የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡለትን ሹመቶች አጽድቋል፡፡
በዚሁ መሰረት
1ኛ. አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ፣
2ኛ. አቶ አሰግደዉ ኃ/ጊዮርጊስ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ፣
3ኛ. አቶ ሰለሞን ዲባባ - የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነዉ ተሹመዋል፡፡
በተጨማሪም ምክር ቤቱ ለ2018 ዓ.ም 9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል፡፡
ከዚህ ውስጥ 8 ነጥብ 5 ቢሊየን ብሩ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች በፌደራል መንግስት ለተሰጠ የደመወዝ ድጎማ እንዲሁም 996 ሚሊየን ብሩ ለከተማዋ የልማት ሥራዎች የሚውል መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤው በጥቅሉ 9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀረቡለትን ሹመቶች አጽድቋል፡፡
በዚሁ መሰረት
1ኛ. አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ፣
2ኛ. አቶ አሰግደዉ ኃ/ጊዮርጊስ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ፣
3ኛ. አቶ ሰለሞን ዲባባ - የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነዉ ተሹመዋል፡፡
በተጨማሪም ምክር ቤቱ ለ2018 ዓ.ም 9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል፡፡
ከዚህ ውስጥ 8 ነጥብ 5 ቢሊየን ብሩ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች በፌደራል መንግስት ለተሰጠ የደመወዝ ድጎማ እንዲሁም 996 ሚሊየን ብሩ ለከተማዋ የልማት ሥራዎች የሚውል መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤው በጥቅሉ 9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡
❤3
ምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ዕጩዎች ሹመትን አጸደቀ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ የምክር ቤቱን የፍትሕና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላትን ዕጩዎች ሹመት አጽድቋል፡፡
አቶ በላይ ደጀን በምክር ቤቱ የፍትሕና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነዉ ተሹመዋል፡፡
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክን አቅም እና ተደራሽነት ይበልጥ ለማጠናከር በቀረበዉ ሹመት መሰረት
1ኛ. አቶ ሞገስ ባልቻ - የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ
2ኛ. ነብዩ ባዬ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል
3ኛ. አቶ ሠለሞን ካሳ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል
4ኛ. ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ -የሥራ አመራር ቦርድ አባል
5ኛ. ሚኤሳ ኤሌማ (ዶ/ር)-የሥራ አመራር ቦርድ አባል
6 ኛ. ወ/ሮ ዘሃራ መሃመድ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል ሆነዉ ተሹመዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ የምክር ቤቱን የፍትሕና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላትን ዕጩዎች ሹመት አጽድቋል፡፡
አቶ በላይ ደጀን በምክር ቤቱ የፍትሕና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነዉ ተሹመዋል፡፡
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክን አቅም እና ተደራሽነት ይበልጥ ለማጠናከር በቀረበዉ ሹመት መሰረት
1ኛ. አቶ ሞገስ ባልቻ - የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ
2ኛ. ነብዩ ባዬ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል
3ኛ. አቶ ሠለሞን ካሳ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል
4ኛ. ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ -የሥራ አመራር ቦርድ አባል
5ኛ. ሚኤሳ ኤሌማ (ዶ/ር)-የሥራ አመራር ቦርድ አባል
6 ኛ. ወ/ሮ ዘሃራ መሃመድ - የሥራ አመራር ቦርድ አባል ሆነዉ ተሹመዋል፡፡
❤4
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 የተገነቡ የአቅመ ደካሞችና አረጋውያን ቤቶች ተመርቀው ለተጠቃሚዎች ተላለፉ።
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር የተገነቡ 6 ልፍሎች ያሉት የG+1 ቤት ግንባታው ተጠናቆ ዛሬ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
የህንፃው፦
* የቦታው ስፋት፦230 ካሬ ሜትር
* የክፍሎች ብዛት፦ 30 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ያደረጉ 6 መኖሪያ ክፍሎችን አካቷል።
ይህ ላለፉት ዓመታት በመንግስት ልዩ ትኩረት ሲሰራበት የቆየው የቤት ግንባታ ከቤት እድሳት ተግባር ተነስቶ ዛሬ ላይ ወደ በጎነት መንደር ግዙፍ ፕሮጀክቶች ያደገ ሲሆን ለማኅበራዊ ችግር የተጋለጡ ወገኖቻችንን ህይወት ለመቀየር የተደረገ የከተማችን ትልቅ ስኬት ነው።
አቅመ ደካሞችንና የሀገር ባለውለታዎችን ለመደገፍ ባለሀብቶችንና ማህበረሰቡን በማስተባበር የተጀመሩ ሰው ተኮር ስራዎቻች ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል።
ለዚህ መልካም ተግባር መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እያበረከታችሁ ያላችሁ ባለድርሻ አካላት፣ ተቋማትና ድርጅቶች በሙሉ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን!
አብሮነትና በጎነት ይለምልም!
#kirkos #Voluntarism #HumanCenteredProjects #AddisAbaba #Ethiopia
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር የተገነቡ 6 ልፍሎች ያሉት የG+1 ቤት ግንባታው ተጠናቆ ዛሬ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
የህንፃው፦
* የቦታው ስፋት፦230 ካሬ ሜትር
* የክፍሎች ብዛት፦ 30 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ያደረጉ 6 መኖሪያ ክፍሎችን አካቷል።
ይህ ላለፉት ዓመታት በመንግስት ልዩ ትኩረት ሲሰራበት የቆየው የቤት ግንባታ ከቤት እድሳት ተግባር ተነስቶ ዛሬ ላይ ወደ በጎነት መንደር ግዙፍ ፕሮጀክቶች ያደገ ሲሆን ለማኅበራዊ ችግር የተጋለጡ ወገኖቻችንን ህይወት ለመቀየር የተደረገ የከተማችን ትልቅ ስኬት ነው።
አቅመ ደካሞችንና የሀገር ባለውለታዎችን ለመደገፍ ባለሀብቶችንና ማህበረሰቡን በማስተባበር የተጀመሩ ሰው ተኮር ስራዎቻች ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል።
ለዚህ መልካም ተግባር መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እያበረከታችሁ ያላችሁ ባለድርሻ አካላት፣ ተቋማትና ድርጅቶች በሙሉ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን!
አብሮነትና በጎነት ይለምልም!
#kirkos #Voluntarism #HumanCenteredProjects #AddisAbaba #Ethiopia
በቦሌ ክፍለ ከተማ በህብረተሰብ ተሳትፎ በ112 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የጃክሮስ-ኢቢኤስ የአስፋልት መንገድ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ!
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ጃክሮስ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ መንደር በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ የተገነባው ዘመናዊ የውስጥ ለውስጥ የአስፋልት መንገድ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቋል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አደፍርስ ኮራን ጨምሮ አመራሮች፣ የአካባቢው ባለሀብቶችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ፕሮጀክቱ፦
* 1.35 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ስፋት
* ደረጃውን የጠበቀ የእግረኛ መንገድ እና የአረንጓዴ ስፍራዎችን
* እንዲሁም በኅብረተሰቡ አቅም 112 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል።
* የሕዝብ አቅምን ማስተባበር ከተቻለ ምን ያህል ታላላቅ ለውጦችን ማምጣት እንደሚቻል ማረጋገጫ ነው።
* የአካባቢው ነዋሪዎች ቀደም ሲል በጭቃና በአቧራ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት በዘላቂነት በመቅረፍ፣ ለአካባቢው የንግድና ኢንቨስትመንት መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
#BoleSubCity #Woreda7 #Infrastructure #RoadProject #AddisAbaba #Ethiopia
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ጃክሮስ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ኢንዱስትሪ መንደር በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ የተገነባው ዘመናዊ የውስጥ ለውስጥ የአስፋልት መንገድ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቋል።
በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አደፍርስ ኮራን ጨምሮ አመራሮች፣ የአካባቢው ባለሀብቶችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ፕሮጀክቱ፦
* 1.35 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ስፋት
* ደረጃውን የጠበቀ የእግረኛ መንገድ እና የአረንጓዴ ስፍራዎችን
* እንዲሁም በኅብረተሰቡ አቅም 112 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል።
* የሕዝብ አቅምን ማስተባበር ከተቻለ ምን ያህል ታላላቅ ለውጦችን ማምጣት እንደሚቻል ማረጋገጫ ነው።
* የአካባቢው ነዋሪዎች ቀደም ሲል በጭቃና በአቧራ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን እንግልት በዘላቂነት በመቅረፍ፣ ለአካባቢው የንግድና ኢንቨስትመንት መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
#BoleSubCity #Woreda7 #Infrastructure #RoadProject #AddisAbaba #Ethiopia
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነባ ባለሁለት ወለል ዘመናዊ ፖሊስ ጣቢያ ተመረቀ።
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር በኅብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ እና በመንግስት ትብብር የተገነባ ዘመናዊ የፖሊስ ጣቢያ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ባለሁለት ወለል (G+1) ህንፃ ሆኖ የተገነባው ይህ ጣቢያ፣ ለፖሊስ አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽነትና ቅልጥፍና ምቹ የሆኑ በቂ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎችን አካቶ የያዘ ነው።
በዚሁ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ማህበረሰቡን በማስተባበር የህዝብን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መመለስ መቻሉን አድንቀዋል። የፖሊስ ጣቢያው መገንባት ህብረተሰቡና ፖሊስ በወንጀል ቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ ይበልጥ ተቀራርበውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ ለማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በህዝብና መንግስት የጋራ ቅንጅት የተገኘው የላቀ ስኬት፣ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላምና ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጉዞ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው። አዲሱ የፖሊስ ጣቢያ ወንጀልን ከመቀነስና የህዝብን ደህንነት ከመጠበቅ አንጻር የላቀ ሚና የሚጫወት ነው።
በህዝብና መንግስት ቅንጅት የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን!
#KolfeKeranio #CommunityPolicing #PeaceAndSecurity #AddisAbaba #Ethiopia
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር በኅብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ እና በመንግስት ትብብር የተገነባ ዘመናዊ የፖሊስ ጣቢያ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ባለሁለት ወለል (G+1) ህንፃ ሆኖ የተገነባው ይህ ጣቢያ፣ ለፖሊስ አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽነትና ቅልጥፍና ምቹ የሆኑ በቂ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎችን አካቶ የያዘ ነው።
በዚሁ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ማህበረሰቡን በማስተባበር የህዝብን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ መመለስ መቻሉን አድንቀዋል። የፖሊስ ጣቢያው መገንባት ህብረተሰቡና ፖሊስ በወንጀል ቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ ይበልጥ ተቀራርበውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ ለማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በህዝብና መንግስት የጋራ ቅንጅት የተገኘው የላቀ ስኬት፣ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላምና ልማትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጉዞ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው። አዲሱ የፖሊስ ጣቢያ ወንጀልን ከመቀነስና የህዝብን ደህንነት ከመጠበቅ አንጻር የላቀ ሚና የሚጫወት ነው።
በህዝብና መንግስት ቅንጅት የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን!
#KolfeKeranio #CommunityPolicing #PeaceAndSecurity #AddisAbaba #Ethiopia
👍3❤1