የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ዐድዋ ለሰላም የተደረገ ዘመቻ ነው- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ዐድዋ ለሰላም የተደረገ ዘመቻ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለ129ኛው የዐድዋ ድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል-
ለ129ኛው የዐድዋ ድል በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ። ዐድዋ ለሰላም የተደረገ ዘመቻ ነው።
ከዐድዋ ዘመቻ በፊት ኢትዮጵያውያን ለሰላም ያላቸውን የጸና አቋም ደጋግመው ገልጸዋል። ለሰላም ያላቸው አቋም የጠላት ፉከራዎችንና ትንኮሳዎችን በትዕግሥት እስከማለፍ የደረሰ ነበር።
እንደሚታወሰው የወራሪው የኢጣልያ ጦር ባንዳ ይመለምል ነበር። ባንዳ ያስታጥቅ ነበር።
የባንዳ ተላላኪዎችን በመንግሥት ውስጥ ለማሥረግ ይሞክር ነበር። ሽብር ይነዛ ነበር። የኢትዮጵያን መንግሥት ይከስ ነበር። አንዳንድ ቦታዎችን ለመያዝ ይሞክር ነበር። በዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን ለማሳጣት ይፍጨረጨር ነበር።
ኢትዮጵያ ይሄንን ሁሉ በትዕግሥት እና በዝግጅት ትመለከተው ነበር።
ኢትዮጵያውያን ከጥንት ጀምሮ በጦርነት ኖረዋል። በዚህ የተነሣ የጦርነትን አስከፊ ገጽታ ያውቁታል። ስለሚያውቁትም በቻሉት አማራጭ ሁሉ ይሸሹታል። ለሰላማዊ አማራጭ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋሉ። አንዳንድ ጊዜም ለሰላም ሲሉ ከአስፈላጊው በላይም ያደርጋሉ። ይሄንን ሁሉ ገፍቶ የሚመጣ ጠላት ሲገጥማቸው ግን ለሰላም ሲሉ ዘምተው፤ ለሰላም ሲሉ ያሸንፋሉ።
የዐድዋ ዘመቻም እንደዚሁ ነው። የወራሪው የኢጣልያ ጦር ወደ ጦርነት እንዳይገባ ተለምኗል። የሰላም አማራጮች ቀርበውለታል። "ኩራትና ትዕቢት የሞሉት አናት፣ ሰይፍና ጎራዴ የመቱት አንገት" እንደሚሉት ሆነ። የኢትዮጵያን ትዕግሥት እንደ ፍርሃት፣ የኢትዮጵያን የሰላም መንገድ እንደ ሽንፈት ቆጠረው።
ጠላቶቻችን ምንጊዜም የስሌት ስሕተት ይሠራሉ። ትኅትናችን፣ ትዕግሥታችንና ሰላም ወዳድነታችን ያሳስታቸዋል። ወራሪው የኢጣልያ ጦርም ተሳሳተ።
ኢትዮጵያውያን ግን እየታገሡ ይዘጋጁ ነበሩ። በሁሉም ረገድ ሰላማቸውን ለመጠበቅ ዝግጁ ነበሩ። ነጻነት ፣ ሉዓላዊነት እና ክብር የሚገኙት የሀገር ሰላምን በመጠበቅ መሆኑን ያውቃሉ። ስለዚህ ሰላማቸውን በክንዳቸው ለመጠበቅ ተዘጋጁ።
የዐድዋ ጦርነት ለሰላምና ለጦርነት በሚዋጉ ኃይሎች መካከል የተደረገ ጦርነት ነው። የአሸናፊነታችን አንዱ ምሥጢርም ይሄው ነው። ከጦርነቱ በኋላ ወደ በቀልና ጥላቻ እንዳናመራ ያደረገንም ይሄው ነው። ለሰላም ስንል እንጂ ለጦርነት ስንል አልተዋጋንምና።
የዐድዋ ድል ለሰው ልጅ ሉላዊ ዕሴቶች ያለንን ዋጋ አሳይተንበታል። በምርኮኛ አያያዛችን፣ ከተዋጉን ጋር መልሰን ለሰላማዊ ውይይት በመቀመጣችን፣ ለዘላቂ ሰላም በመሥራታችን።
እናቶቻችንንና አባቶቻችንን በድል አድራጊነታቸው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ዕሴቶች በከፈሉት ዋጋ ጭምር እናመሰግናቸዋለን። የተዋጉት ለሰላም ሲሉ ነው። የተዋጉት ሰላምን እና ሰላማዊ መንገድን እምቢ ካለ ኃይል ጋር ነው።
የዐድዋ ዘማቾች ልጆች ነን። ለሰላም ቅድሚያ እንሰጣለን። ዛሬም ጠላቶቻችን ከተሳሳተ ስሌት እንዳልወጡ እናውቃለን። በሰላማዊ መንገድ የሚመጡትን መቀበል ከዐድዋ ዘማቾች ተምረናል። በሰላም የማይመጡትንም መቅጣት ከዐድዋ ዘማቾች አይተናል። እኛም እንደቀደምቶቻችን የሰላሙን መንገድ እንመርጣለን። ነገር ግን እንደ ቀደምቶቻችን ሁሉ፣ ለሁለቱም ምንጊዜም ዝግጁዎች ነን። የዐድዋ ዘማቾች ልጆች ነንና።
መልካም በዓል ይሁን።
ዐድዋ ለሰላም የተደረገ ዘመቻ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለ129ኛው የዐድዋ ድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል-
ለ129ኛው የዐድዋ ድል በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ። ዐድዋ ለሰላም የተደረገ ዘመቻ ነው።
ከዐድዋ ዘመቻ በፊት ኢትዮጵያውያን ለሰላም ያላቸውን የጸና አቋም ደጋግመው ገልጸዋል። ለሰላም ያላቸው አቋም የጠላት ፉከራዎችንና ትንኮሳዎችን በትዕግሥት እስከማለፍ የደረሰ ነበር።
እንደሚታወሰው የወራሪው የኢጣልያ ጦር ባንዳ ይመለምል ነበር። ባንዳ ያስታጥቅ ነበር።
የባንዳ ተላላኪዎችን በመንግሥት ውስጥ ለማሥረግ ይሞክር ነበር። ሽብር ይነዛ ነበር። የኢትዮጵያን መንግሥት ይከስ ነበር። አንዳንድ ቦታዎችን ለመያዝ ይሞክር ነበር። በዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን ለማሳጣት ይፍጨረጨር ነበር።
ኢትዮጵያ ይሄንን ሁሉ በትዕግሥት እና በዝግጅት ትመለከተው ነበር።
ኢትዮጵያውያን ከጥንት ጀምሮ በጦርነት ኖረዋል። በዚህ የተነሣ የጦርነትን አስከፊ ገጽታ ያውቁታል። ስለሚያውቁትም በቻሉት አማራጭ ሁሉ ይሸሹታል። ለሰላማዊ አማራጭ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋሉ። አንዳንድ ጊዜም ለሰላም ሲሉ ከአስፈላጊው በላይም ያደርጋሉ። ይሄንን ሁሉ ገፍቶ የሚመጣ ጠላት ሲገጥማቸው ግን ለሰላም ሲሉ ዘምተው፤ ለሰላም ሲሉ ያሸንፋሉ።
የዐድዋ ዘመቻም እንደዚሁ ነው። የወራሪው የኢጣልያ ጦር ወደ ጦርነት እንዳይገባ ተለምኗል። የሰላም አማራጮች ቀርበውለታል። "ኩራትና ትዕቢት የሞሉት አናት፣ ሰይፍና ጎራዴ የመቱት አንገት" እንደሚሉት ሆነ። የኢትዮጵያን ትዕግሥት እንደ ፍርሃት፣ የኢትዮጵያን የሰላም መንገድ እንደ ሽንፈት ቆጠረው።
ጠላቶቻችን ምንጊዜም የስሌት ስሕተት ይሠራሉ። ትኅትናችን፣ ትዕግሥታችንና ሰላም ወዳድነታችን ያሳስታቸዋል። ወራሪው የኢጣልያ ጦርም ተሳሳተ።
ኢትዮጵያውያን ግን እየታገሡ ይዘጋጁ ነበሩ። በሁሉም ረገድ ሰላማቸውን ለመጠበቅ ዝግጁ ነበሩ። ነጻነት ፣ ሉዓላዊነት እና ክብር የሚገኙት የሀገር ሰላምን በመጠበቅ መሆኑን ያውቃሉ። ስለዚህ ሰላማቸውን በክንዳቸው ለመጠበቅ ተዘጋጁ።
የዐድዋ ጦርነት ለሰላምና ለጦርነት በሚዋጉ ኃይሎች መካከል የተደረገ ጦርነት ነው። የአሸናፊነታችን አንዱ ምሥጢርም ይሄው ነው። ከጦርነቱ በኋላ ወደ በቀልና ጥላቻ እንዳናመራ ያደረገንም ይሄው ነው። ለሰላም ስንል እንጂ ለጦርነት ስንል አልተዋጋንምና።
የዐድዋ ድል ለሰው ልጅ ሉላዊ ዕሴቶች ያለንን ዋጋ አሳይተንበታል። በምርኮኛ አያያዛችን፣ ከተዋጉን ጋር መልሰን ለሰላማዊ ውይይት በመቀመጣችን፣ ለዘላቂ ሰላም በመሥራታችን።
እናቶቻችንንና አባቶቻችንን በድል አድራጊነታቸው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ዕሴቶች በከፈሉት ዋጋ ጭምር እናመሰግናቸዋለን። የተዋጉት ለሰላም ሲሉ ነው። የተዋጉት ሰላምን እና ሰላማዊ መንገድን እምቢ ካለ ኃይል ጋር ነው።
የዐድዋ ዘማቾች ልጆች ነን። ለሰላም ቅድሚያ እንሰጣለን። ዛሬም ጠላቶቻችን ከተሳሳተ ስሌት እንዳልወጡ እናውቃለን። በሰላማዊ መንገድ የሚመጡትን መቀበል ከዐድዋ ዘማቾች ተምረናል። በሰላም የማይመጡትንም መቅጣት ከዐድዋ ዘማቾች አይተናል። እኛም እንደቀደምቶቻችን የሰላሙን መንገድ እንመርጣለን። ነገር ግን እንደ ቀደምቶቻችን ሁሉ፣ ለሁለቱም ምንጊዜም ዝግጁዎች ነን። የዐድዋ ዘማቾች ልጆች ነንና።
መልካም በዓል ይሁን።
👍4
ዛሬ በይፋ የሚመረቀው የአዲስ አለምአቀፍ የኮንቬንሽን ማዕከል:-
👉 40 ሄክታር መሬት ላይ አርፏል፣
👉እያንዳንዳቸው ከ3 ሺሕ እስከ 4 ሺሕ ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው 2 ትላልቅ አዳራሾች፣ 8 አነስተኛ እና መካከለኛ የመሰብሰቢያ አዳራሾች በጠቅላላ እስከ 10 ሺሕ ሰዎችን የሚያስተናግዱ፣
👉 እስከ 1 ሺሕ ሰዎችን የሚያስተናግዱ አልጋዎችን የያዙ 2 ሆቴሎች ፣
👉ከቤት ውጪ እስከ 50 ሺሕ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል የኤግዚቢሽን ስፍራ፤
👉ሁለት አንፊ ቴአትር፣
👉2 ሄክታር የዉጪ ኤግዚቢሽ ቦታ፣
👉ሁለት ሞሎች፣
👉ሬስቶራንቶች፣ በርካታ የንግድ ሱቆች፣ ባንኮች እንዲሁም ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣
👉በሀገራችን ትልቁ የኮንፍራንስ ማዕከል፣
👉አለምአቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሁነቶችን የሚያስተናግድ፣
👉 በከተማችን ከመስቀል አደባባይ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ አደባባይ ከሆነው የለሚ ፓርክ ጋር ተያይዞ የተሰራ በአጠቃላይ እስከ 2 ሺሕ መኪናዎችን የማቆም አቅም ያላው ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
👉 40 ሄክታር መሬት ላይ አርፏል፣
👉እያንዳንዳቸው ከ3 ሺሕ እስከ 4 ሺሕ ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው 2 ትላልቅ አዳራሾች፣ 8 አነስተኛ እና መካከለኛ የመሰብሰቢያ አዳራሾች በጠቅላላ እስከ 10 ሺሕ ሰዎችን የሚያስተናግዱ፣
👉 እስከ 1 ሺሕ ሰዎችን የሚያስተናግዱ አልጋዎችን የያዙ 2 ሆቴሎች ፣
👉ከቤት ውጪ እስከ 50 ሺሕ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል የኤግዚቢሽን ስፍራ፤
👉ሁለት አንፊ ቴአትር፣
👉2 ሄክታር የዉጪ ኤግዚቢሽ ቦታ፣
👉ሁለት ሞሎች፣
👉ሬስቶራንቶች፣ በርካታ የንግድ ሱቆች፣ ባንኮች እንዲሁም ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣
👉በሀገራችን ትልቁ የኮንፍራንስ ማዕከል፣
👉አለምአቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሁነቶችን የሚያስተናግድ፣
👉 በከተማችን ከመስቀል አደባባይ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ አደባባይ ከሆነው የለሚ ፓርክ ጋር ተያይዞ የተሰራ በአጠቃላይ እስከ 2 ሺሕ መኪናዎችን የማቆም አቅም ያላው ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
👍8
"አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ኢትዮጵያ ሰርታ የምታሳይ ሀገር መሆኗን የሚያሳይ ነው።" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
“በዚህ ዓለም ዐቀፍ ማዕከል ንግድ እንነግድበታለን፣ እውቀት እንለዋወጥበታለን፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን እንቀምርበታለን” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ማዕከሉ በኢትዮጵያ ሀሳብን አልቆ መፈፀም ልምድ እየሆነ መምጣቱን ማሳያ ነውም ብለዋል።
በሀሳብ ደረጃ የነበረውን ጅምር ከዕቅዱ በላይ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ያሟላ አድርገን አልቀን መስራታችንም ለዚህ ዋቢ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
“መፍጠን፣ መፍጠር፣ መስራት ይጠበቅብናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመሩት ስራዎች ውጤት እያሳዩ ነው ብለዋል።
“ነገር ግን ስራዎች በችግር ውስጥ እንደሚሰራ መረዳት ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምንፈልገውን ለውጥ እስክናመጣ አበክረን መስራት ይገባናል ሲሉ ነው ያሳሰቡት።
“ኢትዮጵያን የሚያህል አዲስ አበባን የሚመጥን ለውጥ ማምጣት አላማችን ነው። ለልጆቻችን በረከት ለማውረስ የምታኮራ ሀገር ለማስረከብ እንሰራለን። ኢትዮጵያም ይህንን ማድረግ ትችላለች” ብለዋል።
አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ለቀጣዮቹ 10 ቀናት ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ህዝቡ መጥቶ እንዲጎበኝም ጋብዘዋል።
“በዚህ ዓለም ዐቀፍ ማዕከል ንግድ እንነግድበታለን፣ እውቀት እንለዋወጥበታለን፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን እንቀምርበታለን” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ማዕከሉ በኢትዮጵያ ሀሳብን አልቆ መፈፀም ልምድ እየሆነ መምጣቱን ማሳያ ነውም ብለዋል።
በሀሳብ ደረጃ የነበረውን ጅምር ከዕቅዱ በላይ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ያሟላ አድርገን አልቀን መስራታችንም ለዚህ ዋቢ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
“መፍጠን፣ መፍጠር፣ መስራት ይጠበቅብናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመሩት ስራዎች ውጤት እያሳዩ ነው ብለዋል።
“ነገር ግን ስራዎች በችግር ውስጥ እንደሚሰራ መረዳት ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምንፈልገውን ለውጥ እስክናመጣ አበክረን መስራት ይገባናል ሲሉ ነው ያሳሰቡት።
“ኢትዮጵያን የሚያህል አዲስ አበባን የሚመጥን ለውጥ ማምጣት አላማችን ነው። ለልጆቻችን በረከት ለማውረስ የምታኮራ ሀገር ለማስረከብ እንሰራለን። ኢትዮጵያም ይህንን ማድረግ ትችላለች” ብለዋል።
አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ለቀጣዮቹ 10 ቀናት ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ህዝቡ መጥቶ እንዲጎበኝም ጋብዘዋል።
ከሁሉ በማስቀደም የረዳን እና ያከናወነልን ፈጣሪ ይመስገን!
ዛሬ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ያስመረቅነው የአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማእከል ለከተማችን ብሎም ለሀገራችን አዳዲስ እድሎችን የሚከፍት፣ የማያቋርጥ የሃብት ምንጭ መፍጠሪያ የሚሆን እንዲሁም ለገጽታ ግንባታ እና ለቱርስት ስበት ትልቅ ሚና የሚጫወት ማዕከል ነው::
ማዕከሉ አለምአቀፋዊ ኮንፍራንሶችን፣ የንግድ ውይይቶችንና ስምምነቶችን፣ ባህላዊ መድረኮችንና ልዩ ልዩ ኤግዚቢሽኖችን ለማስተናገድ እንዲሁም አዳዲስ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩበት የንግድና የኢኮኖሚ ስምምነቶች የሚጎለብቱበት ነው::
15ሺ ካሬ የውጪ ሁነት ማስተናገጃ ቦታ ያለው የአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማእከል ባለ 5 ኮከብ ዘመናዊ ሆቴል፣ ሪስቶራንቶች፣ የስፖርት፣ የጤና፣ የመዝናኛ እና የልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫን ያከተተ ግዙፍ ማዕከል ነዉ።
ከዚህም ባሻገር፣ በአንድ ጊዜ እስከ 2000 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችል ፓርኪንግ ያለዉ ሲሆን የለሚ ፓርክ እና በቀጥታ ከአየር መንገድ ጋር የሚያገናኝ ሰፊ የመንገድ መሰረተ ልማትም ከማዕከሉ ጋር ተያይዞ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ፤ይህም ኢኮኖሚያችንን የሚያነቃቃ፣ ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር ከመሆኑ በላይ እንግዶች ሲመጡ ያለምንም እንግልት ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ስፍራ እንዲያገኝ ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡
ይህ ስራ ከዳር እንዲደርስ የቅርብ ድጋፍና ክትትል ላደረጉልን ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ከፍ ያለ ምስጋናና አክብሮቴን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ላቀርብ እወዳለሁ::
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ያስመረቅነው የአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማእከል ለከተማችን ብሎም ለሀገራችን አዳዲስ እድሎችን የሚከፍት፣ የማያቋርጥ የሃብት ምንጭ መፍጠሪያ የሚሆን እንዲሁም ለገጽታ ግንባታ እና ለቱርስት ስበት ትልቅ ሚና የሚጫወት ማዕከል ነው::
ማዕከሉ አለምአቀፋዊ ኮንፍራንሶችን፣ የንግድ ውይይቶችንና ስምምነቶችን፣ ባህላዊ መድረኮችንና ልዩ ልዩ ኤግዚቢሽኖችን ለማስተናገድ እንዲሁም አዳዲስ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩበት የንግድና የኢኮኖሚ ስምምነቶች የሚጎለብቱበት ነው::
15ሺ ካሬ የውጪ ሁነት ማስተናገጃ ቦታ ያለው የአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማእከል ባለ 5 ኮከብ ዘመናዊ ሆቴል፣ ሪስቶራንቶች፣ የስፖርት፣ የጤና፣ የመዝናኛ እና የልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫን ያከተተ ግዙፍ ማዕከል ነዉ።
ከዚህም ባሻገር፣ በአንድ ጊዜ እስከ 2000 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችል ፓርኪንግ ያለዉ ሲሆን የለሚ ፓርክ እና በቀጥታ ከአየር መንገድ ጋር የሚያገናኝ ሰፊ የመንገድ መሰረተ ልማትም ከማዕከሉ ጋር ተያይዞ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ፤ይህም ኢኮኖሚያችንን የሚያነቃቃ፣ ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር ከመሆኑ በላይ እንግዶች ሲመጡ ያለምንም እንግልት ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ስፍራ እንዲያገኝ ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡
ይህ ስራ ከዳር እንዲደርስ የቅርብ ድጋፍና ክትትል ላደረጉልን ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ከፍ ያለ ምስጋናና አክብሮቴን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ላቀርብ እወዳለሁ::
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍4
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
የኅብረተሰቡን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በመንግስትና በህዝብ አጋርነት ለኅብረተሰቡ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራትን በየክፍለ ከተማው በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
የአካባቢ ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወነባቸው ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች መካከል የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ይገኝበታል። ማኅበረሰቡ የሚያነሳቸውን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ነዋሪውን እና በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን አስተዳደሩ አስታውቋል።
የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባደረሰን መረጃ በወረዳ 12 አስተዳደር ልዩ መጠሪያው ሳሎ ጎራ ማህበር ቤቶች በመንግስትና በማኅበረሰቡ አጋርነት የኮብልስቶን መንገድ ንጣፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
"ለረጅም ጊዜያት ስንጠይቅ የነበረዉ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ አግኝቷል!" ያሉት የአካባቢው ነዋሪ አቶ ካህሳይ መዝገቡ አካባቢው ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት የዉስጥ ለዉስጥ ኮብልስቶን መሰረተ ልማት ያልነበረውና በክረምት ወቅት በነዋሪዎች ላይ በተደጋጋሚ የጎርፍ አደጋ ሲያደርስ የነበረ መሆኑን አንስተው ኅብረተሰቡ ከወረዳ አስተዳደሩ ጋር ደረጃውን የጠበቀ የኮብልስቶን መንገድ መዘርጋቱን ተናግረዋል።
የወረዳ 12 የህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ዘውዱ በበኩላቸው አስተዳደሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበረውን የኮብልስቶን መንገድ ንጣፍ ችግር ለመፍታት ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀናጅቶ 2.7 ኪ.ሜትር ደረጃውን የጠበቀ ኮብልስቶን ፕሮጀክት ማጠናቀቁን ጠቅሰዋል።
በመዲናዋ በህዝብና መንግስት ትብብር መሰል የአካባቢ መሰረተ ልማት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል።
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
Instagram - https://www.instagram.com/aacpvcc/
Twitter - https://x.com/aacpvcc
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በመንግስትና በህዝብ አጋርነት ለኅብረተሰቡ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራትን በየክፍለ ከተማው በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
የአካባቢ ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወነባቸው ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች መካከል የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ይገኝበታል። ማኅበረሰቡ የሚያነሳቸውን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ነዋሪውን እና በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን አስተዳደሩ አስታውቋል።
የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባደረሰን መረጃ በወረዳ 12 አስተዳደር ልዩ መጠሪያው ሳሎ ጎራ ማህበር ቤቶች በመንግስትና በማኅበረሰቡ አጋርነት የኮብልስቶን መንገድ ንጣፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
"ለረጅም ጊዜያት ስንጠይቅ የነበረዉ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ አግኝቷል!" ያሉት የአካባቢው ነዋሪ አቶ ካህሳይ መዝገቡ አካባቢው ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት የዉስጥ ለዉስጥ ኮብልስቶን መሰረተ ልማት ያልነበረውና በክረምት ወቅት በነዋሪዎች ላይ በተደጋጋሚ የጎርፍ አደጋ ሲያደርስ የነበረ መሆኑን አንስተው ኅብረተሰቡ ከወረዳ አስተዳደሩ ጋር ደረጃውን የጠበቀ የኮብልስቶን መንገድ መዘርጋቱን ተናግረዋል።
የወረዳ 12 የህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ዘውዱ በበኩላቸው አስተዳደሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበረውን የኮብልስቶን መንገድ ንጣፍ ችግር ለመፍታት ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀናጅቶ 2.7 ኪ.ሜትር ደረጃውን የጠበቀ ኮብልስቶን ፕሮጀክት ማጠናቀቁን ጠቅሰዋል።
በመዲናዋ በህዝብና መንግስት ትብብር መሰል የአካባቢ መሰረተ ልማት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል።
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
Instagram - https://www.instagram.com/aacpvcc/
Twitter - https://x.com/aacpvcc
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👍1👏1
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
ታላቁን የረመዳን ፆም ምክንያት በመድረግ የተለያዩ የበጎነት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል።
ረመዳን በህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ የእዝነትና የርህራሄ ወር ተደርጎ ይወሰዳል። ያለው ለሌለው በማካፈል ከፈጣሪ መንፈሳዊ ፀጋ የሚያስገኝ የበጎነት ስራ ይከናወንበታል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በጎ ፈቃደኛ ለጋሾች ይህን የበጎነት ወር ከተቸገሩ ወገኖች ጋር እንዲያሳልፉና ካላቸው እንዲለግሱ በማስተባበር ላይ ይገኛል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አብነት አካባቢ የሚገኘው የኡመር ኢብኑል ኸጣብ 26 መስጊድ ወጣት ጀመዓ 1 ሺህ 446ኛው የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ ለ500 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ አደርጓል። በዚሁ ክፍለ ከተማ የወረዳ 1 የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ከሰላም መስጊድ እና ከተለያዩ በጎ ፈቃደኞች ጋር በመተባበር ከ161,000 ብር በላይ ማዕድ አጋርቷል።
የሲር ለና በጎ አድራጎት ድርጅት በበኩሉ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ለሚገኙ 900 አቅመ ደካሞች 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የረመዳን ማዕድ አጋርቷል። በጎ አድራጎት ድርጅቱ የማዕድ ድጋፉን ከሰሎሜ የሴቶች አቅም ግንባታ፣ ከዳሽን ባንክ ሸሪክ፣ ከአምሪን አግሪካልቸራልና ፕሮሰሲግ ድርጅት፣ ከሱመያ ት/ቤት 12ተኛ ክፍል ተማሪዎች እና በተለያየ ሀገር ከሚኖሩ የግል ባለሀብቶች እንዳሰባሰበው ገልጿል።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ወረዳ 9 አስተዳደር ከዳሩል ዝክር የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ከ900 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን የረመዳን ማዕድ አጋርቷል።
የአራዳ ክፍለ ከተማ በበኩሉ ከ800 በላይ ለሚሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ ለግሷል።
1 ሺህ 446ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ የተቸገሩ ወገኖችን የመደገፍ፣ የአፍጥር መርሃ ግብር የማዘጋጀትና እርስ በርስ መደጋገፍ እንዲጎለብት የማስተባበር ስራው በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተጠናክሮ ቀጥሏል።
"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
Instagram - https://www.instagram.com/aacpvcc/
Twitter - https://x.com/aacpvcc
ረመዳን በህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ የእዝነትና የርህራሄ ወር ተደርጎ ይወሰዳል። ያለው ለሌለው በማካፈል ከፈጣሪ መንፈሳዊ ፀጋ የሚያስገኝ የበጎነት ስራ ይከናወንበታል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በጎ ፈቃደኛ ለጋሾች ይህን የበጎነት ወር ከተቸገሩ ወገኖች ጋር እንዲያሳልፉና ካላቸው እንዲለግሱ በማስተባበር ላይ ይገኛል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አብነት አካባቢ የሚገኘው የኡመር ኢብኑል ኸጣብ 26 መስጊድ ወጣት ጀመዓ 1 ሺህ 446ኛው የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ ለ500 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ አደርጓል። በዚሁ ክፍለ ከተማ የወረዳ 1 የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ከሰላም መስጊድ እና ከተለያዩ በጎ ፈቃደኞች ጋር በመተባበር ከ161,000 ብር በላይ ማዕድ አጋርቷል።
የሲር ለና በጎ አድራጎት ድርጅት በበኩሉ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ለሚገኙ 900 አቅመ ደካሞች 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የረመዳን ማዕድ አጋርቷል። በጎ አድራጎት ድርጅቱ የማዕድ ድጋፉን ከሰሎሜ የሴቶች አቅም ግንባታ፣ ከዳሽን ባንክ ሸሪክ፣ ከአምሪን አግሪካልቸራልና ፕሮሰሲግ ድርጅት፣ ከሱመያ ት/ቤት 12ተኛ ክፍል ተማሪዎች እና በተለያየ ሀገር ከሚኖሩ የግል ባለሀብቶች እንዳሰባሰበው ገልጿል።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ወረዳ 9 አስተዳደር ከዳሩል ዝክር የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ከ900 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን የረመዳን ማዕድ አጋርቷል።
የአራዳ ክፍለ ከተማ በበኩሉ ከ800 በላይ ለሚሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ ለግሷል።
1 ሺህ 446ኛውን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ የተቸገሩ ወገኖችን የመደገፍ፣ የአፍጥር መርሃ ግብር የማዘጋጀትና እርስ በርስ መደጋገፍ እንዲጎለብት የማስተባበር ስራው በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተጠናክሮ ቀጥሏል።
"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@aacpvcc
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.aacpvcc.gov.et
Instagram - https://www.instagram.com/aacpvcc/
Twitter - https://x.com/aacpvcc
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👍4👏1