በቦሌ ክፍለ ከተማ በህብረተሰብ ተሳትፎ በ112 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የጃክሮስ-ኢቢኤስ የአስፋልት መንገድ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ!
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ጃክሮስ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ መንደር በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ የተገነባው ዘመናዊ የውስጥ ለውስጥ የአስፋልት መንገድ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቋል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አደፍርስ ኮራን ጨምሮ አመራሮች፣ የአካባቢው ባለሀብቶችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ፕሮጀክቱ፦
* 1.35 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ስፋት
* ደረጃውን የጠበቀ የእግረኛ መንገድ እና የአረንጓዴ ስፍራዎችን
* እንዲሁም በኅብረተሰቡ አቅም 112 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል።
* የሕዝብ አቅምን ማስተባበር ከተቻለ ምን ያህል ታላላቅ ለውጦችን ማምጣት እንደሚቻል ማረጋገጫ ነው።
* የአካባቢው ነዋሪዎች ቀደም ሲል በጭቃና በአቧራ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት በዘላቂነት በመቅረፍ፣ ለአካባቢው የንግድና ኢንቨስትመንት መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
#BoleSubCity #Woreda7 #Infrastructure #RoadProject #AddisAbaba #Ethiopia
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ጃክሮስ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ መንደር በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ የተገነባው ዘመናዊ የውስጥ ለውስጥ የአስፋልት መንገድ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቋል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አደፍርስ ኮራን ጨምሮ አመራሮች፣ የአካባቢው ባለሀብቶችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ፕሮጀክቱ፦
* 1.35 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ስፋት
* ደረጃውን የጠበቀ የእግረኛ መንገድ እና የአረንጓዴ ስፍራዎችን
* እንዲሁም በኅብረተሰቡ አቅም 112 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል።
* የሕዝብ አቅምን ማስተባበር ከተቻለ ምን ያህል ታላላቅ ለውጦችን ማምጣት እንደሚቻል ማረጋገጫ ነው።
* የአካባቢው ነዋሪዎች ቀደም ሲል በጭቃና በአቧራ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት በዘላቂነት በመቅረፍ፣ ለአካባቢው የንግድና ኢንቨስትመንት መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
#BoleSubCity #Woreda7 #Infrastructure #RoadProject #AddisAbaba #Ethiopia
👍1
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነባ ባለሁለት ወለል ዘመናዊ ፖሊስ ጣቢያ ተመረቀ።
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር በኅብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ እና በመንግስት ትብብር የተገነባ ዘመናዊ የፖሊስ ጣቢያ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ባለሁለት ወለል (G+1) ህንፃ ሆኖ የተገነባው ይህ ጣቢያ፣ ለፖሊስ አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽነትና ቅልጥፍና ምቹ የሆኑ በቂ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎችን አካቶ የያዘ ነው።
በዚሁ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ማህበረሰቡን በማስተባበር የህዝብን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መመለስ መቻሉን አድንቀዋል። የፖሊስ ጣቢያው መገንባት ህብረተሰቡና ፖሊስ በወንጀል ቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ ይበልጥ ተቀራርበውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ ለማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በህዝብና መንግስት የጋራ ቅንጅት የተገኘው የላቀ ስኬት፣ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላምና ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጉዞ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው። አዲሱ የፖሊስ ጣቢያ ወንጀልን ከመቀነስና የህዝብን ደህንነት ከመጠበቅ አንጻር የላቀ ሚና የሚጫወት ነው።
በህዝብና መንግስት ቅንጅት የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን!
#KolfeKeranio #CommunityPolicing #PeaceAndSecurity #AddisAbaba #Ethiopia
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር በኅብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ እና በመንግስት ትብብር የተገነባ ዘመናዊ የፖሊስ ጣቢያ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ባለሁለት ወለል (G+1) ህንፃ ሆኖ የተገነባው ይህ ጣቢያ፣ ለፖሊስ አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽነትና ቅልጥፍና ምቹ የሆኑ በቂ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎችን አካቶ የያዘ ነው።
በዚሁ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ማህበረሰቡን በማስተባበር የህዝብን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መመለስ መቻሉን አድንቀዋል። የፖሊስ ጣቢያው መገንባት ህብረተሰቡና ፖሊስ በወንጀል ቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ ይበልጥ ተቀራርበውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ ለማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በህዝብና መንግስት የጋራ ቅንጅት የተገኘው የላቀ ስኬት፣ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላምና ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጉዞ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው። አዲሱ የፖሊስ ጣቢያ ወንጀልን ከመቀነስና የህዝብን ደህንነት ከመጠበቅ አንጻር የላቀ ሚና የሚጫወት ነው።
በህዝብና መንግስት ቅንጅት የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን!
#KolfeKeranio #CommunityPolicing #PeaceAndSecurity #AddisAbaba #Ethiopia
👍4❤2
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በበጋ የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም የተገነቡ ከ20 በላይ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚዎች ተላለፉ።
በክፍለ ከተማው በሚገኙ ልዩ ልዩ ወረዳዎች በጥቅሉ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአቅመ ደካማና አረጋውያን መኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ለባለቤቶቻቸው ተረክበዋል።
የቤት ግንባታ ተጠቃሚ የሆኑት ወ/ሮ አሰገደች አሰፋ ከዚህ ቀደም ይኖሩበት የነበረው ቤት በጣም የተጎሳቆለ፣ ለዝናብና ለፀሀይ የተጋለጠ በመሆኑ ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገው እንደነበር ይናገራሉ። ዛሬ ቤታቸው በሚያስደስት ደረጃ ተገንብቶ በመረከባቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ለበጎ ፈቃደኞች ምስጋና አቅርበዋል።
ሌላኛው የቤት ግንባታው ተጠቃሚ አቶ አያሌው ይማም በበኩላቸው፣ ለብዙ ዓመታት ለመኖሪያነት ፍፁም በማይመችና ሙሉ በሙሉ ቆርቆሮ በቆርቆሮ በነበረ ጠባብ ቤት ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸው፤ "ዛሬ ያ አሰቃቂ ታሪክ ተቀይሮ ቤታችን በብሉኬት ተሰርቶና ዘምኖ በመረከባችን የተሰማንን ደስታ በቃል መግለጽ ይከብዳል" ሲሉ አስተያየታቸውን መስጠታቸውን የላፍቶ ኮሙኒኬሽን ዘገባ ያመለክታል።
የክፍለ ከተማው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብዙአየሁ መኮንን ዛሬ ለተጠቃሚዎች የተላለፉት ቤቶች በበጋ ወቅት በልዩ ትኩረት በእቅድ ተይዘው ሲከናወኑ የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመው ፕሮጀክቶቹ ከጅምር እስከ ፍጻሜ ስኬታማ እንዲሆኑ ከጎናቸው ላልተለዩ ቅን ባለሀብቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች ምስጋና አቅርበዋል።
በከተማችን ለአቅመ ደካሞች፣ ለአረጋውያን እንዲሁም ለሀገር ባለውለታዎች ደረጃቸውን የጠበቁ መኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ ከመስጠት ባለፈ፤ የተዛመሙ ጎጆዎችን ባሉበት መልሶ በመገንባት ለኑሮ ምቹ የማድረግ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በክፍለ ከተማው በሚገኙ ልዩ ልዩ ወረዳዎች በጥቅሉ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአቅመ ደካማና አረጋውያን መኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ለባለቤቶቻቸው ተረክበዋል።
የቤት ግንባታ ተጠቃሚ የሆኑት ወ/ሮ አሰገደች አሰፋ ከዚህ ቀደም ይኖሩበት የነበረው ቤት በጣም የተጎሳቆለ፣ ለዝናብና ለፀሀይ የተጋለጠ በመሆኑ ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገው እንደነበር ይናገራሉ። ዛሬ ቤታቸው በሚያስደስት ደረጃ ተገንብቶ በመረከባቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ለበጎ ፈቃደኞች ምስጋና አቅርበዋል።
ሌላኛው የቤት ግንባታው ተጠቃሚ አቶ አያሌው ይማም በበኩላቸው፣ ለብዙ ዓመታት ለመኖሪያነት ፍፁም በማይመችና ሙሉ በሙሉ ቆርቆሮ በቆርቆሮ በነበረ ጠባብ ቤት ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸው፤ "ዛሬ ያ አሰቃቂ ታሪክ ተቀይሮ ቤታችን በብሉኬት ተሰርቶና ዘምኖ በመረከባችን የተሰማንን ደስታ በቃል መግለጽ ይከብዳል" ሲሉ አስተያየታቸውን መስጠታቸውን የላፍቶ ኮሙኒኬሽን ዘገባ ያመለክታል።
የክፍለ ከተማው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብዙአየሁ መኮንን ዛሬ ለተጠቃሚዎች የተላለፉት ቤቶች በበጋ ወቅት በልዩ ትኩረት በእቅድ ተይዘው ሲከናወኑ የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመው ፕሮጀክቶቹ ከጅምር እስከ ፍጻሜ ስኬታማ እንዲሆኑ ከጎናቸው ላልተለዩ ቅን ባለሀብቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች ምስጋና አቅርበዋል።
በከተማችን ለአቅመ ደካሞች፣ ለአረጋውያን እንዲሁም ለሀገር ባለውለታዎች ደረጃቸውን የጠበቁ መኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ ከመስጠት ባለፈ፤ የተዛመሙ ጎጆዎችን ባሉበት መልሶ በመገንባት ለኑሮ ምቹ የማድረግ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል።
👍1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
በአዲስ አበባ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር 2,500 ቤቶች ሊገነቡ ነው።
አዲስ አበባ| ሰኔ 15/2018 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአራዳ ክፍለ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተጀመረው የቤት ግንባታና የአካባቢ ማደስ ፕሮጀክት፥ የመንግስትን ፖለቲካዊ ቃል ኪዳን ወደ መሬት የመቀየር ስትራቴጂ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ። ከንቲባዋ "የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ሳይሆን በተግባራዊ ምላሽ ነው" ያሉ ሲሆን፥ ይህም ብልፅግና ፓርቲ በምርጫ ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ የአምስት ዓመት እምነት በተሰጠው ማግስት የተጀመረ መሆኑን ገልጸዋል።
በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማ ደረጃ 2,500 ቤቶችን ለመገንባት የታቀደ ሲሆን፥ የዚሁ አካል የሆነውና ከከንቲባ ፅህፈት ቤት በስተጀርባ የሚገነባው የ“አራዳ የበጎነት መንደር” ግንባታ በይፋ ተጀምሯል። ይህ ሜጋ ፕሮጀክት ባለ 9 ወለል 8 ዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃዎችን እና ባለ 4 ወለል ሁለት የገበያ ማዕከላትን ያካተተ ሲሆን፥ ለዘመናት የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በመቀየር ለሰው ልጆች ክብር የሚመጥን ዘመናዊ የጋራ መገልገያ፣ አረንጓዴ ስፍራና የስፖርት ሜዳዎችን ያካተተ መንደር እንደሚሆን ተገልጿል።
ከቤት ግንባታው በተጨማሪ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ አካባቢን የማጽዳት፣ የጎርፍ መከላከያ ግንባታ፣ አቅም ለሌላቸው ማዕድ የማጋራት፣ የደም ልገሳ እና የነፃ ህክምና አገልግሎቶች እንደሚሰጡ ከንቲባዋ አስታውቀዋል። በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ፣ የተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እና የመንገድ ትራፊክ ማሳለጥ ስራዎችን በማከናወን ከተማዋን ለኑሮ ምቹ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቅሷል።
ለዚህ ታላቅ ግንባታ ስኬት የከተማዋ ባለሀብቶች ፈጣን ምላሽ የሰጡ ሲሆን፥ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በላይነህ ክንዴ እና ያደታ ጁነዲን እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ባለ 9 ወለል ህንፃ ለመገንባት ቃል ገብተዋል። በተመሳሳይ ቲኤንቲ ኮንስትራክሽን፣ ግራንድ ሌጋሲ ሃውስ፣ ኢቲ ኦንላይን፣ አብይ ማስረሻ፣ ዴማ ሪልስቴት፣ ቴምር ሪልስቴት፣ ስናፕ ትሬዲንግ፣ ጊፍት ሪልስቴት፣ መሃመድ አድናን እና አሚር በድሩ ቀሪዎቹን ህንፃዎች በጋራ ለመገንባት አጋርነታቸውን ማረጋገጣቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸው ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ| ሰኔ 15/2018 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአራዳ ክፍለ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተጀመረው የቤት ግንባታና የአካባቢ ማደስ ፕሮጀክት፥ የመንግስትን ፖለቲካዊ ቃል ኪዳን ወደ መሬት የመቀየር ስትራቴጂ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ። ከንቲባዋ "የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ሳይሆን በተግባራዊ ምላሽ ነው" ያሉ ሲሆን፥ ይህም ብልፅግና ፓርቲ በምርጫ ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ የአምስት ዓመት እምነት በተሰጠው ማግስት የተጀመረ መሆኑን ገልጸዋል።
በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማ ደረጃ 2,500 ቤቶችን ለመገንባት የታቀደ ሲሆን፥ የዚሁ አካል የሆነውና ከከንቲባ ፅህፈት ቤት በስተጀርባ የሚገነባው የ“አራዳ የበጎነት መንደር” ግንባታ በይፋ ተጀምሯል። ይህ ሜጋ ፕሮጀክት ባለ 9 ወለል 8 ዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃዎችን እና ባለ 4 ወለል ሁለት የገበያ ማዕከላትን ያካተተ ሲሆን፥ ለዘመናት የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በመቀየር ለሰው ልጆች ክብር የሚመጥን ዘመናዊ የጋራ መገልገያ፣ አረንጓዴ ስፍራና የስፖርት ሜዳዎችን ያካተተ መንደር እንደሚሆን ተገልጿል።
ከቤት ግንባታው በተጨማሪ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ አካባቢን የማጽዳት፣ የጎርፍ መከላከያ ግንባታ፣ አቅም ለሌላቸው ማዕድ የማጋራት፣ የደም ልገሳ እና የነፃ ህክምና አገልግሎቶች እንደሚሰጡ ከንቲባዋ አስታውቀዋል። በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ፣ የተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እና የመንገድ ትራፊክ ማሳለጥ ስራዎችን በማከናወን ከተማዋን ለኑሮ ምቹ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቅሷል።
ለዚህ ታላቅ ግንባታ ስኬት የከተማዋ ባለሀብቶች ፈጣን ምላሽ የሰጡ ሲሆን፥ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በላይነህ ክንዴ እና ያደታ ጁነዲን እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ባለ 9 ወለል ህንፃ ለመገንባት ቃል ገብተዋል። በተመሳሳይ ቲኤንቲ ኮንስትራክሽን፣ ግራንድ ሌጋሲ ሃውስ፣ ኢቲ ኦንላይን፣ አብይ ማስረሻ፣ ዴማ ሪልስቴት፣ ቴምር ሪልስቴት፣ ስናፕ ትሬዲንግ፣ ጊፍት ሪልስቴት፣ መሃመድ አድናን እና አሚር በድሩ ቀሪዎቹን ህንፃዎች በጋራ ለመገንባት አጋርነታቸውን ማረጋገጣቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸው ምስጋና አቅርበዋል።
👍1
በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር 2,500 ዘመናዊ ቤቶች ይገነባሉ፡፡
አዲስ አበባ | ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተያዘው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር 2,500 የመኖሪያ ቤቶች ይገነባሉ። የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ አካል የሆነውን ይህንን የቤት ግንባታ ፕሮጀክት፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአራዳ ክፍለ ከተማ 8 ባለ ዘጠኝ ወለል ህንፃዎችን ያካተተ "የበጎነት መንደር" ግንባታን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት፣ "የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ሳይሆን በተግባራዊ ምላሽ ነው" ያሉ ሲሆን፤ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት ብልፅግና ፓርቲ በምርጫ ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ የአምስት ዓመት እምነት በተሰጠው ማግስት የተጀመረ መሆኑንም ገልጸዋል።
ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ከዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃዎች በተጨማሪ ባለ 4 ወለል ሁለት የገበያ ማዕከላትን ያካተተ ነው። የበጎነት መንደሩ ለዘመናት የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በመቀየር ለሰው ልጆች ክብር የሚመጥን ዘመናዊ የጋራ መገልገያዎችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና የስፖርት ሜዳዎችን ያካተተ ይሆናል።
የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ16 ዓበይት ፕሮግራሞችና በ19 ንዑስ መርሃ ግብሮች የሚተገበር ሲሆን፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 5,846 ቤቶችን በመገንባት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 38,898 ነዋሪዎች ማስተላለፍ ተችሏል።
የዘንድሮው የክረምት የቤት ግንባታ መርሃ ግብር ከሌላው ጊዜ የሚለየው፣ የሚገነቡት 2,500 ቤቶች በሙሉ ከሁለት ወለል በላይ መሆናቸው ነው።
አዲስ አበባ | ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተያዘው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር 2,500 የመኖሪያ ቤቶች ይገነባሉ። የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ አካል የሆነውን ይህንን የቤት ግንባታ ፕሮጀክት፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአራዳ ክፍለ ከተማ 8 ባለ ዘጠኝ ወለል ህንፃዎችን ያካተተ "የበጎነት መንደር" ግንባታን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት፣ "የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ሳይሆን በተግባራዊ ምላሽ ነው" ያሉ ሲሆን፤ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት ብልፅግና ፓርቲ በምርጫ ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ የአምስት ዓመት እምነት በተሰጠው ማግስት የተጀመረ መሆኑንም ገልጸዋል።
ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ከዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃዎች በተጨማሪ ባለ 4 ወለል ሁለት የገበያ ማዕከላትን ያካተተ ነው። የበጎነት መንደሩ ለዘመናት የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በመቀየር ለሰው ልጆች ክብር የሚመጥን ዘመናዊ የጋራ መገልገያዎችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና የስፖርት ሜዳዎችን ያካተተ ይሆናል።
የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ16 ዓበይት ፕሮግራሞችና በ19 ንዑስ መርሃ ግብሮች የሚተገበር ሲሆን፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 5,846 ቤቶችን በመገንባት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 38,898 ነዋሪዎች ማስተላለፍ ተችሏል።
የዘንድሮው የክረምት የቤት ግንባታ መርሃ ግብር ከሌላው ጊዜ የሚለየው፣ የሚገነቡት 2,500 ቤቶች በሙሉ ከሁለት ወለል በላይ መሆናቸው ነው።