ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀረቡ ጥያቄዎች‼️
ከሶማሊላንድ ጋር በተደረገው ስምምነት ተፈጥሮ የነበረውን አላስፈላጊ ውጥረት ለማርገብ የተሰሩ ስራዎችን ቢብራሩ፤
የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ማሻሻያ ከመደረጉ በፊት ነባሩ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር በኢኮኖሚያችን ላይ ያስከትላቸው የነበሩ ችግሮች ምን ነበሩ ቢያብራሩልን፣
ማሻሻያው በ2017 በጀት ዓመት የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማሳደግ አንፃር ምን አስተዋፅኦ አለው ተብሎ ይጠበቃል፣
የሃገራችን የፋይናንስ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት በሁሉም የአገልግሎት መስኮች ጥሩ ውጤት እያስመዘገበ እንደመጣ ተገልጿል፤ የዘርፉ የእስካሁን አፈፃፀም ቢያብራሩልንን፣
2017 በጀት ዓመትን ጨምሮ ለቀጣይ አመታት የፋይናንስ ዘርፍ ተወዳዳሪና ጤናማ ሆኖ እንዲቀጥል እንዲሁም አገልግሎቱን ለዜጎች በተገቢ ሁኔታ እንዲያቀርብ በመንግስት በኩል ምን ታቅዷል፣
ያልተፈቱ የህዝብ ጥያቄዎችን ከመመለስ አኳያ ምን ታስቧል፤ የህዝብ ማንነነት ከመመለስ አንፃር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቁጫ ህዝብና ራስ አስተዳደር የማንነነት ጥያቄ ማግኘት ላይ የርሰዎ ምላሽ ምንድን ነው፣
የሀገራችን ዜጎች በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ በፍጹም ልበ ሙሉነት እንዲሳተፉ ለማድረግ ምን ታስቧል፣
ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ደመወዝ ማሻሻያው እስካሁን ተግባረዊ አልሆነም ለምን
የሥራ ፈላጊዎች ቁጥር እየጨመረ ቢመጣም በፌደራልና በክልል የተፈጠረውን የሥራ እድል በቋሚና በጊዜያዊነት ምን ያህ እንደሆነ ቢብራራ
ከቻይና ጋር ያለው ሁለትዮሽ ግንኙነት ከአለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያለው አንድምታ ምንድነው፣
በሀገራዊ ምክክር ላይ ያለተሳተፉ አካላትን ለማሳተፍ ምን እየተሰራ ነው፣
ከሶማሊላንድ ጋር በተደረገው ስምምነት ተፈጥሮ የነበረውን አላስፈላጊ ውጥረት ለማርገብ የተሰሩ ስራዎችን ቢብራሩ፤
የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ማሻሻያ ከመደረጉ በፊት ነባሩ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር በኢኮኖሚያችን ላይ ያስከትላቸው የነበሩ ችግሮች ምን ነበሩ ቢያብራሩልን፣
ማሻሻያው በ2017 በጀት ዓመት የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማሳደግ አንፃር ምን አስተዋፅኦ አለው ተብሎ ይጠበቃል፣
የሃገራችን የፋይናንስ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት በሁሉም የአገልግሎት መስኮች ጥሩ ውጤት እያስመዘገበ እንደመጣ ተገልጿል፤ የዘርፉ የእስካሁን አፈፃፀም ቢያብራሩልንን፣
2017 በጀት ዓመትን ጨምሮ ለቀጣይ አመታት የፋይናንስ ዘርፍ ተወዳዳሪና ጤናማ ሆኖ እንዲቀጥል እንዲሁም አገልግሎቱን ለዜጎች በተገቢ ሁኔታ እንዲያቀርብ በመንግስት በኩል ምን ታቅዷል፣
ያልተፈቱ የህዝብ ጥያቄዎችን ከመመለስ አኳያ ምን ታስቧል፤ የህዝብ ማንነነት ከመመለስ አንፃር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቁጫ ህዝብና ራስ አስተዳደር የማንነነት ጥያቄ ማግኘት ላይ የርሰዎ ምላሽ ምንድን ነው፣
የሀገራችን ዜጎች በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ በፍጹም ልበ ሙሉነት እንዲሳተፉ ለማድረግ ምን ታስቧል፣
ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ደመወዝ ማሻሻያው እስካሁን ተግባረዊ አልሆነም ለምን
የሥራ ፈላጊዎች ቁጥር እየጨመረ ቢመጣም በፌደራልና በክልል የተፈጠረውን የሥራ እድል በቋሚና በጊዜያዊነት ምን ያህ እንደሆነ ቢብራራ
ከቻይና ጋር ያለው ሁለትዮሽ ግንኙነት ከአለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያለው አንድምታ ምንድነው፣
በሀገራዊ ምክክር ላይ ያለተሳተፉ አካላትን ለማሳተፍ ምን እየተሰራ ነው፣
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-
👉 እንደ ሀገር በተለያዩ ተቋማት እና ዘርፎች ሪፎርም ሥንሠራ ቆይተናል፤ ከዚህ ዓመት ጀምሮ እንደ ሀገር የምናንሠራራበት ጊዜ ነው፡፡ በርካታ ውጤቶችም ይጠበቃሉ፡፡ ቀጣዩ የማጽናት ጊዜ ይሆናል፡፡
👉 አንዳንዶች ትፈርሳላችሁ ቢሉም፤ እንደማንፈርስ እንደ ሀገር በተግባር እያሳየን ነው፡፡ ይህ ጥንካሬ በይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
👉 ባለፈው ዓመት 8 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግበናል፤ ይህም እጅግ አበረታች እና ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሁሉ አስደማሚ ሆኗል፡፡
👉 በያዝነው ዓመት ደግሞ 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በቅንጅት ርብርብ እያደረግን ነው፡፡
👉 የግብርናው ዘርፍ ብቻ በዚህ ዓመት 6 ነጥበ1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ብለን እንጠብቃለን፤ ለዚህም አስፈላጊውን ሁሉ እያደረግን ነው፡፡
👉 እንደ ሀገር በተለያዩ ተቋማት እና ዘርፎች ሪፎርም ሥንሠራ ቆይተናል፤ ከዚህ ዓመት ጀምሮ እንደ ሀገር የምናንሠራራበት ጊዜ ነው፡፡ በርካታ ውጤቶችም ይጠበቃሉ፡፡ ቀጣዩ የማጽናት ጊዜ ይሆናል፡፡
👉 አንዳንዶች ትፈርሳላችሁ ቢሉም፤ እንደማንፈርስ እንደ ሀገር በተግባር እያሳየን ነው፡፡ ይህ ጥንካሬ በይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
👉 ባለፈው ዓመት 8 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግበናል፤ ይህም እጅግ አበረታች እና ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሁሉ አስደማሚ ሆኗል፡፡
👉 በያዝነው ዓመት ደግሞ 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በቅንጅት ርብርብ እያደረግን ነው፡፡
👉 የግብርናው ዘርፍ ብቻ በዚህ ዓመት 6 ነጥበ1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ብለን እንጠብቃለን፤ ለዚህም አስፈላጊውን ሁሉ እያደረግን ነው፡፡
ኢኮኖሚያዊ እድገትን በተመለከተ
በ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፡፡ ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት ዓመትም 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል፡፡ ከዚህም ውስጥ ግብርና 6 ነጥብ 1 በመቶ እንደሚያደግ የሚጠበቅ ሲሆን፤ 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
በ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፡፡ ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት ዓመትም 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል፡፡ ከዚህም ውስጥ ግብርና 6 ነጥብ 1 በመቶ እንደሚያደግ የሚጠበቅ ሲሆን፤ 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👍1
ሌማት ትሩፋት
የሌማት ትሩፋት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተስፋ ሰጪ እድገት የተመዘገበበት ዘርፍ ሆኗል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በሌማት ትሩፋት ምርቶች የ5 ነጥብ 4 በመቶ እድገት የሚያስመዘግቡ ሲሆን፡፡ ለአብነትም በወተት ብቻ በዓመቱ 12 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ይጠበቃል፡፡ በዓመቱ 8 ቢሊዮን የዶሮ እንቁላል እንዲሁም 218 ሺህ ቶን ስጋ እና 297 ሺህ ቶን ማር ምርት ለማምረት የሚያስችል አቅም ተፈጥሯል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የሌማት ትሩፋት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተስፋ ሰጪ እድገት የተመዘገበበት ዘርፍ ሆኗል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በሌማት ትሩፋት ምርቶች የ5 ነጥብ 4 በመቶ እድገት የሚያስመዘግቡ ሲሆን፡፡ ለአብነትም በወተት ብቻ በዓመቱ 12 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ይጠበቃል፡፡ በዓመቱ 8 ቢሊዮን የዶሮ እንቁላል እንዲሁም 218 ሺህ ቶን ስጋ እና 297 ሺህ ቶን ማር ምርት ለማምረት የሚያስችል አቅም ተፈጥሯል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👏3👍1
ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማነቃቃት ከፍተኛ ስራ ተከናውኗል፡፡ በተለይ ከኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ረገድ የተሻል ስራ የተከናወነ ሲሆን፤ አሁን ላይ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም 67 በመቶ ማድረስ ተችሏል፡፡ የኢንዱስትሪ ዘርፉም በተያዘው በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማነቃቃት ከፍተኛ ስራ ተከናውኗል፡፡ በተለይ ከኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ረገድ የተሻል ስራ የተከናወነ ሲሆን፤ አሁን ላይ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም 67 በመቶ ማድረስ ተችሏል፡፡ የኢንዱስትሪ ዘርፉም በተያዘው በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድን በተመለከተ
በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ ይህ አዲስ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያም በዓመት ከ100 አስከ 130 ሚሊዮን መንገደኞችን ያስተነናግዳል፡፡ አሁን ላይ 124 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለማግዛት አዘናል፡፡ ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ የአውሮፕላን ባለቤት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ያለው ተቋም ያደርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ በተለይ በአገልግሎት ዘርፍ ለማስመዝገብ የተያዘውን ውስጥ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው፡፡ በተያዘው በጀት ዓመትም የአገልግሎት ዘርፉ 7 ነጥብ 1 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ ይጠበቃል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ ይህ አዲስ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያም በዓመት ከ100 አስከ 130 ሚሊዮን መንገደኞችን ያስተነናግዳል፡፡ አሁን ላይ 124 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለማግዛት አዘናል፡፡ ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ የአውሮፕላን ባለቤት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ያለው ተቋም ያደርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ በተለይ በአገልግሎት ዘርፍ ለማስመዝገብ የተያዘውን ውስጥ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው፡፡ በተያዘው በጀት ዓመትም የአገልግሎት ዘርፉ 7 ነጥብ 1 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ ይጠበቃል፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👍2
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በ6 ነጥብ 4 በመቶ አድጓል፡፡በተለይ ለኢንቨስትመንት ምቹ ከባቢ በመፍጠር ረገድ የተከናወኑ ስራዎችም ኢንቨስትመንት ለመሳብ ትልቅ አቅም እየፈጠሩ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያላት መሬትና ታዳሽ ኃይል፣ እንዲሁም የሰው ሃይል ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓታል፡፡
የወጪ ንግድን በተመለከተ
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ባላፉት ሶስት ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡በዚህ አፈጻጸም ከቀጠልን በበጀት ዓመቱ መጠናቀቂያ ላይ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ይገኛል፡፡ ይህ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር የ1 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ አለው፡፡ በተለይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በወርቅ ምርት ወጪ ንግድ ላይ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል፡፡ ባለፉት ሶስት ወራት ከወርቅ ወጪ ንግድ 500 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ ይህም የወርቅ ምርት ምን ያህል ለህገ ወጥ ንግድ ተጋልጦ እንደነበር የሚያሳይ ነው፡፡
የመንግስት ገቢን በተመለከተ
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመንግስት ገቢ በእጅጉን ጨምሯል፡፡ ባላፉት ሶስት ወራት 180 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የተሻለ እድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ 109 ቢሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡
የውጭ ሃብት ፍሰትን በተመለከተ
ባላፉት ሶስት ወራት በተለያየ መንገድ ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር መጥቷል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር እጅግ ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ ተመዝግቦበታል፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ሃብት 400 ሚሊዮን ዶላር ነበር፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በ6 ነጥብ 4 በመቶ አድጓል፡፡በተለይ ለኢንቨስትመንት ምቹ ከባቢ በመፍጠር ረገድ የተከናወኑ ስራዎችም ኢንቨስትመንት ለመሳብ ትልቅ አቅም እየፈጠሩ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያላት መሬትና ታዳሽ ኃይል፣ እንዲሁም የሰው ሃይል ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓታል፡፡
የወጪ ንግድን በተመለከተ
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ባላፉት ሶስት ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡በዚህ አፈጻጸም ከቀጠልን በበጀት ዓመቱ መጠናቀቂያ ላይ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ይገኛል፡፡ ይህ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር የ1 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ አለው፡፡ በተለይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በወርቅ ምርት ወጪ ንግድ ላይ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል፡፡ ባለፉት ሶስት ወራት ከወርቅ ወጪ ንግድ 500 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ ይህም የወርቅ ምርት ምን ያህል ለህገ ወጥ ንግድ ተጋልጦ እንደነበር የሚያሳይ ነው፡፡
የመንግስት ገቢን በተመለከተ
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመንግስት ገቢ በእጅጉን ጨምሯል፡፡ ባላፉት ሶስት ወራት 180 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የተሻለ እድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ 109 ቢሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡
የውጭ ሃብት ፍሰትን በተመለከተ
ባላፉት ሶስት ወራት በተለያየ መንገድ ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር መጥቷል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር እጅግ ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ ተመዝግቦበታል፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ሃብት 400 ሚሊዮን ዶላር ነበር፡፡
👍3
የኑሮ ውድነትንና የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በተመለከተ
የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መቅረፍ የምንችለው ምርታማነትን በመጨመር ነው፡፡ የንግድ ስርዓቱን ማዘምንም ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እጅ አጠር ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግስት ከ300 እስከ 400 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መድቧል፡፡ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርት ቤት ምገባ እና እሁድ ገበያ መንግስት አቅመ ደካሞችን ለማገዝ የሚያደርገው ጥረት አካል ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም 249 ሺህ አቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ ይህ መንግስት ባለሃብቶችን በማስተባበር ያከናወነው ስራ ነው፡፡ የዋጋ ንረቱ አሁን ላይ ወደ 17 በመቶ ዝቅ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፤ ይህን ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ የመንግስት ቀዳሚ ትኩረት ነው፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መቅረፍ የምንችለው ምርታማነትን በመጨመር ነው፡፡ የንግድ ስርዓቱን ማዘምንም ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እጅ አጠር ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግስት ከ300 እስከ 400 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መድቧል፡፡ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርት ቤት ምገባ እና እሁድ ገበያ መንግስት አቅመ ደካሞችን ለማገዝ የሚያደርገው ጥረት አካል ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም 249 ሺህ አቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ ይህ መንግስት ባለሃብቶችን በማስተባበር ያከናወነው ስራ ነው፡፡ የዋጋ ንረቱ አሁን ላይ ወደ 17 በመቶ ዝቅ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፤ ይህን ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ የመንግስት ቀዳሚ ትኩረት ነው፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
❤1👍1
ስላምና ደህንነትን በተመለከተ
ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን፡፡ ጦርነትን በተግባር እናውቀዋለን፤ አንፈልገውም፡፡ ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሰላም አማራጭ ውጤቱ ከፍተኛ ነው፡፡ መንግስት ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ቅድሚያ ሰጥቶ ሰርቷል፡፡ አሁንም ያለን አቋም የትኛውም አይነት አለመግባባት በሰላም እንዲፈታ ነው፡፡ ነገር ግን የትኛውም አካል በኃይል እና ጥላቻ መጠፋፋትን እንጂ ዓላማውን ማሳካት አይችልም፡፡ ሰከን ብሎ ማሳብ ይገባል፡፡ ሃሳብ አልባ ትግል ፍሬ የለውም፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን፡፡ ጦርነትን በተግባር እናውቀዋለን፤ አንፈልገውም፡፡ ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሰላም አማራጭ ውጤቱ ከፍተኛ ነው፡፡ መንግስት ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ቅድሚያ ሰጥቶ ሰርቷል፡፡ አሁንም ያለን አቋም የትኛውም አይነት አለመግባባት በሰላም እንዲፈታ ነው፡፡ ነገር ግን የትኛውም አካል በኃይል እና ጥላቻ መጠፋፋትን እንጂ ዓላማውን ማሳካት አይችልም፡፡ ሰከን ብሎ ማሳብ ይገባል፡፡ ሃሳብ አልባ ትግል ፍሬ የለውም፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
ስላምና ደህንነትን በተመለከተ ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን፡፡ ጦርነትን በተግባር እናውቀዋለን፤ አንፈልገውም፡፡ ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሰላም አማራጭ ውጤቱ ከፍተኛ ነው፡፡ መንግስት ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ቅድሚያ ሰጥቶ ሰርቷል፡፡ አሁንም ያለን አቋም የትኛውም አይነት አለመግባባት በሰላም እንዲፈታ ነው፡፡ ነገር ግን የትኛውም አካል በኃይል እና ጥላቻ መጠፋፋትን እንጂ ዓላማውን ማሳካት አይችልም፡፡…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ማብራሪያ
- ስለሰላምና ደህንነት:- ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን፡፡ ጦርነትን በተግባር እናውቀዋለን፤ አንፈልገውም፡፡ ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሰላም አማራጭ ውጤቱ ከፍተኛ ነው፡፡ መንግስት ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ቅድሚያ ሰጥቶ ሰርቷል፡፡ አሁንም ያለን አቋም የትኛውም አይነት አለመግባባት በሰላም እንዲፈታ ነው፡፡ ነገር ግን የትኛውም አካል በኃይል እና ጥላቻ መጠፋፋትን እንጂ ዓላማውን ማሳካት አይችልም፡፡ ሰከን ብሎ ማሳብ ይገባል፡፡ ሃሳብ አልባ ትግል ፍሬ የለውም፡፡
- ስለአማራ ክልል አሁናዊ ሁኔታ:- በአማራ ክልል ላይ ከየትኛውም መንግስት በላይ አሁን ያለው መንግስት በርካታ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በክልሉ ታላላቅ የመንገድ፣ የኢንዱስትሪ የቱሪዝም ልማቶች እየተከናወኑ ነው፡፡ በዚህም ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ የፋሲል ቤተ-መንግስት እየታደሰ ነው፤ በዋና ዋና ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው፡፡ የመገጭ ግድብን 7 ቢሊዩን ብር መድበን ከበርካታ ዓመታት የግንባታ መቋረጥ በኋላ ቀን ከሌት እየገነባን ነው፡፡ ነገር ግን በክልሉ ልማት እንዳይከናወን ለማደናቀፍ የሚጥሩ ኃይሎች አሉ፡፡ ይህን ተባብረን ማስቆም አለብን፡፡ የአማራ ህዝብ ማን እንደሚሰራለትና ማን እንደሚያወራለት ጠንቅቆ የሚያውቅ ጨዋ ህዝብ ነው፡፡ መንግስት ክልሉን የማልማት ስራውን አሁንም አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
- ስለገዥ ትርክት:- ህገመንግስታዊነት-የህግ መንግስት መርሆችና ዴሞክራሲን ያከበረ የጋራ ትርክት መገንባት ፣ ህብረብሔራዊነት - ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር፣ ብሔረሰብና ህዘቦች ሀገር መሆኗን መቀበል ያስፈልጋል ፣ ብልጽግናን በየደረጃው ማረጋገጥ - በሁለም አግባብ በየደረጃው ልማትና ብልጽግናን በማረጋገጥ ድህነትን ለመድፈቅ በጋራ መስራት ይገባል ፣ ማረምና ማስቀጠል-
ትናንት የነበሩ ድክመቶችን ማረም፤ ያሉ ጥንካሬና ወረቶችን ደግሞ ማስቀጠል ይገባል ፣ ሀገራዊ መግባባትን መፍጠር -የጋራ ህልም በመፈጠር የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን ለማየት በጋራ መሰለፍ ይገባል፡፡ ከፓርቲ ባለፈ ትውልድን የሚሻገር እሳቤ መፍጠር ይገባል፡፡
- ስለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን:- ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የተሻለ ስኬት እንዲያስመዘግበ የምክር ቤቱ አባላት ጠንካራ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ለታሃድሶ ኮሚሽንን እና ለሽግግር ፍትህም መሰል ድጋፍ መደረግ አለበት፡፡ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ኮሚሽኖች ትምህርት በመውሰድ አሁን ያሉ እድሎችን መጠቀም ይገባል፡፡ ከዚህ አኳያ መንግስት እንደ አስፈጻሚ አካል የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
-ስለኮሪደር ልማት :- ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ማለት ነው፡፡ ከከተሜነት እድገት ጋር የተሳሳረ ልማት ነው፡፡ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመስራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሰርተዋል፡፡ ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሃዊ ልማት ለዜጎቻችን ያቀረብንበት ነው፡፡ አሁን ላይ በተለያዩ ከተሞች ከምንሰራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት ጀምረናል፡፡ ይህም ኢትዮጵያዊያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ ነው፡፡ የተሟላ ብልጽግናን የምናረጋግጠውም በዚሁ መንገድ ነው፡፡
- ስለዲፕሎማሲ:- የኢትዮጵያ አቋም ከሁሉም ጋር በትብብርና ሰጥቶ በመቀበል መርህ መኖር ነው፡፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል ናት፤ ከራሷ ባለፈ ለአፍሪካ ልማት ቁርጠኛ ናት፡፡ ከየትኛውም ጎራ ጋር ሳንሰለፍ ከሁሉም ጋር በሰጥቶ መቀበል መርህ ለብሔራዊ ጥቅማችን እንሰራለን፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይህን በመገንዘብ ሀገርን አስቀድሞ መስራት አለበት፡፡ በውስጥ የሚኖረን አንድነትና ሰላም ለዲፕሎማሲያዊ ጥንካሬያችን ከፍተኛ ሚና አለው፡፡
- ስለባህር በር ጥያቄ: - ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል፡፡ በዚህ ጉዳይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም አለን፡፡ ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም፡፡ ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ አማራጭ ነው፡፡ ይህ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው፤ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል፡፡ ኢትዮጵያ የትኛውንም ሀገር ላይ ወረራም ሆነ ጥቃት አትፈጽምም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያን ለመንካት የሚሞክሩ ካሉ አሳፍረን እንመልሳለን፡፡ ይህን ማድረግ የሚያስችል በቂ አቅም አለን፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
- ስለሰላምና ደህንነት:- ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን፡፡ ጦርነትን በተግባር እናውቀዋለን፤ አንፈልገውም፡፡ ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሰላም አማራጭ ውጤቱ ከፍተኛ ነው፡፡ መንግስት ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ቅድሚያ ሰጥቶ ሰርቷል፡፡ አሁንም ያለን አቋም የትኛውም አይነት አለመግባባት በሰላም እንዲፈታ ነው፡፡ ነገር ግን የትኛውም አካል በኃይል እና ጥላቻ መጠፋፋትን እንጂ ዓላማውን ማሳካት አይችልም፡፡ ሰከን ብሎ ማሳብ ይገባል፡፡ ሃሳብ አልባ ትግል ፍሬ የለውም፡፡
- ስለአማራ ክልል አሁናዊ ሁኔታ:- በአማራ ክልል ላይ ከየትኛውም መንግስት በላይ አሁን ያለው መንግስት በርካታ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በክልሉ ታላላቅ የመንገድ፣ የኢንዱስትሪ የቱሪዝም ልማቶች እየተከናወኑ ነው፡፡ በዚህም ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ የፋሲል ቤተ-መንግስት እየታደሰ ነው፤ በዋና ዋና ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው፡፡ የመገጭ ግድብን 7 ቢሊዩን ብር መድበን ከበርካታ ዓመታት የግንባታ መቋረጥ በኋላ ቀን ከሌት እየገነባን ነው፡፡ ነገር ግን በክልሉ ልማት እንዳይከናወን ለማደናቀፍ የሚጥሩ ኃይሎች አሉ፡፡ ይህን ተባብረን ማስቆም አለብን፡፡ የአማራ ህዝብ ማን እንደሚሰራለትና ማን እንደሚያወራለት ጠንቅቆ የሚያውቅ ጨዋ ህዝብ ነው፡፡ መንግስት ክልሉን የማልማት ስራውን አሁንም አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
- ስለገዥ ትርክት:- ህገመንግስታዊነት-የህግ መንግስት መርሆችና ዴሞክራሲን ያከበረ የጋራ ትርክት መገንባት ፣ ህብረብሔራዊነት - ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር፣ ብሔረሰብና ህዘቦች ሀገር መሆኗን መቀበል ያስፈልጋል ፣ ብልጽግናን በየደረጃው ማረጋገጥ - በሁለም አግባብ በየደረጃው ልማትና ብልጽግናን በማረጋገጥ ድህነትን ለመድፈቅ በጋራ መስራት ይገባል ፣ ማረምና ማስቀጠል-
ትናንት የነበሩ ድክመቶችን ማረም፤ ያሉ ጥንካሬና ወረቶችን ደግሞ ማስቀጠል ይገባል ፣ ሀገራዊ መግባባትን መፍጠር -የጋራ ህልም በመፈጠር የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን ለማየት በጋራ መሰለፍ ይገባል፡፡ ከፓርቲ ባለፈ ትውልድን የሚሻገር እሳቤ መፍጠር ይገባል፡፡
- ስለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን:- ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የተሻለ ስኬት እንዲያስመዘግበ የምክር ቤቱ አባላት ጠንካራ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ለታሃድሶ ኮሚሽንን እና ለሽግግር ፍትህም መሰል ድጋፍ መደረግ አለበት፡፡ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ኮሚሽኖች ትምህርት በመውሰድ አሁን ያሉ እድሎችን መጠቀም ይገባል፡፡ ከዚህ አኳያ መንግስት እንደ አስፈጻሚ አካል የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
-ስለኮሪደር ልማት :- ኮሪደር ልማት ማለት ኢትዮጵያን የሚመጥን ከተማ መገንባት ማለት ነው፡፡ ከከተሜነት እድገት ጋር የተሳሳረ ልማት ነው፡፡ በኮሪደር ልማት ሰፋፊ መንገድ ከመስራት ባለፈ ታዳጊዎች እግር ኳስ የሚጫወቱባቸውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና የእግረኛ መንገዶች ተሰርተዋል፡፡ ይህም ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሃዊ ልማት ለዜጎቻችን ያቀረብንበት ነው፡፡ አሁን ላይ በተለያዩ ከተሞች ከምንሰራው የኮሪደር ልማት ባሻገር፤ የገጠር ኮሪደር ልማት ጀምረናል፡፡ ይህም ኢትዮጵያዊያን የተሻለ ኑሮ ይገባቸዋል በሚል የተጀመረ ነው፡፡ የተሟላ ብልጽግናን የምናረጋግጠውም በዚሁ መንገድ ነው፡፡
- ስለዲፕሎማሲ:- የኢትዮጵያ አቋም ከሁሉም ጋር በትብብርና ሰጥቶ በመቀበል መርህ መኖር ነው፡፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል ናት፤ ከራሷ ባለፈ ለአፍሪካ ልማት ቁርጠኛ ናት፡፡ ከየትኛውም ጎራ ጋር ሳንሰለፍ ከሁሉም ጋር በሰጥቶ መቀበል መርህ ለብሔራዊ ጥቅማችን እንሰራለን፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይህን በመገንዘብ ሀገርን አስቀድሞ መስራት አለበት፡፡ በውስጥ የሚኖረን አንድነትና ሰላም ለዲፕሎማሲያዊ ጥንካሬያችን ከፍተኛ ሚና አለው፡፡
- ስለባህር በር ጥያቄ: - ኢትዮጵያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በቀይ ባህር ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል፡፡ በዚህ ጉዳይ ወደ ኋላ የማይል ይፋዊ አቋም አለን፡፡ ነገር ግን ይህን ለማሳካት ጦርነትም ሆነ የኃይል አማራጭ አንፈልግም፡፡ ፍላጎታችንን ማሳካት የምንሻው በሰላማዊ አማራጭ ነው፡፡ ይህ ምክንያታዊና ፍትሃዊ ጥያቄ ነው፤ እኛ ባናሳካው ልጆቻችን ያሳኩታል፡፡ ኢትዮጵያ የትኛውንም ሀገር ላይ ወረራም ሆነ ጥቃት አትፈጽምም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያን ለመንካት የሚሞክሩ ካሉ አሳፍረን እንመልሳለን፡፡ ይህን ማድረግ የሚያስችል በቂ አቅም አለን፡፡
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
በስኬታማ የሀብት አጠቃቀም ዙሪያ በቂ ግንዛቤ በመያዝ ለተቋማዊ ውጤት መረባረብ ይገባል።
ኮሚሽኑ በሀብት አጠቃቀምና በኦዲት ዙሪያ ለተቋሙ ባለሙያዎችና አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት ኮሚሽነር ይመር ከበደ አንድ ተቋም ለተደራጀበት ዓላማ አሰራሮችንና መመሪያዎችን ለማስጠበቅ የኦዲት ስራ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው የኮሚሽኑ አሰራሮች እንዲጠበቁ በቂ ግንዛቤ በመያዝ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ሀብት ከብክነት በፀዳ መልኩ በትክክል ስራ ላይ መዋሉን ማረጋገጥ ለተቋማዊ ለውጥ ወሳኝ እንደሆነ ነው ኮሚሽነሩ የተናገሩት።
ኮሚሽኑ በሀብት አጠቃቀምና በኦዲት ዙሪያ ለተቋሙ ባለሙያዎችና አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት ኮሚሽነር ይመር ከበደ አንድ ተቋም ለተደራጀበት ዓላማ አሰራሮችንና መመሪያዎችን ለማስጠበቅ የኦዲት ስራ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው የኮሚሽኑ አሰራሮች እንዲጠበቁ በቂ ግንዛቤ በመያዝ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ሀብት ከብክነት በፀዳ መልኩ በትክክል ስራ ላይ መዋሉን ማረጋገጥ ለተቋማዊ ለውጥ ወሳኝ እንደሆነ ነው ኮሚሽነሩ የተናገሩት።
👍7