የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
835 subscribers
2.14K photos
47 videos
265 links
Download Telegram
ተግተዉ የሰሩትን ሁሉ እናመሰግናለን !

የከተማ አስተዳደራችን 15,960 ፕሮጀክቶችን ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ማድረግ ጀምረናል ።

በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች የተገነቡ አጭር እና አቋራጭ መንገዶች ፤ የትራፊክ ማሳለጫ ተሻጋጋሪ ድልድዮች የትራፊክ ፍሰትን በማቀላጠፍ እና ፕሮጀክቶቻችን በማያያዝ ለነዋሪው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ጉልህ ድርሻ ያለቸው ናቸው ።

ፕሮጀክቶቹ ከ50 እስከ 60 ስፋት ያላቸዉ ድልድዮቹ እስከ 300 ሜትር ርዝመት ያላቸዉ ግዙፍ መንገዶች ያካተቱ ናቸው።
እነዚህ ፕሮጀክቶች፤ ከዉጪ በሚገኝ ብድር ይገነባል ተብሎ የተጀመረ ቢሆንም ብድሩ ሳይገኝ ቀርቶ በከተማ አስተዳደሩ አቅም መገንባት የተቻለ ነዉ።

የከተማችን ነዋሪዎችም የተገነቡ መንገዶችን በአግባቡ እንድትጠቀሙበት አደራ እያልኩኝ ፤ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የበኩላችሁን ድርሻ ላበረከታችሁ የአዲስ አበባ ከተማ መንገድ ባለስልጣን ፤ የመንግስት እና የግል ድርጅቶች ፣ ኮንትራክተሮች ፣ አማካሪ ድርጅቶች እና የአቃቂ ቃሊቲ እና የቦሌ ክለከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች እና ድርሻ ለነበራችሁ ሁሉ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿን ይባርክ!
👍2
በእርግጥም የተሻለው ሁሉ ይገባችኋል !

ዛሬ ማለዳ በ11 ክፍለ ከተሞች ከ5 ቢለዬን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸዉ የተገነቡ 122 የስፖርት ማዘውተሪያ እና 1,155 የህፃናት መጫወቻ ማዕከላትን በጥቅሉ 1277 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።

ይህ ውሳኔያችን በአዕምሮና በአካል የዳበረ ትውልድ ለመገንባት ከከተማችን ሀብት መሬት እና በጀት፤ ከእኛ ከአመራሮች እና ከሰራተኛው ደግሞ ጉልበት እና ጊዜ እፍታውን ወስደን እንዲሁም ማህበረሰቡን በማስተባበር ለትውልዱ ቅድሚያ ስጥተን ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን ገንብተናል ።
ባለፋት 3 ዓመታት ለስራ ቦታዎች እና ለመኖሪያ አካባቢዎች ጭምር ትኩረት በመስጠት በድምሩ 3,789 የህፃናት የመጫወቻ ማዕከላትን እና 1,530 የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎችን ገንብተን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።

“ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንዲሉ እነዚህ ደረጃዉን ጠብቀን የገነባናቸዉ መሰረተ ልማቶች 50 % ወጪያቸው የተሸፈነዉ በማህበረሰቡ መሆኑ ልዩ ያደርጋቸዋል።

በመጨረሻም፣ ለወጣቶችና ህጻናት የስፖርት ማዘውተሪያና መጫወቻ ማዕከላትን ለመገንባት ስናደርገው በነበረው ጥረት ሁሉ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱና ላስተባበሩ አካላት ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቧቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
3
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
በአዕምሮና በአካል የዳበረ ትውልድ ለመገንባት በሰጠነው ልዩ ትኩረት ዛሬ በ11 ክ/ከተሞች የሰራናቸው ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለወጣቶችና ህፃናት ክፍት ተደርገዋል::

👉 122 የስፖርት ማዘውተሪያዎዎች
👉1155 የህፃናት መጫወቻ ማዕከላት
👉ባለፋት 2 ዓመታት ደግሞ ለህፃናት መጫወቻ በድምሩ 3,789
👉ባለፉት 3 ዓመታት ደግሞ የስፖርት ማዘውተሪያ 1,530 ሥፍራዎችን ገንብተን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።

የዚህ ሥራ ውጤት ሰው ተኮር መሆናችንን ያስመሰከረ እና የገባነውን ቃል በተግባይ ለመፈፀማችን ማሳያ ነው።
👍2
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤን ዛሬ ማካሄድ ይጀምራል

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ እና የበጀት አመቱን ማጠቃለያ ጉባኤ ሃምሌ 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ያካሄዳል።

በጉበኤዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
👏1
3ኛው የአዲስ አበባ ምክር ቤት 4ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል።

የጉባኤው አጀንዳዎች፦

1. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ የትኩረት አቅጣጫዎች፣

2. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የ2017 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርትን ማድመጥ፤

3. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፣

4. የአዲስ አበባ ከተማ አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 84/2016 ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤

5. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ በመወያየት ማጽደቅ

6. ልዩ ልዩ ሹመቶችን ማጽደቅ፣

#addisababa
ሰላምና ፀጥታን በተመለከተ፣

👉በሠላምና ፀጥታ ጉዳዮች የኅብረተሰቡን ተሳትፎ ለማጎልበት በአካባቢ ሠላም፣ በአብሮነትና ትብብር የሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ በድግግሞሽ ከ7.9 ሚሊዮን በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በግንዛቤ በብሎክ የማኅበረሰብ አቀፍ ምክክር መድረኮች ላይ ማሳተፍ ተችሏል።

👉በማኅበረሰብ አቀፍ ፀጥታ አጠባበቅ ላይም አካባቢን በመጠበቅ፣ ለወንጀለኞች መደበቂያ ሊሆኑ የሚችሉ ሁኔታዎች በማጽዳትና የሥጋት ቦታዎችን ለይቶ መከላከል እንዲቻል የሠላም ሠራዊት አደረጃጀቶችን እና የማኅበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ ሕዝቡን የሰላም ባለቤት ማድረግ ተችሏል።

👉የወንጀል ድርጊቶችን በመቀነስ ረገድ ከ3,628 በላይ የፀጥታ መረጃዎችና ጥቆማዎች በመሰብሰብና በማደራጀት ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሃሰተኛ ሰነድ፣ከከባድና ቀላል ወንጀል፣ ከትምህርት ተቋማት ደህንነት፣ ለፀጥታና ደህንነት አስጊ ከሆኑ ሁኔታዎችና ግጭቶች እንዲሁም ከተለያዩ አዋኪ ድርጊቶች፤ ከኢኮኖሚ አሻጥርና ህገ ወጥ የንግድ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ ከሌሎች ሕግ አስከባሪ አካላት ጋር በመቀናጀት 11,517 የወንጀል ድርጊቶችና የፀጥታ ስጋቶችን የመለየት፣ የመከላከል እና እርምጃ እንዲወሰድ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል።
1
የተቋም ግንባታና አገልግሎነት አሰጣጥ በተመለከተ

👉በተቋማት ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር ከ2 ሽህ 147 በላይ የመንግስት ሰራተኞች በህጻናት ማቆያ ልጆቻቸውን እንዲከባከቡ በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል።

👉በተቋማት ከ185 በላይ የመንግስት ሰራተኞች ካፍቴሪያዎችን በመገንባት እና አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ እንዲሁም ከ150 የሸማች ሱቆችን ወደ ስራ በማስገባት ሰራተኞ የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋም የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል።

👉ከ21 ሽህ 046 የተገልጋይ ማረፊያ በማዘጋጀት ምቹ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ተገንብተዋል።

👉በተቋማት 347 አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ብልሹ አሰራር፣የተገልጋይ እንግልትና ምልልስ በማስቀረት የሚቀርቡ ቅሬታዎች እንዲቀንሱ አድርጓል።

👉በሌብነትና ብልሹ አሰራር ተግባር ውስጥ የገቡ 4 ሽህ 965 አመራሮች፣ ፈጻሚዎች እና ተገልጋዩችን ተጠያቂ በማድረግ ህጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ተወስዷል።
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
በበጀት ዓመቱ የትምህርት ዘርፍ በተመለከተ

👉የትምህርት ዘርፉ ዋና ትኩረት የነበረውን የትምህርት ተሣትፎና ፍትሐዊነት በማሳደግ በዕውቀትና በሥነ- ምግባር የታነፀ ትውልድን ለማፍራት በተሻሻለው ስርአተ ትምህርት መሰረት

👉በበጀት ዓመቱ የትምህርት አጠቃላይ ከቅድመ አንደኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ቅበላ ሥራችንን ከ1,159,684  ወደ 1,184,326 ለማድረስ ታቅዶ ክንውን 1,253,737 (105.86%) ማድረስ መቻሉ፤ይህም  ከ 2016 የትምህርት ቅበላ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 98,129 ዕድገት አሳይቷል፡፡

👉የትምህርት ፍትሃዊነትን ለማስፈን በተደረገው ጥረትም በሁሉም ት/ቤቶች የልዩ ፍላጎት ትምህርትን በማስፋፋት የተማሪዎችን ቁጥር ከ 33,203 ወደ 33,604 ለማድረስ ታቅዶ 34,015 (101.22%) ማድረስ ተችሏል፡፡

👉ትምህርት ቤቶች ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች አመቺ እንዲሆኑ ለማድረግ የተማሪ መማሪያና የመምህሩ መምሪያ መፅሃፍትን በድምፅ በመቅረፅና አዘጋጅቶ በማሰራጨት 10,294 የዕይታ ችግር ላለባቸው ተማሪዎች ተጠቃሚ በማድረግ ውጤታቸው እንዲሻሻል አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡

👉የት/ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል በሶስተኛው ዙር “ትምህርት ለትውልድ” ንቅናቄ በተሰራው ሥራ  በገንዘብ፤ በጉልበትና በዕውቀት በአጠቃላይ ከ 4 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት በማሰባሰብ የት/ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ለመማር ማስተማር ሂደቱ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ተችሏል፡፡

👉ትውልድ ላይ ኢንቨስት እናድርግ በሚለው የመንግስት አቅጣጫ መሰረት በተማሪዎች ምገባ 840,585 በላይ ተማሪዎች በቀን ሁለት ጊዜ እንዲመገቡ የተደረገ ሲሆን የተማሪ ዩኒፎርም፣ የትምህርት ቁሳቁስ እና የመምህራን ጋዋን ጨምሮ እንዲደርሳቸው ከማድረግ በተጨማሪ የተማሪ ውጤት ለማሻሻል እየሰራን ያለዉ ስራ ከፍተኛ ውጤት እያመጣ ይገኛል፡፡

👉በ2017 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና 50% በላይ በማምጣት ወደ ቀጣይ ክፍል የተሸጋገሩ ተማሪዎችን ከነበረበት 94.3% ወደ 95% ለማድረስ ታቅዶ 95% (100% ) ማድረስ የተቻለ ሲሆን በተመሳሳይ የ8ኛ ክፍል ከተማ ዓቀፍ ፈተና ውጤት  ከነበረበት 79% ወደ  82% ለማድረስ ታቅዶ 88.8% (108.3) ማድረስ ተችሏል፡፡
👏1
ቀዳማይ ልጅነትን ልማት ፕሮግራምን በተመለከተ

👉ፐሮግራሙ የከተማችንን 1.3 ሚሊዮን ህጻናትን በተለይ ደግሞ 330‚000 አነስተኛ ገቢ ካላቸው ቤተሰብ የተገኙ ህጻናት ለመድረስ ያለሙ አምስት አንኳር ኢኒሼቲቮሽን አቅደን ስንተገብር ቆይተናል።

👉ከተቀመጡት ግቦች አንጻር የወላጆችን እና አሳዳጊዎች የምክር እና የሙያ አገልግሎት የሚሰጡ 5‚000 ሰራተኞችን በማሰማራት በ 4‚979 የመኖሪያ ብሎኮች ለሚገኙ ለ 487,544 ወላጆች/አሳዳጊዎች በየአስራ አምስት ቀኑ የቤት ለቤት የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል።

👉ለ11,900 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለድገት ውስኑነት ተጋላጭ የሆኑ ነፍሰ ጡር እና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ከ 3 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት የቀጥታ አልሚ ምግብ ድጋፍ በየወሩ ተሰጥቷል።

👉ስራውን አጠናክሮ ለመቀጠል በዚህ በጀት አመትም ከ 5ዐዐ ሚሊየን በላይ በጀት ለአልሚ ምግብ በጅተናል፡፡

👉እድሜያቸው ከ 0 እስከ 3 ዓመት የሆኑ እና በኢኮኖሚ ሁኔታቸው ለዕድገት ውሱንነት ተጋላጭ የሆኑ ህጻናት የዕድገት ሁኔታ ፕሮግራሙ በተጀመረበት ወቅት ከነበረበት 66.9% ወደ 73.1% በማደግ የ 6.2 በመቶ መሻሻል አሳይቷል።

👉በጨዋታ መልክ በማስተማር በቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ይታይ የነበረው የትምህርት ዝግጁነት ምጣኔም ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ ወደ 89.03% ከፍ በማለት የልጆች ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ ችለናል፡፡
የፍትህ ሥርዓትና የሕግ የበላይነትን ማስከበር በተመለከተ

👉በፍትህ ሥርዓታችን የሕግ የበላይነትን በማስከበር የሰብዓዊ መብት አያያዝ እንዲጎለብት ለማድረግ በፍትሐብሔር ጉዳዮች የከተማ አስተዳደሩንና የነዋሪውን መብትና ጥቅም ከማስጠበቅ አንፃር ክርክር በፍ/ቤት የመርታት አቅም 96.05 % ማድረስ ታቅዶ በፍርድ ቤት ክርክር የቀረቡ 6,379 መዝገቦች፣ በፍ/ቤት ውሳኔ ካገኙ 3,963 መዝገቦች 3,683 ለአስተዳደሩ ማስወሰን በመቻሉ አፈፃፀሙ 96.8% ደርሷል፡፡

👉የመንግስት እና ሕዝብ መብትና ጥቅም በማስከበርም በገንዘብ 5,608,175,281.16 ብር ሆኖ በአይነት ደግሞ 272 ቤቶች፣ 64 ሼዶች እንዲሁም 260.32 ሄክታር መሬት ማስከበር መቻሉ፤ምርመራ ከተጠናቀቀ 12,828 የግል አቤቱታ የወንጀል ምርመራ መዝገቦች ውስጥ 88% በእርቅ ለመጨረስ ታቅዶ 9,822 መዛግብት በፖሊስና በዐቃብያን ሕግ፣ 1,048 መዛግብት በፍርድ ቤት በአጠቃላይ 10,870 ክንውኑ 84.7% ሲሆን አፈፃፀሙ 96.2% ነው፡፡
2
በበጀት ዓመቱ ቱሪዝምን በተመለከተ

👉1ሚሊዮን የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ከተማችንን እንዲጎበኙ በማድረግ፣ከ15ዐ በላይ ኮንፍረንሶች፣ እግዚቢሽኖችና ኤክስፖዎች በማካሄድ ከ143 ቢሊየን በላይ ገቢ ተሰብስቧል፡፡

👉ከ9 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ከ56 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ የሚሆን ገቢ ወደ መዲናችን ኢኮኖሚ ፈሰስ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
የድህነት ቅነሳና ስራ እድል ፈጠራን በተመለከተ
👉በከተማችን ለሚገኙ ለ366,044 ስራ ፈላጊዎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠር ተችሏል፡፡

👉በከተማ ግብርና ዘርፍ 40,230 በኢንዱስትሪ ዘርፍ 91,737 እና በአገልግሎት ዘርፍ 234,077

👉ለሴቶች የስራ እድል ፈጠራ 201,309
👉ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ 290,360 ምሩቃን 52,866 የስራ እድል ተጠቃሚ ሆነዋል።

👉ተረጂነትን በማስቀረት ምርታማነት ለማሳደግ የልማታዊ ሴፍትኔት ሦስት ዓመት የሆናቸው የሁለተኛ ምእራፍ ተጠቃሚዎች የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግና ስልጠና በመስጠት 31,002 የቤተሰብ ተወካዮች በማስመረቅ የራሳቸውን ገቢ የሚፈጥሩበት ቌሚ የስራ መስክ ማስገባት ችለናል፡፡

👉በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት የሚጎዳ የህብረተሰብ ክፍል እንዳይኖር 130,135 በላይ በዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የከተማችን ነዋሪዎችን ለቀጣይ ሶስት ዓመት የሚደግፍ ስራ በበጀት ዓመቱ አስጀምረናል፡፡

👉የቁጠባ ባህልን ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች 27,293 ኢንተርፕራይዞች 5,132,495,487 ብር ቁጠባ እንዲቆጥቡ ተደርጓል፡፡
👉 ለኢንተርፕራይዞች ብድር በማመቻቸት 3,559,287,049 ብር ማበደር ተችሏል፡፡
2
በበጀት ዓመቱ የተጠናቀቁ የፕሮጀክቶችን አስመልክቶ

የሕዝባችንን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎችን ከመመለስ አንጻር በመንግስትና በህብረተሰብ ተሣትፎ 15‚69ዐ ግንባታዎችን ማጠናቀቅ የተቻለ ሲሆን፤ ካቀድነው በላይ ማከናወን ተችሏል፡፡

👉 205 በህብረተሰብ ተሳትፎ የተሰሩ የተለያዩ ኘሮጀክቶች
👉 8,786 በበጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ ቤቶች
👉 5,176 በከተማ አስተዳደር የተገነቡ ቤቶች
👉 1064 የመስሪያ ሼዶች
👉 5,563 ሱቆች / ካዛንቺስ፣ ቦሌ፣ ላፍቶ፣ ልደታ፣ አራዳ እና አራት ኪሎ ሽሮሜዳ/ የተገነቡ
👉 1,155 የህፃናት መጫወቻ ቦታዎች
👉 122 የእስፖርት ማዘወተሪያ ሜዳዎች
👉 245 የአረንጓዴ ልማት ስራ
👉 153 የመኪና ፓርኪንጎችና ተርሚናሎች
👉ከዚህ ውስጥ 16 ቱ ሜጋ ኘሮጀክቶች ሲሆኑ ወደ 9ሺ ኘሮጀክቶች በህብረተሰብ ተሳትፎና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰሩ ናቸው፡፡