በአዲስ አበባ ከተማ ማኅበረሰቡን በስፋት ያሳተፉ የአካባቢ መሠረተ ልማት ግንባታዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በተያዘው የበጀት ዓመት የታቀዱ የሰቤዝ መንገድ ልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ፣ በአሁኑ ወቅት የኮብልስቶን ንጣፍ ሥራዎች በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በስፋት እየተተገበሩ ነው።
እነዚህ የልማት ሥራዎች "የራስን ችግር በራስ የመፍታት" ከተማ አቀፍ እሳቤን በተግባር እያሳዩ ያሉ ውጤቶች ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው በሚከናወኑ የልማት ተግባራት ላይ በቀጥታ እንዲሳተፉ በማድረግ፣ የባለቤትነት ስሜት እንዲሰማቸውና የጋራ ችግሮቻቸውን በጋራ ጥረት እንዲፈቱ ዕድል ፈጥረዋል። ይህም ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ይበልጥ ተስማሚ የማድረግ ስትራቴጂ አንዱ አካል ነው።
የአካባቢው ማኅበረሰብ ከልማት ጠባቂነት መንፈስ ወጥቶ የራሱን አካባቢ ለማልማት እያሳየ ያለው ተነሳሽነት፣ ለዓመታት ሲስተዋሉ የነበሩ የመልካም አስተዳደርና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ አስችሏል። ነዋሪዎች በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በጉልበታቸው እያደረጉት ያለው ንቁ ተሳትፎ የልማት ሥራዎች እንዲፋጠኑና ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ እያደረገ ይገኛል።
የመንግሥትና የሕዝብ ቅንጅት ይበልጥ እንዲጠናከር ለማድረግም፣ መንግሥት ለነዚህ የሕዝብ ተሳትፎ ፕሮጀክቶች የ35 በመቶ የፋይናንስ ድጎማ እያደረገ ይገኛል። ይህ ድጋፍ ማኅበረሰቡ የጀመራቸው የልማት ጥረቶች ግባቸውን እንዲመቱና የፋይናንስ ክፍተቶች እንዳያጋጥሙ ትልቅ አቅም ሆኗል።
በተያዘው የበጀት ዓመት የታቀዱ የሰቤዝ መንገድ ልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ፣ በአሁኑ ወቅት የኮብልስቶን ንጣፍ ሥራዎች በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በስፋት እየተተገበሩ ነው።
እነዚህ የልማት ሥራዎች "የራስን ችግር በራስ የመፍታት" ከተማ አቀፍ እሳቤን በተግባር እያሳዩ ያሉ ውጤቶች ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው በሚከናወኑ የልማት ተግባራት ላይ በቀጥታ እንዲሳተፉ በማድረግ፣ የባለቤትነት ስሜት እንዲሰማቸውና የጋራ ችግሮቻቸውን በጋራ ጥረት እንዲፈቱ ዕድል ፈጥረዋል። ይህም ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ይበልጥ ተስማሚ የማድረግ ስትራቴጂ አንዱ አካል ነው።
የአካባቢው ማኅበረሰብ ከልማት ጠባቂነት መንፈስ ወጥቶ የራሱን አካባቢ ለማልማት እያሳየ ያለው ተነሳሽነት፣ ለዓመታት ሲስተዋሉ የነበሩ የመልካም አስተዳደርና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ አስችሏል። ነዋሪዎች በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በጉልበታቸው እያደረጉት ያለው ንቁ ተሳትፎ የልማት ሥራዎች እንዲፋጠኑና ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ እያደረገ ይገኛል።
የመንግሥትና የሕዝብ ቅንጅት ይበልጥ እንዲጠናከር ለማድረግም፣ መንግሥት ለነዚህ የሕዝብ ተሳትፎ ፕሮጀክቶች የ35 በመቶ የፋይናንስ ድጎማ እያደረገ ይገኛል። ይህ ድጋፍ ማኅበረሰቡ የጀመራቸው የልማት ጥረቶች ግባቸውን እንዲመቱና የፋይናንስ ክፍተቶች እንዳያጋጥሙ ትልቅ አቅም ሆኗል።
❤4👍1
የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላትን ለአገልግሎት ምቹ የማድረግ ስራ እየተከናወነ ነው
📌 የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በከተማዋ የሚገነቡ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላት ደረጃቸውን የጠበቁ እና ለህዝብ አገልግሎት ምቹ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።
📌 በከተማዋ ባሉ 4,350 ብሎኮች ውስጥ ከ834 በላይ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን፣ አንድ ማዕከል ከ1 እስከ 6 የሚደርሱ ብሎኮችን በማቀፍ የጸጥታና የሰላም ስራዎችን ያከናውናል።
📌 የማዕከላቱ ዋና ዋና ጥቅሞች፦
👉ለማህበረሰቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት፣
👉የአካባቢን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ፣
👉የወንጀል ድርጊቶችን አስቀድሞ መከላከልና ጥቆማዎችን መቀበል፣
👉ማህበራዊ አንድነትንና የህዝብ ተሳትፎን ማጠናከር።
📌 ኮሚሽኑ ማዕከላቱን ገንብቶ የማስረከብ፣ ከብሎክ አመራሮችና ከነዋሪዎች ጋር የማስተሳሰር እንዲሁም የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን በቅንጅት እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ ፀሀይ ኪባሞ ገልጸዋል።
#የማህበረሰብ_አቀፍ_ፖሊስ #ሰላምና_ጸጥታ #የህብረተሰብ_ተሳትፎ #አዲስ_አበባ
📌 የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በከተማዋ የሚገነቡ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላት ደረጃቸውን የጠበቁ እና ለህዝብ አገልግሎት ምቹ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።
📌 በከተማዋ ባሉ 4,350 ብሎኮች ውስጥ ከ834 በላይ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን፣ አንድ ማዕከል ከ1 እስከ 6 የሚደርሱ ብሎኮችን በማቀፍ የጸጥታና የሰላም ስራዎችን ያከናውናል።
📌 የማዕከላቱ ዋና ዋና ጥቅሞች፦
👉ለማህበረሰቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት፣
👉የአካባቢን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ፣
👉የወንጀል ድርጊቶችን አስቀድሞ መከላከልና ጥቆማዎችን መቀበል፣
👉ማህበራዊ አንድነትንና የህዝብ ተሳትፎን ማጠናከር።
📌 ኮሚሽኑ ማዕከላቱን ገንብቶ የማስረከብ፣ ከብሎክ አመራሮችና ከነዋሪዎች ጋር የማስተሳሰር እንዲሁም የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን በቅንጅት እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ ፀሀይ ኪባሞ ገልጸዋል።
#የማህበረሰብ_አቀፍ_ፖሊስ #ሰላምና_ጸጥታ #የህብረተሰብ_ተሳትፎ #አዲስ_አበባ
❤3
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
የበጎነት ብርሐን በሰው ተኮር ልማት ሲገለጥ!
ወይዘሮ ዙፋን ገብረመስቀል በእርጅና አጎንብሳ፣ የጉስቁልና ጥላ ባጠላባት ደሳሳ ጎጆ ውስጥ ሆና፣ በጨለማው ስንጥቅ በኩል የነገን ፋና የምታማትር የትዕግሥት ተምሳሌት ነች። ኑሮዋን በጉሊት ንግድ ስታቃና የኖረችው ይህች ብርቱ ሴት፣ በምስቅልቅል ሕይወት ውስጥ ሆና የነገን ብርሃን ትናፍቅ ነበር።
ይሁን እንጂ የከተማዋ መሪዎችና የበጎነት መላእክት የሆኑት በጎ ፈቃደኞች፣ ይህችን በፈራረሰ መጠለያ ውስጥ ያለች ነፍስ በሰብዓዊነት ዓይን ተመለከቷት። የከተማዋ አስተዳደር "ሰው ተኮር" ልማት ለሰውነት ቅድሚያ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለጋስ እጆች የተገነባውን የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ቁልፍ ለወይዘሮ ዙፋን አስረከቡ። በዚያች ቅጽበት፣ ለዘመናት በድህነት የታጠረው ዓለሟ በድንገት በብርሃን ተጥለቀለቀ፤ ያ ያዘመመና የጎሰቆለ ሕይወቷም ለታሪክ ማጣቀሻነት ተሸኝቶ ወደ ክብር ማማ ተሸጋገረች።
በጎነት የተሰበረን ልብ የሚጠግንና የወደቀን ሕይወት የሚያቀና የሰብዓዊነት ድልድይ እንደሆነ ዙፋንና መሰል በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ሕያው ምስክሮች ናቸው። ዛሬ ወይዘሮ ዙፋን በኩራት ቀና ብላ የምትራመድ፣ የነገ ተስፋ የሆኑ ልጆቿን በጥበብ የምታሳድግ ብርቱ እናት ሆናለች። ይህም በጎነት በልዩ ልዩ አቅጣጫዎች እየፈሰሰ፣ እንደ ዙፋን ያሉ ብዙዎችን ከጉስቁልና አዘቅት አውጥቶ ወደ ክብር አሸጋግሯቸዋል።
የሰው ልጅ ቀና ልብና ርኅራኄ ሲታከልበት፣ ልማት ከኮንክሪትና ከድንጋይ ድርደራ አልፎ የሕይወት እስትንፋስን የሚዘራ ሰውን የሚያስቀድም ይሆናል። የከተማችን የልማት ስልትም በጎ ፈቃድን በዜጎች ማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ እንደ ባህል በማፍሰስ፣ የማኅበረሰቡን የኑሮ ሸክም የሚያቀልና ሰብዓዊነትን የሚያነግሥ ጥልቅ ፍልስፍና ነው። በዚህም መሠረት ዙፋንን ያነሳው በጎነት፣ የከተማዋን ሰብዓዊ ልማት ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሻግር የድል አርማ ሆኖ ይቀጥላል።
በጎነት ይለምልም!
#አዲስአበባ #በጎፈቃድ #የኅብረተሰብተሳትፎ #ኢትዮጵያ #Volunteerism #AddisAbaba #SocialImpact
ወይዘሮ ዙፋን ገብረመስቀል በእርጅና አጎንብሳ፣ የጉስቁልና ጥላ ባጠላባት ደሳሳ ጎጆ ውስጥ ሆና፣ በጨለማው ስንጥቅ በኩል የነገን ፋና የምታማትር የትዕግሥት ተምሳሌት ነች። ኑሮዋን በጉሊት ንግድ ስታቃና የኖረችው ይህች ብርቱ ሴት፣ በምስቅልቅል ሕይወት ውስጥ ሆና የነገን ብርሃን ትናፍቅ ነበር።
ይሁን እንጂ የከተማዋ መሪዎችና የበጎነት መላእክት የሆኑት በጎ ፈቃደኞች፣ ይህችን በፈራረሰ መጠለያ ውስጥ ያለች ነፍስ በሰብዓዊነት ዓይን ተመለከቷት። የከተማዋ አስተዳደር "ሰው ተኮር" ልማት ለሰውነት ቅድሚያ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለጋስ እጆች የተገነባውን የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ቁልፍ ለወይዘሮ ዙፋን አስረከቡ። በዚያች ቅጽበት፣ ለዘመናት በድህነት የታጠረው ዓለሟ በድንገት በብርሃን ተጥለቀለቀ፤ ያ ያዘመመና የጎሰቆለ ሕይወቷም ለታሪክ ማጣቀሻነት ተሸኝቶ ወደ ክብር ማማ ተሸጋገረች።
በጎነት የተሰበረን ልብ የሚጠግንና የወደቀን ሕይወት የሚያቀና የሰብዓዊነት ድልድይ እንደሆነ ዙፋንና መሰል በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ሕያው ምስክሮች ናቸው። ዛሬ ወይዘሮ ዙፋን በኩራት ቀና ብላ የምትራመድ፣ የነገ ተስፋ የሆኑ ልጆቿን በጥበብ የምታሳድግ ብርቱ እናት ሆናለች። ይህም በጎነት በልዩ ልዩ አቅጣጫዎች እየፈሰሰ፣ እንደ ዙፋን ያሉ ብዙዎችን ከጉስቁልና አዘቅት አውጥቶ ወደ ክብር አሸጋግሯቸዋል።
የሰው ልጅ ቀና ልብና ርኅራኄ ሲታከልበት፣ ልማት ከኮንክሪትና ከድንጋይ ድርደራ አልፎ የሕይወት እስትንፋስን የሚዘራ ሰውን የሚያስቀድም ይሆናል። የከተማችን የልማት ስልትም በጎ ፈቃድን በዜጎች ማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ እንደ ባህል በማፍሰስ፣ የማኅበረሰቡን የኑሮ ሸክም የሚያቀልና ሰብዓዊነትን የሚያነግሥ ጥልቅ ፍልስፍና ነው። በዚህም መሠረት ዙፋንን ያነሳው በጎነት፣ የከተማዋን ሰብዓዊ ልማት ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሻግር የድል አርማ ሆኖ ይቀጥላል።
በጎነት ይለምልም!
#አዲስአበባ #በጎፈቃድ #የኅብረተሰብተሳትፎ #ኢትዮጵያ #Volunteerism #AddisAbaba #SocialImpact
❤4👍1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ከቤት እድሳት ወደ በጎነት መንደር ምስረታ ያደገ እምርታ!
የአንዲት ከተማ ትልቁ ሀብቷ የመሰረተ ልማት ግንባታዎቿ ብቻ ሳይሆኑ በውስጧ የሚኖሩ ዜጎች ሰብአዊ ክብርና ደህንነት ነው። የከተማ አስተዳደሩ "ሰው ተኮር" ልማትን የስትራቴጂው ማዕከል በማድረግ፣ ነዋሪዎችን ከችግርና ከጎስቁልና ህይወት የሚያወጡ ግዙፍ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ይህ ስራ ዛሬ ላይ ከመደበኛ የቤት እድሳት ተነስቶ፣ ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ "የበጎነት መንደሮችን" ወደ መገንባት ተሸጋግሯል።
የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት አነሳሽ (Initiative) ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሲሆኑ በአዋሬ አካባቢ ለዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ቤት በመገንባት ከተጀመረው ተግባር ነው። ይህ አርአያነት ያለው ተግባር በከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጥቶት፣ ወደ ላቀ አፈፃፀምና ውጤት በመቀየር ዛሬ ላይ በመላው ከተማዋ ከ5 በላይ ግዙፍ የበጎነት መንደሮች እንዲፈጠሩ መሰረት ሆኗል።
ለዚህ ስኬታማ የልማት አቅጣጫ የልደታ በጎነት መንደርን እንደ ዋነኛ አብነት መጥቀስ ይቻላል። በተለምዶ "ቆርቆሮ ሰፈር" በሚል ስያሜ ይታወቅ የነበረውና ለኑሮ እጅግ ምቹ ያልነበረው አካባቢ፣ ዛሬ በሰው ተኮር ልማት አማካኝነት መልክ ቀይሮ የትውልድ አሻራ ወደሚያርፍበት ዘመናዊ መንደርነት ተቀይሯል። ይህ ለውጥ የአካባቢውን ገጽታ ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎቹን የስነ-ልቦና እና የማህበራዊ ህይወት ደረጃ ከፍ ያደረገ ነው።
በዚህ በልደታ በጎነት መንደር ውስጥ እያንዳንዳቸው ዘጠኝ ወለል ያላቸው 11 ዘመናዊ ህንፃዎችና 967 ቤቶች ተገንብተው ለነዋሪዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል። ግንባታው ዜጎች በሰውነታቸው ሊያገኙ የሚገባውን ክብርና ምቾት እንዲያገኙ ታስቦ የተሰራ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች የከተማ አስተዳደሩ ለዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳዩ ህያው ምስክሮች ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ እየተከተለው ያለው የልማት አቅጣጫ ሰውን ያላገለለና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ ነው። ከአዋሬ የተጀመረው የበጎነት ጥንስስ፣ ዛሬ በልደታና በሌሎችም አካባቢዎች በግዙፍ ህንፃዎችና በተሟላ መሰረተ ልማት ታጅቦ "የበጎነት መንደር" ሆኖ አብቧል። ይህ ጉዞ ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹና በጎነት ባህል የሆነባት የሰብአዊነት መገለጫ ወደመሆን ከፍ ያደረጋት ታሪካዊ ክንውን ነው።
የአንዲት ከተማ ትልቁ ሀብቷ የመሰረተ ልማት ግንባታዎቿ ብቻ ሳይሆኑ በውስጧ የሚኖሩ ዜጎች ሰብአዊ ክብርና ደህንነት ነው። የከተማ አስተዳደሩ "ሰው ተኮር" ልማትን የስትራቴጂው ማዕከል በማድረግ፣ ነዋሪዎችን ከችግርና ከጎስቁልና ህይወት የሚያወጡ ግዙፍ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ይህ ስራ ዛሬ ላይ ከመደበኛ የቤት እድሳት ተነስቶ፣ ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ "የበጎነት መንደሮችን" ወደ መገንባት ተሸጋግሯል።
የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት አነሳሽ (Initiative) ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሲሆኑ በአዋሬ አካባቢ ለዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ቤት በመገንባት ከተጀመረው ተግባር ነው። ይህ አርአያነት ያለው ተግባር በከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጥቶት፣ ወደ ላቀ አፈፃፀምና ውጤት በመቀየር ዛሬ ላይ በመላው ከተማዋ ከ5 በላይ ግዙፍ የበጎነት መንደሮች እንዲፈጠሩ መሰረት ሆኗል።
ለዚህ ስኬታማ የልማት አቅጣጫ የልደታ በጎነት መንደርን እንደ ዋነኛ አብነት መጥቀስ ይቻላል። በተለምዶ "ቆርቆሮ ሰፈር" በሚል ስያሜ ይታወቅ የነበረውና ለኑሮ እጅግ ምቹ ያልነበረው አካባቢ፣ ዛሬ በሰው ተኮር ልማት አማካኝነት መልክ ቀይሮ የትውልድ አሻራ ወደሚያርፍበት ዘመናዊ መንደርነት ተቀይሯል። ይህ ለውጥ የአካባቢውን ገጽታ ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎቹን የስነ-ልቦና እና የማህበራዊ ህይወት ደረጃ ከፍ ያደረገ ነው።
በዚህ በልደታ በጎነት መንደር ውስጥ እያንዳንዳቸው ዘጠኝ ወለል ያላቸው 11 ዘመናዊ ህንፃዎችና 967 ቤቶች ተገንብተው ለነዋሪዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል። ግንባታው ዜጎች በሰውነታቸው ሊያገኙ የሚገባውን ክብርና ምቾት እንዲያገኙ ታስቦ የተሰራ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች የከተማ አስተዳደሩ ለዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳዩ ህያው ምስክሮች ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ እየተከተለው ያለው የልማት አቅጣጫ ሰውን ያላገለለና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ ነው። ከአዋሬ የተጀመረው የበጎነት ጥንስስ፣ ዛሬ በልደታና በሌሎችም አካባቢዎች በግዙፍ ህንፃዎችና በተሟላ መሰረተ ልማት ታጅቦ "የበጎነት መንደር" ሆኖ አብቧል። ይህ ጉዞ ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹና በጎነት ባህል የሆነባት የሰብአዊነት መገለጫ ወደመሆን ከፍ ያደረጋት ታሪካዊ ክንውን ነው።
❤2
❤2
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ለበጎነት የተዘረጉ ለጋስ እጆች!
በከተማችን የጤና ተቋማት ውስጥ ሌት ተቀን የሚታይ አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ እርሱም የሕክምና ባለሙያዎቻችን ለሕሙማን ፈውስ የሚያሳዩት ተከታታይነት ያለው ትጋትና ርኅራኄ ነው። ሆኖም በነዚህ የፈውስ ማዕከላት ውስጥ ሕክምናውን በጽናት የሚከታተሉ፣ ነገር ግን በቁሳቁስና በአስታማሚ እጥረት የሚፈተኑ ጥቂት ወገኖች መኖራቸው አይካድም። ይህን ክፍተት ለመሙላትና የሐኪሞችን ድካም በበጎነት ለማገዝ የቆረጡ ተቋማትና በጎ ፈቃደኞች መኖራቸው ደግሞ ለከተማችን ትልቅ ኩራት ነው።
ከነዚህም መካከል ታፍ ኢነርጂስ ይጠቀሳል። ታፍ ኢነርጂስ ነዳጅና ቅባቶችን በማቅረብ ብቻ የሚታወቅ ተቋም አይደለም፤ ከዚያ ይልቅ የሰውን ልጅ ችግር ተረድቶ "ለወገኔ ምን ላድርግ?" የሚል የቆሰሉ ልቦችን ጠጋኝ እንጂ። ዛሬ ላይ ተቋሙ 80 አቅመ ደካሞችን በቋሚነት ይደገፋል። ከእነዚህም መካከል ነገ የአገር ተረካቢ የሆኑ 10 ሕፃናት ይገኙበታል። እነዚህ ሕፃናት ዛሬ የታፍ ኦይልን እጅ ይዘው ትምህርታቸውን ሲከታተሉ፣ አረጋውያኑም የዕለት ጉርሳቸውን ሳያጡ በክብር ሲኖሩ ማየት የተቋሙ ትልቁ ትርፍ ነው።
ድርጅቱ ረዳትና አስታማሚ አጥተው በዘውዲቱ ሆስፒታል ለሚገኙ ሕሙማን ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፣ የተቋሙ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መቅደስ አሰፋ "ረዳት የሌላቸውን ወገኖች መርዳት መቻላችን ትልቅ የሕሊና እርካታ ሰጥቶናል" ሲሉ ታፍ ኢነርጂስ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በሚገባ ተረድቶ በተግባር የሚፈጽም ተቋም መሆኑን አረጋግጠዋል። ታፍ ኢነርጂስ ማኅበራዊ ኃላፊነትን እንደ ግዴታ ሳይሆን እንደ ሰብአዊ ጥሪም በመቁጠር፣ ሌሎች የግል ተቋማት የዚህ ቅዱስ ተግባር ተካፋይ እንዲሆኑ አርአያነቱን በተግባር አሳይቷል።
ኮሚሽኑ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ባከናወናቸው ከ15 በላይ በሚሆኑ የበጎ ፈቃድ ፕሮግራሞች በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወይዘሮ አስራ ንጉሴ እንደ ታፍ ኢነርጂስ ያሉ ልበ-ቀና ድርጅቶችን በማስተባበር ለአቅመ ደካሞች ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን ከመገንባት ጀምሮ እስከ ሕሙማን ድጋፍ ድረስ የተከናወኑት ተግባራት የማኅበረሰቡ የመረዳዳት ዕሴት ማደጉን አመላካች እንቅስቃሴ መሆኑን በአንክሮ ገልጸዋል።
በጎነት ዛሬ የምንዘራውና ነገ የምናጭደው የሰላም ሰብል ነው ያሉት ኮሚሽነሯ፤ ሁላችንም በጋራ ከቆምን፣ በአዲስ አበባ ውስጥ ማንም አቅመ ደካማ ብቻውን አይሆንም፤ ማንም ሕመምተኛም ያለ ረዳት አይቀርም ሲሉ አክለዋል፡፡
የዘውዲቱ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ቴዎድሮስ አቡሌ በበኩላቸው በጤና ተቋማት ውስጥ ረዳት ለሌላቸው ወገኖች የሚደረግ ማንኛውም ድጋፍ ከመድኃኒት እኩል ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፣ ይህ በከተማ አስተዳደሩና በበጎ ፈቃደኞች የሚከናወነው "በጎነት በሆስፒታል" ንቅናቄ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#በጎነት #አዲስአበባ #ታፍኢነርጂስ #TaffEnergies #ሰብአዊነት #ኢትዮጵያ #AddisAbaba
በከተማችን የጤና ተቋማት ውስጥ ሌት ተቀን የሚታይ አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ እርሱም የሕክምና ባለሙያዎቻችን ለሕሙማን ፈውስ የሚያሳዩት ተከታታይነት ያለው ትጋትና ርኅራኄ ነው። ሆኖም በነዚህ የፈውስ ማዕከላት ውስጥ ሕክምናውን በጽናት የሚከታተሉ፣ ነገር ግን በቁሳቁስና በአስታማሚ እጥረት የሚፈተኑ ጥቂት ወገኖች መኖራቸው አይካድም። ይህን ክፍተት ለመሙላትና የሐኪሞችን ድካም በበጎነት ለማገዝ የቆረጡ ተቋማትና በጎ ፈቃደኞች መኖራቸው ደግሞ ለከተማችን ትልቅ ኩራት ነው።
ከነዚህም መካከል ታፍ ኢነርጂስ ይጠቀሳል። ታፍ ኢነርጂስ ነዳጅና ቅባቶችን በማቅረብ ብቻ የሚታወቅ ተቋም አይደለም፤ ከዚያ ይልቅ የሰውን ልጅ ችግር ተረድቶ "ለወገኔ ምን ላድርግ?" የሚል የቆሰሉ ልቦችን ጠጋኝ እንጂ። ዛሬ ላይ ተቋሙ 80 አቅመ ደካሞችን በቋሚነት ይደገፋል። ከእነዚህም መካከል ነገ የአገር ተረካቢ የሆኑ 10 ሕፃናት ይገኙበታል። እነዚህ ሕፃናት ዛሬ የታፍ ኦይልን እጅ ይዘው ትምህርታቸውን ሲከታተሉ፣ አረጋውያኑም የዕለት ጉርሳቸውን ሳያጡ በክብር ሲኖሩ ማየት የተቋሙ ትልቁ ትርፍ ነው።
ድርጅቱ ረዳትና አስታማሚ አጥተው በዘውዲቱ ሆስፒታል ለሚገኙ ሕሙማን ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፣ የተቋሙ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መቅደስ አሰፋ "ረዳት የሌላቸውን ወገኖች መርዳት መቻላችን ትልቅ የሕሊና እርካታ ሰጥቶናል" ሲሉ ታፍ ኢነርጂስ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በሚገባ ተረድቶ በተግባር የሚፈጽም ተቋም መሆኑን አረጋግጠዋል። ታፍ ኢነርጂስ ማኅበራዊ ኃላፊነትን እንደ ግዴታ ሳይሆን እንደ ሰብአዊ ጥሪም በመቁጠር፣ ሌሎች የግል ተቋማት የዚህ ቅዱስ ተግባር ተካፋይ እንዲሆኑ አርአያነቱን በተግባር አሳይቷል።
ኮሚሽኑ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ባከናወናቸው ከ15 በላይ በሚሆኑ የበጎ ፈቃድ ፕሮግራሞች በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወይዘሮ አስራ ንጉሴ እንደ ታፍ ኢነርጂስ ያሉ ልበ-ቀና ድርጅቶችን በማስተባበር ለአቅመ ደካሞች ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን ከመገንባት ጀምሮ እስከ ሕሙማን ድጋፍ ድረስ የተከናወኑት ተግባራት የማኅበረሰቡ የመረዳዳት ዕሴት ማደጉን አመላካች እንቅስቃሴ መሆኑን በአንክሮ ገልጸዋል።
በጎነት ዛሬ የምንዘራውና ነገ የምናጭደው የሰላም ሰብል ነው ያሉት ኮሚሽነሯ፤ ሁላችንም በጋራ ከቆምን፣ በአዲስ አበባ ውስጥ ማንም አቅመ ደካማ ብቻውን አይሆንም፤ ማንም ሕመምተኛም ያለ ረዳት አይቀርም ሲሉ አክለዋል፡፡
የዘውዲቱ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ቴዎድሮስ አቡሌ በበኩላቸው በጤና ተቋማት ውስጥ ረዳት ለሌላቸው ወገኖች የሚደረግ ማንኛውም ድጋፍ ከመድኃኒት እኩል ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፣ ይህ በከተማ አስተዳደሩና በበጎ ፈቃደኞች የሚከናወነው "በጎነት በሆስፒታል" ንቅናቄ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#በጎነት #አዲስአበባ #ታፍኢነርጂስ #TaffEnergies #ሰብአዊነት #ኢትዮጵያ #AddisAbaba
❤3👍2
እባክዎን ከሐሰተኛ ዜናዎች እና የተሳሳቱ መረጃዎች ስርጭት ይጠበቁ!
ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተብሎ የሚደርስዎትን ማንኛውም ይፋዊ መልዕክት ከማጋራትዎ በፊት ሁልጊዜም በጽሕፈት ቤቱ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና ድህረ-ገጽ በመግባት፣ ትክክለኛነቱን እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን።
Please remain vigilant against the spread of fake news and misinformation.
To ensure authenticity, always cross-check any official messages attributed to the Office of the Prime Minister (PMO) against the office’s official social media pages and website before sharing.
Facebook: https://www.facebook.com/share/1DbRTPiYUF/?mibextid=wwXIfr
X: https://x.com/pmethiopia?s=21
Website: https://pmo.gov.et
#PMOEthiopia
ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተብሎ የሚደርስዎትን ማንኛውም ይፋዊ መልዕክት ከማጋራትዎ በፊት ሁልጊዜም በጽሕፈት ቤቱ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና ድህረ-ገጽ በመግባት፣ ትክክለኛነቱን እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን።
Please remain vigilant against the spread of fake news and misinformation.
To ensure authenticity, always cross-check any official messages attributed to the Office of the Prime Minister (PMO) against the office’s official social media pages and website before sharing.
Facebook: https://www.facebook.com/share/1DbRTPiYUF/?mibextid=wwXIfr
X: https://x.com/pmethiopia?s=21
Website: https://pmo.gov.et
#PMOEthiopia
❤3👍1
ከትግራይ ክልል ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ የምክክር ኮምሽን የአጀንዳ ልየታ ጉባኤ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ የልማት ሥራዎች ጎበኙ!
በምክክር ኮምሽን አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የሶስት ቀናት ውይይት ሲጠናቀቅ፤ በአጀንዳ ልየታው ለመሳተፍ ከትግራይ ክልል የመጡ ከሶስት መቶ (300) በላይ የሚሆኑ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተሳታፊዎች፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ኮርደር ልማት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የወንዝ ዳርቻ ልማት እና በመልሶ ማልማት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
ጎብኝዎቹ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከማሳደግ ባሻገር ዓለምዓቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልፀዋል ። እንዲሁም “ይህን መሰል የመሰለ የልማት ስራ በተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች መድገም እንደሚያስፈልግ፣ ይህንኑ ሃላፊነትም ወጣቱ ትውልድ ወስዶ የመፈፀም ሃላፊነት እንዳለበት” በቁጭት ገልፀዋል።
ተሳታፊዎቹ፥ “ሰላም የሁሉም መሰረት እንደሆነ፣ ለዚህ በቂ ማሳያም የላቀ የስራ ባህል በመገንባት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት፣ አለማቀፍ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለውን አዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች እየታዩ ያሉ የልማት ስራዎች በቂ ማሳያ ነው” ሲሉ ገልፀዋል። በአዲስ አበባ በተመለከቱት ሁለንተናዊ የልማት ስራዎች መደሰታቸውንም አብራርተዋል።
በምክክር ኮምሽን አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የሶስት ቀናት ውይይት ሲጠናቀቅ፤ በአጀንዳ ልየታው ለመሳተፍ ከትግራይ ክልል የመጡ ከሶስት መቶ (300) በላይ የሚሆኑ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተሳታፊዎች፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ኮርደር ልማት፣ ሳይንስ ሙዝየም፣ የወንዝ ዳርቻ ልማት እና በመልሶ ማልማት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
ጎብኝዎቹ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከማሳደግ ባሻገር ዓለምዓቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን የሚያስችላት መሆኑን ገልፀዋል ። እንዲሁም “ይህን መሰል የመሰለ የልማት ስራ በተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች መድገም እንደሚያስፈልግ፣ ይህንኑ ሃላፊነትም ወጣቱ ትውልድ ወስዶ የመፈፀም ሃላፊነት እንዳለበት” በቁጭት ገልፀዋል።
ተሳታፊዎቹ፥ “ሰላም የሁሉም መሰረት እንደሆነ፣ ለዚህ በቂ ማሳያም የላቀ የስራ ባህል በመገንባት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት፣ አለማቀፍ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለውን አዲስ አበባ እና በሌሎች አካባቢዎች እየታዩ ያሉ የልማት ስራዎች በቂ ማሳያ ነው” ሲሉ ገልፀዋል። በአዲስ አበባ በተመለከቱት ሁለንተናዊ የልማት ስራዎች መደሰታቸውንም አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ዛሬ መርቀን ከፍተናል።
በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው።
የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን፣ እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካትቷል። በተጨማሪም ተቋሙ ለድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነትና ምላሽ የመስጠት አቅምን በመገንባት ረገድ እንደ ማገር ሆኖ ያገለግላል።
ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው።
የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን፣ እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካትቷል። በተጨማሪም ተቋሙ ለድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነትና ምላሽ የመስጠት አቅምን በመገንባት ረገድ እንደ ማገር ሆኖ ያገለግላል።
ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍3❤1