የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
823 subscribers
2.14K photos
47 videos
265 links
Download Telegram
እባክዎን ከሐሰተኛ ዜናዎች እና የተሳሳቱ መረጃዎች ስርጭት ይጠበቁ!

‎ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተብሎ የሚደርስዎትን ማንኛውም ‎ይፋዊ መልዕክት ከማጋራትዎ በፊት ሁልጊዜም በጽሕፈት ቤቱ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና ድህረ-ገጽ በመግባት፣ ትክክለኛነቱን እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን።

Please remain vigilant against the spread of fake news and misinformation.

To ensure authenticity, always cross-check any official messages attributed to the Office of the Prime Minister (PMO) against the office’s official social media pages and website before sharing.

Facebook: https://www.facebook.com/share/1DbRTPiYUF/?mibextid=wwXIfr

X: https://x.com/pmethiopia?s=21

Website: https://pmo.gov.et

#PMOEthiopia
3👍1
ከትግራይ ክልል ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ የምክክር ኮምሽን የአጀንዳ ልየታ ጉባኤ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ የልማት ሥራዎች ጎበኙ!

በምክክር ኮምሽን አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የሶስት ቀናት ውይይት ሲጠናቀቅ፤ በአጀንዳ ልየታው ለመሳተፍ ከትግራይ ክልል የመጡ ከሶስት መቶ (300) በላይ የሚሆኑ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተሳታፊዎች፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ኮርደር ልማት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የወንዝ ዳርቻ ልማት እና በመልሶ ማልማት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

ጎብኝዎቹ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከማሳደግ ባሻገር ዓለምዓቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልፀዋል ። እንዲሁም “ይህን መሰል የመሰለ የልማት ስራ በተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች መድገም እንደሚያስፈልግ፣ ይህንኑ ሃላፊነትም ወጣቱ ትውልድ ወስዶ የመፈፀም ሃላፊነት እንዳለበት” በቁጭት ገልፀዋል።

ተሳታፊዎቹ፥ “ሰላም የሁሉም መሰረት እንደሆነ፣ ለዚህ በቂ ማሳያም የላቀ የስራ ባህል በመገንባት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት፣ አለማቀፍ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለውን አዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች እየታዩ ያሉ የልማት ስራዎች በቂ ማሳያ ነው” ሲሉ ገልፀዋል። በአዲስ አበባ በተመለከቱት ሁለንተናዊ የልማት ስራዎች መደሰታቸውንም አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ዛሬ መርቀን ከፍተናል።
‎በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው።

የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን፣ እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካትቷል። በተጨማሪም ተቋሙ ለድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነትና ምላሽ የመስጠት አቅምን በመገንባት ረገድ እንደ ማገር ሆኖ ያገለግላል።
‎ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍31
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት ተደርጓል።

Via PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የአቅርቦት ችግር በመቅረፍ ረገድ የሸማቾች ማህበራት ዋነኛ መፍትሄ ናቸው- አቶ ጃንጥራር አባይ

በልደታ ክፍለ ከተማ የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ አምራችና ሸማቹን የሚያገናኝ ባዛር እና የገበያ ማዕከል የመክፈቻ መርሐ ግብር ተከናውኗል ፡፡

ባዛሩን ከፍተው ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ የአቅርቦት ችግር በሚኖርበት ወቅት የሸማቾች ማህበራት ዋነኛ መፍትሄ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭትና በነዳጅ እጥረት ምክንያት የትራንስፖርት ዋጋ መጨምሩን ተከትሎ፣ በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስ አስተዳደሩ ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በመዲናችን አዲስ አበባ መጪው የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የንግድና ባዛር መርሀ ግብር በዛሬው እለት በይፋ ተከፈተ

በመዲናችን በ11ዱም ክፍለ-ከተሞች መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የንግድና ባዛር መርሀ ግብር በዛሬው እለት በይፋ ተከፍቷል፡፡

ንግድና ባዛሩ የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል እና የገበያ ዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ያለመ ይህም ከተማ አሰተዳደሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸዉ ተግባራት አንዱ እና ተጠናክሮ የቀጠለ ዉጤታማ ስራ ነዉ፡፡

በተጨማሪም ህብረተሰቡ በአቅራቢያው የበዓል መጠቀሚያ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ የሚያስችል ሲሆን ህብረተሰቡን ካላስፈላጊ ወጪ ለማዳን በከተማዋ በአምስቱ የገበያ ማዕከላት ጭምር የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በጥራት እየቀረቡ ይገኛሉ፡፡

ነጋዴው ማህበረሰብ የተፈጠረለትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ጥራት ያለዉ ምርት እንዲያቀርብ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸጥ ሸማቹም አቅሙን ባገነዘበ መልክ በተዘረጋለት ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት ተጠቃሚ እንዲሆን ከተማ አስተዳደሩ ጥሪዉን ያቀርባል፡፡
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ።

አምባሳደር ቆንጂት ከልጅነት እስከ ዕውቀት ኢትዮጵያን በዲፕሎማትነት በማገልገል፣ ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥለው ሁለተኛዋ ሴት የኢትዮጵያ አምባሳደር ናቸው። ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን። ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል።

ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እና ለመላ ኢትዮጵያውያን መጽናናት እመኛለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
በአንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን እየገለፃኩ፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እና ለመላዉ ኢትዮዽያዊያን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።

Hangafa diploomaatii Itoophiyaa Ambaasaaddar Qoonjiit Sina-giyoorgis lubbuun boqachuusaaniitti gadda guddaa natti dhaga'ame ibsachaa; maatii, firoottan, hiriyoota hojii isaanii fi guutuu uummata Itoophiyaaf maqaa koofi bulchiinsa magaalaatiin jajjabina onneerraa maddeen hawwa.

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
3
የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት የሚረዱ የገቢያ ማዕከላት በአዲስ አበባ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአምስቱም የከተማይቱ መግቢያ በሮች የመሰረታዊ ሸቀጦችን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት የሚረዱ የግብርና ምርቶች መሸጫ ገቢያ ማዕከላት ገንብቶ ለአገልግሎት አውሏል፡፡ ማዕከላቱ በላፍቶ ቁጥር1 እና 2፣አቃቂ ቃሊቲ፣ ለሚ ኩራ እና ኮልፌ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ እና ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ናችው፡፡

ከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነትና ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት ችግሩን ለማስቀረትና ገበያውን ለማረጋጋት ከወሰዳቸው ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች መካከል ግንባር ቀደም እና ለነዋሪው ትልቅ እፎይታን የሰጠ ተግባር ነው፡፡

በነዚህ የገቢያ ማዕከላት በሌማት ትሩፋትና በከተማ ግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ህብረተሰቡ ከሸማችነት ወደ አምራችነት እንዲሸጋገር ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ተችሏል፡፡

በዚህም ህገወጥ ንግድና ደላላን በማስቀረት የመሰረታዊ ሸቀጦችን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት የሚረዱ የግብርና ምርቶች በገበያ ማዕከላቱ በስፋት እንዲሰራጩ አስችሏል፡፡
👍31
ከመሸጋገሪያ ወደ ማዘውተሪያ የተቀየረችው አዲስ አበባ

ከተማችን አዲስ አበባ ደረጃቸውን የጠበቁ ውብ የመዝናኛ የማዘውተሪያ ስፍራዎችን መገንባቷ ለቱሪስቱ አዲስ እይታን ለነዋሪው ደግሞ ውብ ማዘውተሪያን እያበረከተች ትገኛለች::

ይህ ደግሞ ከዚህ ቀደም ከተማዋ ወደሌሎች ሀገራት መተላለፊያ ብቻ አድርጓት የነበረውን ታሪክ በመቀየር መዳረሻ እሆነች እንድትመጣ አድርጓታል፡፡

ከታሪክና ከተፈጥሮ ባለፈ ወደ ልምድና መዳረሻ እየተቀየረች ያለችው ከተማችን የቱሪዝም ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ለቱሪዝም መነቃቃት የመጀመሪያው የባህልና የታሪክ ሀብት በመሆኑ ከተማችን ይህንን በተግባር እየገለጠች ሲሆን በተጨማሪም የደህንነትና የሰላም ዋስትና የመሰረተ ልማት ግንባታን በመገንባትና በማረጋገጥ ለቱሪስቶች ቆይታቸውን ማራኪ በማድርግ እንዲያራዝሙ እያደረገች ነው፡፡

በከተማዋ የተገነቡት እንደ አንድነት እና እንጦጦ ፓርክ ያሉ ፕሮጀክቶች ከተማዋን አረንጓዴ ከማልበሳቸው ባለፈ፣ የቱሪስቶችን ቆይታ የሚያራዝሙና ለቤተሰብ ምቹ የሆኑ የገጽታ ግንባታ ውጤቶች ሆነዋል፡፡

በተጨማሪም እንደ የሳይንስ ሙዚየምና የታሪክ ማዕከላት መገንባታቸው የኢትዮጵያን ጥንታዊ ጥበብ ከዘመናዊ የቴክኖሎጂ ግስጋሴ ጋር በማጣመር፣ ለጎብኚዎች የተሟላ እውቀትና መዝናኛ የሚሰጡ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስፍራዎች አድርጓቸዋል፡፡

ይህም ይህችን ውብ ከተማ በቱሪዝም እና በቱሪስት እንቅስቃሴ ከመሻጋገሪያ ወደ ማዘውተሪያ እየቀየራት መሆኑን እያስመሰከረች ነው፡፡
👍1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ዛሬ መጪውን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ፤ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው የአገር ባለውለታ አረጋውያንና በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የመንግስት ሰራተኞች በአጠቃላይ  ከ233 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖቻችን ማዕድ አጋርተናል።

ይህ ተግባር በከተማችን የማዕከል መስሪያ ቤቶች፣ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እየተከናወነ  ያለ በጎ ተግባር ነው።
በሁሉም በዓላት የምናደርገው የማዕድ ማጋራት፤ ድጋፍ የሚሹ የከተማችን ነዋሪዎችን  “ምን ጎደለ?" ብለን  በመመልከትና በመጠየቅ ክፍተታቸውን የምንሞላበት  ለነዋሪዎቻችን ያለንን ክብር የገለፅንበት ሰው ተኮር ተግባር ነው።
ማዕድ ከማጋራት ባለፈ አሁን ላይ በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭትና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ የሚከሰተውን ጊዜያዊ የኑሮ ጫና ለማቃለልና የገበያ ጉድለትን ለመሙላት፣ ከፍተኛ በጀት መድበን መሰረታዊ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ እያደረግን እንገኛለን። በዚህም የምርት እጥረት እንዳያጋጥም በሰራነው ሥራ፣ በከተማችን የተረጋጋ የገበያ ሁኔታ እንዲሰፍን ተደርጓል።

ወቅታዊ ችግሮችን ለመሻገር የምናከናውናቸው እነዚህ ተግባራት በሙሉ ከለውጡ ወዲህ የጀመርነው  የ"ሰው ተኮር" ሥራዎቻችን አካል ናቸው።
አዲስ አበባ ለሀብታሙም ለድሃውም፣ ለሁሉም እኩል የተመቸች ፣ ስራዎቻችንም  ማንንም ያልዘነጉ አካታች እንዲሆኑ እየሰራን ሲሆን፤ ከተማዋ እየተቀየረችና እየተለወጠችበት ያለው ልማት በሰዉ ኑሮና አኗኗር  ላይ ለውጥ  እያመጣ ያለ ነው።

"መስጠት አያጎድልም" ብለን ባደረግንላቸው ጥሪ መሰረት  በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ለሚደረገው ማዕድ ማጋራት ለተባበሩን ልበ ቀና ባለሀብቶች፣ እንዲሁም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖቻቸው ሁሌም እየተሸከሙ  በጉልበታቸው በበጎ ፈቃደኝነት እያገለገሉ ላሉ ወጣቶቻችን በሙሉ በራሴና በነዋሪዎቻችን ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ። በተለይም ዛሬ በከንቲባ ፅ/ቤት ያካፈልነውን ያቀረቡልን  Jospong Trading 15 ሚሊዮን ብር፣. አቶ ጀማል (ሚድሮክ) 10 ሚሊዮን ብር፣ የኢትዮዽያ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን 7 ሚሊዮን ብር፣ አቶ በላይነህ ክንዴ (BKG) 5 ሚሊዮን ብር፣. አትሌት ዮሐንስ ቢፋ  2.9 ሚሊዮን ብር፣ አቶ ተካበ ሙሉ 500 ሺህ ብር በመለገሳቸዉ ከልብ እናመሰግናለን።

የትንሳኤ በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ መዳን ፍቅሩን እስከ መስቀል የገለጸበት እና በትንሳኤ የምስራች የተበሰረበት በመሆኑ፣ በዓሉን ስናከብር በታላቅ ፍቅር፣ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖቻችን ያለንን መተሳሰብ በተግባር የምንገልጽበት አንዳችን ለሌላችን የደስታ፣ የሰላም፣ የአብሮነት  ምክንያት እንሁን እያልኩ፣  በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ።
መልካም በዓል!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1