የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት ያነሷቸው ሃሳቦች:-
- ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን እውን ለማድረግ በታቀደው መሰረት ለወጣቶች እና ለሴቶች ሰፋፊ የሆኑ የስራ ዕድሎች መፈጠራቸውን አንስተዋል።
- በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድም ተስፋ ሰጪ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸውን ነገር ግን ልክ በኮሪደር ልማት፣ መልሶ ማልማት እና በወንዞች ዳርቻዎች ልማት አመርቂ ውጤቶች እንደተመዘገቡ ሁሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይም መሰረታዊ ለውጦችን ለማምጣት የከተማ አስተዳደሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባው በአስተያየት እና ጥያቄ መልክም ተነስቷል።
- የሰው ተኮር ስራዎች በተለይም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ውስጥ ያሉ ዜጎች ከተማ አስተዳደሩ ከሚያመነጨው ኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስቻለ ከመሆኑም በላይ ህዝቡም ተገቢውን እውቅና እየሰጠ ይገኛል።
- የውሀ ስርጭት በስታንዳርድ እንዲሆን እየተሰራ ቢሆንም ፍትሀዊ ስርጭት እንዲኖር አሁንም ትኩረት እንዲሰጠው የህዝቡ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።
- ከመብራት ጋር ተያይዞ በተለይም መኃል ከተማ በሚገኙ ክፍለ ከተሞች ያረጁ እና ሊወድቁ የደረሱ ፖሎች በነዋሪዎች ዘንድ ስጋት የደቀኑ በመሆናቸው አስቸኳይ እልባት ያስፈልጋል።
- ከኑሮ ውድነት አንፃር የሰብል ምርቶች የዋጋ መረጋጋት ያሳየ መሆኑን ሆኖም የዘይት ዋጋን ጨምሮ በሌሎች ምርቶች ዙሪያ ዘላቂ እልባት እንዲሰጥ::
- የእሁድ ገበያዎች፣ የተማሪዎች ምገባ ፣ የትራንስፖርት አቅርቦት፣ በጤና መድህን እንዲሁም ዓለም አቀፍ አንድምታ ያለው የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የሚከናወኑ ሰው ተኮር ተግባራት አበረታች ውጤቶችን በማስመዝገብ ላይ ይገኛሉ።
- ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን እውን ለማድረግ በታቀደው መሰረት ለወጣቶች እና ለሴቶች ሰፋፊ የሆኑ የስራ ዕድሎች መፈጠራቸውን አንስተዋል።
- በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድም ተስፋ ሰጪ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸውን ነገር ግን ልክ በኮሪደር ልማት፣ መልሶ ማልማት እና በወንዞች ዳርቻዎች ልማት አመርቂ ውጤቶች እንደተመዘገቡ ሁሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይም መሰረታዊ ለውጦችን ለማምጣት የከተማ አስተዳደሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባው በአስተያየት እና ጥያቄ መልክም ተነስቷል።
- የሰው ተኮር ስራዎች በተለይም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ውስጥ ያሉ ዜጎች ከተማ አስተዳደሩ ከሚያመነጨው ኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስቻለ ከመሆኑም በላይ ህዝቡም ተገቢውን እውቅና እየሰጠ ይገኛል።
- የውሀ ስርጭት በስታንዳርድ እንዲሆን እየተሰራ ቢሆንም ፍትሀዊ ስርጭት እንዲኖር አሁንም ትኩረት እንዲሰጠው የህዝቡ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።
- ከመብራት ጋር ተያይዞ በተለይም መኃል ከተማ በሚገኙ ክፍለ ከተሞች ያረጁ እና ሊወድቁ የደረሱ ፖሎች በነዋሪዎች ዘንድ ስጋት የደቀኑ በመሆናቸው አስቸኳይ እልባት ያስፈልጋል።
- ከኑሮ ውድነት አንፃር የሰብል ምርቶች የዋጋ መረጋጋት ያሳየ መሆኑን ሆኖም የዘይት ዋጋን ጨምሮ በሌሎች ምርቶች ዙሪያ ዘላቂ እልባት እንዲሰጥ::
- የእሁድ ገበያዎች፣ የተማሪዎች ምገባ ፣ የትራንስፖርት አቅርቦት፣ በጤና መድህን እንዲሁም ዓለም አቀፍ አንድምታ ያለው የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የሚከናወኑ ሰው ተኮር ተግባራት አበረታች ውጤቶችን በማስመዝገብ ላይ ይገኛሉ።
👍1
ኢ/ር ወንድሙ ሲታ በም/ከንቲባ ማአረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ
👉የከተማዋን የፍሳሽ ማስጋጃ ስርዓት የማዘመንና በአዲስ መልከ የመገንባት ስራ በስፋት እየተከነወነ ይገኛል፡፡
👉የአደጋ ስጋት ተጋላጭነትን ለመቀነስ በልዩ በትኩረት አካባቢዎችን በመለየት እየሰራ ነው፡፡
👉የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት ላይ ያመጣነው ለውጥና ያስገኘነው ውጤት በከተማችን ገፅታ ላይ ግልፅ ለውጥ እያመጣ ነው::
👉ቆሻሻን ወደ ኢነርጂ ከመቀየር አንፃር አሁንም የሚቀሩን ስራዎች አሉ፤ የከተማዋን ፅዳት አረጋግጠን ቆሻሻን ወደ ኢነርጂ መቀየር ላይ በትኩረት መስራት ይኖርብናል።
👉ከውሃ ፍትሃዊ ስርጭት አንፃር 377,000 ሜ.ኪዩብ ውሃ የማምረት አቅም በማጎልበት ተደራሽነታችንን ለማሰደግ የተሰራ ሲሆን በቀጣይ 100,000 ሜ.ኪዩብ ተጨማሪ የውሃ አቅርቦት አቅም ለመፍጠር በትኩረት እየሰራን ነው::
👉የመብራት መቆራረጥ ችግር መንስኤዎች በነባር መንደሮች ያለውን አሮጌ መሰረተ ልማት ጋር የተገናኘ በመሆኑ በቀጣይ የመብራት ሃይል አቅርቦት መሰረተ ልማትን በአዲስ መልክ ለመገንባት በማስተርፕላኑ ውስጥ ማስገባት በዘላቂነት ለመፍታት ያግዘናል ፡፡
👉የኮሪደር ልማት ሰራችን ይህንን የመሰረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ እየተሰራ ይገኛል፡፡
👉የከተማዋን የፍሳሽ ማስጋጃ ስርዓት የማዘመንና በአዲስ መልከ የመገንባት ስራ በስፋት እየተከነወነ ይገኛል፡፡
👉የአደጋ ስጋት ተጋላጭነትን ለመቀነስ በልዩ በትኩረት አካባቢዎችን በመለየት እየሰራ ነው፡፡
👉የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት ላይ ያመጣነው ለውጥና ያስገኘነው ውጤት በከተማችን ገፅታ ላይ ግልፅ ለውጥ እያመጣ ነው::
👉ቆሻሻን ወደ ኢነርጂ ከመቀየር አንፃር አሁንም የሚቀሩን ስራዎች አሉ፤ የከተማዋን ፅዳት አረጋግጠን ቆሻሻን ወደ ኢነርጂ መቀየር ላይ በትኩረት መስራት ይኖርብናል።
👉ከውሃ ፍትሃዊ ስርጭት አንፃር 377,000 ሜ.ኪዩብ ውሃ የማምረት አቅም በማጎልበት ተደራሽነታችንን ለማሰደግ የተሰራ ሲሆን በቀጣይ 100,000 ሜ.ኪዩብ ተጨማሪ የውሃ አቅርቦት አቅም ለመፍጠር በትኩረት እየሰራን ነው::
👉የመብራት መቆራረጥ ችግር መንስኤዎች በነባር መንደሮች ያለውን አሮጌ መሰረተ ልማት ጋር የተገናኘ በመሆኑ በቀጣይ የመብራት ሃይል አቅርቦት መሰረተ ልማትን በአዲስ መልክ ለመገንባት በማስተርፕላኑ ውስጥ ማስገባት በዘላቂነት ለመፍታት ያግዘናል ፡፡
👉የኮሪደር ልማት ሰራችን ይህንን የመሰረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ እየተሰራ ይገኛል፡፡
👍1
ማህበራዊ ችግር ያለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ከተረጂነት ባለፈ በቂ ስልጠና በመስጠት መስራት የሚችሉትን የማሸጋገር ስራ ሰርተናል።ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የኑሮ ውድነትና ጫናን ለማቃለል አለሜቀፋዊ ሁኔታን አገናዝበን ምላሽ ለመስጠት ሞክረናል።
* ኑሮ ውድነትን ለመቅረፍ አቅርቦትን ማሳደግ ላይ በትኩረት በመስራት በአምስቱም የከተማችን መግቢያ በሮች የግብርና ምርቶችን አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግና የደላሎችን ሰንሰለት መበጣጠስ ችለናል።
* የኑሮ ውድነት ችግርን ማቃለል የምንችልበት መንገድ አምራችነትን በማሳደግ እንደመሆኑ መጠን የከተማችን ነዋሪ በተለያዩ አግባባች አምራችነቱ እንዲያድግ ስልጠና የመስጠትና የግብአት አቅርቦት እገዛ እያደረግን ነው።
* የገበያ ማረጋጋት ስራን በተመለከተ በቁጥጥር፣ በክትትልና፣ በድጎማ ህቦረተሰባችንን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰራን ነው።ውጤትም አግኝተንበታል።
* ለማህበራዊ ችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችና የእናቶችን የኑሮ ጫና ለማቃለል የሰራነው ስራ ሁሌም የምንኮራበት ነው።
* 26 የምገባ ማዕከላን በመክፈት ዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመመገብ ፍትሀዊ ተጠቃሚነታቸዉን ከማረጋገጥ ባሻገር ዜጎች አብሮ የማደግ ባህል እንዲጎለብት አድርገናል።
የኑሮ ውድነትና ጫናን ለማቃለል አለሜቀፋዊ ሁኔታን አገናዝበን ምላሽ ለመስጠት ሞክረናል።
* ኑሮ ውድነትን ለመቅረፍ አቅርቦትን ማሳደግ ላይ በትኩረት በመስራት በአምስቱም የከተማችን መግቢያ በሮች የግብርና ምርቶችን አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግና የደላሎችን ሰንሰለት መበጣጠስ ችለናል።
* የኑሮ ውድነት ችግርን ማቃለል የምንችልበት መንገድ አምራችነትን በማሳደግ እንደመሆኑ መጠን የከተማችን ነዋሪ በተለያዩ አግባባች አምራችነቱ እንዲያድግ ስልጠና የመስጠትና የግብአት አቅርቦት እገዛ እያደረግን ነው።
* የገበያ ማረጋጋት ስራን በተመለከተ በቁጥጥር፣ በክትትልና፣ በድጎማ ህቦረተሰባችንን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰራን ነው።ውጤትም አግኝተንበታል።
* ለማህበራዊ ችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችና የእናቶችን የኑሮ ጫና ለማቃለል የሰራነው ስራ ሁሌም የምንኮራበት ነው።
* 26 የምገባ ማዕከላን በመክፈት ዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመመገብ ፍትሀዊ ተጠቃሚነታቸዉን ከማረጋገጥ ባሻገር ዜጎች አብሮ የማደግ ባህል እንዲጎለብት አድርገናል።
👍2
የኮሪደር ልማቱ ዙሪያ
👉በኮሪደር ልማት የመጣው ለውጥ "አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ እናደርጋታለን" ብለን ለህዝባችን ከገባነው ቃል የመነጨ ነው። ለአብነት የኮሪደር ስራችን ከመጀመራችን በፊት ባደረግነው ጥናት የአዲስ አበባ የመንገድ መሰረተ ልማት እና የአረንጓዴ ሽፋን እጅጎ ከፍ እንዲል ያስቻለን ሲሆን ይህም ለከተማችን ነዋሪዎች አጠቃላይ ጤና ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑን ሁሉም የሚገነዘበው ጉዳይ ነው።
👉በኮሪደር ልማት መኪና መንገድ ብቻ ሳይሆን 80% በላይ ተሽከርካሪ የሌለውን የከተማችን ነዋሪዎች በቀላሉ ሊጠቀሙበት የሚችሉትን የእግረኛ መንገዶችን አስፋፍተናል የሳይክል መንገዶችንም ማስፋፋት በመጀመራችን ህዝቡ ተጠቃሚ ሆኗል።
👉 በኮሪደር ልማትና መልሶ ማልማት ስራ የታየው ወሳኘ ጉዳይ የህዝባችን ያላሰለሰ ድጋፍና ትብብር የተረጋገጠበት መሆኑ ነው። በዚህ ስራ ውስጥ ወጣቶች እና ሴቶች በጉልበታቸው አግዘዋል፤ ባለሀብቶች ገንዘባቸውን አፍስሰዋል፤ የልማት ተነሺዎች አስደናቂ ትብብር አድርገዋል።
👉ኮሪደር ልማቱ የከተማችንን ገፅታ መቀየሩ እና ለህዝባችን ምቹ መኖሪያ እንድትሆን ከማድረጉ ጎንለጎን ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ፈጥሯል።
👉 የከተማችን ነዋሪዎች ልማቱ ወደ ሁሉም የከተማችን አካባቢዎች እንዲመጣ መጠየቃቸው አግባብነት ያለው ጥያቄ ቢሆንም ስራው ሰፊ ሀብት እና ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በጥናት እና በቅደም ተከተል ወደ ሁሉም የከተማችን ክፍሎች በመምጣት የምናለማ ይሆናል::
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👉በኮሪደር ልማት የመጣው ለውጥ "አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ እናደርጋታለን" ብለን ለህዝባችን ከገባነው ቃል የመነጨ ነው። ለአብነት የኮሪደር ስራችን ከመጀመራችን በፊት ባደረግነው ጥናት የአዲስ አበባ የመንገድ መሰረተ ልማት እና የአረንጓዴ ሽፋን እጅጎ ከፍ እንዲል ያስቻለን ሲሆን ይህም ለከተማችን ነዋሪዎች አጠቃላይ ጤና ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑን ሁሉም የሚገነዘበው ጉዳይ ነው።
👉በኮሪደር ልማት መኪና መንገድ ብቻ ሳይሆን 80% በላይ ተሽከርካሪ የሌለውን የከተማችን ነዋሪዎች በቀላሉ ሊጠቀሙበት የሚችሉትን የእግረኛ መንገዶችን አስፋፍተናል የሳይክል መንገዶችንም ማስፋፋት በመጀመራችን ህዝቡ ተጠቃሚ ሆኗል።
👉 በኮሪደር ልማትና መልሶ ማልማት ስራ የታየው ወሳኘ ጉዳይ የህዝባችን ያላሰለሰ ድጋፍና ትብብር የተረጋገጠበት መሆኑ ነው። በዚህ ስራ ውስጥ ወጣቶች እና ሴቶች በጉልበታቸው አግዘዋል፤ ባለሀብቶች ገንዘባቸውን አፍስሰዋል፤ የልማት ተነሺዎች አስደናቂ ትብብር አድርገዋል።
👉ኮሪደር ልማቱ የከተማችንን ገፅታ መቀየሩ እና ለህዝባችን ምቹ መኖሪያ እንድትሆን ከማድረጉ ጎንለጎን ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ፈጥሯል።
👉 የከተማችን ነዋሪዎች ልማቱ ወደ ሁሉም የከተማችን አካባቢዎች እንዲመጣ መጠየቃቸው አግባብነት ያለው ጥያቄ ቢሆንም ስራው ሰፊ ሀብት እና ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በጥናት እና በቅደም ተከተል ወደ ሁሉም የከተማችን ክፍሎች በመምጣት የምናለማ ይሆናል::
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍2
የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት ባካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጨማሪ በጀት አፀደቀ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ለ2017 ዓ.ም የሚውል ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት አፅድቋል፡፡
ተጨማሪ በጀቱ በከተማዋ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ልማቶችን ለማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑ በምክር ቤቱ ተገልጿል፡፡
#followerseveryone
#viralreelschallenge
#highlighteveryone
#አዲስ_አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ለ2017 ዓ.ም የሚውል ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት አፅድቋል፡፡
ተጨማሪ በጀቱ በከተማዋ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ልማቶችን ለማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑ በምክር ቤቱ ተገልጿል፡፡
#followerseveryone
#viralreelschallenge
#highlighteveryone
#አዲስ_አበባ
👍1
አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ
.አገልግሎትን ከማዘመን አንፃር ኮሪደር ልማቱ የፈጠረልንን ቴክኖሎጂ የማዘመን እድል በአግባቡ በመጠቀም 347 በቴክኖሎጂ የታገዙ አገልግሎቶችን ማዘመን ችለናል።
• የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለማዘመን በትኩረት መስራት ይኖርብናል።
• የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ በመንግሥት ተቋማት ካደረግነው ውጤታማ ሪፎርም ጎን ለጎን በብልሹ አሰራር ላይ የተሳተፉ 1726 ሠራተኞችና ከ90 በላይ አመራሮች ላይ እርምጃ በመውሰድ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን መታገል በልዩ ትኩረት እየሰራን ነው።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
.አገልግሎትን ከማዘመን አንፃር ኮሪደር ልማቱ የፈጠረልንን ቴክኖሎጂ የማዘመን እድል በአግባቡ በመጠቀም 347 በቴክኖሎጂ የታገዙ አገልግሎቶችን ማዘመን ችለናል።
• የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለማዘመን በትኩረት መስራት ይኖርብናል።
• የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ በመንግሥት ተቋማት ካደረግነው ውጤታማ ሪፎርም ጎን ለጎን በብልሹ አሰራር ላይ የተሳተፉ 1726 ሠራተኞችና ከ90 በላይ አመራሮች ላይ እርምጃ በመውሰድ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን መታገል በልዩ ትኩረት እየሰራን ነው።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍1
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤው ለ2017 ዓ.ም ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት እና ልዩ ልዩ ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቅቋል:: በዚህም መሰረት:-
1. ወ/ሮ ቆንጆት ደበላ ዎላ - የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ሕጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ(በሽግሽግ)
2. አቶ አወሌህ መሐመድ ኦመር - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
3. ወ/ሮ አይሻ መሐመድ አደን - የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር
4. ኢ/ር ሕይወት ሣሙኤል ጸጋዬ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር
5. ሲ/ር ሶፊያ አለሙ - የሴቶች፣ የወጣቶችና ህፃናት ቋሚ ኮሚቴ ሆነው ተሹመዋል::
በሌላ በኩል ተጨማሪ በጀቱ በከተማዋ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ልማቶችን ለማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑንም ምክር ቤቱ ተወያይቶ በሙሉ ድፅ አፅድቋል፡፡
1. ወ/ሮ ቆንጆት ደበላ ዎላ - የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ሕጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ(በሽግሽግ)
2. አቶ አወሌህ መሐመድ ኦመር - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
3. ወ/ሮ አይሻ መሐመድ አደን - የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር
4. ኢ/ር ሕይወት ሣሙኤል ጸጋዬ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር
5. ሲ/ር ሶፊያ አለሙ - የሴቶች፣ የወጣቶችና ህፃናት ቋሚ ኮሚቴ ሆነው ተሹመዋል::
በሌላ በኩል ተጨማሪ በጀቱ በከተማዋ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ልማቶችን ለማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑንም ምክር ቤቱ ተወያይቶ በሙሉ ድፅ አፅድቋል፡፡
ኑሮ ውድነት ከሰብል ምርት ጋር እጥረት እንዳይገጥም ህብረት ስራ ማህበራትን ያላቸውን ካፒታል የሰብል ምርቶችን በመግዛት ስቶክ እንዲኖራቸው ተደርገዋል:: ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ
• 216 የእሁድ ገበያዎች በአይነትና በጥራት ምርቶቻቸዉን በወጣላቸው ስታንዳርድ መሰረት እንደቀርቡ የማድረግ ስራን በከተማዋ የተቋቋመው የግብረ ሃይል አደረጃጀት ቁጥጥር እያደረገ እና ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
• ኮሪደር ልማቱን በተመለከተ ዘለቄታዊነት ያላቸውን የከተማውን እድገት ሊያፋጥኑ የሚችሉ ሁሉን አቀፍ ስራዎችን ለመስራት አስተዳደሩ ያለውን ምቹ ሁኔታ በማየት የቀጣይ ስራዎችን ጨምሮ በቅድመ ዝግጀት ስራዎች የሚሰሩትን በትኩረት አቅደን እና ዲዛይን አድርገን ተወያይተን በቀጣይ የበለጠ የሚሰራ ይሆናል፡:
• የአዲስ አበባ ከተማ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የከተማ አስተዳደሩ የፐብሊክ ትራንስፖርት፤የቤት አቅርቦት፣የስራ እድል ፈጠራ ፣የትምህርት ቤት ምገባ እና ምገባ ማዕከላት ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ በጀት በመደብ እየሰራ ይገኛል::
ከዚህም በተጨማሪ በከተማችን የሚገኙ 4 የገበያ ማዕከላት በቂ ምርት እንዲኖራቸው የማድረግ ስራ እተሰራ ሲሆን እነዚህም ስራዎች የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸዉ መሆኑን ልንገነዘብ ይገባል::
• 216 የእሁድ ገበያዎች በአይነትና በጥራት ምርቶቻቸዉን በወጣላቸው ስታንዳርድ መሰረት እንደቀርቡ የማድረግ ስራን በከተማዋ የተቋቋመው የግብረ ሃይል አደረጃጀት ቁጥጥር እያደረገ እና ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
• ኮሪደር ልማቱን በተመለከተ ዘለቄታዊነት ያላቸውን የከተማውን እድገት ሊያፋጥኑ የሚችሉ ሁሉን አቀፍ ስራዎችን ለመስራት አስተዳደሩ ያለውን ምቹ ሁኔታ በማየት የቀጣይ ስራዎችን ጨምሮ በቅድመ ዝግጀት ስራዎች የሚሰሩትን በትኩረት አቅደን እና ዲዛይን አድርገን ተወያይተን በቀጣይ የበለጠ የሚሰራ ይሆናል፡:
• የአዲስ አበባ ከተማ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የከተማ አስተዳደሩ የፐብሊክ ትራንስፖርት፤የቤት አቅርቦት፣የስራ እድል ፈጠራ ፣የትምህርት ቤት ምገባ እና ምገባ ማዕከላት ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ በጀት በመደብ እየሰራ ይገኛል::
ከዚህም በተጨማሪ በከተማችን የሚገኙ 4 የገበያ ማዕከላት በቂ ምርት እንዲኖራቸው የማድረግ ስራ እተሰራ ሲሆን እነዚህም ስራዎች የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸዉ መሆኑን ልንገነዘብ ይገባል::
👍5
የበጎ ፈቃድ ማኅበራት ጥምረት በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና ማኅበራዊ ኃላፊነት ደንብ ዙሪያ ምክክር አካሄደ።
በአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን የቋቋመው የበጎ ፈቃድ ማኅበራት ጥምረት ከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጀው የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና ማኅበራዊ ኃላፊነት ደንብ ቁጥር 161/2017 ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።
ውይይቱ የጥምረቱ አባል ማኅበራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተቋማዊ ቅርፅ እንዲይዝና ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖው እንዲታወቅ፣ የመረዳዳትና የመተሳሰብ እሴት እንዲዳብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላወጣው ደንብ ተግባራዊነት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማድረግ እንደሚያግዝ በመድረኩ ተመላክቷል።
በሌላ በኩል ጥምረቱ በበጀት ዓመቱ ያለፉ ወራት ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት አፈፃጸም ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የጥምረቱን አባል ማህበራት የእርስ በርስ ግንኙነት በማጠናከረ የነዋሪዎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን መፍታት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የበጎ ፈቃድ ማኅበራት ከአንድ ዓመት በፊት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውንና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡበት እንዲሁም እርስ በርስ ተሞክሯቸውን የሚለዋወጡበት ጥምረት መመስረታቸው ይታወሳል።
"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
ሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
በአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን የቋቋመው የበጎ ፈቃድ ማኅበራት ጥምረት ከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጀው የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና ማኅበራዊ ኃላፊነት ደንብ ቁጥር 161/2017 ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።
ውይይቱ የጥምረቱ አባል ማኅበራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተቋማዊ ቅርፅ እንዲይዝና ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖው እንዲታወቅ፣ የመረዳዳትና የመተሳሰብ እሴት እንዲዳብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላወጣው ደንብ ተግባራዊነት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማድረግ እንደሚያግዝ በመድረኩ ተመላክቷል።
በሌላ በኩል ጥምረቱ በበጀት ዓመቱ ያለፉ ወራት ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት አፈፃጸም ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የጥምረቱን አባል ማህበራት የእርስ በርስ ግንኙነት በማጠናከረ የነዋሪዎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን መፍታት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የበጎ ፈቃድ ማኅበራት ከአንድ ዓመት በፊት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውንና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡበት እንዲሁም እርስ በርስ ተሞክሯቸውን የሚለዋወጡበት ጥምረት መመስረታቸው ይታወሳል።
"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
ሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
የ2017/18 በጀት ዓመት የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮግራሞች ውጤታማ ለማድረግ በጎ ፈቃደኞችን ለአገልግሎት የማብቃት ስራ እየተከናወነ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን የ2017/18 በጀት ዓመት የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮግራሞች ለማሳካት በጎ ፈቃደኞችን ለአገልግሎት ብቁ የማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ ይገኛል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በራስ ተነሳሽነት ጊዜን፣ ጉልበትንና ገንዘብን ለማህበረሰብ ሁለንተናዊ ለውጥ በነፃ የማዋል ተግባር ሲሆን ይህንን ዓለም አቀፍና ወሰን የሌለው አገልግሎት በጥሩ ስብዕናና በመልካም ሥነ-ምግባር መተግበር ይገባል።
በከተማ ደረጃ አንድ ሺህ በጎ ፈቃደኞች በበጎ ፈቃድ ጽንሰ ሀሳብና በአገልግሎት ሥነ-ምግባር ዙሪያ በተለያዩ ዙሮች ስልጠና የወሰዱ ሲሆን ለመጭው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እስከ ወረዳ ድረስ ከ11 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የሥነ-ምግባር ስልጠና ይወስዳሉ።
የ2017/18 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የከተማዋን ነዋሪዎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ እየተዘጋጀ ሲሆን ከግንቦት 30 በፊት በተለያዩ ፕሮግራሞችና መርሀ ግብሮች ይፋ ይደረጋል።
"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
ሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን የ2017/18 በጀት ዓመት የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮግራሞች ለማሳካት በጎ ፈቃደኞችን ለአገልግሎት ብቁ የማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ ይገኛል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በራስ ተነሳሽነት ጊዜን፣ ጉልበትንና ገንዘብን ለማህበረሰብ ሁለንተናዊ ለውጥ በነፃ የማዋል ተግባር ሲሆን ይህንን ዓለም አቀፍና ወሰን የሌለው አገልግሎት በጥሩ ስብዕናና በመልካም ሥነ-ምግባር መተግበር ይገባል።
በከተማ ደረጃ አንድ ሺህ በጎ ፈቃደኞች በበጎ ፈቃድ ጽንሰ ሀሳብና በአገልግሎት ሥነ-ምግባር ዙሪያ በተለያዩ ዙሮች ስልጠና የወሰዱ ሲሆን ለመጭው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እስከ ወረዳ ድረስ ከ11 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የሥነ-ምግባር ስልጠና ይወስዳሉ።
የ2017/18 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የከተማዋን ነዋሪዎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ እየተዘጋጀ ሲሆን ከግንቦት 30 በፊት በተለያዩ ፕሮግራሞችና መርሀ ግብሮች ይፋ ይደረጋል።
"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
ሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
👍3
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የሰው ተኮር ስራዎች መሰራታቸዉን እና እየተሰሩ መሆናቸዉን ከኢቲቪ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ገልፀዋል፡፡
ከንቲባዋ እንደገለፁት ምንም ገቢ የሌላቸዉ የከተማችን ነዋሪዎች በቀን 1 ጊዜ እንኳን መመገብ የሚቸገሩ የከተማችን ነዋሪዎች አሁን 36 ሺ የሚሆኑ ወገኖቻችን ትኩስ እና ንፁህ ምግብ በቀን 1 ጊዜ መመገብ የቻሉበት እና በዚህም ምግብ ብቻ ሳይሆን ክብርም፤ፍቅርም ያገኙበት ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል::
በተጨማሪም ትዉልድ ላይ ትኩረት በማድረግ በተማሪዎች ምገባ በየትቤ/ቱ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች በቀን 2 ጊዜ እንዲመገቡ ማድረግ የተቻለበትና የትምህርት ቁሳቁስ ግብዓት በሟሟላት የወላጆችን ጫናን ለማቃለል መንግስት ሃላፊነት ወስዶ እየሰራበት መሆኑንም አብራርተዋል፡፤
ከንቲባዋ አክለዉም በሰዉ ተኮር ስራወች ሰፋፊ እና በሚሊዮን የሚቆጠር የስራ እድል መፍጠር የተቻለበት እና በመሰረታዊነት የሰዉ ህይወት የተቀየረበት መሆኑን ገልፀዉ በሴፍቲኔት ብቻ ወደ 100ሺ የሚሆኑ የከተማችን ነዋሪዎች ባለፉት ዓመታት ወደ ተሻለ ህይወት በተጨባጭ ማሻገር የተቻለበት ነዉ ብለዋል፡፡
#viralreelschallenge
#followerseveryone
#addisababa
#Ethiopia
#etv@CommunityPVC
ከንቲባዋ እንደገለፁት ምንም ገቢ የሌላቸዉ የከተማችን ነዋሪዎች በቀን 1 ጊዜ እንኳን መመገብ የሚቸገሩ የከተማችን ነዋሪዎች አሁን 36 ሺ የሚሆኑ ወገኖቻችን ትኩስ እና ንፁህ ምግብ በቀን 1 ጊዜ መመገብ የቻሉበት እና በዚህም ምግብ ብቻ ሳይሆን ክብርም፤ፍቅርም ያገኙበት ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል::
በተጨማሪም ትዉልድ ላይ ትኩረት በማድረግ በተማሪዎች ምገባ በየትቤ/ቱ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች በቀን 2 ጊዜ እንዲመገቡ ማድረግ የተቻለበትና የትምህርት ቁሳቁስ ግብዓት በሟሟላት የወላጆችን ጫናን ለማቃለል መንግስት ሃላፊነት ወስዶ እየሰራበት መሆኑንም አብራርተዋል፡፤
ከንቲባዋ አክለዉም በሰዉ ተኮር ስራወች ሰፋፊ እና በሚሊዮን የሚቆጠር የስራ እድል መፍጠር የተቻለበት እና በመሰረታዊነት የሰዉ ህይወት የተቀየረበት መሆኑን ገልፀዉ በሴፍቲኔት ብቻ ወደ 100ሺ የሚሆኑ የከተማችን ነዋሪዎች ባለፉት ዓመታት ወደ ተሻለ ህይወት በተጨባጭ ማሻገር የተቻለበት ነዉ ብለዋል፡፡
#viralreelschallenge
#followerseveryone
#addisababa
#Ethiopia
#etv@CommunityPVC