የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መክፈቻ ወቅት አቶ ይመር ከበደ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር በንግግራቸው ስለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያነሷቸው ነጥቦች፡-
የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ትርጉም እንደዬማህበረሰቡ የእድገት ደረጃና ከባቢያዊ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን በዋንኛነት ሰዎች/ግለሰቦች ከሰብአዊነት አመለካከት ተነስተው ለሚኖሩበት ማህበረሰብ ልማት “ያለማንም አስገዳጅነት በራሳቸው መልካም ፈቃድ ብቻ ተነሳስተው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ዘር፣ ቋንቋ፣ ኃይማኖት ወይም የኑሮ ደረጃ ሳይለዩ በተቋም ወይም በተናጠል ለሰዎች የሚያደርጉት ከክፍያ ነፃ አገልግሎት ነው፡፡
በጎነት ባለፀጋዎች ብቻ የሚከዉኑት፣ ከገንዘብ ጋር የሚያያዝ ተግባር አድርገው የሚያስቡ አሉ፡፡ ነገር ግን በጎ ፈቃደኝነት በምንሰጠው ገንዘብ ብቻ የሚለካ ፅንሰ ሀሳብ አይደለም፡፡ ማንኛውም ሰው ጉልበቱን፣ ጊዜውን፣ ገንዘቡን፣ ሀሳቡን ወይም አብሮነቱን በመግለፅና በመስጠት በጎ ማድረግ እንደሚችል የበጎ ፈቃደኝነት ዓለም አቀፍ ብያኔ ያስረዳል፡፡
ዓለም ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ተግዳሮቶች በሚገጥሟት ጊዜ፤ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ቀድመዉ የሚገኙት በጎ ፈቃደኞች ናቸው፡፡ ምድር ለሰው ልጆች የተሻለች ትሆን ዘንድ ፈተናዎችን በመጋፈጥና ተፈጥሮን በመንከባከብ ረገድ በጎ ፈቃደኝነት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ይህንንም በመረዳት በአንዳንድ የአለማችን ሀገራት የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ተሳትፎ የህዝባቸዉን 40 ከመቶ በላይ የሚሸፍን የበጎነት አገልግሎት ስራ ላይ ይሳተፋሉ፡፡
በበርካታ ሀገራት ደግሞ በኢኮኖሚያቸዉ ላይ አወንታዊ ተፅዕኖ ከመፍጠር አኳያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዓመታዊ ነፍስ ወከፍ ገቢያቸውን (GDP) ከ2-3 በመቶ አስተዋፅኦ ያበረክታል። ከአፍሪካ ሀገራት በጎ ፈቃደኝነት ከፍተኛው ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖ የሚያበረክትባት ሀገር ሩዋንዳ በቀዳሚነት ተጠቀሳለች፡፡ በሩዋንዳ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከዓመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ አኳያ ሲሰላ 30 በመቶ ይሸፍናል፡፡ በጎረቤት ሀገር ኬኒያ ደግሞ 3.66 በመቶ አስተዋፅዖ እንዳለው በጥናት የተረጋገጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
በኢትዮጵያ እስከአሁን ድረስ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖ ተለክቶ ባይታወቅም በጎ ፈቃደኝነት ተቋማዊ ባልነበረበትም ወቅት የመስጠት፣ የመደጋገፍ ባህልና እሴት የነበራት፣ ዜጎች ተደጋግፈው የሚኖሩባት፤ ችግራቸውን በጋራ የሚፈቱባት፣ ማህበራዊ መስተጋብር ያቆራኛቸው ህዝቦች ያሉባት ሀገር ናት፡፡ ይህ ባህል ከጥቂት ዘመን ወዲህ በመጤ ባህሎች ተቀዛቅዞ አደጋ ላይ ወድቆ የነበረ ቢሆንም ከለውጡ ወዲህ ተቋማዊ በሆነ መንገድ እንዲመራ በማድረግ የመተሳሰብ እሴት እንደገና እንዲያብብ፣ መረዳዳትና መደጋገፍ እንዲጎለብት በፖሊሲ ተደግፎ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ከ2010 ዓ.ም የክረምት ወራት ጀምሮ እጅግ በተለየ መንገድ በለውጡ አመራር የብልፅና መንግስት ሰው ተኮር ፕሮግራም የሚመራ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲስፋፋ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን አማካኝነት የአረጋዊያንን ቤቶች በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራት፣ ደም በመለገስ እና በአርንጓዴ አሻራ ፕሮግራሞች ሰፋፊ አገልግሎቶች የተጀመሩበትና በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች ይህንን በጎ አርዓያ የተከተሉበት ሁኔታ እንዲፈጠር አስችሏል፡፡ በሂደቱም የብልፅግና መንግስት ሰው ተኮር ክዋኔዎች በርካታ ስኬቶችን አስገኝቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት በከተማችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎችን ለመሻገር አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝቦ ተግባሩ በተቋም እንዲመራ በማድረግ ስኬታማ ስራዎችን አከናውኗል፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተቋማዊ ከሆነበት ባለፉት 7 የለውጥ ዓመታት ወዲህ በተለያዩ ፕሮግራሞች በተፈጠረው ግንዛቤ የከተማችን ነዋሪዎች፣ ባለሃብቶች፣ ወጣቶችና ሌሎች ተቋማት፣ የበጎ ፈቃድ ማህበራት እና ግለሰቦች በአገልግሎቱ ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተሳትፏቸው እያደገ መጥቷል፡፡ ይህም የበጎነት አገልግሎት ባህል ወደመሆን በመሸጋገር ላይ መሆኑን ማሳያ ነው፡፡
#በጎነት_አያጎድልም
#followerseveryone
#volunteersmakeadifference
#viralreelschallenge
#addisababa
#Ethiopia
የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ትርጉም እንደዬማህበረሰቡ የእድገት ደረጃና ከባቢያዊ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን በዋንኛነት ሰዎች/ግለሰቦች ከሰብአዊነት አመለካከት ተነስተው ለሚኖሩበት ማህበረሰብ ልማት “ያለማንም አስገዳጅነት በራሳቸው መልካም ፈቃድ ብቻ ተነሳስተው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ዘር፣ ቋንቋ፣ ኃይማኖት ወይም የኑሮ ደረጃ ሳይለዩ በተቋም ወይም በተናጠል ለሰዎች የሚያደርጉት ከክፍያ ነፃ አገልግሎት ነው፡፡
በጎነት ባለፀጋዎች ብቻ የሚከዉኑት፣ ከገንዘብ ጋር የሚያያዝ ተግባር አድርገው የሚያስቡ አሉ፡፡ ነገር ግን በጎ ፈቃደኝነት በምንሰጠው ገንዘብ ብቻ የሚለካ ፅንሰ ሀሳብ አይደለም፡፡ ማንኛውም ሰው ጉልበቱን፣ ጊዜውን፣ ገንዘቡን፣ ሀሳቡን ወይም አብሮነቱን በመግለፅና በመስጠት በጎ ማድረግ እንደሚችል የበጎ ፈቃደኝነት ዓለም አቀፍ ብያኔ ያስረዳል፡፡
ዓለም ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ተግዳሮቶች በሚገጥሟት ጊዜ፤ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ቀድመዉ የሚገኙት በጎ ፈቃደኞች ናቸው፡፡ ምድር ለሰው ልጆች የተሻለች ትሆን ዘንድ ፈተናዎችን በመጋፈጥና ተፈጥሮን በመንከባከብ ረገድ በጎ ፈቃደኝነት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ይህንንም በመረዳት በአንዳንድ የአለማችን ሀገራት የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ተሳትፎ የህዝባቸዉን 40 ከመቶ በላይ የሚሸፍን የበጎነት አገልግሎት ስራ ላይ ይሳተፋሉ፡፡
በበርካታ ሀገራት ደግሞ በኢኮኖሚያቸዉ ላይ አወንታዊ ተፅዕኖ ከመፍጠር አኳያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዓመታዊ ነፍስ ወከፍ ገቢያቸውን (GDP) ከ2-3 በመቶ አስተዋፅኦ ያበረክታል። ከአፍሪካ ሀገራት በጎ ፈቃደኝነት ከፍተኛው ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖ የሚያበረክትባት ሀገር ሩዋንዳ በቀዳሚነት ተጠቀሳለች፡፡ በሩዋንዳ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከዓመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ አኳያ ሲሰላ 30 በመቶ ይሸፍናል፡፡ በጎረቤት ሀገር ኬኒያ ደግሞ 3.66 በመቶ አስተዋፅዖ እንዳለው በጥናት የተረጋገጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
በኢትዮጵያ እስከአሁን ድረስ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖ ተለክቶ ባይታወቅም በጎ ፈቃደኝነት ተቋማዊ ባልነበረበትም ወቅት የመስጠት፣ የመደጋገፍ ባህልና እሴት የነበራት፣ ዜጎች ተደጋግፈው የሚኖሩባት፤ ችግራቸውን በጋራ የሚፈቱባት፣ ማህበራዊ መስተጋብር ያቆራኛቸው ህዝቦች ያሉባት ሀገር ናት፡፡ ይህ ባህል ከጥቂት ዘመን ወዲህ በመጤ ባህሎች ተቀዛቅዞ አደጋ ላይ ወድቆ የነበረ ቢሆንም ከለውጡ ወዲህ ተቋማዊ በሆነ መንገድ እንዲመራ በማድረግ የመተሳሰብ እሴት እንደገና እንዲያብብ፣ መረዳዳትና መደጋገፍ እንዲጎለብት በፖሊሲ ተደግፎ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ከ2010 ዓ.ም የክረምት ወራት ጀምሮ እጅግ በተለየ መንገድ በለውጡ አመራር የብልፅና መንግስት ሰው ተኮር ፕሮግራም የሚመራ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲስፋፋ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን አማካኝነት የአረጋዊያንን ቤቶች በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራት፣ ደም በመለገስ እና በአርንጓዴ አሻራ ፕሮግራሞች ሰፋፊ አገልግሎቶች የተጀመሩበትና በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች ይህንን በጎ አርዓያ የተከተሉበት ሁኔታ እንዲፈጠር አስችሏል፡፡ በሂደቱም የብልፅግና መንግስት ሰው ተኮር ክዋኔዎች በርካታ ስኬቶችን አስገኝቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት በከተማችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎችን ለመሻገር አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝቦ ተግባሩ በተቋም እንዲመራ በማድረግ ስኬታማ ስራዎችን አከናውኗል፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተቋማዊ ከሆነበት ባለፉት 7 የለውጥ ዓመታት ወዲህ በተለያዩ ፕሮግራሞች በተፈጠረው ግንዛቤ የከተማችን ነዋሪዎች፣ ባለሃብቶች፣ ወጣቶችና ሌሎች ተቋማት፣ የበጎ ፈቃድ ማህበራት እና ግለሰቦች በአገልግሎቱ ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተሳትፏቸው እያደገ መጥቷል፡፡ ይህም የበጎነት አገልግሎት ባህል ወደመሆን በመሸጋገር ላይ መሆኑን ማሳያ ነው፡፡
#በጎነት_አያጎድልም
#followerseveryone
#volunteersmakeadifference
#viralreelschallenge
#addisababa
#Ethiopia
❤6👍1
605 ሚሊዮን ብር የሚገመት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በለሚኩራ ክፍለ ከተማ
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ" በሚል መሪ ቃል ከ300 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስጀመረ።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት ወይንሸት አስናቀ የብልጽግና መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ሰው ተኮር ተግባራትን ማካሄዱንና እርስ በርስ በመደጋገፍ የእህትማማችነትና የወንድማማችነት ስሜትን ለመፍጠር ብዙ ጥረቶችን ማድረጉን ጠቅሰው በቀጣይም ሰፋፊ የሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
የክፍለ ከተማው የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ገ/ጊዮርጊስ በበጋው መርሃ ግብር በርካታ የበጎ ፈቃድ ስራዎች በስኬት መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።
ከሰኔ/2017 ጀምሮ እስከ መስከረም 30/ 2018 በሚቆየው የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ከ300 ሺ በላይ በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ በ18 የበጎ ፈቃድ ዘርፎች 77 ሺ ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ መንግስት ሊያወጣው የሚችለውን ከ605 ሚሊዮን በላይ ብር ለማዳን መታቀዱ ኃላፊው መናገራቸውን የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ዘገባ ያስረዳል።
#volunteersmakeadifference
#addisababa
#vol@CommunityPVC
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ" በሚል መሪ ቃል ከ300 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስጀመረ።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት ወይንሸት አስናቀ የብልጽግና መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ሰው ተኮር ተግባራትን ማካሄዱንና እርስ በርስ በመደጋገፍ የእህትማማችነትና የወንድማማችነት ስሜትን ለመፍጠር ብዙ ጥረቶችን ማድረጉን ጠቅሰው በቀጣይም ሰፋፊ የሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
የክፍለ ከተማው የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ገ/ጊዮርጊስ በበጋው መርሃ ግብር በርካታ የበጎ ፈቃድ ስራዎች በስኬት መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።
ከሰኔ/2017 ጀምሮ እስከ መስከረም 30/ 2018 በሚቆየው የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ከ300 ሺ በላይ በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ በ18 የበጎ ፈቃድ ዘርፎች 77 ሺ ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ መንግስት ሊያወጣው የሚችለውን ከ605 ሚሊዮን በላይ ብር ለማዳን መታቀዱ ኃላፊው መናገራቸውን የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ዘገባ ያስረዳል።
#volunteersmakeadifference
#addisababa
#vol@CommunityPVC
❤1👍1
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በልደታ ክፍለ ከተማ!
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን በተለያዩ መርሃ ግብሮች አስጀምሯል።
መርሃ ግብሩ በይፋ መከፈቱን ያበሰሩት የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሓፍቱ ብርሃኑ ለሰው ተኮር ተግባሮቻችን ስኬት የባለሀብቶችና የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው ምስጋናቸው አቅርበዋል። በመጭው የክረምት ወቅት በተቀረፁ ሁሉም ሰው ተኪር መርሃ ግብሮች ተሳትፎን ማጠናከርና የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ነው ኃላፊው ያሳሰቡት።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የመዳጋገፍ ባህል ከምንጊዜውም በላይ ጎልቶ የታየበት ተግባር መሆኑን የተናገሩት የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ነፃነት ደረሰ የክረምቱ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ከህብረተሰቡ፣ ከባላሀብቶች እና ከበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የላቀ ተሳትፎና ድጋፍ እንጠብቃለን ብለዋል።
የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንግዳው ጓዴ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በልማት በሰላምና ፀጥታ አጠባበቅ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርትና በቀጣይ ክረምት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች እቅድ ያቀረቡ ሲሆን ለእቅዱ መሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
መርሀ ግብሩ በአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታና በደም ልገሳ ስነ-ሥርዓት መከፈቱን ከክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።
#volunteersmakeadifference
#vol@CommunityPVC
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን በተለያዩ መርሃ ግብሮች አስጀምሯል።
መርሃ ግብሩ በይፋ መከፈቱን ያበሰሩት የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሓፍቱ ብርሃኑ ለሰው ተኮር ተግባሮቻችን ስኬት የባለሀብቶችና የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው ምስጋናቸው አቅርበዋል። በመጭው የክረምት ወቅት በተቀረፁ ሁሉም ሰው ተኪር መርሃ ግብሮች ተሳትፎን ማጠናከርና የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ነው ኃላፊው ያሳሰቡት።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የመዳጋገፍ ባህል ከምንጊዜውም በላይ ጎልቶ የታየበት ተግባር መሆኑን የተናገሩት የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ነፃነት ደረሰ የክረምቱ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ከህብረተሰቡ፣ ከባላሀብቶች እና ከበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የላቀ ተሳትፎና ድጋፍ እንጠብቃለን ብለዋል።
የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንግዳው ጓዴ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በልማት በሰላምና ፀጥታ አጠባበቅ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርትና በቀጣይ ክረምት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች እቅድ ያቀረቡ ሲሆን ለእቅዱ መሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
መርሀ ግብሩ በአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታና በደም ልገሳ ስነ-ሥርዓት መከፈቱን ከክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።
#volunteersmakeadifference
#vol@CommunityPVC
❤1👍1
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ "በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!" በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ከፈተ።
በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ጥላሁን መርሃ ግብሩ ሲከፍቱ ሰው ተኮር ተግባሮቻችን መሳካት የባለሀብቶችና የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ድርሻ ትልቅ መሆኑን ገልፀዋል። ኃላፊው በመጭው የክረምት ወቅት የተያያዘው ፕሮግራም ውጤታማ እንዲሆንም የነዋሪዎችና የአስተዳደሩ የጋራ ርብብር አስፈላጊ በመሆኑ በቁርጠኝነት መሳተፍ ይገባል ብለዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው በበኩላቸው ባለሀብቶች፣ ወጣቶችና ተቋማት ባዳረጉት የተቀናጀ ስራ ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለሁ ጠቁመው በተያዘው የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም ስኬት ለማምጣት ለመሆን ሁሉም የተለመደ ትብብርና ተሳትፎውን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል ሲል የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
የመክፈቻ መርሃግብሩ በጉድጓድ ዝግጅት፣ በቤት ግንባታና በፎቶ አውደ ርዕይ መካሄዱ ተመላክቷል።
#volunteersmakeadifference
#volu@CommunityPVC
በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ጥላሁን መርሃ ግብሩ ሲከፍቱ ሰው ተኮር ተግባሮቻችን መሳካት የባለሀብቶችና የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ድርሻ ትልቅ መሆኑን ገልፀዋል። ኃላፊው በመጭው የክረምት ወቅት የተያያዘው ፕሮግራም ውጤታማ እንዲሆንም የነዋሪዎችና የአስተዳደሩ የጋራ ርብብር አስፈላጊ በመሆኑ በቁርጠኝነት መሳተፍ ይገባል ብለዋል።
የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው በበኩላቸው ባለሀብቶች፣ ወጣቶችና ተቋማት ባዳረጉት የተቀናጀ ስራ ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለሁ ጠቁመው በተያዘው የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም ስኬት ለማምጣት ለመሆን ሁሉም የተለመደ ትብብርና ተሳትፎውን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል ሲል የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
የመክፈቻ መርሃግብሩ በጉድጓድ ዝግጅት፣ በቤት ግንባታና በፎቶ አውደ ርዕይ መካሄዱ ተመላክቷል።
#volunteersmakeadifference
#volu@CommunityPVC
👍1
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮግራሞችን በነፃ ህክምና በደም ልገሳ አስጀምሯል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በጎ ፈቃደኝነት ለማህበረሰብ ለውጥ!" በሚል መሪ ሃሳብ የ2017 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራሞችን በደም ልገሳና በነፃ የህክምና አገልግሎት አስጀምሯል።
መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር አዲሱ ሻንቆ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዜጎች ውስጣቸው ከሚሰማቸው ሰብዓዊ አመለካከት ተነስተው የሚከውኑት መልካም ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።
በጎ ፈቃደኞች በክፍለ ከተማው በበጋ ወቅት በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጋቸውን የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው በአስተዳደሩ ስም ምስጋና አቅርበውላቸዋል።
በበጋ በጎ ፈቃድ 45 ሺ 987 ፈቃደኞችን በማስተባበር የአቅመ ደካሞችን ቤት መገንባት መቻሉን የገለጹት የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አባስ በሌሎች የበጎ ፍቃድ ተግባራትም ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመዋል ሲል የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማ ደረጃ ባለፈው ሳምንት በ15 ፕሮግራሞች በከንቲባ አዳነች አቤቤ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
#volunteersmakeadifference
#voou@CommunityPVC
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በጎ ፈቃደኝነት ለማህበረሰብ ለውጥ!" በሚል መሪ ሃሳብ የ2017 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራሞችን በደም ልገሳና በነፃ የህክምና አገልግሎት አስጀምሯል።
መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር አዲሱ ሻንቆ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዜጎች ውስጣቸው ከሚሰማቸው ሰብዓዊ አመለካከት ተነስተው የሚከውኑት መልካም ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።
በጎ ፈቃደኞች በክፍለ ከተማው በበጋ ወቅት በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጋቸውን የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው በአስተዳደሩ ስም ምስጋና አቅርበውላቸዋል።
በበጋ በጎ ፈቃድ 45 ሺ 987 ፈቃደኞችን በማስተባበር የአቅመ ደካሞችን ቤት መገንባት መቻሉን የገለጹት የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አባስ በሌሎች የበጎ ፍቃድ ተግባራትም ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመዋል ሲል የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማ ደረጃ ባለፈው ሳምንት በ15 ፕሮግራሞች በከንቲባ አዳነች አቤቤ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
#volunteersmakeadifference
#voou@CommunityPVC
👍5