስት ዓመታት የእቅድ አፈፃፀማችን ከ90 በመቶ በላይ እያደገ መጥቶ በ2018 ደግሞ 96 በመቶ የደረሰበት ውጤታማ አፈፃፀም መኖሩን በመገምገም፣ ይህንን እያደገ የመጣ የመፈፀም ልምድ አጠናክረን መቀጠል እንድንችል በትኩረት እንገመግማለን ።
በተጨማሪም 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ነፃ፣ ተዓማኒና ገለልተኛ ሆኖ እንዲከናወን ሁሉም አመራራችን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ትልቅ ሃላፊነት መወጣት እንዲችሉ የግምገማ አቅጣጫን አስቀምጠናል።
የነበሩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፣ ጉድለቶችን በመሙላት በቀሪዎች ወራት በላቀ መፈፀም የግምግማችን ማዕከል ይሆናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍3
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
በመዲናዋ በ9 ወራት ውስጥ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ለበርካታ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ተችሏል።
አዲስ አበባ | ሚያዚያ 2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙ ከ4.9 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ገንዘብ በርካታ የአካባቢ መሰረተ ልማት ጥያቄዎችን መመለስ ችሏል። ኮሚሽኑ በከተማዋ የነዋሪዎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻልና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ በኪሎ ሜትር የሚለኩና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በስኬት አጠናቋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 188.5 ኪሎ ሜትር የሰቤዝ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለኮብልስቶን ንጣፍ ስራ ዝግጁ ተደርጓል። የኅብረተሰቡን ተሳትፎ በማስተባበር 57.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የውስጥ ለውስጥ የጠጠር መንገድ ግንባታ የተከናዎነ ሲሆን 174.5 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ (Cobblestone) ጥገና ተጠናቋል።
ኮሚሽኑ የህዝብን አቅም ለአካባቢ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት በሚያስችል ስልት በመጠቀም 39 አነስተኛ ድልድዮችን፣ 42 የማኅበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላትን እንዲሁም 104 የጋራ መፀዳጃ ቤቶችን ገንብቶ ለተጠቃሚዎች አስተላልፏል።
በዘጠኝ ወራት ውስጥ 58.4 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መብራት ዝርጋታ፣ 93.1 ኪ.ሜትር የቴራዞ መንገድ ግንባታ፣ 460.8 ኪዩቢክ ሜትር የድጋፍ ግንብ እንዲሁም 79 ኪሎ ሜትር የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ግንባታ ስራ ተከናውኗል።
በተከናወኑ የአካባቢ ልማት ስራዎችም ከ1.7 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የተፈታ ሲሆን 8 ሺህ 715 ስራ ፈላጎ ዜጎች ጊዜያዊ የስራ እድል እና ከ771 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትሥስር አግኝተዋል።
#አዲስአበባ #የልማትዳታ #በጎፈቃድ #የመሠረተልማት #የ9ወራትሪፖርት #ኢትዮጵያዊነት
አዲስ አበባ | ሚያዚያ 2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙ ከ4.9 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ገንዘብ በርካታ የአካባቢ መሰረተ ልማት ጥያቄዎችን መመለስ ችሏል። ኮሚሽኑ በከተማዋ የነዋሪዎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻልና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ በኪሎ ሜትር የሚለኩና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በስኬት አጠናቋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 188.5 ኪሎ ሜትር የሰቤዝ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለኮብልስቶን ንጣፍ ስራ ዝግጁ ተደርጓል። የኅብረተሰቡን ተሳትፎ በማስተባበር 57.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የውስጥ ለውስጥ የጠጠር መንገድ ግንባታ የተከናዎነ ሲሆን 174.5 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ (Cobblestone) ጥገና ተጠናቋል።
ኮሚሽኑ የህዝብን አቅም ለአካባቢ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት በሚያስችል ስልት በመጠቀም 39 አነስተኛ ድልድዮችን፣ 42 የማኅበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላትን እንዲሁም 104 የጋራ መፀዳጃ ቤቶችን ገንብቶ ለተጠቃሚዎች አስተላልፏል።
በዘጠኝ ወራት ውስጥ 58.4 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መብራት ዝርጋታ፣ 93.1 ኪ.ሜትር የቴራዞ መንገድ ግንባታ፣ 460.8 ኪዩቢክ ሜትር የድጋፍ ግንብ እንዲሁም 79 ኪሎ ሜትር የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ግንባታ ስራ ተከናውኗል።
በተከናወኑ የአካባቢ ልማት ስራዎችም ከ1.7 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የተፈታ ሲሆን 8 ሺህ 715 ስራ ፈላጎ ዜጎች ጊዜያዊ የስራ እድል እና ከ771 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትሥስር አግኝተዋል።
#አዲስአበባ #የልማትዳታ #በጎፈቃድ #የመሠረተልማት #የ9ወራትሪፖርት #ኢትዮጵያዊነት
የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል፤ በስራና ክህሎት ዘርፍ በለውጡ ዓመታት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችውን ስኬቶች አብራርተዋል። ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት በማድረግና ብቁ የሰው ሀብት እንዲሁም ምቹ እና አስተማማኝ የሥራ ዕድል የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ማየት የተለመው ይህ ዘርፍ፤ ከለውጡ በኋላ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የስራ ስመሪት እንዲሁም ዜጎች በቤት ውስጥ እና ባሉበት ሆነው በሚሰሯቸው ስራዎች አማካኝነት ለ19,872,846 ዜጎች የስራ እድል ፈጥሯል።
ይህን ታላቅ ስኬት ለማስመዝገብ ያስቻለው፤ ኢንተርፕርነር ተቋማትን በመፍጠር፣ ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር ተቋማት ጋር አጋርነት በመፍጠር፣ የቢዝነስ መስፋፋት እና የልህቀት ማዕከላት በማሳደግ፣ ቲቬት ዲጂታላይዜሽን በማረጋገጥ ሰፊ ስራዎች በመተግበራቸው የተገኘ ውጤት ነው።
#PMOEthiopia
ይህን ታላቅ ስኬት ለማስመዝገብ ያስቻለው፤ ኢንተርፕርነር ተቋማትን በመፍጠር፣ ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር ተቋማት ጋር አጋርነት በመፍጠር፣ የቢዝነስ መስፋፋት እና የልህቀት ማዕከላት በማሳደግ፣ ቲቬት ዲጂታላይዜሽን በማረጋገጥ ሰፊ ስራዎች በመተግበራቸው የተገኘ ውጤት ነው።
#PMOEthiopia