ዛሬ በኮሪደር ልማት የተገነቡ 315 የንግድ ሱቆችን፣ በቀበሌና በንግድ ቤቶች በኪራይ ሲሰሩ ለነበሩ የኮሪደር ልማት ተነሺዎች በዕጣ አስተላልፈናል።
በከተማችን ከዚህ ቀደም የመንግስት የቀበሌና የንግድ ቤቶችን ተከራይተው ሲሰሩ ለነበሩ ነዋሪዎች አስተዳደራችን ሁለት አማራጮችን አቅርቦ እንደየምርጫቸው በአክሲዮን ተደራጅተው ወደ ንግድ ሱቃቸው ገብተው ሥራ እንዲጀምሩ፣ ይህ ካልሆነም መንግስት የሚያቀርብላቸውን ሱቆች ተከራይተው እንዲሰሩ እድል ሰጥቶ ነበር።
አብዛኛዎቹ መንግስት ገንብቶ ያቀረብላቸውን ሱቆች ተከራይተው ንግዳቸውን የቀጠሉ ሲሆን፣ በአክሲዮን ተደራጅተው ወደ ንግድ ሱቃቸው ገንብተው ለመነገድ የመረጡም በርካቶች ነበሩ። ከእነዚህ በአክሲዮን እንዲደራጁና መሬት ተረክበው እንዲገነቡ ከተፈቀደላቸው ውስጥ የመገንባት አቅም በማጣታቸው በተለያዩ የውይይት መድረኮች ሌላ አማራጭ እንዲሰጣቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል።
በመሆኑም አስተዳደራችን ችግሩን ለመቅረፍ፤ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ ዳርቻ ልማት እና በመልሶ ማልማት ሥራዎች ምክንያት ለተነሱ ነዋሪዎች፤ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ 315 ዘመናዊ የንግድ ሱቆችን በዕጣ እንዲተላለፉላቸው አድርጓል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በከተማችን ከዚህ ቀደም የመንግስት የቀበሌና የንግድ ቤቶችን ተከራይተው ሲሰሩ ለነበሩ ነዋሪዎች አስተዳደራችን ሁለት አማራጮችን አቅርቦ እንደየምርጫቸው በአክሲዮን ተደራጅተው ወደ ንግድ ሱቃቸው ገብተው ሥራ እንዲጀምሩ፣ ይህ ካልሆነም መንግስት የሚያቀርብላቸውን ሱቆች ተከራይተው እንዲሰሩ እድል ሰጥቶ ነበር።
አብዛኛዎቹ መንግስት ገንብቶ ያቀረብላቸውን ሱቆች ተከራይተው ንግዳቸውን የቀጠሉ ሲሆን፣ በአክሲዮን ተደራጅተው ወደ ንግድ ሱቃቸው ገንብተው ለመነገድ የመረጡም በርካቶች ነበሩ። ከእነዚህ በአክሲዮን እንዲደራጁና መሬት ተረክበው እንዲገነቡ ከተፈቀደላቸው ውስጥ የመገንባት አቅም በማጣታቸው በተለያዩ የውይይት መድረኮች ሌላ አማራጭ እንዲሰጣቸው ሲጠይቁ ቆይተዋል።
በመሆኑም አስተዳደራችን ችግሩን ለመቅረፍ፤ በኮሪደር ልማት፣ በወንዝ ዳርቻ ልማት እና በመልሶ ማልማት ሥራዎች ምክንያት ለተነሱ ነዋሪዎች፤ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ 315 ዘመናዊ የንግድ ሱቆችን በዕጣ እንዲተላለፉላቸው አድርጓል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍1
ከንቲባ አዳነች አቤቤ አዲስ ከተሾሙት በኢትዮጵያ የጣሊያን ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ ጋር ተወያዩ።
በውይይታቸውም አዲስ አበባ ከጣሊያን ከተሞች ጋር ያላትን ትብብር እና አጋርነት አጠናክሮ ለማስቀጠል፤ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የቆየ የታሪክ፣ የባህል እና የልማት ትብብር ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ምክክር አድርገዋል።
ኢትዮጵያና ጣሊያን የቆየ የታሪክ፣ የባህል፣ የልማት ትብብር እና የሁለትዮሽ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው።
በውይይታቸውም አዲስ አበባ ከጣሊያን ከተሞች ጋር ያላትን ትብብር እና አጋርነት አጠናክሮ ለማስቀጠል፤ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የቆየ የታሪክ፣ የባህል እና የልማት ትብብር ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ምክክር አድርገዋል።
ኢትዮጵያና ጣሊያን የቆየ የታሪክ፣ የባህል፣ የልማት ትብብር እና የሁለትዮሽ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው።
❤3
ዛሬ ማለዳ የዒድ አል-ፈጥር በዓልን አስመልክቶ፣ ከ100 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖቻችን ማዕድ አጋርተናል።
ወትሮም በሌሎች በዓላት ላይ እንደምናደርገው ሁሉ ፣ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ፣ ለአቅመ ደካሞች ፣ ለአካል ጉዳተኞች ፣ እንዲሁም ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው የከተማችን ነዋሪዎች የሚደረገው ይህ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር በሁሉም የከተማችን ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ የረመዳን ወቅትም 27 ሺህ ያህል ወገኖቻችን ወሩን በሙሉ በ28ቱም የምገባ ማዕከሎቻችን የአፍጥር ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸው ያለ ችግር እንዲያሳልፉ አድርገናል።
የማዕድ ማጋራት የምናደርገው ጊዜያዊ ችግርን ለመቅረፍ ብቻ ሳይሆን ለሕዝባችን ያለንን ክብር ለመግለጽ ሲሆን፤ ወንድማማችነትን እና የእርስ በእርስ መደጋገፍ እሴትን ለማጎልበት ነዉ።
እንደ ሁልጊዜውም በከተማችን በምናከናውናቸው የማዕድ ማጋራት ሥራዎች ላይ በማስተባበር፣ አቅመ ደካሞችን በጉልበታቸው በማገዝ ደፋ ቀና ለሚሉ የከተማችን ወጣቶችን፣ካላቸው ቆርሰው ለመስጠት ለማይሳሱ ባለሀብቶችና የከተማችን ነዋሪዎች በተጠቃሚዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
በተለይም ዛሬ በከንቲባ ጽሕፈት ቤት ያደረግነውን የማዕድ ማጋራት ለደገፉት ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለአቶ ጀማል አሕመድ እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ኤምባሲ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በዓሉ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆን ከወዲሁ እመኛለሁ!
ዒድ ሙባረክ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ወትሮም በሌሎች በዓላት ላይ እንደምናደርገው ሁሉ ፣ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ፣ ለአቅመ ደካሞች ፣ ለአካል ጉዳተኞች ፣ እንዲሁም ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው የከተማችን ነዋሪዎች የሚደረገው ይህ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር በሁሉም የከተማችን ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ የረመዳን ወቅትም 27 ሺህ ያህል ወገኖቻችን ወሩን በሙሉ በ28ቱም የምገባ ማዕከሎቻችን የአፍጥር ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸው ያለ ችግር እንዲያሳልፉ አድርገናል።
የማዕድ ማጋራት የምናደርገው ጊዜያዊ ችግርን ለመቅረፍ ብቻ ሳይሆን ለሕዝባችን ያለንን ክብር ለመግለጽ ሲሆን፤ ወንድማማችነትን እና የእርስ በእርስ መደጋገፍ እሴትን ለማጎልበት ነዉ።
እንደ ሁልጊዜውም በከተማችን በምናከናውናቸው የማዕድ ማጋራት ሥራዎች ላይ በማስተባበር፣ አቅመ ደካሞችን በጉልበታቸው በማገዝ ደፋ ቀና ለሚሉ የከተማችን ወጣቶችን፣ካላቸው ቆርሰው ለመስጠት ለማይሳሱ ባለሀብቶችና የከተማችን ነዋሪዎች በተጠቃሚዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
በተለይም ዛሬ በከንቲባ ጽሕፈት ቤት ያደረግነውን የማዕድ ማጋራት ለደገፉት ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለአቶ ጀማል አሕመድ እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ኤምባሲ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
በዓሉ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆን ከወዲሁ እመኛለሁ!
ዒድ ሙባረክ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
🥰4
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ከጠባቧ የቀበሌ ቤት ወደ ዘመናዊው አፓርታማ፦ የወይዘሮ ሀዋ ሸሪፍ የሕይወት ለውጥ
በልደታ ክፍለ ከተማ "ሳር ቤት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለበርካታ ዓመታት በአንድ ጠባብ የቀበሌ ቤት ውስጥ ከአምስት የቤተሰብ አባላቶቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት ወይዘሮ ሀዋ ሸሪፍ፣ "ከሞተ በላይ፣ በሕይወት ካለው በታች" ሆነው የመከራ ሕይወት ማሳለፋቸውን በምሬት ይናገራሉ።
ይኖሩበት የነበረው አንድ ጠባብ ክፍል ቤት ውስጥ አንድ ፍራሽ ብቻ ዘርግተው፣ ገሚሱ ቤተሰብ በራስጌ ገሚሱ ደግሞ በግርጌ ተፋፍገው ለማደር ይገደዱ እንደነበር ወይዘሮ ሀዋ ከኤ ኤም ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
ከመኝታ ችግር ባለፈ፣ የዕድሜያቸውና የጤናቸው ሁኔታ ችግሩን ይበልጥ አክብዶት እንደነበር አንስተው፣ በሌሊት ወደ መፀዳጃ ቤት እንኳን ለመሄድ መነሳት የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ያወጋሉ፡፡
እንዴትም ብለው ለሊት ሲነሱም እንኳን፣ በልጆቻቸው ላይ እንዳይወድቁ ይፈሩ እንደነበር ያስታውሳሉ።
ቤቱ ለኑሮ ምቹ ባለመሆኑ እና በጠባብነቱ ምክንያት ልጆቻቸው እና የልጅ ልጆቻቸው በዓላትን አብረው ለማሳለፍ ይቸገሩ እንደነበርም ይናገራሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባከናወነው "ሰው ተኮር" የልማት ሥራ፣ ወይዘሮ ሀዋ ባለ አራት ወለል ዘመናዊ ህንፃ ላይ ሰፊና ምቹ መኖሪያ ቤት አግኝተዋል።
አሁን ያለሁበትን ሁኔታ ለመግለጽ ቃላት ያጥረኛል የሚሉት ወይዘሮ ሀዋ፣ ዘንድሮ ከልጅ ልጆቻቸው እና ከቅርብ ዘመዶቻቸው ጋር በአዲሱ ቤታቸው በደስታ የኢድ በዓልን ማሳለፋቸውን ገልጸዋል።
በዐረብ ሀገር ለብዙ ዓመታት ሠርታ የተመለሰችው ልጃቸውም፣ ቀደም ሲል ለእናቷ ያመጣቻቸውን እቃዎች ለማውጣት ትቸገር እንደነበር በማንሳት፣ አሁን ላይ ግን አውጥታ እናትና አባቷን ማሳመር በመቻሏ ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ተናግራለች።
ወይዘሮ ሀዋ እና ቤተሰባቸው ይህንን እድል ላመቻቹ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ በተለይም ለከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ለባለሀብቶች ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ይህ ታሪክ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የዜጎችን ሕይወት እንዴት እንደሚቀይሩ የሚያሳይ ህያው ምስክር እንደሆነ የእድሉ ተጠቃሚዎች የሰጡት ምስክርነት ያረጋግጣል።
Via AMN
በልደታ ክፍለ ከተማ "ሳር ቤት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለበርካታ ዓመታት በአንድ ጠባብ የቀበሌ ቤት ውስጥ ከአምስት የቤተሰብ አባላቶቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት ወይዘሮ ሀዋ ሸሪፍ፣ "ከሞተ በላይ፣ በሕይወት ካለው በታች" ሆነው የመከራ ሕይወት ማሳለፋቸውን በምሬት ይናገራሉ።
ይኖሩበት የነበረው አንድ ጠባብ ክፍል ቤት ውስጥ አንድ ፍራሽ ብቻ ዘርግተው፣ ገሚሱ ቤተሰብ በራስጌ ገሚሱ ደግሞ በግርጌ ተፋፍገው ለማደር ይገደዱ እንደነበር ወይዘሮ ሀዋ ከኤ ኤም ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
ከመኝታ ችግር ባለፈ፣ የዕድሜያቸውና የጤናቸው ሁኔታ ችግሩን ይበልጥ አክብዶት እንደነበር አንስተው፣ በሌሊት ወደ መፀዳጃ ቤት እንኳን ለመሄድ መነሳት የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ያወጋሉ፡፡
እንዴትም ብለው ለሊት ሲነሱም እንኳን፣ በልጆቻቸው ላይ እንዳይወድቁ ይፈሩ እንደነበር ያስታውሳሉ።
ቤቱ ለኑሮ ምቹ ባለመሆኑ እና በጠባብነቱ ምክንያት ልጆቻቸው እና የልጅ ልጆቻቸው በዓላትን አብረው ለማሳለፍ ይቸገሩ እንደነበርም ይናገራሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባከናወነው "ሰው ተኮር" የልማት ሥራ፣ ወይዘሮ ሀዋ ባለ አራት ወለል ዘመናዊ ህንፃ ላይ ሰፊና ምቹ መኖሪያ ቤት አግኝተዋል።
አሁን ያለሁበትን ሁኔታ ለመግለጽ ቃላት ያጥረኛል የሚሉት ወይዘሮ ሀዋ፣ ዘንድሮ ከልጅ ልጆቻቸው እና ከቅርብ ዘመዶቻቸው ጋር በአዲሱ ቤታቸው በደስታ የኢድ በዓልን ማሳለፋቸውን ገልጸዋል።
በዐረብ ሀገር ለብዙ ዓመታት ሠርታ የተመለሰችው ልጃቸውም፣ ቀደም ሲል ለእናቷ ያመጣቻቸውን እቃዎች ለማውጣት ትቸገር እንደነበር በማንሳት፣ አሁን ላይ ግን አውጥታ እናትና አባቷን ማሳመር በመቻሏ ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ተናግራለች።
ወይዘሮ ሀዋ እና ቤተሰባቸው ይህንን እድል ላመቻቹ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ በተለይም ለከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ለባለሀብቶች ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ይህ ታሪክ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የዜጎችን ሕይወት እንዴት እንደሚቀይሩ የሚያሳይ ህያው ምስክር እንደሆነ የእድሉ ተጠቃሚዎች የሰጡት ምስክርነት ያረጋግጣል።
Via AMN
ውቧ አዲስ አበባ፦
በሴቶች ቆራጥነት በውጤት ተምሳሌትነት እየተገነባች ያለችው የሁላችን ከተማ አዲስ አበባ!
#በመላ ኑሪ፣ በኮንፊደንስ ሩጪ!" ሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ
በሴቶች ቆራጥነት በውጤት ተምሳሌትነት እየተገነባች ያለችው የሁላችን ከተማ አዲስ አበባ!
#በመላ ኑሪ፣ በኮንፊደንስ ሩጪ!" ሴቶች 5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ