ዛሬ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ እጅግ የተጎሳቆሉ ቤቶችን በማፍረስ የገነባናቸውን 253 ቤቶች የቅድሚያ ቅድሚያ ለሚገባቸዉ የሀገር ባለውለታዎች፣ ሀገር ሲያገለግሉ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ የአልጋ ቁራኛዎች፣ ጧሪ ደጋፊ ለሌላቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች አስተላልፈናል ።
ባለፈዉ እሁድ ያስተላለፍናቸው ላይ የዛሬው 253 ቤቶች ሲጨመሩ እሰከአሁን በዘንድሮው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በ 3 ወራት ጊዜ ውስጥ ከገነባናቸው 3 ሺህ በላይ ቤቶች ውስጥ 1 ሺህ 924 ቤቶችን የቅድሚያ ቅድሚያ ለሚገባቸው ወገኖቻችን ማስተላለፍ ችለናል።
ቤቶቹ የጸዱ፣ መሰረታዊ ግብአቶች የተሟሉላቸዉ፣ ዘመናዊ እና ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን የሚፈጥሩ፣ የራሳቸው ቅጥር ጊቢና የጋራ መገልገያዎች ያላቸው፣ የህፃናት መዝናኛና መጫወቻ እንዲሁም የንግድ ሱቆችን ያካተቱ ናቸው።
ይህንን የበጎ ፈቃድ ተግባር ከጎናችን ሆናችሁ ለምትደግፉ ልበ ቀናዎች እና ያተባበራችሁ የከተማችን አመራሮች በሙሉ በተጠቃሚዎች ስም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
መልካም የመስቀል ደመራ በዓል
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ባለፈዉ እሁድ ያስተላለፍናቸው ላይ የዛሬው 253 ቤቶች ሲጨመሩ እሰከአሁን በዘንድሮው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በ 3 ወራት ጊዜ ውስጥ ከገነባናቸው 3 ሺህ በላይ ቤቶች ውስጥ 1 ሺህ 924 ቤቶችን የቅድሚያ ቅድሚያ ለሚገባቸው ወገኖቻችን ማስተላለፍ ችለናል።
ቤቶቹ የጸዱ፣ መሰረታዊ ግብአቶች የተሟሉላቸዉ፣ ዘመናዊ እና ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን የሚፈጥሩ፣ የራሳቸው ቅጥር ጊቢና የጋራ መገልገያዎች ያላቸው፣ የህፃናት መዝናኛና መጫወቻ እንዲሁም የንግድ ሱቆችን ያካተቱ ናቸው።
ይህንን የበጎ ፈቃድ ተግባር ከጎናችን ሆናችሁ ለምትደግፉ ልበ ቀናዎች እና ያተባበራችሁ የከተማችን አመራሮች በሙሉ በተጠቃሚዎች ስም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
መልካም የመስቀል ደመራ በዓል
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤6👍1👏1
ዛሬ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎችም ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በአይነቱ የመጀመሪያ እና እጅግ ዘመናዊ የሆነዉን የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስን መርቀን ስራ አስጀምረናል ።
የከተማችን አስተዳደር በሚሰራቸዉ የልማት ስራዎች ሁሉ ኪነ ጥበብን አበይት የትኩረት አቅጣጫዉ አድርጎ እየተገበረ ይገኛል ።በዚህም ባለፉት ጥቂት አመታት ነባሮቹን በማደስ እና ዘመናዊ እና ደረጃቸዉን የጠበቁ እንዲሆኑ በማድረግ እንዲሁም አዳዲስ እና ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸዉ የቲያትርና የሲኒማ ኮምፕሌክሶች ገንብተን ለኪነ ጥበብ ዘርፉ እድገት አስተዋፆ እያበረከትን እንገኛለን ።
ዛሬ ያስመረቅነዉ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ ፦
ባለ14 ወለል ህንፃ ፣2 ዘመናዊ ሲኒማ ቤቶችን
፣የቲያትር አዳራሽ ፣ 3 የተለያዩ አዳራሾችን ፣ የሆቴል እና ሪስቶ ራት ዘመናዊ ካፍቴሪያዎችን እና ፓርኪንግ አገልግሎት ይዟል ።
የጥበብ ስራ በአዳራሽ ብቻ የተወሰነ ባለመሆኑ እና ወደ ማህበረሰቡ ቀረብ እንዲል በከተማችን በተገበርነዉ ሁለንተናዊ ለዉጥ የተለያዩ የዉጭ የኪነ ጥበብ ስራ የሚከወንባቸዉ ከ 160 በላይ አንፊ ቲአትርና ፕላዛዎችን ገንብተን ለአገልግሎት አዉለናል ።
የኪነ ጥበብ ዘርፉ በፈጠረዉ ምቹ ሁኔታ የዉስጥ ቁጭትን በመፍጠር ትዉልድን በመልካም ስራ እንድናንፅ ከወዲሁ ጥሪዬን አቀርባለዉ ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የከተማችን አስተዳደር በሚሰራቸዉ የልማት ስራዎች ሁሉ ኪነ ጥበብን አበይት የትኩረት አቅጣጫዉ አድርጎ እየተገበረ ይገኛል ።በዚህም ባለፉት ጥቂት አመታት ነባሮቹን በማደስ እና ዘመናዊ እና ደረጃቸዉን የጠበቁ እንዲሆኑ በማድረግ እንዲሁም አዳዲስ እና ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸዉ የቲያትርና የሲኒማ ኮምፕሌክሶች ገንብተን ለኪነ ጥበብ ዘርፉ እድገት አስተዋፆ እያበረከትን እንገኛለን ።
ዛሬ ያስመረቅነዉ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ ፦
ባለ14 ወለል ህንፃ ፣2 ዘመናዊ ሲኒማ ቤቶችን
፣የቲያትር አዳራሽ ፣ 3 የተለያዩ አዳራሾችን ፣ የሆቴል እና ሪስቶ ራት ዘመናዊ ካፍቴሪያዎችን እና ፓርኪንግ አገልግሎት ይዟል ።
የጥበብ ስራ በአዳራሽ ብቻ የተወሰነ ባለመሆኑ እና ወደ ማህበረሰቡ ቀረብ እንዲል በከተማችን በተገበርነዉ ሁለንተናዊ ለዉጥ የተለያዩ የዉጭ የኪነ ጥበብ ስራ የሚከወንባቸዉ ከ 160 በላይ አንፊ ቲአትርና ፕላዛዎችን ገንብተን ለአገልግሎት አዉለናል ።
የኪነ ጥበብ ዘርፉ በፈጠረዉ ምቹ ሁኔታ የዉስጥ ቁጭትን በመፍጠር ትዉልድን በመልካም ስራ እንድናንፅ ከወዲሁ ጥሪዬን አቀርባለዉ ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤1👍1
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ አከባበር ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ እጅግ በደመቀና ባማረ ሁኔታ ተጠናቅቋል ።
የሆረ ፊንፊኔ እሬቻ ክብረ በዓል የኦሮሞ ህዝብ ብቻ ሳይሆን በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች፣ የተለያዩ አገራት ጎብኚዎች፣ የባህልና ታሪክ ተመራማሪዎች በታደሙበት በልዩ ሁኔታ ደምቆ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ተጠናቅቋል ።
በኮሪደር እና በወንዝ ዳርቻዎች ልማት ያማረችዉ አዲስ አበባችን ለአደባባይ ክብረ በዓላት፣ ለበዓሉ ታዳሚያንና ከመላዉ ዓለም ለሚመጡ ቱሪስቶች ተጨማሪ ድምቀት እና ምቾት ሆናለች ።
በዓሉ እጅግ ባማረ፣ ደማቅና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እሴቱንና ቱፊቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁ አካላት ሁሉ ፣ በተለይም ለከተማችን ነዋሪዎች የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የሆረ ፊንፊኔ እሬቻ ክብረ በዓል የኦሮሞ ህዝብ ብቻ ሳይሆን በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች፣ የተለያዩ አገራት ጎብኚዎች፣ የባህልና ታሪክ ተመራማሪዎች በታደሙበት በልዩ ሁኔታ ደምቆ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ተጠናቅቋል ።
በኮሪደር እና በወንዝ ዳርቻዎች ልማት ያማረችዉ አዲስ አበባችን ለአደባባይ ክብረ በዓላት፣ ለበዓሉ ታዳሚያንና ከመላዉ ዓለም ለሚመጡ ቱሪስቶች ተጨማሪ ድምቀት እና ምቾት ሆናለች ።
በዓሉ እጅግ ባማረ፣ ደማቅና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እሴቱንና ቱፊቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁ አካላት ሁሉ ፣ በተለይም ለከተማችን ነዋሪዎች የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤7👍1
3ኛውየአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡
ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ ዙር አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባኤ በማጽደቅ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያስተላልፋል::
ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ተመራጭ አባላት ከመራጩ ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ምላሽ ይሰጣል፡፡
በተመሳሳይ ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ይጠናቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ ዙር አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባኤ በማጽደቅ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያስተላልፋል::
ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ተመራጭ አባላት ከመራጩ ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ምላሽ ይሰጣል፡፡
በተመሳሳይ ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ይጠናቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
❤2
3ኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛመደበኛ ጉባዔዉን እያካሄደ ይገኛል
ምክር ቤቱ 3ኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛመደበኛ ጉባዔዉን በእድዋ ድል መታሰቢያ በሚገኘዉ የምክር ቤቱ አዳራሽ እያካሄደ ነዉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር በመክፈቻ ንግግራቸዉ እንደተናገሩት 2018 ዓ.ም ህዳሴ ግድብን ያጠናቀቅንበት በርካታ ፕሮጀክት በሩብ ዓመቱ የተጀመሩበት ዓመት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡
አክለዉም ለ18ኛዉ የሰንደቅ ዓላማ ቀን እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል፡፡
የዛሬዉ አጀንዳዎችም ፤-የምክር ቤቱን 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባዔ ማፅደቅ፤በከተማዋ ባሉ ክፍለ ከተሞች የተመረጡ የምክር ቤት ዓባላት በበጀት ዓመቱ በ1ኛ ሩብ ዓመት ህዝብ ጋር ወርደዉ በአደረጉት ዉይይት ለቀረቡላቸዉ ጥያቄዎች ለጉባዔዉ በማቅረብ በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና በሌሎች የምክር ቤት አባላት ምላሽ መስጠት እና ልዩ ልዩ ሹመቶችን ማፅደቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም በቀረበዉ የምክር ቤቱ 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ቃለ ጉባዔ ላይ ምክር ቤቱ ሃሳብ ሰጥቶበት በሙሉ ድምፅ ፀድቆ ጥያቄዎች በምክር ቤት አባላት እየቀረቡ ይገኛሉ፡፡
ምክር ቤቱ 3ኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛመደበኛ ጉባዔዉን በእድዋ ድል መታሰቢያ በሚገኘዉ የምክር ቤቱ አዳራሽ እያካሄደ ነዉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር በመክፈቻ ንግግራቸዉ እንደተናገሩት 2018 ዓ.ም ህዳሴ ግድብን ያጠናቀቅንበት በርካታ ፕሮጀክት በሩብ ዓመቱ የተጀመሩበት ዓመት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡
አክለዉም ለ18ኛዉ የሰንደቅ ዓላማ ቀን እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል፡፡
የዛሬዉ አጀንዳዎችም ፤-የምክር ቤቱን 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባዔ ማፅደቅ፤በከተማዋ ባሉ ክፍለ ከተሞች የተመረጡ የምክር ቤት ዓባላት በበጀት ዓመቱ በ1ኛ ሩብ ዓመት ህዝብ ጋር ወርደዉ በአደረጉት ዉይይት ለቀረቡላቸዉ ጥያቄዎች ለጉባዔዉ በማቅረብ በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና በሌሎች የምክር ቤት አባላት ምላሽ መስጠት እና ልዩ ልዩ ሹመቶችን ማፅደቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም በቀረበዉ የምክር ቤቱ 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ቃለ ጉባዔ ላይ ምክር ቤቱ ሃሳብ ሰጥቶበት በሙሉ ድምፅ ፀድቆ ጥያቄዎች በምክር ቤት አባላት እየቀረቡ ይገኛሉ፡፡
❤2
በአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት የተነሱ ጥያቄዎች
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል፡፡
በጉባኤው የምክር ቤት አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ባደረጉት የመራጭ ተመራጭ የገፅ ለገፅ ውይይት ምላሽ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል፡፡
የተነሱት ጥያቄዎች ፡-
👉 በበዓል ሰሞን እና ምሽትን ተገን በማድረግ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ ነዋሪዎችን ያማረሩ በመሆናቸው ለዚህም በቀጣይ ምን ታስቧል?
👉 ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለነዋሪዎች ለማቅረብ ከተማ አስተዳደሩ የያዛቸው እቅዶች ምንድን ናቸው?
👉 በአንድ አንድ የእሁድ ገበያ መደብሮች ከተቀመጠው ዋጋ በላይ ማስከፈል፣ ጥራታቸው ዝቅ ላሉ ምርቶች እኩል ዋጋ መጠየቅ እንደሚስተዋል እና ይህን ችግር ለመቅረፍ በቀጣይ ምን ታስቧል?
👉 በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ያልደረሰባቸው አካባቢዎች የኮሪደር ልማትን ለማዳረስ ከተማ አስተዳደሩ ምን አቅዷል?
👉 የጤና ጣብያ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ምን እንደታቀደ ቢገለፅ?
👉 መሰረቱ የማይናወጥ አካታች የወል ትርክት ለመገንባት ብሎም ተራማጅ አስተሳሰብ ማስረጽ፤ የእንችላለን ስነ-ልቦና ብሎም ልመናና ኋላ ቀር አስተሳሰብን በመስበር በኪነ- ጥበብ እያዋዙ ጠንካራ ኢንዱስትሪ ለመገንባትና ዘርፉን ለመደገፍ ከተማ አስተዳደሩ ምን አስቧል?
👉 የኑሮ ሁኔታን በተመለከተ እየተሰራ ያለው ስራ ጎን ለጎን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ፣ የነዋሪዎችን እርካታ ለማረጋገጥ የት፣ ምን ተሰርቷል?
👉 በመስከረም ወር የተካሄዱት ታላላቅ በዓላት በስኬት የመጠናቀቃቸውን ያህል በቀጣይም መሰል በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ ምን ታስቧል? ይሄንንስ ድል እንዴት አገኘነው?
👉 የኮሪደር ልማቱን ህብረተሰቡ በእኔነት እንዲጠብቀው፤ ከተማውን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል ወይ?
👉 ህብረተሰብ ከተማዋን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የሕግ ማዕቀፍ አለ? ማዕቀፍ አያስፈልግም ወይ?
👉 ወጣቶች ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ አልገቡም፤ ምን ታስቧል?
👉 የፌዴራል መንግስት የሰራተኞች ደሞዝ እንዲስተካከል ወስኗል ከተማ አስተዳደሩ ይህንን ተፈፃሚ ለማድረግ ምን ዝግጅት አድርጓል?
የሚሉ ጥያቄዎች በምክር ቤቱ አባላት የተነሱ ሲሆን ለጥያቆዎቹም በከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ ይሰጥባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል፡፡
በጉባኤው የምክር ቤት አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ባደረጉት የመራጭ ተመራጭ የገፅ ለገፅ ውይይት ምላሽ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቅርበዋል፡፡
የተነሱት ጥያቄዎች ፡-
👉 በበዓል ሰሞን እና ምሽትን ተገን በማድረግ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ ነዋሪዎችን ያማረሩ በመሆናቸው ለዚህም በቀጣይ ምን ታስቧል?
👉 ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለነዋሪዎች ለማቅረብ ከተማ አስተዳደሩ የያዛቸው እቅዶች ምንድን ናቸው?
👉 በአንድ አንድ የእሁድ ገበያ መደብሮች ከተቀመጠው ዋጋ በላይ ማስከፈል፣ ጥራታቸው ዝቅ ላሉ ምርቶች እኩል ዋጋ መጠየቅ እንደሚስተዋል እና ይህን ችግር ለመቅረፍ በቀጣይ ምን ታስቧል?
👉 በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ያልደረሰባቸው አካባቢዎች የኮሪደር ልማትን ለማዳረስ ከተማ አስተዳደሩ ምን አቅዷል?
👉 የጤና ጣብያ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ችግር ለመቅረፍ ምን እንደታቀደ ቢገለፅ?
👉 መሰረቱ የማይናወጥ አካታች የወል ትርክት ለመገንባት ብሎም ተራማጅ አስተሳሰብ ማስረጽ፤ የእንችላለን ስነ-ልቦና ብሎም ልመናና ኋላ ቀር አስተሳሰብን በመስበር በኪነ- ጥበብ እያዋዙ ጠንካራ ኢንዱስትሪ ለመገንባትና ዘርፉን ለመደገፍ ከተማ አስተዳደሩ ምን አስቧል?
👉 የኑሮ ሁኔታን በተመለከተ እየተሰራ ያለው ስራ ጎን ለጎን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ፣ የነዋሪዎችን እርካታ ለማረጋገጥ የት፣ ምን ተሰርቷል?
👉 በመስከረም ወር የተካሄዱት ታላላቅ በዓላት በስኬት የመጠናቀቃቸውን ያህል በቀጣይም መሰል በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ ምን ታስቧል? ይሄንንስ ድል እንዴት አገኘነው?
👉 የኮሪደር ልማቱን ህብረተሰቡ በእኔነት እንዲጠብቀው፤ ከተማውን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል ወይ?
👉 ህብረተሰብ ከተማዋን ከተሜ ሆኖ እዲጠብቃት የሕግ ማዕቀፍ አለ? ማዕቀፍ አያስፈልግም ወይ?
👉 ወጣቶች ኮደርስ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ አልገቡም፤ ምን ታስቧል?
👉 የፌዴራል መንግስት የሰራተኞች ደሞዝ እንዲስተካከል ወስኗል ከተማ አስተዳደሩ ይህንን ተፈፃሚ ለማድረግ ምን ዝግጅት አድርጓል?
የሚሉ ጥያቄዎች በምክር ቤቱ አባላት የተነሱ ሲሆን ለጥያቆዎቹም በከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ ይሰጥባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
❤2
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤያችንን ማካሄድ ጀምረናል ።
በመራጭ ተመራጭ መድረክ ላይ ከመረጠን ህዝብ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሚሰጥ ይሆናል።
Mana maree 3ffaa magaalaa Finfinnee bara hojii 5ffaa yaa'ii idilee 1ffaa gaggeessuu eegalleerea.
Waltajjii filataa fi filatamaa irratti gaafiilee uummata nu filate irraa ka'aniif deebii fi ibsi kan kennamu ta'a.
Waaqni Itoophiyaa Uummata Ishee Haa Eebbisu
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በመራጭ ተመራጭ መድረክ ላይ ከመረጠን ህዝብ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሚሰጥ ይሆናል።
Mana maree 3ffaa magaalaa Finfinnee bara hojii 5ffaa yaa'ii idilee 1ffaa gaggeessuu eegalleerea.
Waltajjii filataa fi filatamaa irratti gaafiilee uummata nu filate irraa ka'aniif deebii fi ibsi kan kennamu ta'a.
Waaqni Itoophiyaa Uummata Ishee Haa Eebbisu
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ አቶ ጥራቱ በየነ
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ተመራጭ አባላት በኩል ከመራጩ ህዝብ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል፡፡
የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል 10 በመቶ ለአዳዲስ ምሩቃን እንዲሁም 56 በመቶ ለሴቶች ስራ እድል እንደተፈጠረላቸው አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል፡፡
ለኢንተርፕራይዞች በመንግስት የልማት ስራዎችና በኢንዱስርሪዎች የጥሬ እቃ እንዲያቀርቡ በማድረግ የ2 ቢሊዩን የገቢያ ትስስር እንደተፈጠረላቸውም ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ 996 የመስሪያ ሸዶችን ለአዳዲስ ስራ ፈላጊዎች ማስተላለፍ መቻሉንም እና ሌሎችን በፍጥነት ለማስተላፍ በአመቱ መጨረሻ ለ350 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እተሰራ መሆኑንም አቶ ጥራቱ በየነ አስረድተዋል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ተመራጭ አባላት በኩል ከመራጩ ህዝብ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት 3 ወራት ከ96 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል፡፡
የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል 10 በመቶ ለአዳዲስ ምሩቃን እንዲሁም 56 በመቶ ለሴቶች ስራ እድል እንደተፈጠረላቸው አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል፡፡
ለኢንተርፕራይዞች በመንግስት የልማት ስራዎችና በኢንዱስርሪዎች የጥሬ እቃ እንዲያቀርቡ በማድረግ የ2 ቢሊዩን የገቢያ ትስስር እንደተፈጠረላቸውም ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ 996 የመስሪያ ሸዶችን ለአዳዲስ ስራ ፈላጊዎች ማስተላለፍ መቻሉንም እና ሌሎችን በፍጥነት ለማስተላፍ በአመቱ መጨረሻ ለ350 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እተሰራ መሆኑንም አቶ ጥራቱ በየነ አስረድተዋል፡፡
❤2
3ተኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛመደበኛ ጉባዔ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር በሰጡት ማብራሪያ እና ምላሽ እንደገለፁት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በከተማችን በቅርቡ ተመርቀዉ ወደስራ የገቡት አዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ለዚህ ማሳያ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በዚህ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰፊ አገልግሎት እና ሰፊ ተገልጋይ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸዉ ተቋማት በመለየት አደረጃጀትን እና አሰራርን በመዘርጋት እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ ትግበራ መግባት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
በዋና መስሪያ ቤት በአራዳ ክፍለ ከተማ 13 የሚሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 107 አገልግሎቶችን በመያዝ የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት እየተሰራ አንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይም በቦሌ ክፍለ ከተማ በአዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 96 አገልግሎቶችን እንዲሁም የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት በጥቅሉ 114 አገልግሎቶች እንዲገቡ ተደርጓል፤
በአመለካከት ፣በእዉቀት እና በክህሎት የበቁ ነባርና አዳዲስ ተመረቂ ባለሙያዎችን በማሰልጠንና በመመደብ ፤የቅሬታ አፈታት ስርዓትን በማዘመን ፤ከተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ይፈጠራሉ ተብለዉ የሚገመቱ ችግሮችን ከወዲሁ ለማረም የተቻለበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡
በዚህም ከየትኛዉም በኩል የሚመጡ የዜጎች ምልልስ በማስቀረት፤ወጪና ጊዜን በመቆጠብ የተገልጋይን እርካታ ከፍ ማድረግ የተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር ተናግረዋል፡፡
ይህም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት እቅድ ተይዞ በልዩ ትኩረት በቅንጅት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩልም አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ በተመለከተ ለተነሳላቸዉ ጥያቁ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸዉና ክፍያዉ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን አመላክተዋል ::
በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር በሰጡት ማብራሪያ እና ምላሽ እንደገለፁት የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በከተማችን በቅርቡ ተመርቀዉ ወደስራ የገቡት አዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ለዚህ ማሳያ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በዚህ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰፊ አገልግሎት እና ሰፊ ተገልጋይ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸዉ ተቋማት በመለየት አደረጃጀትን እና አሰራርን በመዘርጋት እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ ትግበራ መግባት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
በዋና መስሪያ ቤት በአራዳ ክፍለ ከተማ 13 የሚሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 107 አገልግሎቶችን በመያዝ የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት እየተሰራ አንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይም በቦሌ ክፍለ ከተማ በአዲስ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 12 የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት 96 አገልግሎቶችን እንዲሁም የተለዩ የፌደራል ተቋማትን በማካተት በጥቅሉ 114 አገልግሎቶች እንዲገቡ ተደርጓል፤
በአመለካከት ፣በእዉቀት እና በክህሎት የበቁ ነባርና አዳዲስ ተመረቂ ባለሙያዎችን በማሰልጠንና በመመደብ ፤የቅሬታ አፈታት ስርዓትን በማዘመን ፤ከተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ይፈጠራሉ ተብለዉ የሚገመቱ ችግሮችን ከወዲሁ ለማረም የተቻለበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡
በዚህም ከየትኛዉም በኩል የሚመጡ የዜጎች ምልልስ በማስቀረት፤ወጪና ጊዜን በመቆጠብ የተገልጋይን እርካታ ከፍ ማድረግ የተቻለበት ሁኔታ መፈጠሩን ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር ተናግረዋል፡፡
ይህም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት እቅድ ተይዞ በልዩ ትኩረት በቅንጅት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩልም አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ በተመለከተ ለተነሳላቸዉ ጥያቁ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸዉና ክፍያዉ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን አመላክተዋል ::
❤2
በከተማዋ የተከናወኑ ሁነቶች እና አበይት የአደባባይ በዓላት ስኬት ከህዝቡ ጋር በጋራ በመሰራቱ የተገኘ ውጤት መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል ፡፡
በጉባኤው የተለያዩ የምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ያስፈልጋቸዋል ያሉትን ጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል ፡፡
የምክር ቤት አባላት ያቀረቧቸውን ጥያቄ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ፡፡
አዲስ አበባ ላይ በተሰሩና እየተሰሩ ባሉ የኮሪደር ልማት ከተማዋ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤዎችን የማዘጋጀት ዓቅሟ እያደገ መጥቷል፤ በእነዚህ ጉባኤዎችና በመስከረም ወር የተከናወኑ ዓበይት የአደባባይ በዓላት በከተማዋ የተከናወኑበት ወር ሲሆን እነዚህ ሁነቶች በድምቀት ተከብረው አልፈዋል ለዚህ ሰኬት የተሰሩ ስራዎች ምንድናቸው ለሚለው የምክር ቤት አባላት ጥያቄ ከንቲባዋ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ለበዓላቱና ለሁነቶቹ ስኬት ከህዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ግልፅነት በመፍጠር ወደ ስራ መገባቱን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የገለፁት፡፡
በተለይ በተከናወኑ ጉባኤዎች፣ ሆቴሎች የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ እና ክፍያን ተመጣጣኝ በማድረግ ላደረጉት ትብብር ምስጋና ይገባል ሲሉ ከንቲባዋ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ አጠቃላይ እንግዶቹን በኢትዮጵያዊ አንግዳ ተቀባይነት ያደረገው ተሳትፎ የሚደነቅ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በከተማዋ የተከናወኑ ሁነትና የአደባባይ በዓላት አብሮነትን እና አንድነትን በተግባር ያሳዩ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ መሰረተ ልማቶች የኔ ናቸው ብሎ በመንቀሳቀሱ በከተዋማ በተከበሩ በርካታ ዓበይት በዓላት እና ሁነቶች አንድም የተበላሸ የኮሪደር ልማት አለመኖሩን የገለፁት ከንቲባዋ ይህም በሌሎቹ ስራዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል ፡፡
በጉባኤው የተለያዩ የምክር ቤት አባላት ምላሽና ማብራሪያ ያስፈልጋቸዋል ያሉትን ጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል ፡፡
የምክር ቤት አባላት ያቀረቧቸውን ጥያቄ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ፡፡
አዲስ አበባ ላይ በተሰሩና እየተሰሩ ባሉ የኮሪደር ልማት ከተማዋ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤዎችን የማዘጋጀት ዓቅሟ እያደገ መጥቷል፤ በእነዚህ ጉባኤዎችና በመስከረም ወር የተከናወኑ ዓበይት የአደባባይ በዓላት በከተማዋ የተከናወኑበት ወር ሲሆን እነዚህ ሁነቶች በድምቀት ተከብረው አልፈዋል ለዚህ ሰኬት የተሰሩ ስራዎች ምንድናቸው ለሚለው የምክር ቤት አባላት ጥያቄ ከንቲባዋ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ለበዓላቱና ለሁነቶቹ ስኬት ከህዝቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ግልፅነት በመፍጠር ወደ ስራ መገባቱን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የገለፁት፡፡
በተለይ በተከናወኑ ጉባኤዎች፣ ሆቴሎች የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ እና ክፍያን ተመጣጣኝ በማድረግ ላደረጉት ትብብር ምስጋና ይገባል ሲሉ ከንቲባዋ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ አጠቃላይ እንግዶቹን በኢትዮጵያዊ አንግዳ ተቀባይነት ያደረገው ተሳትፎ የሚደነቅ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በከተማዋ የተከናወኑ ሁነትና የአደባባይ በዓላት አብሮነትን እና አንድነትን በተግባር ያሳዩ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ህዝቡ መሰረተ ልማቶች የኔ ናቸው ብሎ በመንቀሳቀሱ በከተዋማ በተከበሩ በርካታ ዓበይት በዓላት እና ሁነቶች አንድም የተበላሸ የኮሪደር ልማት አለመኖሩን የገለፁት ከንቲባዋ ይህም በሌሎቹ ስራዎች ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
❤2
ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል የሚደረገውን ብርቱ ጥረት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ :-
👉በበዓላት ወቅት የሚፈጠሩ የዋጋ ውድነቶችን ለመከላከል አቅደን ሰርተናል።
👉በታላላቅ የገበያ ማዕከላት የምርት እጥረት እንዳይኖር ተሰርቷል።
👉በክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ አቅጣጫ መሰረት ምርቶች ከሁለም ክፍሎች እንዲገቡ ከማህበራት በጋራ እየተሰራ ነው።
👉የንግድ ኮርፖሬሽንን የማጠናከር ስራ ተሰርቷል። የእሁዱ ገበያ እና የምገባ ማዕከላትን ማጠናከር ስራ ተከናውኗል። 500 ሺህ ለሚሆኑ ነዋሪዎችም የማዕድ ማጋራት ስራ ባለሀብቶችን በማሳተፍ ተከናውኗል። የዳቦ ዋጋንም በመደጎም ለህዝባችን ማሻሻል ተችሏል።
👉የእሁድ ገበያን ለማጠናከርም ብርቱ ስራዎች ተሰርተዋል ፤ ክፍተቶች እንዲታረሙ ይሰራል።
👉የጤና መድህን ፣ ትራንስፖርት ወዘተ 14 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዞ እየተሰራ ሲሆን በዋንኛነት ግን የህዝባችንን ህይወት በዘላቂነት ለማሻሻል እየተሰራ ነው፡፡
👉በበዓላት ወቅት የሚፈጠሩ የዋጋ ውድነቶችን ለመከላከል አቅደን ሰርተናል።
👉በታላላቅ የገበያ ማዕከላት የምርት እጥረት እንዳይኖር ተሰርቷል።
👉በክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ አቅጣጫ መሰረት ምርቶች ከሁለም ክፍሎች እንዲገቡ ከማህበራት በጋራ እየተሰራ ነው።
👉የንግድ ኮርፖሬሽንን የማጠናከር ስራ ተሰርቷል። የእሁዱ ገበያ እና የምገባ ማዕከላትን ማጠናከር ስራ ተከናውኗል። 500 ሺህ ለሚሆኑ ነዋሪዎችም የማዕድ ማጋራት ስራ ባለሀብቶችን በማሳተፍ ተከናውኗል። የዳቦ ዋጋንም በመደጎም ለህዝባችን ማሻሻል ተችሏል።
👉የእሁድ ገበያን ለማጠናከርም ብርቱ ስራዎች ተሰርተዋል ፤ ክፍተቶች እንዲታረሙ ይሰራል።
👉የጤና መድህን ፣ ትራንስፖርት ወዘተ 14 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዞ እየተሰራ ሲሆን በዋንኛነት ግን የህዝባችንን ህይወት በዘላቂነት ለማሻሻል እየተሰራ ነው፡፡
❤2
በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በዘላቂነት በኮሪደር ልማት ደረጃ እንደሚሰሩ፡- ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም አካባቢዎች የኮሪደር ልማት ስራን ለማዳረስ ምን እንደታቀደ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ በቂ ዝግጅትን የሚጠይቅ ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም በዚህ ዓመት አዲስ የኮሪደር ልማት ስራዎች እንደማይኖር የገለጹት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ነገር ግን በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በኮሪደር ልማት እስታንዳርድ ዘላቂነት እንዲኖራቸው ተደርጎ ይሰራሉ ብለዋል፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም አካባቢዎች የኮሪደር ልማት ስራን ለማዳረስ ምን እንደታቀደ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ በቂ ዝግጅትን የሚጠይቅ ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም በዚህ ዓመት አዲስ የኮሪደር ልማት ስራዎች እንደማይኖር የገለጹት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ነገር ግን በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በኮሪደር ልማት እስታንዳርድ ዘላቂነት እንዲኖራቸው ተደርጎ ይሰራሉ ብለዋል፡፡
❤2