ዛሬ በጉለሌ ክፍለ-ከተማ ተገኝተን 27ኛውን የተስፉ ብርሃን የምገባ ማዕከል ስራ በማስጀመር ከማዕከሉ ተጠቃሚዎች ጋር የትንሳዔ በዓልን በጋራ አክብረናል።
በጉለሌ ክፍለከተማ ሶስተኛ ቅርንጫፍ የሆነውን ይህ 27ኛው የተስፉ ብርሃን የምገባ ማዕከል ስራ በማስጀመር፣ የምገባ ማዕከሉ ተጠቃሚ ከሆኑ ለማህበራዊ ችግር ከተጋለጡ ፣ አልባሽ አጉራሽ ለሌላቸው የሀገር ባለውለታ፣ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖቻች ፣ ከአረጋዊያን እና ከአካል ጉዳተኞች ወገኖቻችንን እንኳን አደረሳችሁ ብለን በዓሉን በጋራ አክብረናል።
በዓሉ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ያለአንዳች ልዩነት ለሰው ልጆች ሁሉ ራስን እስከ መስጠት ያሳየንን ፍቅር፣ በአብሮነት በፍቅና በመተሳሰብ ምሳሌነቱ በመከተል ልንኖር እንደሚገባ የሚስተምር በዓል ነው።
እኛም በ28ቱም የተስፉ ብርሃን የምገባ ማዕከል በዚሁ በትንሳኤ በዓል ብቻ ሳይሆን ሁሌም ወገኖቻችን ስንመግብ ለዜጐቻችን ክብራችንና ፍቅራችንን የምንገልጥበትና ማህበራዊ ፍትህን የምናነግስበት ተግባር ነው።
በዓሉን ምክንያት በማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መዓድ የማቋደስ መርሐ-ግብር በማዕከላቱ እየተከናወኑ ይገኛሉ።
“መስጠት አያጎድልም” በሚል መርሕ የተደረገላቸዉን ጥሪ በመቀበል የገነቡት በጎ ፈቃደኛ “የአዲስ ቪው ሆቴል ባለቤት አቶ አብይ አበራ” እና በየቀኑ ለሚመመገብ የተረከበዉን “አኳስ ኮንስትራክሽን ፒ ኤል ሲ ባለቤት አቶ ወሰንን” በተጠቃሚዉ ወገን፣ በከተማ አስተዳደሩና በራሴ ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በዓሉ የመተባበር፣ የመደጋገፍ እና የፍቅር በዓል ይሁንልን! መልካም በዓል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በጉለሌ ክፍለከተማ ሶስተኛ ቅርንጫፍ የሆነውን ይህ 27ኛው የተስፉ ብርሃን የምገባ ማዕከል ስራ በማስጀመር፣ የምገባ ማዕከሉ ተጠቃሚ ከሆኑ ለማህበራዊ ችግር ከተጋለጡ ፣ አልባሽ አጉራሽ ለሌላቸው የሀገር ባለውለታ፣ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖቻች ፣ ከአረጋዊያን እና ከአካል ጉዳተኞች ወገኖቻችንን እንኳን አደረሳችሁ ብለን በዓሉን በጋራ አክብረናል።
በዓሉ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ያለአንዳች ልዩነት ለሰው ልጆች ሁሉ ራስን እስከ መስጠት ያሳየንን ፍቅር፣ በአብሮነት በፍቅና በመተሳሰብ ምሳሌነቱ በመከተል ልንኖር እንደሚገባ የሚስተምር በዓል ነው።
እኛም በ28ቱም የተስፉ ብርሃን የምገባ ማዕከል በዚሁ በትንሳኤ በዓል ብቻ ሳይሆን ሁሌም ወገኖቻችን ስንመግብ ለዜጐቻችን ክብራችንና ፍቅራችንን የምንገልጥበትና ማህበራዊ ፍትህን የምናነግስበት ተግባር ነው።
በዓሉን ምክንያት በማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መዓድ የማቋደስ መርሐ-ግብር በማዕከላቱ እየተከናወኑ ይገኛሉ።
“መስጠት አያጎድልም” በሚል መርሕ የተደረገላቸዉን ጥሪ በመቀበል የገነቡት በጎ ፈቃደኛ “የአዲስ ቪው ሆቴል ባለቤት አቶ አብይ አበራ” እና በየቀኑ ለሚመመገብ የተረከበዉን “አኳስ ኮንስትራክሽን ፒ ኤል ሲ ባለቤት አቶ ወሰንን” በተጠቃሚዉ ወገን፣ በከተማ አስተዳደሩና በራሴ ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በዓሉ የመተባበር፣ የመደጋገፍ እና የፍቅር በዓል ይሁንልን! መልካም በዓል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤2
የአካባቢያችንን ገጽታ ለመቀየርና የተሻለ የመኖሪያ አካባቢ ለመፍጠር የጀመርነው የተቀናጀ የልማት ስራ በነዋሪዎቻችን ንቁ ተሳትፎ ተጠናክሮ ቀጥሏል። እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል በጉልበቱ፣ በእውቀቱና በገንዘቡ እያደረገ ያለው ያልተቆጠበ ድጋፍ ለስራችን መሳካት ትልቁን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል።
ይህ በጋራ የመልማት ባህላችን የአካባቢያችንን የመሰረተ-ልማት ጥያቄዎች በራስ አቅም ለመፍታት እንደምንችል ትልቅ ማሳያ ነው። ዛሬ የምናደርገው ርብርብ ነገ ለልጆቻችን የምታምርና ምቹ የሆነች አዲስ አበባን ለማውረስ የሚደረግ ትልቅ ኢንቨስትመንት በመሆኑ ኩራት ይሰማናል።
በአንድነት ከቆምን የማንለውጠው ነገር የለም፤ የአካባቢያችን ልማት በጋራ እጃችን ነው!
#የህብረተሰብተሳትፎ #የአካባቢልማት #ልማትበጋራ #ኢትዮጵያ
ይህ በጋራ የመልማት ባህላችን የአካባቢያችንን የመሰረተ-ልማት ጥያቄዎች በራስ አቅም ለመፍታት እንደምንችል ትልቅ ማሳያ ነው። ዛሬ የምናደርገው ርብርብ ነገ ለልጆቻችን የምታምርና ምቹ የሆነች አዲስ አበባን ለማውረስ የሚደረግ ትልቅ ኢንቨስትመንት በመሆኑ ኩራት ይሰማናል።
በአንድነት ከቆምን የማንለውጠው ነገር የለም፤ የአካባቢያችን ልማት በጋራ እጃችን ነው!
#የህብረተሰብተሳትፎ #የአካባቢልማት #ልማትበጋራ #ኢትዮጵያ
በመዲናችን አዲስ አበባ በዚህ ሚያዝያ ወር ሶስት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች ይከናወናሉ።
በዚህ ወር ከሚካሄዱ ሶስት ዓለምአቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች ውስጥ አንዱ በመጪው ቅዳሜ የሚካሄደው የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአንድ ቀን የአትሌቲክስ ውድድር ነው።
ይህ ውድድር በመዲናችን አዲስ አበባ ሲካሄድ የመጀመሪያው ሲሆን ለዘርፍ መንግስት በሰጠው ትኩረት የስፖርት መሰረተ ልማቶች መስፋፋት እንደ ምክንያት ሊገለጽ ይችላል።
ውድድሩ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ እና ብዙ ተከታይ ያላቸው አትሌቶች ይሳተፉበታል። የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ ሚያዝያ 10 በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሚካሄድ ይሆናል።
በዚሁ ሚያዝያ ወር ከሚካሄዱ ውድድሮች ውስጥ ሲቲ ማውንቴን ባይክ ኢሊሚኔተር ዓለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር እና ግራንድ ኢትዮጵያን ረን የሚካሄዱ ይሆናል።
ከተማ አስተዳደሩ ውድድሩን ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቂ ዝግጅቶች ከማድረግ በዘለለ በኢትዮጵያ ያሉትን የስፖርት መሰረተ ልማቶች ለማስተዋወቅ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።
በዚህ ወር ከሚካሄዱ ሶስት ዓለምአቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች ውስጥ አንዱ በመጪው ቅዳሜ የሚካሄደው የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአንድ ቀን የአትሌቲክስ ውድድር ነው።
ይህ ውድድር በመዲናችን አዲስ አበባ ሲካሄድ የመጀመሪያው ሲሆን ለዘርፍ መንግስት በሰጠው ትኩረት የስፖርት መሰረተ ልማቶች መስፋፋት እንደ ምክንያት ሊገለጽ ይችላል።
ውድድሩ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ እና ብዙ ተከታይ ያላቸው አትሌቶች ይሳተፉበታል። የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ ሚያዝያ 10 በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሚካሄድ ይሆናል።
በዚሁ ሚያዝያ ወር ከሚካሄዱ ውድድሮች ውስጥ ሲቲ ማውንቴን ባይክ ኢሊሚኔተር ዓለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር እና ግራንድ ኢትዮጵያን ረን የሚካሄዱ ይሆናል።
ከተማ አስተዳደሩ ውድድሩን ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቂ ዝግጅቶች ከማድረግ በዘለለ በኢትዮጵያ ያሉትን የስፖርት መሰረተ ልማቶች ለማስተዋወቅ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።
👍2
ኢትዮጵያን የማኑፋክቸሪንግ ማዕክል የማድረግ ትልምን በተመለከተ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ቀዳሚውን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለመሆን በቢሾፍቱ የሚገነባውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ የሎጂስቲክስ መሠረተ ልማትን በማዘመን፣ እንደ ህዳሴ ግድብና ኒውክሌር ኢነርጂ ባሉ ፕሮጀክቶች አማካኝነት አስተማማኝና ንጹህ ኃይልን በማቅረብ፣ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ዝግጁነት ያለውን የወጣት የሰው ኃይል በሥልጠና በማብቃት ስልታዊ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። በተጨማሪም የግሉን ዘርፍ የሚያነቃቁ ምቹ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ፣ የፋይናንስ ሥርዓቱን በማሻሻልና ለስትራቴጂካዊ ምርቶች (እንደ ሶላር፣ ኤሌክትሮኒክስና መድኃኒት ያሉ) ትኩረት በመስጠት ሀገሪቱን የኢንዱስትሪና የማኑፋክቸሪንግ ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተሠራ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ቀዳሚውን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለመሆን በቢሾፍቱ የሚገነባውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ የሎጂስቲክስ መሠረተ ልማትን በማዘመን፣ እንደ ህዳሴ ግድብና ኒውክሌር ኢነርጂ ባሉ ፕሮጀክቶች አማካኝነት አስተማማኝና ንጹህ ኃይልን በማቅረብ፣ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ዝግጁነት ያለውን የወጣት የሰው ኃይል በሥልጠና በማብቃት ስልታዊ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። በተጨማሪም የግሉን ዘርፍ የሚያነቃቁ ምቹ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ፣ የፋይናንስ ሥርዓቱን በማሻሻልና ለስትራቴጂካዊ ምርቶች (እንደ ሶላር፣ ኤሌክትሮኒክስና መድኃኒት ያሉ) ትኩረት በመስጠት ሀገሪቱን የኢንዱስትሪና የማኑፋክቸሪንግ ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተሠራ ነው።
ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚያደርጉበት፣ ህዝቡ የሚመራውን አካል በነፃነት በመምረጥ የስልጣን ባለቤትነትን የሚያረጋግጥበት ዲሞክራሲያዊ መድረክ ነዉ፡፡
በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲኖር ማድረግ፣ ከምርጫ ባለፈ ለሀገር ግንባታና ለሰላም ያለው ፋይዳ እጅግ ከፍተኛ ሲሆን፣ በህግና በህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሰላማዊ መንግስት ለማፅናት፣ ሀገር ከድህነት እና ከኋላቀርነት ለመታደግ የሚረዳ የስልጡን ዜጎች መገለጫ ነዉ።
ነፃና ፍትሃዊ በሆነ የምርጫ ሂደት የተመረጠ መንግስት፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት የሚኖረዉ ሲሆን፣ ይህም መንግስት የልማት ስራዎችን ለማከናወንና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡
በአጠቃላይ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለኢትዮጵያ የነፃነት፣ የፍትህና የዘላቂ እድገት መሰረት በመሆኑ፣ የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በሚንፀባረቁበት በ7ኛዉ ሃገራዊ ምርጫ የሚበጅዎትን ለመምረጥ የሚያስችልዎትን የምርጫ ካርድ በመዉሰድ በድምፅዎ ወሳኝ ቢሆኑ ያተርፋሉ እንጂ ሃገርና ትዉልድን ኪሳራ ላይ አይጥሉምና ታሪካዊ ሃላፊነታችንን በጋራ እንወጣ !!!
በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲኖር ማድረግ፣ ከምርጫ ባለፈ ለሀገር ግንባታና ለሰላም ያለው ፋይዳ እጅግ ከፍተኛ ሲሆን፣ በህግና በህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሰላማዊ መንግስት ለማፅናት፣ ሀገር ከድህነት እና ከኋላቀርነት ለመታደግ የሚረዳ የስልጡን ዜጎች መገለጫ ነዉ።
ነፃና ፍትሃዊ በሆነ የምርጫ ሂደት የተመረጠ መንግስት፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት የሚኖረዉ ሲሆን፣ ይህም መንግስት የልማት ስራዎችን ለማከናወንና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡
በአጠቃላይ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለኢትዮጵያ የነፃነት፣ የፍትህና የዘላቂ እድገት መሰረት በመሆኑ፣ የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶችና ፍላጎቶች በሚንፀባረቁበት በ7ኛዉ ሃገራዊ ምርጫ የሚበጅዎትን ለመምረጥ የሚያስችልዎትን የምርጫ ካርድ በመዉሰድ በድምፅዎ ወሳኝ ቢሆኑ ያተርፋሉ እንጂ ሃገርና ትዉልድን ኪሳራ ላይ አይጥሉምና ታሪካዊ ሃላፊነታችንን በጋራ እንወጣ !!!
አስተዳደሩ ባለፉት ስምንት ዓመታት 45 ሺህ 566 መኖሪያ ቤቶች በበጎ ፈቃድ ፕሮግራም ገንብቶ ለተጠቃሚዎች አስተላልፏል።
በከተማችን ለሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞችና ለሀገር ባለውለታዎች ምቹ መኖሪያን ለመፍጠር የተጀመረው የተቀናጀ የቤት ግንባታ መርሃ ግብር ታላቅ ሰብዓዊ ድል አስመዝግቧል። ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ 45,566 ቤቶች በአዲስ መልክ ተገንብተው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሲሆን፣ በዚህም ከ198,480 በላይ ቤተሰቦች የቤት ባለቤት መሆን ችለዋል።
ይህ ግዙፍ የልማት ስራ በበጎ ፈቃደኞችና በባለሀብቶች ያልተቆጠበ ድጋፍ የተከናወነ ሲሆን ለቤት ግንባታው በወቅቱ በነበረው የገበያ ሁኔታ በገንዘብ ሲተመን ከ25.3 ቢሊዮን ብር በላይ በበጎ ፈቃድ ሞብላይዝ ተደርጓል። ይህም የማህበረሰባችን የመረዳዳት አቅም ምን ያህል ግዙፍ እንደሆነና በአብሮነት መቆም ያለውን ፋይዳ በግልጽ የሚያመላክት ውጤታማ ስራ ነው።
ስኬቱ እውን እንዲሆን በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበት ላገዛችሁ ባለሀብቶች፣ በጎ ፈቃደኞችና የልማት አጋሮቻችን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችን እናቀርባለን። በቀጣይም ይህንን የበጎነት ጉዞ በማጠናከር ለብዙዎች መጠለያና ተስፋ መሆናችንን እንቀጥላለን።
#ቤትግንባታ #በጎፈቃደኝነት #ለወገንደራሽ #የአካባቢልማት #ኢትዮጵያ
በከተማችን ለሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞችና ለሀገር ባለውለታዎች ምቹ መኖሪያን ለመፍጠር የተጀመረው የተቀናጀ የቤት ግንባታ መርሃ ግብር ታላቅ ሰብዓዊ ድል አስመዝግቧል። ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ 45,566 ቤቶች በአዲስ መልክ ተገንብተው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሲሆን፣ በዚህም ከ198,480 በላይ ቤተሰቦች የቤት ባለቤት መሆን ችለዋል።
ይህ ግዙፍ የልማት ስራ በበጎ ፈቃደኞችና በባለሀብቶች ያልተቆጠበ ድጋፍ የተከናወነ ሲሆን ለቤት ግንባታው በወቅቱ በነበረው የገበያ ሁኔታ በገንዘብ ሲተመን ከ25.3 ቢሊዮን ብር በላይ በበጎ ፈቃድ ሞብላይዝ ተደርጓል። ይህም የማህበረሰባችን የመረዳዳት አቅም ምን ያህል ግዙፍ እንደሆነና በአብሮነት መቆም ያለውን ፋይዳ በግልጽ የሚያመላክት ውጤታማ ስራ ነው።
ስኬቱ እውን እንዲሆን በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበት ላገዛችሁ ባለሀብቶች፣ በጎ ፈቃደኞችና የልማት አጋሮቻችን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችን እናቀርባለን። በቀጣይም ይህንን የበጎነት ጉዞ በማጠናከር ለብዙዎች መጠለያና ተስፋ መሆናችንን እንቀጥላለን።
#ቤትግንባታ #በጎፈቃደኝነት #ለወገንደራሽ #የአካባቢልማት #ኢትዮጵያ
❤1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ባለፉት ስምንት ዓመታት በህፃናት ድጋፍና "አንድ ቤተሰብ ለአንድ ሰው" በተሰኙ ሰብዓዊ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ከ200 ሺህ በላይ ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ተጠቃሚ ሆነዋል።
ባለፉት ስምንት ዓመታት "በአንድ ቤተሰብ ለአንድ ሰው" የተሰኘው መርሃ ግብር ድጋፍ ፈላጊን ከደጋፊ ጋር በቀጥታ በማገናኘት አስተማማኝ የመረዳዳት ባህልና ዘላቂ ስርዓት መዘርጋት ተችሏል። በዚህ ሂደት ውስጥ ባለሀብቶች፣ በጎ አድራጊ ድርጅቶችና የሃይማኖት ተቋማት ተቀናጅተው መስራታቸው የድጋፍ ስራው በአንድ ወገን ላይ ብቻ እንዳይወድቅ ከማድረጉም በላይ፣ 199,426 አቅመ ደካሞችን ተጠቃሚ በማድረግ በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን የኑሮ ጫና መቀነስ አስችሏል።
ይህ ተግባር ከቁሳዊ ድጋፍ ባለፈ፣ በማህበረሰቡ መካከል ያለውን መተጋገዝና መተሳሰብ አጠናክሮ የዘለቀ ሲሆን ችግርን በብቸኝነት ሳይሆን በጋራ መጋፈጥ እንደሚቻል በተግባር የታየበት ታላቅ ስኬት ነው። ድጋፉ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ በማድረግ፤ አቅመ ደካሞች የነገ ተስፋቸው እንዲለመልም እና አስተማማኝ የኑሮ ዋስትና እንዲሰማቸው በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ነበረው። ይህም ማህበራዊ ትስስር ችግርን በጋራ የመወጣት ትልቅ አቅም መሆኑን በተግባር አሳይቷል።
በሌላ በኩል፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ለሆኑ ህጻናት ልዩ ትኩረት በመስጠት ወላጆቻቸውን ያጡና ለችግር ተጋላጭ የሆኑ 2,351 ህጻናትን መደገፍ ተችሏል። ይህ በጎ አገልግሎት ለሀገር ቀጣይነት የሚደረግ ትልቅ መዋዕለ ንዋይ ነው። እነዚህ ህጻናት የሚደረግላቸው ድጋፍ በችግር ምክንያት ለተለያዩ ጥቃቶች እንዳይጋለጡ ከማድረጉም በላይ፣ በትምህርትና በጤና ዘርፍ ተገቢውን እንክብካቤ አግኝተው ለቁም ነገር እንዲበቁ መሰረት ጥሏል። ይህ ተግባር የሰብአዊነት ስራዎች በዘመናዊና ስልታዊ በሆነ መንገድ ከተመሩ ምን ያህል ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ትልቅ ማሳያ ነው።
በአጠቃላይ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑት ተግባራት "አብሮነት ተደማሪ አቅም ነው" የሚለውን መርህ በመከተል የተገኙ ውጤቶች ናቸው። ይህንን ስኬታማ ተሞክሮ መሰረት በማድረግ፣ የተጀመሩ የትስስርና የድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል የማህበረሰባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ሰብአዊነትን በተግባር በመግለጽና ለተጎዱ ወገኖች ፈጥኖ በመድረስ የምናደርገው ጉዞ ሀገራዊ አንድነታችንን ይበልጥ የሚያጸና ይሆናል።
"ሰብዓዊነት ይለምልም!"
የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን
#ሰብአዊነት #ነጻህክምና #የህጻናትድጋፍ #ትስስር #አብሮነት #ኢትዮጵያዊነት
ባለፉት ስምንት ዓመታት "በአንድ ቤተሰብ ለአንድ ሰው" የተሰኘው መርሃ ግብር ድጋፍ ፈላጊን ከደጋፊ ጋር በቀጥታ በማገናኘት አስተማማኝ የመረዳዳት ባህልና ዘላቂ ስርዓት መዘርጋት ተችሏል። በዚህ ሂደት ውስጥ ባለሀብቶች፣ በጎ አድራጊ ድርጅቶችና የሃይማኖት ተቋማት ተቀናጅተው መስራታቸው የድጋፍ ስራው በአንድ ወገን ላይ ብቻ እንዳይወድቅ ከማድረጉም በላይ፣ 199,426 አቅመ ደካሞችን ተጠቃሚ በማድረግ በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን የኑሮ ጫና መቀነስ አስችሏል።
ይህ ተግባር ከቁሳዊ ድጋፍ ባለፈ፣ በማህበረሰቡ መካከል ያለውን መተጋገዝና መተሳሰብ አጠናክሮ የዘለቀ ሲሆን ችግርን በብቸኝነት ሳይሆን በጋራ መጋፈጥ እንደሚቻል በተግባር የታየበት ታላቅ ስኬት ነው። ድጋፉ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ በማድረግ፤ አቅመ ደካሞች የነገ ተስፋቸው እንዲለመልም እና አስተማማኝ የኑሮ ዋስትና እንዲሰማቸው በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ነበረው። ይህም ማህበራዊ ትስስር ችግርን በጋራ የመወጣት ትልቅ አቅም መሆኑን በተግባር አሳይቷል።
በሌላ በኩል፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ለሆኑ ህጻናት ልዩ ትኩረት በመስጠት ወላጆቻቸውን ያጡና ለችግር ተጋላጭ የሆኑ 2,351 ህጻናትን መደገፍ ተችሏል። ይህ በጎ አገልግሎት ለሀገር ቀጣይነት የሚደረግ ትልቅ መዋዕለ ንዋይ ነው። እነዚህ ህጻናት የሚደረግላቸው ድጋፍ በችግር ምክንያት ለተለያዩ ጥቃቶች እንዳይጋለጡ ከማድረጉም በላይ፣ በትምህርትና በጤና ዘርፍ ተገቢውን እንክብካቤ አግኝተው ለቁም ነገር እንዲበቁ መሰረት ጥሏል። ይህ ተግባር የሰብአዊነት ስራዎች በዘመናዊና ስልታዊ በሆነ መንገድ ከተመሩ ምን ያህል ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ትልቅ ማሳያ ነው።
በአጠቃላይ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑት ተግባራት "አብሮነት ተደማሪ አቅም ነው" የሚለውን መርህ በመከተል የተገኙ ውጤቶች ናቸው። ይህንን ስኬታማ ተሞክሮ መሰረት በማድረግ፣ የተጀመሩ የትስስርና የድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል የማህበረሰባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ሰብአዊነትን በተግባር በመግለጽና ለተጎዱ ወገኖች ፈጥኖ በመድረስ የምናደርገው ጉዞ ሀገራዊ አንድነታችንን ይበልጥ የሚያጸና ይሆናል።
"ሰብዓዊነት ይለምልም!"
የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን
#ሰብአዊነት #ነጻህክምና #የህጻናትድጋፍ #ትስስር #አብሮነት #ኢትዮጵያዊነት
❤1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ባለፉት ዓመታት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ከፍለው መታከም የማይችሉ የመዲናዋ ነዋሪዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት አግኝተዋል።
የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት የከተማዋ ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዋና መገለጫ ነው። ይህም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ከከፍተኛ የህክምና ወጪ በመታደግ ማህበራዊ ፍትህን የማረጋገጥ ስራ ነው። ባለፉት ስምንት ዓመታት 547,990 ዜጎች ከቅድመ ምርመራ እስከ ከፍተኛ ቀዶ ጥገና ድረስ ያለውን የህክምና አገልግሎት በነጻ እንዲያገኙ ተደርጓል። ይህ ሰብዓዊ ተግባር በገንዘብ ሲተመን ከ661.8 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን በጎ ፈቃደኝነት ለሀገር ኢኮኖሚና ለዜጎች ደህንነት ያለውን የማይተካ ሚና አመላካች ነው። አገልግሎቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የከተማዋ ነዋሪዎችን ህይወት በመታደግ ረገድም የከተማዋን የማህበራዊ ልማት ግቦች ስኬታማ አድርጎታል።
ከተማ አስተዳደሩ በሰው ተኮር ስትራቴጂው የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ለማህበረሰባዊ ደህንነት እንዲውል በማድረግ፣ ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። "በጎነት ለጤና!" የበጎ ፈቃድ ሰው ተኮር አገልግሎት ከከተማዋ የረጅም ጊዜ የማህበራዊ ልማት ግቦች ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው። ዓላማውም ማንኛውም ዜጋ በገንዘብ እጥረት ምክንያት ህይወቱ እንዳያልፍ ዋስትና መስጠት ነው።
ይህንን የተጀመረ ጥረት ይበልጥ በማጠናከር፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች እኩል ተጠቃሚ የሚያደርግና የዜጎችን ሰብአዊ ክብር የሚጠብቅ የጤና ስርዓት በመገንባት ሂደት ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሚና ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን
#ሰብአዊነት #ነጻህክምና #የህጻናትድጋፍ #ትስስር #አብሮነት #ኢትዮጵያዊነት
የጤና አገልግሎትን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት የከተማዋ ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዋና መገለጫ ነው። ይህም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ከከፍተኛ የህክምና ወጪ በመታደግ ማህበራዊ ፍትህን የማረጋገጥ ስራ ነው። ባለፉት ስምንት ዓመታት 547,990 ዜጎች ከቅድመ ምርመራ እስከ ከፍተኛ ቀዶ ጥገና ድረስ ያለውን የህክምና አገልግሎት በነጻ እንዲያገኙ ተደርጓል። ይህ ሰብዓዊ ተግባር በገንዘብ ሲተመን ከ661.8 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን በጎ ፈቃደኝነት ለሀገር ኢኮኖሚና ለዜጎች ደህንነት ያለውን የማይተካ ሚና አመላካች ነው። አገልግሎቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የከተማዋ ነዋሪዎችን ህይወት በመታደግ ረገድም የከተማዋን የማህበራዊ ልማት ግቦች ስኬታማ አድርጎታል።
ከተማ አስተዳደሩ በሰው ተኮር ስትራቴጂው የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ለማህበረሰባዊ ደህንነት እንዲውል በማድረግ፣ ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። "በጎነት ለጤና!" የበጎ ፈቃድ ሰው ተኮር አገልግሎት ከከተማዋ የረጅም ጊዜ የማህበራዊ ልማት ግቦች ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው። ዓላማውም ማንኛውም ዜጋ በገንዘብ እጥረት ምክንያት ህይወቱ እንዳያልፍ ዋስትና መስጠት ነው።
ይህንን የተጀመረ ጥረት ይበልጥ በማጠናከር፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች እኩል ተጠቃሚ የሚያደርግና የዜጎችን ሰብአዊ ክብር የሚጠብቅ የጤና ስርዓት በመገንባት ሂደት ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሚና ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን
#ሰብአዊነት #ነጻህክምና #የህጻናትድጋፍ #ትስስር #አብሮነት #ኢትዮጵያዊነት
በአዲስ አበባ ባለፉት ስምንት ዓመታት 369,220 ዩኒት ደም ተሰብስቧል።
ባለፉት ስምንት ዓመታት በአዲስ አበባ 369,220 ዩኒት ደም ከበጎ ፈቃደኛ ለጋሾች ተሰብስቧል። የከተማዋ ነዋሪዎች ለወገን ያላቸውን የማይናወጥ ፍቅርና ጥልቅ ሰብዓዊነት በተግባር ያረጋገጡበት ይህ በጎ አገልግሎት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖችን ከሞት አፋፍ ከመታደጉም በላይ በወሊድ ምክንያት የሚከሰትን የእናቶች ሞት ቀንሷል።
በሕክምና ሳይንስ አንድ ዩኒት ደም ለሦስት ዋና ዋና የደም ክፍሎች (ቀይ የደም ሴል፣ ፕላቴሌት እና ፕላዝማ) ተከፍሎ ጥቅም ላይ ስለሚውል አንድ ለጋሽ ብቻውን የሦስት ሰዎችን ሕይወት መታደግ የሚያስችል አቅም አለው። በዚህም ስሌት መሠረት በአዲስ አበባ ባለፉት ስምንት ዓመታት የተሰበሰበው 369,220 ዩኒት ደም ከአንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎችን ሕይወት ከሞት ታድጓል። ይህ አኃዝ በድንገተኛ አደጋ፣ በወሊድና በሌሎች ህመሞች ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የተደረገ ታላቅ የሰብዓዊነት ስጦታ ነው።
ደም መስጠት በምንም ዓይነት ቁሳቁስ የማይተካ፣ በገንዘብ የማይለካ፣ የሕይወት ገፀ በረከት፣ ምትክ የሌለውን የሰው ልጅ ህይወት በራስ ህይወት የመታደግ አገልግሎት ነው። ደም መለገስ ከምንም በላይ የላቀና ንጹህ የፍቅር ስጦታ፣ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የሰብዓዊነት ትልቁ መገለጫ ምግባር ነው።
#ደምልገሳ #ህይወትንመታደግ #በጎፈቃደኝነት #ሰብአዊነት #ኢትዮጵያ
ባለፉት ስምንት ዓመታት በአዲስ አበባ 369,220 ዩኒት ደም ከበጎ ፈቃደኛ ለጋሾች ተሰብስቧል። የከተማዋ ነዋሪዎች ለወገን ያላቸውን የማይናወጥ ፍቅርና ጥልቅ ሰብዓዊነት በተግባር ያረጋገጡበት ይህ በጎ አገልግሎት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖችን ከሞት አፋፍ ከመታደጉም በላይ በወሊድ ምክንያት የሚከሰትን የእናቶች ሞት ቀንሷል።
በሕክምና ሳይንስ አንድ ዩኒት ደም ለሦስት ዋና ዋና የደም ክፍሎች (ቀይ የደም ሴል፣ ፕላቴሌት እና ፕላዝማ) ተከፍሎ ጥቅም ላይ ስለሚውል አንድ ለጋሽ ብቻውን የሦስት ሰዎችን ሕይወት መታደግ የሚያስችል አቅም አለው። በዚህም ስሌት መሠረት በአዲስ አበባ ባለፉት ስምንት ዓመታት የተሰበሰበው 369,220 ዩኒት ደም ከአንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎችን ሕይወት ከሞት ታድጓል። ይህ አኃዝ በድንገተኛ አደጋ፣ በወሊድና በሌሎች ህመሞች ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የተደረገ ታላቅ የሰብዓዊነት ስጦታ ነው።
ደም መስጠት በምንም ዓይነት ቁሳቁስ የማይተካ፣ በገንዘብ የማይለካ፣ የሕይወት ገፀ በረከት፣ ምትክ የሌለውን የሰው ልጅ ህይወት በራስ ህይወት የመታደግ አገልግሎት ነው። ደም መለገስ ከምንም በላይ የላቀና ንጹህ የፍቅር ስጦታ፣ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የሰብዓዊነት ትልቁ መገለጫ ምግባር ነው።
#ደምልገሳ #ህይወትንመታደግ #በጎፈቃደኝነት #ሰብአዊነት #ኢትዮጵያ
❤2👍1