የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
809 subscribers
2.14K photos
47 videos
265 links
Download Telegram
የገቢ ግብር አሰባሰብን በተመለከተ

95% የግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ የተደረገ ሲሆን በ6 ወራት ለመሰብሰብ ከታቀደው 176.03 ቢሊዮን ብር ውስጥ 162.72 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የእቅዱን 92.4% መፈፀም ተችሏል፡፡ ይህም ከ2017 ጋር ሲነፃፀር 51.12 ቢሊዮን ብር ( 45.8%) የገቢ ጭማሪ አሳይቷል ::

የግማሽ ዓመት ወጪ አፈጻጸም በተመለከተ ከጠቅላላ ወጪ፡ 148.9 ቢሊዮን ብር የካፒታል ወጪ ድርሻ 70.14% ፤ በማህበራዊ ድጋፍ ቀጥታ ድጎማ 18.72 ቢሊዮን ብር ፤ እንዲሁም ለተማሪ ምገባ ፣ ለዩኒፎርም፣ ለጤና መድህንና ለትራንስፖርት 55.7 ቢሊዮን ብር ወጪ በማድረግ 59.7% የእድገት መጠን ማሳየት ተችሏል፡፡

የቅሬታ አያያዝና አገልግሎት ክትትል በተመለከተ ከከንቲባ ጽ/ቤት ጀምሮ ግልፅ የቅሬታ ስርዓት በመዘርጋት፤ በብልሹ አሰራርና ሌብነት የተሳተፉ 282 ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ ተወሰዷል፡፡

በቴክኖሎጂ በተደገፈ የቁጥጥር ስራ በ7,678 ግብር የሚሰውሩ ነጋዴዎችና በ2,261 የጭነት መኪናዎች ያለ ደረሰኝ ምርት ሲያጓጉዙ በመገኘታቸው ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል፡፡

ከተማዋ በገቢ አሰባሰብና በጀትን በአግባቡ ከመጠቀም አንፃር ከአፍሪካ ከተሞች ጋር በተካሄደ ጥናት ምዘና መሰረት ከተማችን ቀዳሚ በመሆን ልምዷን አካፍላለች፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1👍1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
የመሬት ልማት እና አስተዳደርን በተመለከተ፡-

የኦንላይን አገልግሎትን ለማሳለጥ ባለፉት ስድስት ወራት በተሻሻለው ሲስተም 10,528 ካርታዎች ታትመው ተሰራጭተዋል፡፡

የለማ መሬት ዝግጅትና ማስተላለፍ ሥርዓትን ከማሻሻል አንፃር ለተለያዩ አገልግሎቶች 341 ሄክታር መሬት ለማዘጋጀት ታቅዶ 465 ሄ/ር መሬት ማዘጋጀት ተችሏል፡፡

ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል የከተማዋን ፍላጎት መሠረት ያደረገ 294 ሄክታር መሬት ለማስተላለፍ ታቅዶ 483 ሄ/ር ማስተላለፍ ተችሏል፡፡

የቅድመ ማልማት ጥያቄ ላቀረቡ 54 ባለይዞታዎች በይዞታቸው ላይ ማልማት እንዲችሉ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

በግማሽ ዓመቱ ለልማት ተነሺዎች 7.4 ቢሊዮን ብር በላይ ካሣ መክፈል የተቻለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ በልማት ምክንያት ለተነሱት ልማት ተነሺዎቻችን ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ (ለመብራት) አገልግሎት ከ 400 ሚሊዮን ብር በላይ ከፍያ ተፈጽማል፡፡

የአርሶ አደር መብት ፈጠራ አፈፃፀምን በሚመለከት 6,122 ካርታዎች የታተሙ ሲሆን እስካሁን ድረስ 10,873 ካርታዎች ታትመው አርሶ አደሩ እጅ እንዲደርሱ ተደርጓል፡፡

ለ50 አርሶ አደሮች በይዞታቸዉ ላይ እንዲያለሙ ዉሳኔ ተሰጥቶ ወደ ልማት እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት 41,454 ይዞታዎች ለመመዝገብ ዕቅድ ተይዞ 34,802 ማከናወን ተችሏል፡፡ እንዲሁም ለሚቀርቡ የመብት ምዝገባና የመስክ አገልግሎት ጥያቄዎች ለ84,996 ተገልጋዮች ምላሽ ለመስጠት ታቅዶ ለ94,927 በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡

ለ7,310 ተገልጋዮች አዲስ እና አዝ ቢዊልት የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ ለ7,150 ገንቢዎች ፈቃድ ተሰጥቷል፡፡

ለ1,990 ተገልጋዮች የግንባታ ማሻሻያ፤ ማራዘሚያ እና ማፍረሻ ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ ለ2,477 ገንቢዎች ፈቃድ መስጠት ተችሏል፡፡

ለ12,634 ተገልጋዮች የእድሳት እና ጊዜያዊ የግንባታ ፈቃድ ፣ ለ13,451 ገንቢዎች ፈቃድ በመስጠት በርካታ ሕንፃዎች ታድሰዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍1
ባለፉት 6 ወራት በኢንቨስትመንት በተመለከተ
የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ

የኢንቨስትመንት ፍቃድ አሰጣጥ ከታቀደው በላይ አፈጻጸም አሳይቷል፦

አዲስ ፈቃድ፦ 1,750 ታቅዶ ለ 2,549 ባለሀብቶች ፈቃድ ተሰጥቷል።

ማስፋፊያ፦ ማስፋፊያ ፈቃድ 140 ታቅዶ ለ 162 ተሰጥቷል።

ዕድሳት፦ ለ981 የኢንቨስትመንት ፈቃዶች እድሳት ተደርጓል።

የውጭ ዜጎች የስራ ፈቃድ፦ ለ42 የውጭ ዜጎች የስራ ፈቃድ ተሰጥቷል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍1
የወጣቶችና ስፖርት ዘርፍ በተመለከተ

ወጣቶችን በልማትና በጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ለማሳተፍ የተመዘገቡ ውጤቶች፦
👉በጎ ፈቃድ አገልግሎት፦ 1,445,745 ወጣቶች በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ስራዎች (አረንጓዴ አሻራ፣ ደም መለገስ፣ ፅዳት...) ተሳትፈዋል። ይህም በገንዘብ ሲተመን 217.7 ሚሊዮን ብር ያወጣል።
👉ግንዛቤ መፍጠር፦ ለ 874,460 ወጣቶች በሀገራዊ ጉዳዮችና በሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
👉 ስፖርትና ማዘውተሪያ፦
👉32 አዳዲስ የስፖርት ሜዳዎችና ማዘውተሪያዎች ተገንብተዋል።
👉84,683 ታዳጊዎች በ723 ጣቢያዎች ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
👉17 ታዳጊዎች ለአገርቱ ብሔራዊ ቡድን እንዲመረጡ ተደርጓል።
👉በማህበረሰብ አቀፍ ስፖርት 3.7 ሚሊዮን ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍1
በውኃ ልማት ዘርፍ በተመለከተ

👉የከተማዋን የውኃ አቅርቦት ሽፋን በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በቀን በ60ሺህ ሜ.ኩብ የሚያሳድጉ የተለያዩ የውሃ ልማት ሥራዎች ተቀርጸው ተግባራዊ በመደረግ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከዚህ አንጻር ፤-
👉ባለፉት 6 ወራት በቀን 37,996 ሜ.ኩብ ውሃ መስጠት የሚያስችሉ የ21 ጥልቅ ጉድጓዶች ቁፋሮ ሥራ በማጠናቀቅ በቀን 3,996 ሜ.ኩብ ውሃ መስጠት የሚያስችሉ 3 ጉድጓዶች ወደ ስርጭት ሲስተም እንዲገቡ ተደርጓል፡፡
👉በቀን 100ሺህ ሜ.ኩብ ውኃ ማምረት ከሚያስችለው የጭቋላ ዌል ፊልድ የውሃ ልማት ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ የ20 ጉድጓዶች ቁፋሮ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ወደ ስርጭት ሲስተም ለማስገባት እየተሰራ ይገኛል፡፡
👉የዘመናዊ ፍሳሽ አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ 8 ፕሮጀክቶች በቀን 20ሺህ ሜ.ኩብ ፍሳሽ የማጣራት አቅም በመፍጠር እስከ 235ሺህ የሚደርስ የህብረተሰብ ክፍል የዘመናዊ ፍሳሽ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡
👉የኮዬ ፈጬ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት 75% ፤በቀን 106ሺህ ሜ.ኩብ ፍሳሽ የማጣራት አቅም የሚኖረው የምሰራቅ ተፋሰስ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ 30% ማድረስ ተችሏል፡፡
👉በሌላ በኩል 20.02 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ከመኖርያ ቤቶች የሚፈጠረውን ፍሳሽ ቆሻሻ በመስመር እና በተሸከርካሪ በማሰባሰብ 19.73 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገድ ተችሏል፡፡
ከብቲባ አዳነች አቤቤ
👍4
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
የቤት ልማት አቅርቦትን በተመለከተ

በመንግስት በጀት እና በበጎ አድራጎት 11,550 መኖሪያ እና 707 ንግድ ቤቶች በድምሩ 12,257 መኖሪያ እና ንግድ ቤቶችን ለልማት ተነሺዎች፣ ለአገር ባለውለታዎች፣በጨረታና በመልካም አስተዳደር ማስተላለፍ ተችሏል፡፡

በመንግስትና የግል አጋርነት እና በከተማው በጀት ሊገነቡ ከታቀዱ 100 ሺ ቤቶች ላይ 97,000 ቤቶች ወደ ግንባታ ሂደት የገቡ ሲሆን ሁሉንም በተያዘላቸው ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው፡፡

በግል እና ሪል ስቴት የተገነቡ ቤቶች 13,517 ሲሆን በኮሪደር የለሙ 810 የንግድ ቤቶችን በልማት ለተነሱ አነስተኛ ነጋዴዎች ተላልፏል፡፡

በመንግስት እና በግል አጋርነት በተሰራው ዘርፈ ብዙ ስራ ከ70 በላይ ፕሮጀክቶችን ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል፡፡ በዚህም ከብር 1.3 ትሪሊዮን በላይ ካፒታል ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል፡፡

በ65 ህብረት ሥራ ማህበራት ለተደራጁ 5,110 ቤት ገንቢዎች ጠንካራ ድጋፍ በመደረጉ 42 ማህበራት ወደ ግንባታ ምዕራፍ ተሸጋግረዋል::

ከለውጡ ወዲህ 45,566 ቤቶች የተገነቡ ሲሆን በዚህ 6 ወር ደግሞ 4,990 ቤቶች ተገንብተዋል፡፡

ባለፉት 6 ወራት ብቻ 1.5 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ ለባንክ ተመላሽ በማድረግ የቦንድ ብድር ጫናን መቀነስ የተቻለ ሲሆን በአጠቃላይ ከለውጡ በፊት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች መገንቢያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተወሰደው የቦንድ ብድር ከወለዱ ብር 61.2 ቢሊየን ከለውጡ ወዲህ መክፈል ተችሏል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍1
የመንገድ መሰረተ ልማት በተመለከተ
የመንገድ ሽፋን፣የትራፊክ ፍሰትና ደህንነትን ለማሻሻል የተሰሩ ስራዎች
👉17.5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ለመንገድ ልማት ዘርፍ በመመደብ
👉የመንገድ ግንባታ 134.8 ኪ.ሜ.
👉የመንገድ ጥገና 573.54 ኪ.ሜ.
👉ባለፉት 6 ወራት በመንገድ መሰረተ ልማት 708.34 ኪ.ሜ. ማከናወን ተችሏል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የሴቶችና ማህበራዊ ዘርፍ በተመለከተ(ዘርፈ ብዙ አገልግሎት)
ማህበራዊ ስብራትን ለመጠገንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች፦
👉ተሳትፎ፦ 46,265 ሴቶች በሰላም ግንባታ፣ 144,580 ሴቶች ደግሞ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፈዋል።
የነገዋ የሴቶች ማእከል፦
👉በ3ኛው ዙር 812 ተጋላጭ የነበሩ ሴቶች በክህሎት ሰልጥነው ወደ ሥራ ገብተዋል።
👉በ4ኛው ዙር 1,000 ሴቶች ስልጠናቸውን እያጠናቀቁ ይገኛሉ።
የህብረተሰቡ ተሳትፎና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተመለከተ

👉ከህብረተሰቡና ከባለድርሻ አካላት ለአከባቢ ልማትና ለማህበራዊ ሀላፊነትን በመወጣት ረገድ አገልግሎት የሚውል በጥሬ ገንዘብ ፣ በአይነትና በጉልበት በተደረገ አስተዋፅኦ፤-
• 4,99ዐ የአቅመ ደካማ ቤቶችን፣
• 81 ኪ.ሜ ኮብል ስቶን ጥገና፣
• 30 አነስተኛ ድልድይ ግንባታ ፣
• 28 የኮሚኒቲ ፖሊስ ግንባታ ፣
• 35 የውስጥ ለውስጥ መንገድ መብራት ዝርጋታ ፣
• 68 የጋራ መጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ፣
• 36 ኪ.ሜ ጠጠር መንገድ ግንባታ እና
• 60 ኪ.ሜ የቴራዞ መንገድ ግንባታ ተከናውኖ ለአገልግሎት በቅቷል፡፡

👉ብሎኮችን ለነዋሪው ምቹ ከማድረግ አንፃር 648 ብሎኮችን ሞዴል ማድረግ ተችሏል፡፡

👉በ6ወራት ውስጥ ለ881,559 የህብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ ማጋራት ተችሏል፡፡

👉በአጠቃላይ ባለፉት ስድስት ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት 13,136,434,921 ብር እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የአከባቢ ልማት ስራዎች 2,200,466,477.74 በድምሩ 15,336,901,398 ብር በማሰባሰብ ለህዝብ ጥቅም ማዋል ተችሏል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍5
በኮሚሽኑ ባለፉት 7 ወራት የኅብረተሰቡን አቅም በማስተባበር ከ13 ዓይነት በላይ የአካባቢ መሠረተ ልማት ሥራዎችን አከናውኗል።

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ነዋሪዎች የተገነቡ መሠረተ ልማቶች አካባቢዎቻቸው ሰላም እና ምቹ መኖሪያ እንዲሆን ማስቻሉን የተናገሩ ሲሆን የመልካም አስተዳደር ችግሮች መቀነሳቸውንም አስረድተዋል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ተሳትፎና ንቅናቄ ያልተማከለ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሔኖክ ዘውዴ በተጠቀሱት ወራት በርካታ የአካባቢ መሠረተ ልማት ሥራዎች በኅብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ በስፋት መከናወናቸውን ነው ያስረዱት።

ከተገነቡት መካከል፦
✔️ ከ105 ኪ.ሜ በላይ የሰብ ቤዝ ሥራ
✔️ ከ86 ኪ.ሜ በላይ የኮብልስቶን ጥገና
✔️ 31 አነስተኛ ድልድዮች
✔️ 32 ማኅበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ማዕከላት
✔️ 74 የጋራ መፀዳጃ ቤቶች ይገኙበታል።

ለእነዚህ ፕሮጀክቶች ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ተሰብስቦ ሥራ ላይ መዋሉ የተገለፀ ሲሆን 648 ሞዴል ብሎኮችን መፍጠር ተችሏል። ከ1,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

እነዚህ መሰረተ ልማቶች በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ሰላማዊ፣ ንፁህና ምቹ የመኖሪያ አካባቢ ለመፍጠር በሚደረገው ርብርብ ውስጥ ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ነው።

#ኅብረተሰብ_ተሳትፎ
#ከተማ_ልማት
#በጎፈቃድ
👍5
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
“ብቁ ዜጋ ማለት ለአገሩና ለማህበረሰቡ ኃላፊነት የሚወስድ፣ ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት የሚሰጥ እና በልማት ሥራዎች ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ዜጋ ነው።”
— ወ/ሮ አስራት ንጉሴ

 የኮሚሽኑ የበጎ ፈቃድ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ አስራት ንጉሴ ለኮሚሽኑ ሰራተኞች “ብቁ ዜጋ” በሚል ርዕስ በተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ላይ እንደገለፁት፣ ብቁ ዜጋ ማለት ለአገሩና ለማህበረሰቡ ኃላፊነት የሚወስድ፣ ከሌብነትና ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት የሚሰጥ፣ ህግና መመሪያዎችን የሚያከብር እንዲሁም በልማትና በበጎ ፈቃድ ስራዎች ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ዜጋ ነው ብለዋል።

 ብቁ ዜጎችን መፍጠር የአገር እድገትና የተረጋጋ ማህበረሰብ መሠረት መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዋ፣ በመደመር ዕሳቤ መልካም እሳቤዎችን በማጉላት በከተሞች የሚከናወኑ ልማቶችን መደገፍና ሰው ተኮር ስራዎችን ማጠናከር ለወደፊት ትውልድ የሚተላለፍ እሴት መሆኑን አብራርተዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ የኮሚሽኑ ባለሙያዎችም ብቁ ዜጋነት በፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት፣ በሥነ-ምግባር መንቀሳቀስ፣ እርስ በርስ መከባበር እና በማህበራዊ ተሳትፎ እንደሚገለጽ አስረድተዋል። በአካባቢ ልማቶችና በበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች መሳተፍ እና የተሳለጠ አገልግሎት መስጠት የብቁ ዜጋ መለያ መሆኑንም አክለው ጠቁመዋል።

 የብቁ ዜጋ ግንባታ ከ “civic engagement” እና “good governance” ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው። የማህበራዊ ሳይንስ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት፣ ንቁ የሆኑ ዜጎች ሲኖሩ የመንግስት አገልግሎት ጥራት ያድጋል፣ የህዝብ ተሳትፎ ይጠናከራል እንዲሁም የልማት ፕሮጀክቶች ተፅዕኖ ይጨምራል።

 በኢኮኖሚና በማህበራዊ ልማት ጥናቶች መሠረት፣ የንቁ ዜጎች ተሳትፎ ከህዝብ አገልግሎት ቅልጥፍ፣ ከብልሹ አሰራር መቀነስ፣ ከማህበራዊ መተማመን (social trust)ና መጠናከር እና ከልማት ፕሮጀክቶች ዘላቂነት ጋር በቀጥታ ይገናኛል።

 ንቁና ብቁ ዜጎችን መፍጠር የሥነ-ምግባር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የመንግስትን የልማት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ለማስፈፀም ዋና መሠረት እንደሆነ በብዙ ሀገራት ተሞክሮ ተረጋግጧል።
👍1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ህዝብን ያሳተፈ ልማት፣ የፈጣንና ዘላቂ እድገት መሰረት!

ህዝብ ያሳተፈ የልማት ስራ ማለት ህዝቡ በልማት ሂደት ውስጥ ከእቅድ ዝግጅት ጀምሮ እስከ አፈጻጸምና ክትትል ድረስ በንቃት መተባበርን የሚያመለክት ተግባር ነው። ይህ ፅንሰ ሀሳብ ህዝብ ልማትን ከመንግስት ብቻ እንዳይጠብቅና የራሱን ጉልበት፣ እውቀትና ሀብት በመጠቀም በልማት ሂደት ውስጥ አስተዋፅዖ እንዲያደርግ የሚያበረታታ ነው።

ህዝብን ማሳተፍ ልማትና እድገትን የሚያፋጥን ተግባር ነው። ህዝቡ በልማት ጉድለቶች ውስጥ ሲሳተፍና የድርሻውን ሲወጣ የሰው ኃይል፣ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎች በቀላሉ ሲለሚገኙ መንግስት ብቻውን ሊያከናውናቸው የማይችሉ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ያግዛል።

ሌላኛው የህዝብ ተሳትፎ ፋይዳ የልማት ባለቤትነት ስሜትን መፍጠሩ ነው። ህዝቡ በራሱ ተሳትፎ በተከናወነ የልማት ፕሮጀክት ላይ የባለቤትነት ስሜት ስለሚያድርበት የተገነቡ መሠረተ ልማቶች እንዲጠበቁና ለረዥም ዓመታት ግልጋሎት እንዲሰጡ ያደርጋል።

መልካም አስተዳደርን በማስፈንና በውሳኔ አሰጣጥ ግልፀኝነት ላይም የህዝብ ተሳትፎ ፋይዳው ጉልህ ነው። ህዝቡ በልማት እቅድና በአፈጻጸም ሲሳተፍ ውሳኔዎች ግልፅ ይሆናሉ። ይህም ግልፅነትን (transparency) እና ተጠያቂነትን (accountability) ለማስፈን ምቹ መደላድል ከመፍጠሩም በላይ በመንግስትና በህዝብ መካከል ዘላቂ መተማመንን ይፈጥራል።

የህዝብ ተሳትፎ ማህበራዊ አንድነትንና ትብብርን ያጎለብታል። በጋራ ጉዳይ ላይ ህዝብን ማሳተፍ በተዘዋዋሪ መንገድ መተባበርን፣ መደጋገፍንና መተማመንን ማፅናትና ማጠናከር ተደርጎ መወሰድ አለበት። ይህ ደግሞ የህዝብን ጠንካራ አንድነትና የሀገርን ዘላቂ ሰላም መገንባት ያስችላል።

ተሳትፎ የህዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረገና የሚመጥን ልማትን እውን ለማድረግ ብሎም ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ለማነቃቃት ይጠቅማል። ህዝቡ በልማት ሂደት ውስጥ ሲሳተፍ የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ከህዝቡ እውነተኛ ፍላጎቶች ጋር ይጣጣማሉ። ህዝብ በአካባቢ ልማት ሲሳተፍ ኢኮኖሚ ይነቃቃል፤ የስራ እድሎች ይፈጠራሉ፣ የንግድና የአገልግሎት እንቅስቃሴዎች ይጨምራሉ።

በአጠቃላይ ህዝብን ያሳተፈ የልማት ስራን ማከናወን ፈጣን፣ ዘላቂና የህዝብን ፍላጎት የሚያሟላ ልማት ለማረጋገጥ አስፈላጊ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽንም መላ ህዝቡን በማሳተፍ የነዋሪውን እውነተኛ የልማት ጥያቄዎችና ፍላጎቶች ማዕከል ያደረጉ የአካባቢ ልማት ፕሮጀክቶችን ቀርፆ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው። ኮሚሽኑ ህዝብና መንግስት በትብብር የሚሰሩበትን አውድ በመፍጠር ዘላቂ ልማትን የሚያጠናክሩ የኅብረተሰብ ተሳትፎ ስራዎችን እያስፋፋ ይገኛል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ቡልቡላ አካባቢ በህዝብ ተሳትፎ እየተፈጠሩ የሚገኙ ሞዴል ሞኖሪያ ብሎኮች በከፊል...
3👍1
ባለፉት ሰባት ዓመታት ከዘጠኝ ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በኅብረተሰብ ተሳትፎ ተሰብስቦ ለአካባቢ ልማት ውሏል።

የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮምሽን ባለፉት 7 ዓመታት በኅብረተሰቡ ተሳትፎ የተከናወኑ ተግባራትንና የተመዘገቡ ውጤቶችን ለ3ኛ ዙር ከጉለሌ፣ አዲስ ከተማ እና ኮልፌ ክፍለ ከተሞች የብሎክ ካውንስል አመራሮች ጋር ገምግሟል።

በግምገማው ከ9 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የአካባቢ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን መገንባትና የተቀናጁ ሞዴል ብሎኮችን ማስፋፋት መቻሉ ተመላክቷል።

ነዋሪዎችም በአካባቢያቸው ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በራሳቸው አቅም ለመፍታት ያላቸው ተሳትፎ እየጠናከረ መምጣቱን የኅብረተሰብ ተሳትፎ ዘርፍ ምክትል ኮምሽነር ወ/ሮ ፀሐይ ኪባሞ ተናግረዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ የብሎክ ካውንስል አመራሮች በበኩላቸው በኅብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወኑ የአካባቢ ልማቶች አዲስ አበባን ዘመናዊ ከተማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ገልፀው፣ ወደፊትም ከኮሪደር ልማት ጋር የተናበቡ ሞዴል መኖሪያ ብሎኮችንና የአካባቢ ልማት ፕሮጀክቶችን ለማስፋፋት ከመንግስት ጎን በመቆም እንደሚሰሩ ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
2👍1