ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግም፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል።
#PMOEthiopia
#PMOEthiopia
"በ2016 በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሰጥቷል።" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በ2016 በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መሰጠቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስተዋፅዖ ላበረከቱ በጎ ፈቃደኞች ፣ ባለሀብቶችና ተቋማት እውቅና ሰጥቷል።
በእውቅና መድረኩ ላይ ተገኝተው በጎ ፈቃደኞችን ያመሰገኑት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት ዓመቱ ልበ ቀና ባለሀብቶችን በማስተባበር 7 ሺህ 567 የአቅመ ደካሞችና አረጋውያን ቤቶች መገንባታቸውን ገልፀዋል።
1.2 ሚሊዮን ዜጎች በድግግሞሽ ማዕድ የተጋሩ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባዋ በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች 1.9 ሚሊዮን ዜጎች ቀጥታ ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የገለፁት።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለበጎነት እጃቸውን በመዘርጋት ወገኖቻቸውን ያገዙ እና ማህበራዊ ችግሮችን ያቃለሉ በጎ ፈቃደኞችን ምስጋና አቅርበዋል።
በ2016 በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መሰጠቱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስተዋፅዖ ላበረከቱ በጎ ፈቃደኞች ፣ ባለሀብቶችና ተቋማት እውቅና ሰጥቷል።
በእውቅና መድረኩ ላይ ተገኝተው በጎ ፈቃደኞችን ያመሰገኑት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት ዓመቱ ልበ ቀና ባለሀብቶችን በማስተባበር 7 ሺህ 567 የአቅመ ደካሞችና አረጋውያን ቤቶች መገንባታቸውን ገልፀዋል።
1.2 ሚሊዮን ዜጎች በድግግሞሽ ማዕድ የተጋሩ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባዋ በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች 1.9 ሚሊዮን ዜጎች ቀጥታ ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው የገለፁት።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለበጎነት እጃቸውን በመዘርጋት ወገኖቻቸውን ያገዙ እና ማህበራዊ ችግሮችን ያቃለሉ በጎ ፈቃደኞችን ምስጋና አቅርበዋል።
👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን ለአዲሱ ዘመን ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ!
መልካም አዲስ ዓመት
ምድር አረንጓዴ ለብሳ በአደይ አበባ ስታጌጥ ፤ በተፈጥሮ ኅብር ዜማ አዕዋፋት ሲዘምሩ ፤ ልጆች አበባየሁሽ ሲጨፍሩ ፤ አዲስ አመት ፣ አዲስ ተስፋ ፣ አዲስ ህይወት ሲሰነቅ ፤ ትላንት በትውስታ ሲያልፍ ነጋችን በብርሀን ሲደምቅ ፤ እኛ ኢትዮጵያውያን አብሮነታችን ይበልጥ ይጠብቃል፡፡ የጎደለባቸውን ሞልተን ፣ የወደቁትን አንስተን ፣ የተራቡትን አጉርሰን ፣ የታረዙትን አልብሰን ተደጋግፈን የምንኖር እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡
በበጎነት ያካበትነውን ልምድ ሌትና ቀን በመስራት ከድህነት ለመላቀቅ የምንተጋበት ፣ የህብረት ፣ የሰላም ፣ የመተሳሰብና የፍቅር ዘመን ይሁንልን!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን!
ምድር አረንጓዴ ለብሳ በአደይ አበባ ስታጌጥ ፤ በተፈጥሮ ኅብር ዜማ አዕዋፋት ሲዘምሩ ፤ ልጆች አበባየሁሽ ሲጨፍሩ ፤ አዲስ አመት ፣ አዲስ ተስፋ ፣ አዲስ ህይወት ሲሰነቅ ፤ ትላንት በትውስታ ሲያልፍ ነጋችን በብርሀን ሲደምቅ ፤ እኛ ኢትዮጵያውያን አብሮነታችን ይበልጥ ይጠብቃል፡፡ የጎደለባቸውን ሞልተን ፣ የወደቁትን አንስተን ፣ የተራቡትን አጉርሰን ፣ የታረዙትን አልብሰን ተደጋግፈን የምንኖር እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡
በበጎነት ያካበትነውን ልምድ ሌትና ቀን በመስራት ከድህነት ለመላቀቅ የምንተጋበት ፣ የህብረት ፣ የሰላም ፣ የመተሳሰብና የፍቅር ዘመን ይሁንልን!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን!
👍6
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ለመላው ህዝበ ሙስሊም እንኳን ለ1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል!
ኮሚሽኑ በዓሉን ስናከብር ምንጊዜም እንደምናደርገው ለወገኖቻችን ያለንን ፍቅር የምንገልፅባቸውን የበጎነት ፣ የልግስናና የቸርነት ተግባራትን በማከናወን ፤ አብሮነትን ፣ ወንድማማችነትንና መተሳሰብን በማጠናከር እንዲሆን ጥሪውን እያስተላለፈ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የሰላምና የጤና በዓል ይመኛል፡፡
ኮሚሽኑ በዓሉን ስናከብር ምንጊዜም እንደምናደርገው ለወገኖቻችን ያለንን ፍቅር የምንገልፅባቸውን የበጎነት ፣ የልግስናና የቸርነት ተግባራትን በማከናወን ፤ አብሮነትን ፣ ወንድማማችነትንና መተሳሰብን በማጠናከር እንዲሆን ጥሪውን እያስተላለፈ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የሰላምና የጤና በዓል ይመኛል፡፡
#ወርቃማው_ሰኞ
ጅማሬያችን ለመጨረሻችን መነሻ ነው። በመልካም መጀመር በመልካም ለማጠናቀቅ ወሳኝ ነው። የስራ መጀመሪያችን ወርቃማዋን ሰኞ የስራ መነሳሳትን በሚፈጥር መልኩ በ"ቅንነት!" መጀመር ተገቢ ነው።
በዛሬው ወርቃማ ሰኞ "ቅንነት" ለስኬታማነት ያለውን ሚና የሚያስረዳ ማብራሪያ የሰጡት የበጎ ፈቃድ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ደረጀ ካሳ ናቸው። በረዥም ጊዜ የስራ ልምዳቸው አብረዋቸው የሰሩ ቀና ሰዎች ከፍ ከፍ ብለው ስኬታማ መሆናቸውን ገልፀዋል አቶ ደረጀ።
ቀና ያልሆኑ ሰዎች መጨረሻቸው አያምርም ፤ ስኬት አያመጡም ፤ ለውጥ አልባ ናቸው። ቀና ሰዎች ደግሞ በተቃራኒው የጀመሩትን በስኬት ይጨርሳሉ ፤ ከነበሩበት ኃላፊነት ወደላቀ ደረጃ ያድጋሉ። በአጠቃላይ ለውጥ ለማምጣትና ስኬት ላይ ለመድረስ በቅንነት ማገልገል ያስፈልጋል።
በህዝብ አገልግሎት ከ12ቱ የስነ ምግባር መርሆዎች መካከል ቅንነት አንዱ ነው። እንደ መርህ በየመሥሪያ ቤታችን ግድግዳ ላይ ያስቀመጥነው "ቅንነት" ልንገዛበትና ልንተገብረው የሚገባ ህግ ነው። ህዝብን በቅንነት ማገልገል ደግሞ የምናልማትን ታላቅ ሃገር ለመገንባት ያግዛል። የኮሚሽናችን ባለሙያዎች "ቅንነትን" የሥራቸው መሰረት ፣ የሕይወታቸው ህግ በማድረግ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ቅንነት - ለላቀ ውጤት!
መልካም የስራ ሳምንት!
ጅማሬያችን ለመጨረሻችን መነሻ ነው። በመልካም መጀመር በመልካም ለማጠናቀቅ ወሳኝ ነው። የስራ መጀመሪያችን ወርቃማዋን ሰኞ የስራ መነሳሳትን በሚፈጥር መልኩ በ"ቅንነት!" መጀመር ተገቢ ነው።
በዛሬው ወርቃማ ሰኞ "ቅንነት" ለስኬታማነት ያለውን ሚና የሚያስረዳ ማብራሪያ የሰጡት የበጎ ፈቃድ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ደረጀ ካሳ ናቸው። በረዥም ጊዜ የስራ ልምዳቸው አብረዋቸው የሰሩ ቀና ሰዎች ከፍ ከፍ ብለው ስኬታማ መሆናቸውን ገልፀዋል አቶ ደረጀ።
ቀና ያልሆኑ ሰዎች መጨረሻቸው አያምርም ፤ ስኬት አያመጡም ፤ ለውጥ አልባ ናቸው። ቀና ሰዎች ደግሞ በተቃራኒው የጀመሩትን በስኬት ይጨርሳሉ ፤ ከነበሩበት ኃላፊነት ወደላቀ ደረጃ ያድጋሉ። በአጠቃላይ ለውጥ ለማምጣትና ስኬት ላይ ለመድረስ በቅንነት ማገልገል ያስፈልጋል።
በህዝብ አገልግሎት ከ12ቱ የስነ ምግባር መርሆዎች መካከል ቅንነት አንዱ ነው። እንደ መርህ በየመሥሪያ ቤታችን ግድግዳ ላይ ያስቀመጥነው "ቅንነት" ልንገዛበትና ልንተገብረው የሚገባ ህግ ነው። ህዝብን በቅንነት ማገልገል ደግሞ የምናልማትን ታላቅ ሃገር ለመገንባት ያግዛል። የኮሚሽናችን ባለሙያዎች "ቅንነትን" የሥራቸው መሰረት ፣ የሕይወታቸው ህግ በማድረግ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ቅንነት - ለላቀ ውጤት!
መልካም የስራ ሳምንት!
👍9