#ወርቃማው_ሰኞ
ጅማሬያችን ለመጨረሻችን መነሻ ነው። በመልካም መጀመር በመልካም ለማጠናቀቅ ወሳኝ ነው። የስራ መጀመሪያችን ወርቃማዋን ሰኞ የስራ መነሳሳትን በሚፈጥር መልኩ በ"ቅንነት!" መጀመር ተገቢ ነው።
በዛሬው ወርቃማ ሰኞ "ቅንነት" ለስኬታማነት ያለውን ሚና የሚያስረዳ ማብራሪያ የሰጡት የበጎ ፈቃድ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ደረጀ ካሳ ናቸው። በረዥም ጊዜ የስራ ልምዳቸው አብረዋቸው የሰሩ ቀና ሰዎች ከፍ ከፍ ብለው ስኬታማ መሆናቸውን ገልፀዋል አቶ ደረጀ።
ቀና ያልሆኑ ሰዎች መጨረሻቸው አያምርም ፤ ስኬት አያመጡም ፤ ለውጥ አልባ ናቸው። ቀና ሰዎች ደግሞ በተቃራኒው የጀመሩትን በስኬት ይጨርሳሉ ፤ ከነበሩበት ኃላፊነት ወደላቀ ደረጃ ያድጋሉ። በአጠቃላይ ለውጥ ለማምጣትና ስኬት ላይ ለመድረስ በቅንነት ማገልገል ያስፈልጋል።
በህዝብ አገልግሎት ከ12ቱ የስነ ምግባር መርሆዎች መካከል ቅንነት አንዱ ነው። እንደ መርህ በየመሥሪያ ቤታችን ግድግዳ ላይ ያስቀመጥነው "ቅንነት" ልንገዛበትና ልንተገብረው የሚገባ ህግ ነው። ህዝብን በቅንነት ማገልገል ደግሞ የምናልማትን ታላቅ ሃገር ለመገንባት ያግዛል። የኮሚሽናችን ባለሙያዎች "ቅንነትን" የሥራቸው መሰረት ፣ የሕይወታቸው ህግ በማድረግ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ቅንነት - ለላቀ ውጤት!
መልካም የስራ ሳምንት!
ጅማሬያችን ለመጨረሻችን መነሻ ነው። በመልካም መጀመር በመልካም ለማጠናቀቅ ወሳኝ ነው። የስራ መጀመሪያችን ወርቃማዋን ሰኞ የስራ መነሳሳትን በሚፈጥር መልኩ በ"ቅንነት!" መጀመር ተገቢ ነው።
በዛሬው ወርቃማ ሰኞ "ቅንነት" ለስኬታማነት ያለውን ሚና የሚያስረዳ ማብራሪያ የሰጡት የበጎ ፈቃድ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ደረጀ ካሳ ናቸው። በረዥም ጊዜ የስራ ልምዳቸው አብረዋቸው የሰሩ ቀና ሰዎች ከፍ ከፍ ብለው ስኬታማ መሆናቸውን ገልፀዋል አቶ ደረጀ።
ቀና ያልሆኑ ሰዎች መጨረሻቸው አያምርም ፤ ስኬት አያመጡም ፤ ለውጥ አልባ ናቸው። ቀና ሰዎች ደግሞ በተቃራኒው የጀመሩትን በስኬት ይጨርሳሉ ፤ ከነበሩበት ኃላፊነት ወደላቀ ደረጃ ያድጋሉ። በአጠቃላይ ለውጥ ለማምጣትና ስኬት ላይ ለመድረስ በቅንነት ማገልገል ያስፈልጋል።
በህዝብ አገልግሎት ከ12ቱ የስነ ምግባር መርሆዎች መካከል ቅንነት አንዱ ነው። እንደ መርህ በየመሥሪያ ቤታችን ግድግዳ ላይ ያስቀመጥነው "ቅንነት" ልንገዛበትና ልንተገብረው የሚገባ ህግ ነው። ህዝብን በቅንነት ማገልገል ደግሞ የምናልማትን ታላቅ ሃገር ለመገንባት ያግዛል። የኮሚሽናችን ባለሙያዎች "ቅንነትን" የሥራቸው መሰረት ፣ የሕይወታቸው ህግ በማድረግ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ቅንነት - ለላቀ ውጤት!
መልካም የስራ ሳምንት!
👍9
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ማኅበራዊ ሚዲያን ለሀገራዊ አንድነት ፣ ለሠላም ዕሴትና ለመልካም ገፅታ ግንባታ እንዲሁም ለበጎ ዓላማ መጠቀም እንደሚገባ ተጠቆመ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን "ማኅበራዊ ሚዲያ ለበጎነት" በሚል መሪ ቃል ማኅበራዊ ሚዲያውን ለበጎ ዓላማ ለሚጠቀሙ በጎ ፈቃደኞች ስልጠና ሰጥቷል።
የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ ፀሐይ ኪባሞ ወጣቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን የሚያፀኑ ፣ ሀገራዊ አንድነትንና መልካም ገፅታን የሚገነቡ እንዲሁም ለሠላም ዕሴት ግንባታ ቀዳሚ ትኩረት የሚሠጡ ይዘቶችን ማጋራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ወጣቶች አዎንታዊ አጀንዳዎችን በመሸጥ የተዛቡና አንድነትን የሚሸረሽሩ አሉታዊ መረጃዎች ቦታ እንዳይኖራቸው ማድረግ ፣ የማኅበራዊ ሚዲያውን አልጎሪዝም በልማት ፣ በሠላም ፣ በዲሞክራሲ ፣ በማኅበረሰብ ለውጥና ተጠቃሚነት የበላይነት እንዲይዝ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ምክትል ኮሚሽነሯ።
የአሁኑ ትውልድ አሉታዊ የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ተፅዕኖን በመግታት ለብሔራዊ ጥቅምና ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር የድርሻውን የሚወጣበት ጊዜ መሆኑን ያወሱት ወ/ሮ ፀሐይ በከተማችን አዲስ አበባ በየዘርፉ የተከናወኑ የልማት ፣ የበጎነትና የሠላም ስራዎች የማህበራዊ ሚዲያው ቀዳሚ አጀንዳ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ የወጣት በጎ ፈቃደኞች ሚና ከፍተኛ እንደነበር አውስተው ተሳትፏቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።
ኮሚሽኑ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተያዙ 15 ፕሮግራሞች መካከል "ማኅበራዊ ሚዲያ ለበጎነት" አንደኛው መርሀ ግብር ሲሆን ጤናማ የዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም ባህል እንዲጎለብት ፣ ማኅበራዊ ሚዲያ ኢትዮጵያዊ አብሮ የመኖር እሴትን በማይሸረሽር መልኩ ፣ ወንድማማችነት ፣ አብሮነትና ሠላም እንዲዳብር ለከተማዋ ወጣቶች የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት ግንዛቤዎችን ሲፈጥር ቆይቷል።
በዛሬው የስልጠና መድረክ በጎ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ወጣት በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉ ሲሆን ሥልጠናው በይዘት አዘገጃጀት ፣ በእውነታ ማጣራት እንዲሁም በማህበራዊ ሚዲያ በጎ ፈቃደኝነት ላይ ትኩረት አድርጓል።
"ጤናማ የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም የሥልጡን ዜጋ መገለጫ ነው!"
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@voluntarismaddis16
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.volunteeraddis.et
Instagram - https://www.instagram.com/communitypv/
Twitter - https://x.com/Volunteeraddis
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን "ማኅበራዊ ሚዲያ ለበጎነት" በሚል መሪ ቃል ማኅበራዊ ሚዲያውን ለበጎ ዓላማ ለሚጠቀሙ በጎ ፈቃደኞች ስልጠና ሰጥቷል።
የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ ፀሐይ ኪባሞ ወጣቶች በማኅበራዊ ሚዲያ ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን የሚያፀኑ ፣ ሀገራዊ አንድነትንና መልካም ገፅታን የሚገነቡ እንዲሁም ለሠላም ዕሴት ግንባታ ቀዳሚ ትኩረት የሚሠጡ ይዘቶችን ማጋራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ወጣቶች አዎንታዊ አጀንዳዎችን በመሸጥ የተዛቡና አንድነትን የሚሸረሽሩ አሉታዊ መረጃዎች ቦታ እንዳይኖራቸው ማድረግ ፣ የማኅበራዊ ሚዲያውን አልጎሪዝም በልማት ፣ በሠላም ፣ በዲሞክራሲ ፣ በማኅበረሰብ ለውጥና ተጠቃሚነት የበላይነት እንዲይዝ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ምክትል ኮሚሽነሯ።
የአሁኑ ትውልድ አሉታዊ የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ተፅዕኖን በመግታት ለብሔራዊ ጥቅምና ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር የድርሻውን የሚወጣበት ጊዜ መሆኑን ያወሱት ወ/ሮ ፀሐይ በከተማችን አዲስ አበባ በየዘርፉ የተከናወኑ የልማት ፣ የበጎነትና የሠላም ስራዎች የማህበራዊ ሚዲያው ቀዳሚ አጀንዳ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ የወጣት በጎ ፈቃደኞች ሚና ከፍተኛ እንደነበር አውስተው ተሳትፏቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።
ኮሚሽኑ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተያዙ 15 ፕሮግራሞች መካከል "ማኅበራዊ ሚዲያ ለበጎነት" አንደኛው መርሀ ግብር ሲሆን ጤናማ የዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም ባህል እንዲጎለብት ፣ ማኅበራዊ ሚዲያ ኢትዮጵያዊ አብሮ የመኖር እሴትን በማይሸረሽር መልኩ ፣ ወንድማማችነት ፣ አብሮነትና ሠላም እንዲዳብር ለከተማዋ ወጣቶች የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት ግንዛቤዎችን ሲፈጥር ቆይቷል።
በዛሬው የስልጠና መድረክ በጎ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ወጣት በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉ ሲሆን ሥልጠናው በይዘት አዘገጃጀት ፣ በእውነታ ማጣራት እንዲሁም በማህበራዊ ሚዲያ በጎ ፈቃደኝነት ላይ ትኩረት አድርጓል።
"ጤናማ የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም የሥልጡን ዜጋ መገለጫ ነው!"
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@voluntarismaddis16
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.volunteeraddis.et
Instagram - https://www.instagram.com/communitypv/
Twitter - https://x.com/Volunteeraddis
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👍2
👉ትላንት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ መኖሪያ ህንፃዎች በከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቀው ለተጠቃሚዎች ተላልፈዋል።
👉ዊንጌት እና ገብስ ተራ አካባቢ ደሳሳና ለኑሮ የማያመቹ የነበሩ የቀበሌ ቤቶችን በማፍረስ ምቹ ተደርገው የተገነቡ ናቸው።
👉አጠቃላይ የቤቶች ብዛት 75 ሲሆኑ ባለ 5 ወለል(G+5) ሁለት ህንጻዎች ናቸው።
👉ከ375 በላይ ቤተሰቦች ያሏቸው 75 አባውራ/እማውራዎችን ተጠቃሚ ያደረጉት እነዚህ ቤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቁ ናቸው።
👉የመጸዳጃና የማብሰያ ቦታ ፣ ሰፋፊ ሳሎኖችና መኝታ ቤቶች ያላቸው ናቸው::
👉በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን፣ መተባበር ለኢትዮጵያ አ/ማ ፣ ተምሳሌት በሲዳሞ ተራ አ/ማ ፣ ምዕራብ ገበያ ልማት አ/ማ ፣ ጉሊት አክሲዮን ማህበር ፣ ሸራ ተራ ብርሃን አክሲዮን እንዲሁም ጎሽ ንግድና አክሲዮን ግንባታ ማህበር ተሳትፈዋል።
👉ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቦታው ተገኝተው "የዘመሙ ጎጆዎችን እያቃናን የሚፈሱ እንባዎች ሲታበሱ ማየት እጅግ ደስ ያሰኛል" ያሉ ሲሆን በዚህ የማኅበራዊ ኃላፊነት ስራ ላይ የተሳተፉ ተቋማትን በተጠቃሚ ነዋሪዎች እና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል።
👉በመተባበር የሰው ኑሮ እና አኗኗርን በማሻሻል ሀገር እንገነባለንና ትብብራችንን አጠናክረን እንቀጥል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አቅርበዋል።
👉ዊንጌት እና ገብስ ተራ አካባቢ ደሳሳና ለኑሮ የማያመቹ የነበሩ የቀበሌ ቤቶችን በማፍረስ ምቹ ተደርገው የተገነቡ ናቸው።
👉አጠቃላይ የቤቶች ብዛት 75 ሲሆኑ ባለ 5 ወለል(G+5) ሁለት ህንጻዎች ናቸው።
👉ከ375 በላይ ቤተሰቦች ያሏቸው 75 አባውራ/እማውራዎችን ተጠቃሚ ያደረጉት እነዚህ ቤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቁ ናቸው።
👉የመጸዳጃና የማብሰያ ቦታ ፣ ሰፋፊ ሳሎኖችና መኝታ ቤቶች ያላቸው ናቸው::
👉በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን፣ መተባበር ለኢትዮጵያ አ/ማ ፣ ተምሳሌት በሲዳሞ ተራ አ/ማ ፣ ምዕራብ ገበያ ልማት አ/ማ ፣ ጉሊት አክሲዮን ማህበር ፣ ሸራ ተራ ብርሃን አክሲዮን እንዲሁም ጎሽ ንግድና አክሲዮን ግንባታ ማህበር ተሳትፈዋል።
👉ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቦታው ተገኝተው "የዘመሙ ጎጆዎችን እያቃናን የሚፈሱ እንባዎች ሲታበሱ ማየት እጅግ ደስ ያሰኛል" ያሉ ሲሆን በዚህ የማኅበራዊ ኃላፊነት ስራ ላይ የተሳተፉ ተቋማትን በተጠቃሚ ነዋሪዎች እና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል።
👉በመተባበር የሰው ኑሮ እና አኗኗርን በማሻሻል ሀገር እንገነባለንና ትብብራችንን አጠናክረን እንቀጥል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አቅርበዋል።
👍2
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
39ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች፥
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን 2017-2020 የገቢ ስትራቴጂ ላይ ነው፡፡ ስትራቴጂው የታክስ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ለግል ኢንቨስትመንቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የታለመ ሲሆን አጠቃላይ የታክስ ፖሊሲዎችን እና አስተዳደራዊ ሪፎርሞችን እንዲሁም ማሻሻያዎችን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ሰትራቴጂው ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጎ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በስትራቴጂው ላይ በዝርዝር ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ውሳኔ ካገኘበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል የተወያየው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ከማልታ ሪፐብሊክ መንግስት እና ከቻድ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር የተፈረማቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነቶችን ለማጽደቅ የቀረቡ 2 ረቂቅ አዋጆች ላይ ነው፡፡ ስምምነቶቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ማንኛውም የማልታ ከተማ እና ወደ እንጃሜና ከተማ በ3ኛና 4ኛ ትራፊክ መብት የመንገደኛ እና የጭነት የበረራ ምልልስ ለማድረግ፣ ተወካይ አየር መንገዶችን በሽርክና ለማሰራት፣ በ5ኛ ትራፊክ መብት ወደ ተመረጡ መዳረሻዎች በረራ ለማድረግ የሚያስችል እና አገራችን ከሁለቱ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር፣ ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለወጪ ንግድ፣ ለቱሪዝም፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ስምምነቶች ናቸው፡፡ ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጆቹ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡
3. በመቀጠል የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን ለማጽደቅ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን በአባል አገራት መካከል ሕብረት በመፍጠር የኢንዱስትሪ ንብረትን ለመጠበቅ፣ የፈጠራ ባለቤትነት፣ የግልጋሎት ሞዴሎች፣ የኢንዱስትሪ ንድፎች፣ የንግድ ምልክቶች፣ የአገልግሎት ምልክቶች፣ የንግድ ስሞች፣ የምርቶች ምንጭ አመልካች ምልክቶች ለመጠበቅ እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ውድድር ለመከላከል እና ለግብርና እና ሁሉንም የተመረቱ ወይም ተፈጥሯዊ ምርቶች የሚያካትት ነው፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው የዓለም አቀፍ ምልክቶችን ከሚመለከተው የማድሪድ ስምምነት ጋር የተዛመደውን ፕሮቶኮል ለማጽደቅ በወጣ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ፕሮቶኮሉ የንግድ እና የአገልግሎት ምልክቶች በአገር ውስጥ ሕግ ከሚደረግላቸው ጥበቃ አልፈው በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥበቃ እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ምርቶችና አገልግሎቶች ያላግባብ ለሌሎች ጥቅም እንዳይውሉ በቂ ጥበቃ የሚደረግበትን ሁኔታ የሚፈጥር፣ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና አገልግሎቶች እንዲኖሩና የሀብት ምንጭ እንዲሆኑ ትልቅ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ምክር ቤቱ በፕሮቶኮሉ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
5. በመጨረሻም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ደንብ እና የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ደንብ ላይ ነው፡፡ የጀመረውን ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ፣ ሪፎርሙ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ለማስቻል የአገልግሎቱን ልዩ ባህሪይ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በዝርዝር ከተወያየባቸው በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን 2017-2020 የገቢ ስትራቴጂ ላይ ነው፡፡ ስትራቴጂው የታክስ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ለግል ኢንቨስትመንቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የታለመ ሲሆን አጠቃላይ የታክስ ፖሊሲዎችን እና አስተዳደራዊ ሪፎርሞችን እንዲሁም ማሻሻያዎችን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ሰትራቴጂው ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጎ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በስትራቴጂው ላይ በዝርዝር ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ውሳኔ ካገኘበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል የተወያየው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ከማልታ ሪፐብሊክ መንግስት እና ከቻድ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር የተፈረማቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነቶችን ለማጽደቅ የቀረቡ 2 ረቂቅ አዋጆች ላይ ነው፡፡ ስምምነቶቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ማንኛውም የማልታ ከተማ እና ወደ እንጃሜና ከተማ በ3ኛና 4ኛ ትራፊክ መብት የመንገደኛ እና የጭነት የበረራ ምልልስ ለማድረግ፣ ተወካይ አየር መንገዶችን በሽርክና ለማሰራት፣ በ5ኛ ትራፊክ መብት ወደ ተመረጡ መዳረሻዎች በረራ ለማድረግ የሚያስችል እና አገራችን ከሁለቱ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር፣ ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለወጪ ንግድ፣ ለቱሪዝም፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ስምምነቶች ናቸው፡፡ ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጆቹ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡
3. በመቀጠል የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን ለማጽደቅ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን በአባል አገራት መካከል ሕብረት በመፍጠር የኢንዱስትሪ ንብረትን ለመጠበቅ፣ የፈጠራ ባለቤትነት፣ የግልጋሎት ሞዴሎች፣ የኢንዱስትሪ ንድፎች፣ የንግድ ምልክቶች፣ የአገልግሎት ምልክቶች፣ የንግድ ስሞች፣ የምርቶች ምንጭ አመልካች ምልክቶች ለመጠበቅ እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ውድድር ለመከላከል እና ለግብርና እና ሁሉንም የተመረቱ ወይም ተፈጥሯዊ ምርቶች የሚያካትት ነው፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው የዓለም አቀፍ ምልክቶችን ከሚመለከተው የማድሪድ ስምምነት ጋር የተዛመደውን ፕሮቶኮል ለማጽደቅ በወጣ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ፕሮቶኮሉ የንግድ እና የአገልግሎት ምልክቶች በአገር ውስጥ ሕግ ከሚደረግላቸው ጥበቃ አልፈው በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥበቃ እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ምርቶችና አገልግሎቶች ያላግባብ ለሌሎች ጥቅም እንዳይውሉ በቂ ጥበቃ የሚደረግበትን ሁኔታ የሚፈጥር፣ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና አገልግሎቶች እንዲኖሩና የሀብት ምንጭ እንዲሆኑ ትልቅ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ምክር ቤቱ በፕሮቶኮሉ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
5. በመጨረሻም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ደንብ እና የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ደንብ ላይ ነው፡፡ የጀመረውን ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ፣ ሪፎርሙ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ለማስቻል የአገልግሎቱን ልዩ ባህሪይ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በዝርዝር ከተወያየባቸው በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኢሬቻ የመቻቻል ፣ የአብሮነት ፣ የህብርና የሠላም ምልክት!
ቱባ ባህላዊ እሴቶቻችን ደምቀን የምናጌጥባቸውና የምንኮራባቸው የኅብራዊ መልኮቻችን ነፀብራቆች ፣ የወል ሀብቶቻችን ናቸው፡፡
በዓሉ የመተሳሰብ ፣ የአብሮነት ፣ የሠላምና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እየገለፅን በዓሉን ስናከብር ምንጊዜም እንደምናደርገው ለተቸገሩ እና የእኛን ድጋፍ ለሚሹ ሁሉ አብሮነታችን በማሳየት እንዲሆን እንጠይቃለን፡፡
መልካም በዓል!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን!
ቱባ ባህላዊ እሴቶቻችን ደምቀን የምናጌጥባቸውና የምንኮራባቸው የኅብራዊ መልኮቻችን ነፀብራቆች ፣ የወል ሀብቶቻችን ናቸው፡፡
በዓሉ የመተሳሰብ ፣ የአብሮነት ፣ የሠላምና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እየገለፅን በዓሉን ስናከብር ምንጊዜም እንደምናደርገው ለተቸገሩ እና የእኛን ድጋፍ ለሚሹ ሁሉ አብሮነታችን በማሳየት እንዲሆን እንጠይቃለን፡፡
መልካም በዓል!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን!
👍6
አቶ ይመር ከበደ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተመደቡ።
ኮሚሽነር ይመር ከበደ ከቀድሞው ኮሚሽነር ተንኩዌይ ጆክ ሮም የስራ ርክክብና ከጠቅላላ ካውንስል አባላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል።
የቀድሞው ኮሚሽነር አቶ ተንኩዌይ ጆክ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊ ሆነው ተመድበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ለኮሚሽነር ይመር ከበደ እና ለአቶ ተንኩዌይ ጆክ መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ይመኛል።
ኮሚሽነር ይመር ከበደ ከቀድሞው ኮሚሽነር ተንኩዌይ ጆክ ሮም የስራ ርክክብና ከጠቅላላ ካውንስል አባላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል።
የቀድሞው ኮሚሽነር አቶ ተንኩዌይ ጆክ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊ ሆነው ተመድበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ለኮሚሽነር ይመር ከበደ እና ለአቶ ተንኩዌይ ጆክ መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ይመኛል።
👍6