የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
823 subscribers
2.14K photos
47 videos
265 links
Download Telegram
የኀብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን - አዲስ አበባ
Photo
በአዲስ አበባ ባለፈው ክረምት 5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር የሚገመት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሰጥቷል።

በመዲናችን አዲስ አበባ በ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ 5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር የሚገመት አገልግሎት ተሰጥቷል።

የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ ከግንቦት 1/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 5 ወራት “በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!” በሚል መሪ ቃል በ15 ፕሮግራሞች እና በ18 ንዑሳን ተግባራት ሲካሔድ ቆይቷል፡፡

በድግግሞሽ 3 ሚሊዮን በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉ ሲሆን 764 ሺህ 256 ዜጎች በቀጥታ ተጠቃሚ ሆነውበታል፡፡

በዚኽ መርሀ ግብር 2,574 የአቅመ ደካሞች ፣ የሀገር ባለውለታዎች እና አረጋውያን ቤቶች ተገንብተዋል ፤ 12 ሺህ 870 ቤተሰቦች በቀጥታ የቤት ግንባታና እድሳት አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል።

469,176 የኅብረተሰብ ክፍሎች በበዓላትና በተለያዩ ወቅቶች ማዕድ ተጋርተዋል ፤ 89 ሺህ ከፍለው መታከም የማይችሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች ነፃ የህክምና ድጋፍ አግኝተዋል።

በደም እጥረት ምክንያት የሚፈጠርን ሞት ለመቀነስ ከበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሽ ወጣቶች 32 ሺህ 648 ዩኒት ደም ተሰብስቧል፡፡

94 ሺህ ተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርትና አጫጭር የክህሎት ስልጠና ያገኙ ሲሆን 6 ሺህ 509 የመንገድ ደህንነት ትራፊኮች የትራፊክ መጨናነቅ በሚበዛባቸው አደባባዮችና መንገዶች ላይ እንቅስቃሴውን በማሳለጥ ፣ በመንገድ አጠቃቀምና በትራፊክ አደጋ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር እንዲኹም በእግረኛ መንገዶች አቅመ ደካሞችን በማሻገር ተሳትፈዋል።

ከ2 ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞች በአረንጓዴ አሻራ ተግባር እንዲኹም 6 ሺህ 35 በጎ ፈቃደኞች አገልግሎት በሚበዛባቸው የመንግስት ተቋማት የባለጉዳይ እንግልት በመቀነስ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡

የማኅበረሰባችን እርስ በርስ የመረዳዳት እሴት መጠናከር ፤ በጎ ፈቃደኞች ከማኅረሰባቸው መስጠትን ፣ ልግስናን ፣ መደጋገፍን ፣ ፍቅርንና መልካም እሴቶችን መቅሰም ፤ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከፍ ማለት እና ከተማችን ለኑሮ ምቹና ተምሳሌት እንድትሆን ማስቻል በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች ናቸው።

ለተመዘገበው ሁሉ አቀፍ ውጤት የከተማው በየደረጃው ያለ አመራር ፣ የበጎ ፈቃደኞች ፣ የሚዲያ አካላትና የባለድርሻ ተቋማት ትብብር የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። በዚኽም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ልባዊ ምስጋናውን በአክብሮት ይገልፃል።

"በጎ ፈቃደኝነት ፤ ለማኅበረሰብ ለውጥ!"

የማኀበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን፥
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/cpvcc.2015
ቴሌግራም - https://t.me/CommunityPVC
ቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@voluntarismaddis16
ዩቱዩብ - https://youtube.com/@communityparticipationvolu8714
ዌብሳይት - www.volunteeraddis.et
Instagram - https://www.instagram.com/communitypv/
Twitter - https://x.com/Volunteeraddis
የ2017 በጀት ዓመት የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት

👉መሪ ቃሉ “በጎ ፈቃደኝነት ለማህበረሰብ ለውጥ!” የሚል ነው፡፡
👉ከጥቅምት 1/2017 እስከ ግንቦት 30/2017 ዓ.ም ድረስ ለ8 ወራት ይቆያል፡፡
👉 በ12 ዋና ዋና ፕግራሞችና 13 መርሀ ግብሮች ይተገበራል፡፡
👉1 ሚሊዮን በጎ ፈቃደኞች ይሳተፉበታል፡፡
👉781,844 የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ይደረጋሉ፡፡
👉6,599,778,376 ብር የመንግስት ወጪን ይታደጋል፡፡

👏ዋና ዋና ተግባራት፣
👉780,824 የህብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ ይጋራሉ፡፡
👉4,026 የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች ቤቶች ይገነባሉ፡፡
👉100,000 በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ የችግኝ እንክብካቤ ይደረጋል፡፡
👉12,000 በጎ ፈቃደኞች ከስኬታማ ግለሰቦች የህይወት ልምድና ተሞክሮ እንዲማሩ ይደረጋል፡፡

👉30,480 የህብረተሰብ ክፍሎች ነፃ የህክምና ድጋፍና አገልግሎት ያገኛሉ፡፡
👉ከደም ለጋሽ ወጣት በጎ ፈቃደኞች 33,352 ዩኒት ደም ይሰበሰባል፡፡
👉2,500 በጎ ፈቃደኞችን በማሳተፍ በሆስፒታሎች ህሙማንን የመንከባከብ አገልግሎት ይሰጣል፡፡
👉1965 በጎ ፈቃደኞችን አገልግሎት በሚበዛባቸው የመንግስት ተቋማት ይሰማራሉ፡፡
👉60,000 በጎ ፈቃደኞች በአደባባይ የሚከናወኑ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ ያስተባብራሉ፡፡
👉5000 ወጣቶች በማህበራዊ ሚድያው በጎ ተፅዕኖ እንዲፈጥሩ ይደረጋል፡፡
👉500 የአደጋ ተከላካይ በጎ ፈቃደኞች ወደ አገልግሎት ይገባሉ፡፡
👉1729 በጎ ፈቃደኞችን በተመረጡ ክልሎች የከተማችንን የበጎ ፈቃድ ተሞክሮ እንዲያጋሩ ይደረጋል፡፡

"በጎ ፈቃደኝነት ለማኅበረሰብ ለውጥ!"
ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀረቡ ጥያቄዎች‼️

ከሶማሊላንድ ጋር በተደረገው ስምምነት ተፈጥሮ የነበረውን አላስፈላጊ ውጥረት ለማርገብ የተሰሩ ስራዎችን ቢብራሩ፤

የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ማሻሻያ ከመደረጉ በፊት ነባሩ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር በኢኮኖሚያችን ላይ ያስከትላቸው የነበሩ ችግሮች ምን ነበሩ ቢያብራሩልን፣

ማሻሻያው በ2017 በጀት ዓመት የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማሳደግ አንፃር ምን አስተዋፅኦ አለው ተብሎ ይጠበቃል፣

የሃገራችን የፋይናንስ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት በሁሉም የአገልግሎት መስኮች ጥሩ ውጤት እያስመዘገበ እንደመጣ ተገልጿል፤ የዘርፉ የእስካሁን አፈፃፀም ቢያብራሩልንን፣

2017 በጀት ዓመትን ጨምሮ ለቀጣይ አመታት የፋይናንስ ዘርፍ ተወዳዳሪና ጤናማ ሆኖ እንዲቀጥል እንዲሁም አገልግሎቱን ለዜጎች በተገቢ ሁኔታ እንዲያቀርብ በመንግስት በኩል ምን ታቅዷል፣

ያልተፈቱ የህዝብ ጥያቄዎችን ከመመለስ አኳያ ምን ታስቧል፤ የህዝብ ማንነነት ከመመለስ አንፃር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቁጫ ህዝብና ራስ አስተዳደር የማንነነት ጥያቄ ማግኘት ላይ የርሰዎ ምላሽ ምንድን ነው፣

የሀገራችን ዜጎች በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ በፍጹም ልበ ሙሉነት እንዲሳተፉ ለማድረግ ምን ታስቧል፣

ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ደመወዝ ማሻሻያው እስካሁን ተግባረዊ አልሆነም ለምን

የሥራ ፈላጊዎች ቁጥር እየጨመረ ቢመጣም በፌደራልና በክልል የተፈጠረውን የሥራ እድል በቋሚና በጊዜያዊነት ምን ያህ እንደሆነ ቢብራራ

ከቻይና ጋር ያለው ሁለትዮሽ ግንኙነት ከአለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያለው አንድምታ ምንድነው፣

በሀገራዊ ምክክር ላይ ያለተሳተፉ አካላትን ለማሳተፍ ምን እየተሰራ ነው፣
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-

👉 እንደ ሀገር በተለያዩ ተቋማት እና ዘርፎች ሪፎርም ሥንሠራ ቆይተናል፤ ከዚህ ዓመት ጀምሮ እንደ ሀገር የምናንሠራራበት ጊዜ ነው፡፡ በርካታ ውጤቶችም ይጠበቃሉ፡፡ ቀጣዩ የማጽናት ጊዜ ይሆናል፡፡

👉 አንዳንዶች ትፈርሳላችሁ ቢሉም፤ እንደማንፈርስ እንደ ሀገር በተግባር እያሳየን ነው፡፡ ይህ ጥንካሬ በይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

👉 ባለፈው ዓመት 8 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግበናል፤ ይህም እጅግ አበረታች እና ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሁሉ አስደማሚ ሆኗል፡፡

👉 በያዝነው ዓመት ደግሞ 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በቅንጅት ርብርብ እያደረግን ነው፡፡

👉 የግብርናው ዘርፍ ብቻ በዚህ ዓመት 6 ነጥበ1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ብለን እንጠብቃለን፤ ለዚህም አስፈላጊውን ሁሉ እያደረግን ነው፡፡
ኢኮኖሚያዊ እድገትን በተመለከተ

በ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፡፡ ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት ዓመትም 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል፡፡ ከዚህም ውስጥ ግብርና 6 ነጥብ 1 በመቶ እንደሚያደግ የሚጠበቅ ሲሆን፤ 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል፡፡

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👍1
ሌማት ትሩፋት

የሌማት ትሩፋት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተስፋ ሰጪ እድገት የተመዘገበበት ዘርፍ ሆኗል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በሌማት ትሩፋት ምርቶች የ5 ነጥብ 4 በመቶ እድገት የሚያስመዘግቡ ሲሆን፡፡ ለአብነትም በወተት ብቻ በዓመቱ 12 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ይጠበቃል፡፡ በዓመቱ 8 ቢሊዮን የዶሮ እንቁላል እንዲሁም 218 ሺህ ቶን ስጋ እና 297 ሺህ ቶን ማር ምርት ለማምረት የሚያስችል አቅም ተፈጥሯል፡፡

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👏3👍1
ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ

ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማነቃቃት ከፍተኛ ስራ ተከናውኗል፡፡ በተለይ ከኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ረገድ የተሻል ስራ የተከናወነ ሲሆን፤ አሁን ላይ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም 67 በመቶ ማድረስ ተችሏል፡፡ የኢንዱስትሪ ዘርፉም በተያዘው በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል፡፡

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድን በተመለከተ

በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ ይህ አዲስ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያም በዓመት ከ100 አስከ 130 ሚሊዮን መንገደኞችን ያስተነናግዳል፡፡ አሁን ላይ 124 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለማግዛት አዘናል፡፡ ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ የአውሮፕላን ባለቤት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ያለው ተቋም ያደርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ በተለይ በአገልግሎት ዘርፍ ለማስመዝገብ የተያዘውን ውስጥ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው፡፡ በተያዘው በጀት ዓመትም የአገልግሎት ዘርፉ 7 ነጥብ 1 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ ይጠበቃል፡፡

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
👍2
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በ6 ነጥብ 4 በመቶ አድጓል፡፡በተለይ ለኢንቨስትመንት ምቹ ከባቢ በመፍጠር ረገድ የተከናወኑ ስራዎችም ኢንቨስትመንት ለመሳብ ትልቅ አቅም እየፈጠሩ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያላት መሬትና ታዳሽ ኃይል፣ እንዲሁም የሰው ሃይል ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓታል፡፡

የወጪ ንግድን በተመለከተ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ባላፉት ሶስት ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡በዚህ አፈጻጸም ከቀጠልን በበጀት ዓመቱ መጠናቀቂያ ላይ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ይገኛል፡፡ ይህ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር የ1 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ አለው፡፡ በተለይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በወርቅ ምርት ወጪ ንግድ ላይ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል፡፡ ባለፉት ሶስት ወራት ከወርቅ ወጪ ንግድ 500 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ ይህም የወርቅ ምርት ምን ያህል ለህገ ወጥ ንግድ ተጋልጦ እንደነበር የሚያሳይ ነው፡፡

የመንግስት ገቢን በተመለከተ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመንግስት ገቢ በእጅጉን ጨምሯል፡፡ ባላፉት ሶስት ወራት 180 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የተሻለ እድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ 109 ቢሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡

የውጭ ሃብት ፍሰትን በተመለከተ
ባላፉት ሶስት ወራት በተለያየ መንገድ ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር መጥቷል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር እጅግ ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ ተመዝግቦበታል፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ሃብት 400 ሚሊዮን ዶላር ነበር፡፡
👍3
የኑሮ ውድነትንና የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በተመለከተ

የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መቅረፍ የምንችለው ምርታማነትን በመጨመር ነው፡፡ የንግድ ስርዓቱን ማዘምንም ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እጅ አጠር ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግስት ከ300 እስከ 400 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መድቧል፡፡ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርት ቤት ምገባ እና እሁድ ገበያ መንግስት አቅመ ደካሞችን ለማገዝ የሚያደርገው ጥረት አካል ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም 249 ሺህ አቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ ይህ መንግስት ባለሃብቶችን በማስተባበር ያከናወነው ስራ ነው፡፡ የዋጋ ንረቱ አሁን ላይ ወደ 17 በመቶ ዝቅ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፤ ይህን ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ የመንግስት ቀዳሚ ትኩረት ነው፡፡

#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
1👍1