የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
812 subscribers
2.14K photos
47 videos
265 links
Download Telegram
በክረምት የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የ 3ሺህ 400 ቤቶች ግንባታ የተጀመረ ሲሆን ከእነዚህ መካከል የ2ሺህ 500 ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞችና ለሃገር ባለዉለታ ዜጎች ተላልፏል፡፡ -ከንቲባ አዳነች አቤቤ
3
ከብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን የተጠናቀቀውን የሳር ቤት-ጀርመን አደባባይ-ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተናል። 589 ሄክታር በላይ የሚሸፍነው ከባቢ ከካዛንቺስ ቀጥሎ ሰፊው የልማት ስፍራ ሆኗል። ፕሮጀክቱ 16.5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣ የ3 ኪሎ ሜትር ተጨማሪ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ብሎም 33 ኪሎ ሜትር የተዘረጋ የእግረኛ መንገድ አካትቷል። የፕላዛዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የሕፃናት መጫወቻዎች እና 5.2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራ ተከናውኗል። የመኪና ማቆሚያዎች፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ስፍራዎች፣ በግል እና የመንግሥት ተቋማት የተገቡ 1107 ሱቆች በልማት ሥራው የተሠሩ ናቸው። የኮሪደር ልማቱ 50.5 ሄክታር አረንጓዴ ሥፍራ፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ 13.3 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መጋለቢያ መንገድ፣ 38 የአውቶቡስ እና ታክሲ መጫኛ-ማውረጃዎችን አካትቷል። እንደዚህ ያሉት ሀገራዊ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ከማሳደግ ባሻገር የትራፊክ እንቅስቃሴን በማሻሻል፣ ማኅበራዊ መስተጋብርን በማጠንከር ደማቅ ለእንቅስቃሴ ምቹ እና ዘላቂነት ያላቸው የከተማ ሥፍራዎች በመፍጠር ረገድ ዐቢይ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ።

Together with members of the Prosperity Party Executive Committee, we visited the completed corridor development project extending from Sar Bet to German Square, the Garment Factory, and the Furi area. Covering more than 589 hectares, it stands as the second largest and widest site after Kazanchis. The project includes the construction of 16.5 km of asphalt roads, an additional 3 km of internal roads, and pedestrian walkways stretching a total of 33 km. It features plazas, sports facilities, children’s playgrounds, and 5.2 km of riverbank development. In addition, there are parking areas and terminals, an electric car charging station, and 1,107 shops built by both private and government entities. The development also encompasses 50.5 hectares of green spaces, public toilets, 13.3 km of bicycle lanes, and 38 taxi and bus bays. Our national corridor development projects like this one are playing a vital role in boosting local economic activity, improving mobility, and enhancing social interaction by creating vibrant, accessible, and sustainable urban spaces.

PM Abiy Ahmed Ali
ዛሬም የረዳን ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን !

ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመነት ፉሪ የሚዘልቀውን የኮሪደር ልማት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባላት በተገኙበት መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ።

ሕዝባችንን በታማኝነት፣ በቅንነት ለማገልገል የገባነውን ቃል ቆጥረን እየተገበርን እንገኛለን። የተሰሩት መሰረተ ልማቶች ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የስራ ዕድል የፈጠረ እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ መሰረታዊ የሆነ ለዉጥ ማምጣት በሚያስችል መልኩ የተሰራ ነው።

በልማቱ ከመሬት በላይ ከሚታየው እኩል ከመሬት በታች ጭምር የተሰሩ በርካታ ስራዎች የከተማችንን አገልግሎት የሚያሳልጥ፣ በዘላቂነት ስማርት ሲቲ ለማድረግ የሰነቅነዉን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል መሰረታዊ ስራ የተሰራበት፣ ሰፊ የስራ ዕድል የተፈጠረበት ሲሆን፤ ለቱሪዝም ዘርፉ ተጨማሪ እሴት፤ የስበት ማዕከል የሆኑ ፅዳት፣ ውበት፣ አገልግሎትን ያጣመሩ ስራዎችም በስፋት ተሰርተውበታል ።

ይህ የኮሪደር ልማት በሁለተኛ ዙር ከጀመርነው 6ኛዉና ከካዛንቺስ ኮሪደር ቀጥሎ በከተማችን ሁለተኛው ረጅሙ እና ሰፋ ያለ አካባቢ የሚሸፍነው ሲሆን ከ589 ሄክታር በላይ ቦታ የለማበት ነው።

• እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ 16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ ( በተጨማሪ 3 .5 ኪ. ሜ የውስጥ ለውስጥ መንገድ) አለው ፣
• 33 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ ፣
• 13.3 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ ፣
• 21 የተለያዩ ፕላዛዎች ፣
• ክረምት ከበጋ ፣ በቀን እና በምሽት አገልግሎት የሚሰጡ 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣
• 20 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች ፣
• 5.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፣
• 20 የመኪና ማቆሚያ ቦታና ተርሚናሎች ፣ 1 የመኪና ቻርጂንግ ስቴሽን ፣
• በግለሰቦች እና በመንግስት የተገነቡ 1,107 የንግድ ቤቶች ፣
• 50.5 ሄክታር ስፋት ያላቸዉ አረንጓዴ ቦታዎች ፣
• 40 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ፣
• 38 የታክሲና አውቶቡስ ቤይ ፣
• 13 ካፌዎች እና 1 ሬስቶራንት እንዲሁም ከ 1 ሄክታር በላይ የነርሰሪ ቦታን በዉስጡ አካትቶ ይዟል ።

ይህንን ለከተማችን ተጨማሪ ድምቀት ፣ ለዜጎቻችን መጠነ ሰፊ የስራ እድል እና የእውቀት ሽግግር የፈጠረን ፣ ለነዋሪዎቿ ደግም ምቾትን ያጎናፀፈውን ግዙፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በታለመለት ጊዜ በጥራት እና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁ ፣ ከመደበኛ ስራችሁ ጎን ለጎን ሌት ተቀን ለለፋችሁ በየደረጃዉ ያላችሁ የከተማችን አመራሮች፣ ባለሞያዎች፣ እንዲሁም በልማት ስራው ሁልጊዜም የዘወትር ድጋፍ እና ትብብሩ ላልተለየን የአካባቢው ነዋሪ ማህበረሰብ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
4
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት፣ 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

Prime Minister Abiy Ahmed will respond to questions and provide explanations during the 6th round, 5th year, 2nd regular session of the House of People's Representatives.

#PMOEthiopia
2
ብዝሃ ዘርፍ ትብብርን በተመለከተ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና መር ወደ ብዝሃ ዘርፍ እንዲሸጋገር የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ ሆኗል። መንግስት ከህዝብ ጋር ተሳስሮ ልማት እንዲያመጣ ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠውም ከለውጡ ወዲህ ነው። ለአብነትም መንግስትና ህዝብ ተሳስረው በአረንጓዴ አሻራ አማካኝነት 48 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል ችለዋል። ለዚህ ስኬት ደግሞ ከ25 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ሳይታክቱ በነጻ በየ ዓመቱ ወጥተው ችግኞችን መትከል ችለዋል። ይህም የመንግስትና ህዝብ ቅንጅትን በተግባር ያሳየ ነው።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የእዳ ሽግሽግን በተመለከተ

ኢትዮጵያ አሁን ላይ እዳዋን ለመክፈል ምንም ችግር የለባትም። በሪፎርሙ አመካኝነት ከ4 አስከ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የእዳ ሽግሽግ ተደርጓል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም መንግስት አንድም ዶላር የንግድ ብድር አልወሰደም። ይህም እዳን ለመቆጣጠር ያለንን ጽኑ አቋም ያሳያል።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ግብርናን በተመለከተ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም በሁሉም መመዘኛዎች ከፍተኛ ለውጥ በፍጥነት ማስመዝገብ ችሏል። ለአብነትም ግብርና ብቻውን የ7 ነጥብ 3 በመቶ እድገት አስመዝግቧል።

በምርት ደረጃም ሩዝን ወስደን ብናይ ከነበረበት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 63 ኩንታል ማሳደግ የተቻለ ሲሆን የስንዴ ምርትንም ከለውጡ በፊት ከነበረበት 47 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 280 ሚሊዮን ኩንታል በአጠረ ጊዜ ውስጥ አሳድግነዋል።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ገቢን በተመለከተ

ያለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛ ገቢ ያገኘችበት ነው። ለአብነትም ከሸቀጦች ወጪ ንግድ 8 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል። ከሬሚታንስ 7 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ የተገኘ ሲሆን ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም በቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ ሪዘርቭ በ10 እጥፍ አድጓል።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የዋጋ ንረትን በተመለከተ

መንግስት የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት 440 ቢሊዮን ብር ድጎማ አድርጓል። ከዚህም ውስጥ 160 ቢሊዮን ብር የሚሆነው ለደሞዝ ጭማሪ ድጎማ የተደረገ ነው። ለነዳጅም 140 ቢሊዮን ድጎማ ተደርጓል። በዚህም የጥቅምት ወር የዋጋ ንረት ወደ 11 ነጥብ 7 ወርዷል። ይህም ከሪፎርሙ ዘመን ጀምሮ ትንሹ የዋጋ ንረት ሆኖ ተመዝግቧል። በቀጣይም ይህን አሃዝ ወደ አንድ አሃዝ ለማውረድ ይሰራል።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
2
"ኢትዮጵያ በዘንድሮው ዓመት ያላምንም ጥርጥር ባለሁለት አሃዝ እድገት ታስመዘግባለች።" - ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያን በተመለከተ

አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ በዓመት ከ100 ሚሊዮን በላይ ተጓዦችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፤ ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ በቻ ሳይሆን ትልቁ የአውሮፕላን ማረፊያ ባለቤት ያደርገዋል። ለዚህ ግዙፍ የ10 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንትም ኢትዮጵያን በቀጣይነት የአፍሪካ የአቬሽን ማእከል ሆና እንድትቀጥል ያደርጋታል።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👍2
ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ

ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ፣ ማዳበሪያ፣ አውሮፕላን ማረፊያና ቤቶች ልማት ላይ የምንሰራው ስራ ጨዋታ ቀያሪ ነው። የማዳበሪያ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ብቻ የግብርና ምርታማነትን ቢያንስ በእጥፍ ማሳደግ ይቻላል። ይህም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ትልቅ እጥፋት ነው። ሌሎችም ሲጠናቀቁ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ይመጣል።

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ሃሳቦች -ክፍል አንድ

ብዝሃ ዘርፍ ትብብርን በተመለከተ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና መር ወደ ብዝሃ ዘርፍ እንዲሸጋገር የተነደፈው ፖሊሲ በእጅጉ ውጤታማ ሆኗል። መንግስት ከህዝብ ጋር ተሳስሮ ለምት እንዲያመጣ ግልጽ አቅጣጫ የተቀመጠውም ከለውጡ ወዲህ ነው። ለአብነትም መንግስትና ህዝብ ተሳስረው በአረንጓዴ አሻራ አማካኝነት 48 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል ችለዋል። ለዚህ ስኬት ደግሞ ከ25 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን ሳይታክቱ በነጻ በየ ዓመቱ ወጥተው ችግኞችን መትከል ችለዋል። ይህም የመንግስትና ህዝብ ቅንጅትን በተግባር ያሳየ ነው።

አምስቱ የሪፎርሙ ዓላማዎች:-

1) የተዛባ የኢኮኖሚ ስርዓትን ማረቅ
2) የንግድ ከባቢን ማሻሻል
3) የዘርፎች ምርታማነትና የመወዳዳር አቅም ማሳደግ
4) የማስፈጸም አቅምን ማሳደግ
5) ዘላቂ የፋይናንስ ስርዓት ማረጋገጥ

የእዳ ሽግሽግን በተመለከተ
ኢትዮጵያ አሁን ላይ እዳዋን ለመክፈል ምንም ችግር የለባትም። በሪፎርሙ አመካኝነት ከ4 አስከ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የእዳ ሽግሽግ ተደርጓል። ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎም መንግስት አንድም ዶላር የንግድ ብድር አልወሰደም። ይህም እዳን ለመቆጣጠር ያለንን ጽኑ አቋም ያሳያል።

ግብርናን በተመለከተ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም በሁሉም መመዘኛዎች ከፍተኛ ለውጥ በፍጥነት ማስመዝገብ እሏል። ለአብነትም ግብርና ብቻውን የ7 ነጥብ 3 በመቶ እድገት አስመዝግቧል። በምርት ደረጃም ሩዝን ወስደን ብናይ ከነበረበት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 63 ኩንታል ማሳደግ የተቻለ ሲሆን የስንዴ ምርትንም ከለውጡ በፊት ከነበረበት 47 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 280 ሚሊዮን ኩንታል በአጠረ ጊዜ ውስጥ አሳድግነዋል።

ገቢን በተመለከተ
ያለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛ ገቢ ያገኘችበት ነው። ለአብነትም ከሸቀጦች ወጪ ንግድ 8 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል። ከሬሚታንስ 7 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ የተገኘ ሲሆን ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካትም በቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል። በዚህም የኢትዮጵያ ሪዘርቭ በ10 እጥፍ አድጓል።

የዋጋ ንረትን በተመለከተ
መንግስት የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት 440 ቢሊዮን ብር ድጎማ አድርጓል። ከዚህም ውስጥ 160 ቢሊዮን ብር የሚሆነው ለደሞዝ ጭማሪ ድጎማ የተደረገ ነው። ለነዳጅም 140 ቢሊዮን ድጎማ ተደርጓል። በዚህም የጥቅምት ወር የዋጋ ንረት 11 ነጥብ 7 ወርዷል። ይህም ከሪፎርሙ ዘመን ጀምሮ ትንሹ የዋጋ ንረት ሆኖ ተመዝግቧል። በቀጣይም ይህን አሃዝ ወደ አንድ አሃዝ ለማውረድ ይሰራል።

አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያን በተመለከተ

አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ ከ100 ሚሊዮን በላይ ተጓዦችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፤ ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ በቻ ሳይሆን ትልቁ የአውሮፕላን ማረፊያ ባለቤት ያደርገዋል። ለዚህ ግዙፍ የ10 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንትም ኢትዮጵያን በቀጣይነት የአፍሪካ የአቬሽን ማእከል ሆና እንድትቀጥል ያደርጋታል።

ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ

ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ፣ ማዳበሪያ፣ አውሮፕላን ማረፊያና ቤቶች ልማት ላይ የምንሰራው ስራ ጨዋታ ቀያሪ ነው። የማዳበሪያ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ብቻ የግብርና ምርታማነትን ቢያንስ በእጥፍ ማሳደግ ይቻላል። ይህም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ትልቅ እጥፋት ነው። ሌሎችም ሲጠናቀቁ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ይመጣል።

የኮሪደር ልማትን በተመለከተ
የኮሪደር ልማት የቦታና ጊዜ ምልከታን የሚቀይር ነው። ለአብነትም በአዲስ አበባ ብቻ ከአንድ ኚህ በላይ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ተገንብቷል። በርካታ ወጣቶች ወደ ስፖርት እየተመለሱ ነው። ይህም ማህበረሰብን የመገንባት ስራ ነው። የትውልድ ስነ ልቦና ስብራትን እያረቀ ያለ ስራም ጭምር ነው። ይህን ማንም ሰው የሚያየው፤ ማንም ሰው የሚናገረው ጉዳይ ነው።

የፕሮጀክቶች ክትትልን በሚመለከት
ኢትዮጵያ ውስጥ 346 የመንገድ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ ናቸው። በፌደራል መንግስት ብቻ 26 ሺህ 500 ኪሎ ሜትር በፌደራል መንግስት ብቻ እየተገነባ ነው። እነዚህን ሁሉ ፕሮጀክቶች በተመሳሳይ መከታታል እጅግ አስቸጋሪ ስራ ነው። ግድብን በሚለከትም ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 14 መካከለኛና አነስተኛ የግድብ ፕሮጀክቶች አሉ። መንግስት የማስፈጸም አቅሙን በማሳደግ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየሰራ ነው።

ከተረጂነት መላቀቅን በተመለከተ
ተሪጂነት የመስራት ጉልበትን የሚበላ ካንሰር ነው። በስንዴ፣ ፍራፍሬና ሌማት ትሩፋት የምንሰራው ስራም ከተረጂነት ለመላቀቅ ባለን ቁርጠኝነት ነው። ስለዚህ ጨከን ብለን ተረጂነት ይበቃናል ማለት አለብን። ደግሞም እንችላለን። እርዳታ ብዙ ጣጣ በውስጡ አለበት። ኢትዮጵያን መለመኛ ማድረግ መቆም አለበት።

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እድገት በሚመለከት
በኢትዮጵያ የመጣው የእሳቤ ለውጥ በርካታ እምርታዎችን አምጥቷል። ኢትዮጵያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2032 በአፍሪካ 2ኛ በ2036 ደግሞ ከአፍሪካ የመጀመሪያውን ኢኮኖሚ እንደምትገነባ ጥርጥር የለኝም

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
2