Dildiy - (ድልድይ)
1.33K subscribers
395 photos
82 videos
1 file
116 links
Dildiy | دیل‌دیی Whispers of the soul, echoes of the universe. 

A space where mysticism meets quantum wonder, where love, presence, and oneness awaken us. 

Thoughts, poems, and reflections for the seekers of light and the questioners of truth.

Bridge.
Download Telegram
.
.
.

ሰዎች በአንድም በሌላም መንገድ ሊጎዱህ ይችላሉ፤ የዝቅተኝነት ስሜት እንደሚያንገላታው ሰው ግን የሚያሳምምህ አይኖርም።
___

@bridgethoughts
12👌4💯2
.
.
.

የዓለማችን 'ግዙፍ ሚዲያዎች' - የቀን ውሎ 90% ያህሉ - በጦርነት፣ በሽብር፣ በግጭትና በጉስቁልና ዜናዎች ብቻ ይሸፈናል ቢባል ድምዳሜው ግነት ተጭኖታል አያስብልም...


በጎ ነገር ባለበት በጭራሽ ዝር አይሉም - ቢሉም እንኳ ደጉን ለመዘገብ ሊሆን አይችልም... ይልቁን በሰርግህ ዕለት ተገኝተው ያንተ ደስታ ለሌሎች የሃዘን ምክንያት ሊሆን የሚችልበትን መንገድ በዘገባቸው በማንሳት ሊያስገርሙህ ይችላሉ...


ይህ በተዘዋዋሪ የሚፈጥረው ጫናና ውጥረት ቀላል አይደለም... 


ዓለሚቱ አንዳችም በጎ ነገር የሌላት መስላ ስትቀርብ ዕለታዊ መስተጋብራችን ድንዛዜ ይዋረሰዋል... ተስፋ መቁረጥና ሕይወትን አጨልሞ የማየት አባዜ ይጫነዋል...


ምዕራባውያን ሚዲያዎች ከበጎ ነገር ይልቅ 'ክፉው' ላይ ብቻ የሚረባረቡበት ምክንያት ምንም ይሁን የሚቃኙበት Editorial policy ግን አስገራሚም አሳዛኝም ነው...


ይህን እውነት ይዘን በልካቸው ስናወራ እንዲህ እንላቸዋለን...


CNN - Continuous Negative News

BBC - Brutal Biased Channel

AFP - All Fear Press

NYT - Not Your Truth

____

@bridgethoughts
11👌2
🔔 Before the Drums Beat Again 🔔


Once upon a time, there was no Ethiopia and Eritrea.


There were only brothers — children of the same highlands,
breathing the same wind that rises from the Red Sea
and settles on the mountains.


The rivers did not know borders.
The mothers spoke the same lullabies.
The sky covered us all — without a passport.


But then came the shadow of lines drawn on the earth —
names that separated hearts, flags that replaced embraces.


And in the name of these lines,
thousands of young men and women offered their blood to the soil.
Still, the soil cried — not for victory,
but for the innocence lost.


Years later, the world rejoiced when the two brothers met again —
smiles, handshakes, hope.

The world said, “At last, the Horn of Africa breathes again.”
You both promised peace,
and the earth, weary from the echo of guns, finally rested.


Our Prime Minister received the world’s peace prize —
but more importantly,
our people received the peace itself.


Seven years passed.


Yet now, we hear the sound of old drums beating again.


Excellencies,

Before those drums awaken the ghosts of yesterday, please —
sit and talk.


Sit not as leaders of separate lands,
but as brothers who share one ancient wound.
History has already buried too many sons.
Must we dig new graves for the same reason?


A sea is not worth a single mother’s tear.
A port is not worth the trembling of a child
who hears warplanes in the sky.


The world does not need another headline of sorrow from the Horn;
it needs the light of wisdom from its cradle.


Yes — Ethiopia needs a gate to the sea.
And yes — Eritrea needs her sovereignty respected.
But more than that, both need each other.


The sea and the highlands are not enemies;
they complete each other —
like breath and heartbeat.


If you two meet,
not to debate, but to listen —
the Red Sea will calm its waves.
Trade will flow, families will unite,
and the wounds of decades will begin to heal.


But if the guns speak again,
no one will win —
except those who sell the bullets.


Please, for the sake of history yet to be written,
for the mothers who have already buried too much,
for the youth who dream of life, not war —
Sit and talk.


Let wisdom be your weapon.
Let love be your strategy.
Let peace be your legacy.


The Horn does not need heroes of war anymore.
It needs fathers of peace.


🕊️ May reason rise above rage,
and may love remember what history forgets.

____

@bridgethoughts
🕊103🙏2
.
.
.

ሁሉንም አታወራም አይደል?... ሁሉን ከሁሉ ጋር አትካፈልም... 


አንዳንዴ... 


በግል ጉባኤህ፣ በልብ ሽሽግህ፣ በነፍስያህ ለዛ፣ ካዘመመ ጎጆህ ታዛ - ብቻህን ቆዝመህ የምታንሾካሹከው ጉዳይ ይኖርሃል...


ደግሞስ ሰው ሁሉ በየቤቱ በራሱ ድካም እየደቀቀ፣ በግሉ ሃሳብ እያለቀ፣ በዕጣፈንታው ህመም ታስሮ፣ በራስ ፈተና ተቸንክሮ - ጉስቁልቁል እያለ ምን ብለህ የኔን ብቻ ስማ ትለዋለህ?...


ከመከራህ መከራዬ ይልቃል ነው?... 

ከስቀትህ ሰቀቀኔ ይብሳል ነው?...


[በደንብ ካሰብከው - የሌሎችን ሕማም ለመታመም አይደለም - የራሱን ቁስል ከፍቶ ለማየትም ልቢቱ የሳሳችበት በየቤቱ ብዙ ነው...]

.
.
.


ይልቅ ምን አለ መሰለህ?...


ሰሚህ በችግርህ ውስጥ ጉድለቱን እያየ ከሰማህ - አደመጠህ አይባልም - ተነፈስክበት እንጂ...


ሰሚህ ስለሰማህ ድብርት ከተጫነው - አደመጠህ አይባልም - ጫንክበት እንጂ...


'ይህችማ ምን አላት? እኔ የደረሰብኝን ብታውቅ...' ብሎ ከመለሰልህ - አደመጠህ አይባልም - ቁስልህን ካደብህ እንጂ...


እና እንዳልኩህ ነው...


አንዳንድ ጊዜ... ለብቻህ የምትሸከመው መስቀል ይኖርሃል!!...

____

@bridgethoughts
15❤‍🔥2🫡2
ሰላም ወዳጆች፤

ድልድይ - ቀለም ላይ አምደኛ ሆና ተከስታለች፤ ይህንን የጥበብ ብፌ ስጋብዛችሁ ደስ እያለኝ ነው...

___

ግቡ፣ Join አድርጉ፣ አዲሱን ቅጽ አንብቡ!!

___

ቀለም መጽሔት🗞️

ቅፅ 1  እትም 5


እያነበባቹህ ለወዳጅዎ ያጋሩ
ለሀሳብ አስተያየት

@KelemMagazine

Telegram 👇❤️
@kelemofficial
3🥰1👏1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.

"ምንአገባኝ?" ብሎ መተው እኮ ይቻላል... 

"ማንን ነው የሚያገባው ታዲያ?" ቢሉን መልስ የለንም እንጂ...

__

የገጠመን ፈተና ይህ ነው... ብዙ ሰዎች ብዙ ነገር አያገባቸውም... 

ለዚህ ነው - ሃገር የጥቂት ትጉሃን መዋጮ ውጤት ነች ለማለት የምደፍረው... ብዙሃኑ ነገር ዓለሙን እኒሁ ጥቂቶች ላይ ጥሎ 'ጥቅሙን' ብቻ የሚያሳድድ ነው...

__

በተገኘህበት ቦታ - 'መገኘትህን' የሚናገር አንዳች ቁምነገር ካልተውክ መኖርህ ከቁጥርነት አልዘለለም ነበር ማለት ነው...

__

@bridgethoughts
13
.
.
.

የኔነሽ፣ 
የኔነሽ፣
የኔነሽ ይሏታል
እርሷም ደስ ይላታል


የሁሉ መሆን ግን ምን ያደርግላታል?

.
.
.

የሁሉ የሆነ - እንዳይሆን ለማንም 
ሁሉ ዘንድ የሞቀ - እንዳይገኝ የትም፤


ጸሐይ ነግራናለች - በዘለለት ልሳን
ሰርክ አዲስ እንግዳ - እኛ እንጂ ያልነቃን፤


በጠዋት ፈገግታ

በእኩለ ቀን ዋዕይ

ከባን ብትውልም፣

ጽልመት ሲገማሸር አታስተማምንም።

___

@bridgethoughts
5👏3
.
.
.

"Let him who is without sin among you be the first to throw a stone at her." ~ Jesus

__

ፍርድ እውቀት አይጠይቅም... ማንም ሰው ላይ መፍረድ ቀላል ነው... የሞራል ጥያቄ ግን አለው... 'አንተ ማን ሆነህ ነው ሌላው ላይ ጣት የምትቀስረው?' የሚያስብል...


የ blame shift ጨዋታ በጣም ያስተዛዝባል... 'ከደሙ ንጹህ ነኝ' ክህደት በጣም ያሳቅቃል... 'የወደቀ እንጨት' ላይ ምሳር መጠቅጠቅ የባለ እጁን ቁሸት አይከልልም... 'እነ እከሌ' የማለት ድፍረት የእኔታን በደል አይፍቅም...


ሁላችንም ቤት ጉዶች አሉ... ወይ እስኪመቸን የምንጠብቅ 'አድፋጮች'፣ አልያም ነጥቀን የምንሰጋ 'ድንጉጦች' ነን... ይህን መካድ አይቻልም...


አዎን...


እስክንያዝ እንጂ ሁላችንም የሰረቅነው አለን... ስላልተመቸን እንጂ ልንዘርፍ የምናደባለት አለን... ይህ የሚዋሽ አይደለም...


በነገራችን ላይ ሌሎች ላይ የምንቀስራት ጣት ስሟ 'ሌባ ጣት' ይባላል...

___

ሃበሻ ጥሩ ብሂል አለችው... 


"ስራው ያውጣው" የምትል... 


በምሳሌዋ ውስጥ... በግል - ከፍርድ የመቆጠብ ትህትና፣ ለሌሎች - ከተግባር የሚወለድ አርነት፣ ለሁሉም - በጥፋት ልክ የመዳኘት ፍትሕ ተዛንቆ ይታያል...


አዎን... ሁሉም ስራው ያውጣው!!

__

እጆቹን በማንፃት ላይ የተጠመደ ድንጋይ ይወረውር ዘንድ አይቻለውም...

___

@bridgethoughts
11👍6
ዶ/ር ጴሌ ዳሮታ ...
---
(ፍልስፍናን ከነነፃነቷ የኖራት፣ በልዩ ትወና የሰበካት አይረሴ ምሁር!)
-
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር የነበረውን የጴሌ ዳሮታን (ዶ/ር) ህልፈት የሰማ ከቀድሞ ተማሪዎቹ አንዱ የሆነው ‹‹አሳፍ ኃይሉ›› በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ስለ ጴሌ (ዶ/ር) ካሰፈረው ረዘም ያለ የታሪክ ማስታወሻ በጥቂቱ ቀንጨብ አድርጌ ወደ እኔው ጥቂት ትዝታ ለማለፍ ወደድኹ፤

የዕውቁን የፍልስፍና መምህራችንን የዶ/ር ጴሌ ዳሮታን ህልፈት ሰማሁ። ከልብ አዝኜያለሁ።

በእርግጥ ፔሌ ቀጥታ የእኔ አስተማሪ ሆኖ ባያውቅም፣ ዝናውን በመስማት ጉዱን ለማየት ከጓደኞቼ ጋር ከአንድም ሁለት ቀን በእርሱ ሌክቸር ክፍለጊዜ ገብቼ ሎጂክን እንደ መደሰቻ ሽቶ ተርከፍክፌ ነው የወጣሁት ብል ማጋነን አይደለም!

ጴሌ በጣም ቀልደኛ ሰው ነበረ። ስሙን በእንግሊዝኛ "Pelle" ብሎ ይፅፍና፣ ዕድሜ ለእንግሊዝኛ "ጴ" የሚል ፊደል ስለሌለው ስሜን ከጴሌ ወደ ፔሌ ቀየረልኝ — በማለት ያሳቀንን አልረሳውም!!
--
የፍልስፍና መምህሩን ጴሌ ዳሮታ (ዶ/ር) በጨረፍታ በእኔው ትውስታ!!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ፍልስፍናን ነፍስ ከዘሩበት ምሁራን መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው፤ በ1990ዎቹ አዲስ አበባ ተማሪ በነበርንበት ጊዜ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል መከፈቱ ስለነበር ከሌላ የትምህርት ክፍል/ዲፓርትመንት እያስፈቀድን ጴሌ የሚያስተምርበት ክፍል እንማር ነበር፡፡

አንድ ወቅት ላይ ስለ እውነታ /what is Reality? / በሚል አርእስት የግሪክ ፈላስፋዎችና ጥልቅ አሳቢዎች /Philosophers and Great Thinkers የተናገሩት/የጻፉትን ሐሳብ እያስተማረን ሳለ፤ አብዛኛውን ጊዜ እንደሚያደርገው በሌክቸሩ መካከል አንድ ጥያቄ ለእኛ ለተማሪዎች እንዲህ ሲል አነሳ፤

‹‹እውነት ለእናንተ ምንድን ነው? ማነው?››

ተማሪዎች እርስ በርስ እየተያየን ዝምታን አሰፈንን… ‹‹በሉ እንጂ አይዞአችሁ ባትመልሱት አያሰቅላችሁም እኮ!›› ሲል ለማደፋፋር ሞከረ፡፡ ከጥቂት አፍታ በኋላ ከፊት ተቀምጦ የነበረ ተማሪ ፍርሃትና ሥጋት በቀላቀለ ድምፀት፤

‹‹ለእኔ እውነት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!›› ሲል መለሰ፡፡

ጴሌ፡- መላጣውን አሸት አሸት እያደረገ ‹‹አረ ባክህ… ተው እንጂ… ይሄኔ በእርሱ ዘመን ኖረህ ቢሆን ኖሮ ሲወገርና ሲሰቀል አንዱ ድንጋይ አቀባይ አንተ ትሆን ነበር?!›› ሲለው ክፍሉ በሣቅ አውካካ…

ከዚህ በፍርድ ወንበር ፊት ከተቀመጠው ከጲላጦስ፤ ‹‹እውነት ምንድ ነው?›› ጥያቄ ጋር በተያያዘ ጴሌ አንድ በገሃዱ ዓለም የሆነ ይሁን ወይም ራሱ የፈጠረው ይሁን ለጊዜው ትዝ ባይለኝም አንድ ታሪክ እንዲህ ሲል አወጋን፤

በናዚ ዘመን አይሁዶች በያሉበት እየታደኑ በመርዝ ጋዝ ሲያልቁ በነበረበት ክፉ ጊዜ አንዲት አይሁዳዊት እናት እና ልጇ ተደብቀው ይኖሩ ነበር፡፡ ይህቺ አይሁዳዊት እናት ለብቸኛው ልጇ እንዲህ እያለች ትነግረው/ታስተምረው ነበር፤

‹‹ልጄ እውነትን ውደድ፤ ሁሌም እውነት ተናገር!››

ታዲያ አንድ ወቅት ላይ የናዚ አሳሽ ወታደሮች በጥቆማ ወደ ቤታቸው ይመጣሉ፤ ወታደሮቹ በሩን ሲያንኳኩ ልጅ በሩን ይከፍታል፤ ልጁን በጥያቄ ያፋጥጡታል፤ ‹‹እዚህ ቤት ውስጥ አንተ ብቻ ነህ የምትኖረው?››

ልጅ ይመልሳል… ‹‹አይ እናቴም አለች ግን እናቴ በታችኛው ምሥጢራዊ ክፍል ውስጥ ነው ያለችው፤›› በማለት የናዚ ወታደሮችን እናቱ ወዳለችበት ይመራቸዋል፡፡

ወታደሮቹ እናቱን እና ልጁን ይዘዋቸው ሄዱ፤ የእናቲቱና የልጁ ዕጣ ፈንታ እንደ ወገኖቻቸው ሁሉ በመርዝ ጋዝ ጭስ ተቃጥሎ፣ ታፍኖና ተልብልቦ መሞት ሆነ…

ጴሌ፡- ታሪኩን ተርኮ ከጨረሰልን በኋላ የተለመደውን ጥያቄውን አስከተለ፤

‹‹ለመሆኑ ለዚህ የግፍ ሞት ተጠያቂው ማነው… እናት፣ ልጅ ወይስ የናዚ ወታደሮች?! ከመመለሳችሁ በፊት ጥቂት አስቡ ዝም ብላችሁ እንዳመጣላችሁ እንዳትመልሱ… ጎበዝ ‹‹F›› ለማግኘትም እኮ ትንሽ ማሰብ፤ ማሰላሰል ይጠይቃል…›› ዳግመኛ ክፍሉ በሳቅ ማዕበል ተናወጠ…

ጴሌ እንዲህ ዓይነት የፍልስፍና መምህር ነበር… ነፍሱ በጥበብ ፍቅር የነደደች…!!

ጴሌ ዳሮታ (ዶ/ር) ነፍስህ በሰላም ትረፍ!!
---
ጸሐፊ - ተረፈ ወርቁ (ወዳጄ ምስጋናዬ ይድረስህ) 🙏

—-
@bridgethoughts
🙏64👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.

ሳንወሻሽ 😄

አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ምን ያህል 'ሰነፍ' ናችሁ?...

___

@bridgethoughts
🥴6👀3👍2
.
.
.

'ለፈረሰ ቤት ብርሃን ምኑ ነው?' አትበይኝ፤ ከብርሃኑ የሚያተርፍ እስካለ ድረስ...

___

@bridgethoughts
👏75👍1
The Fallen Lineman

.
.
.

ለእርሱ...

ስሙን ከማወቃችን በፊት፣ ያኔ ድሮ - ራሱን ለመስመር ለሰጠው... ከተሞች ባንቀላፉበት ቀዝቃዛ ለሊት በምድሪቱ ለተመላለሰው... በሚንቀለቀል ነበልባል ሙቀት ከምሰሶ ጋር ለታከከው... ብናኝ ካፈነው ንፋስ ጋር ታግሎ ታወር ለደመረው... ፒንሳ፣ ሽቦ፣ ቀበቶና ስታፌ ታጥቆ ብርሃን ለሚያዋልደው...


ለእርሱ...


በጊዜ ቤት መግባት ለማይሆንለት... ልጆቹን በንቃት ማግኘት ለሚናፍቀው... እንቅልፍ ሲጥላቸው ተኝተው፣ ሲበረቱ ከበር ጠብቀው - አቧራ የጠገበ ጫማውን፣ በላብ የተላቆጠ ልብሱን፣ ድካም ያዛለው ገላውን እያዩ ለሚያዝኑለት...


[ግን ደግሞ ለማያዝኑበት...] 


ብርሃን ለናፈቀ ሕዝብ የሚደርስ አባት እንዳላቸው ስለሚያውቁ ለሚኮሩበት... ለእርሱ!!

__

[ከተማው ሲፈካ ሰዎች ይደሰታሉ... ጨለማው ሲገፈፍ እልፎች ይረካሉ...]

የመጨረሻዋን ምሰሶ በዝናብ እየተደበደበ የወጣትን ሰው ግን አያውቁትም... 

የመጨረሻዋን ገመድ በሃሩር እየደበነ የሳባትን ሰው ግን አያውቁትም... 

ለዚያች ከተማ ድምቀት አካሉን የገበረውን ሰው ግን አያውቁትም... 

ለዚያች አምፑል ብርሃን ሕልውናውን ያጣውን ሰው ግን አያውቁትም...

[ቢያውቁትም አበጀህ አይሉትም... ይልቁን ለስድብ፣ ለውርደት፣ ለነቀፋ የሚቀላቸው ሰው ነው...]

__

ሕዝቤ መብራት ሲጠፋ ጠብቆ 'ዓይናችሁ ይጥፋ!' ለማለት ብርቱ ነው...

ግና...

ለጥቂት የሳቱት የታወር ብረት፣ ዝናብ አርሶት ያዳለጠ መሬት፣ የተወረወረ የሽቦ ብጥሳት፣ የተለኮሰ የመስመር እሳት - የስንቱን ሕይወት ቀጥፎ ብርሃኑ እንደተገኘ አያውቅም...


ወፍ ሳይጮህ፣ ፀሐይ ሳትወጣ ከቤቱ የወጣ - ግና በበሮቹ መሃል መመለስ ያልቻለ ባሏን አስባ ሚስት እንዴት እንደምታነባ አያውቅም... 


የአባት ኮቴ፣ የጎብኚ ድምጽ፣ የዘመድ ሰላምታ ሲርቅ - ልጆች እንዴት እንደሚሆኑ አይገምትም...


[ሕዝብ አንድ ነገር ብቻ ያውቃል... ከሆዳቸው በላይ ሕልም የሌላቸውን ከንቱዎች፣ ከድሆች አፍ መንጠቅ የማይቆረቁራቸውን ነጣቂዎች፣ ለማገልገል የተሰጣቸውን ዕድል የሚገለገሉበት ነውረኞች...]

_

ይህን የወደቀ ሰውን ጓዳ ግን አያውቁም...

__

[እርግጥ ነው -ይህ ሰው በስጋ አልፏል...] 

እያንዳንዲቷ ደማቅ አምፑል ግን ደማቅ ትግሉን ትናገራለች...


[እርግጥ ነው - አንደበቱ በሞት ክንድ ተሸብቧል...] 

እያንዳንዷ መስመር ግን የሕይወት መስዋዕትነቱን ትመሰክራለች... 


[እርግጥ ነው -ስምና ታሪኩ ተዘንግቷል...] 

በእያንዳንዱ ታወር የምትፈሰው ኢነርጂ ግን ቦይ የቀደደላትን እጅ ታስታውሳለች... 

__

እርሱ የመስመር ሰራተኛ ብቻ አልነበረም... 

የማይታይ የሃገር ዋልታ፣ የሰርክ ድምቀቷ ባለውለታ እንጂ...

እርሱ ቴክኒሺያን ብቻ አልነበረም...

የምድሪቱን ጭለማ በብርሃን ስለት የሚገልጥ መምህር፣ አጥንትና ወዙን ለሃገሩ የሰጠ ወታደርም እንጂ... 

__

ዛሬ ይህን ብርቱ ሰው አሰብኩ!!... 


[በእርሱም ውስጥ...] 


እያንዳንዱን ምሰሶ ያለፍርሃት የሚወጣ፣ እያንዳንዱን ታወር በልበ ሙሉነት የሚረግጥ፣ ከእያንዳንዱ ሽቦ ብርሃን የሚያፈስ ቋሚውን የመስመር ሰው አወደስኩ...


___


ክብር ለወደቀው የመስመር ሰው!!...


የወጣባቸው ምሰሶዎች ዛሬም እንደቆሙ ነው... 

የጠገናቸው መስመሮች የብርሃን ጅረት እያፈሰሱ ነው...

በእጁ የዳሰሳቸው አምፑሎች መደብርና መንደሩን እያደመቁ ነው... 

እርሱ በአካል ባይኖርም የስራው ፍሬ በዙሪያችን እንደከበበን ይኖራል...

_

ይህ ሰው ዝነኛ አልነበረም - አይታወስም... 

ሀብታም አልነበረም - በስሙ ሐውልት የለም...

ሆኖም...

[ሃገሩ በግብሩ ቀና እንድትል የሚያደርግ ያልተዘመረለት ጀግና ነው...]

___

ይህ ድምጽ ለእርሱ ለወደቀው ለመስመር ሰው የቀረበ አኮቴት ነው...

___

[ጓዴ ነፍስህ በሰላም ትረፍ]

___

@bridgethoughts
❤‍🔥12👏4
ሰላም ወዳጆች...

___

መጽሔታችን ቀለም በሰዓቷ ከች ብላለች... ቅጽ ፩ ቁጥር ፮ እትምን በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ... 

👇

@kelemofficial


ለምታውቋቸው ጋብዟት፤ ለጥበብ አፍቃሪያን ጠቁሟት...


ቻናሉን ተቀላቀሉ!!


ይህን ስለምታደርጉ እናመሰግናለን 🙏
5🔥1
.
.
.

Responsibility [Response + Ability]
.
.
.

ሰው ፈሪ ሲሆን መሆን የሌለበት ብዙ ነገር ሊኖር ይችላል፤ የስራ ኃላፊ አለመሆንን የሚስተካከል አስተዋይነት ግን አይኖርም...


ፈሪ ሆነህ ውሳኔ በሚፈልግ ወንበር ላይ መቀመጥ ኃላፊነት ለወሰድክበት ጉዳይ የቁም ሞት ግድ ማጣት ብቻ ሳይሆን ለከት አልባ ራስ ወዳድነትም ነው...


ስሙን ሽተህ፣ ኃላፊነቱን ግን ሸሽተህ እንዴት ይቻላል?... ክንውኑን ፈልገህ፣ መከወኑን ግን ገፍተህ እንዴት ይሆናል?...


የምልህ... 


እስከመቼ ነው ከውሳኔ ጋር ሌባና ፖሊስ የምትጫወተው?...


ወይ ውረድ! ወይ ፍረድ...


በየቀኑ ዕዳህን ለሌሎች እየገፋህ መሹለክለክ አትችልም... አንተ የሸሸኸውን ኃላፊነት ሌሎች እንዲወጡት በማድረግ ተራ ብልጣብልጥነት መዝለቅም ብልህ እያስብልም...


ምንድነው እንዲህ መንቀጥቀጥ?... ምንድነው እንዲህ መራድ?... እንዴ... ትንሽ እንኳ ደፈር በል እንጂ ጎበዝ... Risk ውሰድ... 


"The biggest risk is not taking any risk... In a world that is changing really quickly, the only strategy that is guaranteed to fail is not taking risks." ~ M. Zuckerberg

.
.
.

አንዳንድ ሲስተም ግን ይገርመኛል... ያንተ ዓይነቱን ለመሸከም ምንም አያቅማማም... ውሳኔህን የሚፈልጉ ሁሉንም ጉዳዮች ተጠያቂነት በመፍራት ስም እያሸሸህ ተድበስብሰህ ብትኖርም ምንም እርምጃ አይወስድብህም... 


*ምን ጀምረህ - ምን ፈጸምክ?...* 
*አንተ ነክተኸው ምን ከዳር ደረሰ?...* 
*ባንተ ነገር ማወሳሰብ ስንቱ ነገር ተፋረሰ?...* 
*ባንተ ጠርጣሪ ልብ ስንት ዕቅድ ፈረሰ?...*


[ማንም አይጠይቅህም... ያ - ነው ችግሩ...]


ይህ ግን ከሕሊና ወቀሳ አያስጥልህም... የጊዜ ጉዳይ ነው... ቢያንስ በሽኮኮ አያያዝህ እየሞቱ ያሉ ነገሮች በአደባባይ ያሰጡሃል... 'ስንት ነገር እጅህ ላይ ሞተ?' ይሉሃል...


ደግሞ አለመወሰንም የሚያስጠይቅ ሆኖ ይመጣል እኮ... ቀሽም ሲስተም ስለተሸከመህ ሲስተሙን የሚገፋ ዘመን አይመጣም ብለህ አታስብ...


አነሰም በዛ በዙሪያህ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች አሉ... ምንም ሲሆኑ አላየንም... በጤነኛ አዕምሮ ካሰብከው አንተ ስታደርገው የሚያስጠይቅ ሌሎች ሲከውኑት የሚያስፈነድቅ የሚባል ነገር የለም... 


[አንዳንድ ሁኔታህ ሲታይ ግን፣ የሆነ ጥግ ተቀምጦ እስክትፎርሽ የሚጠብቅህ ሰው ያለ ነው የሚመስለው...]


የአንድ ነገር የልክነትና ስህተት ዳሩ የሚመዘነው በተሰጠህ ኃላፊነት ወሰን እንጂ በማን መሆንህ ሚዛን አይደለም...


ሆን ብለህ ካጠፋህ ትጠየቃለህ፣ ካለማህም እሰየው... Period!!


ወትሮስ Position የ Responsibility እና Accountability ድምር ካልሆነ ምን ሊሆን ነው?...

___


እባክህ...


ወይ ከፍርሃት ቆፈንህ ተላቀቅ - ወይ ወንበሩን ልቀቅ!!...

___


“The coward asks the question, Is it safe? The leader asks the question, Is it right?” ~ James Freeman Clarke

___

@bridgethoughts
7👏6👍2🔥1
.
.
.

ለመያዝ የዘረጋ ካልቆመ፣ ለመጨበጥ የሰነዘረም ካልፈጠነ - በያዥና ተያዥ መሐል ፍላጎት ተፈትኗል...
.
.
.

ያልነበረ አይኖርም!!...

____

@bridgethoughts
7👌4👍1
እየራራን
(በእውቀቱ ስዩም)

ዛሬ በስሱ እንድሰብካችሁ ፍቀዱልኝ!

ከአውሮፓ ከተሞች በአንዱ እግር ከጣለህ የሆነ ነገር ታያለህ፤ መንገድ ላይ ስትሄድ የደላቸው የጠገቡ ርግቦች ያጋጥሙሀል’፤ አጠገባቸው መድረስህን አውቀው መንገድ አይለቁልህም፤ ከመጤፍ ሳይቆጥሩህ፥ ለቀማቸውን ወይም ጨዋታቸውን ይቀጥላሉ፤ እንዳትረግጣቸው ርምጃህን ቆጥበህ ለመራመድ ትገደዳለህ፤

‘ቅዲስቲቱ ምድር’ ላይ ነህ፤ አንዲት ወፍ ከከረጢት ያመለጠ እህል እየለቀመች ነው፤ ድንገት ባቅራቢያው ዳናህን ከሰማች ብድግ ብላ ወደ እንጦጦ ብሄራዊ ፓርክ ታፈገፍጋለች፤ በወፎች ዓይን ስንታይ ጭራቆች ነን፤ ግን ያለ ምክንያት ነው?...

አንድ ባለቤት አልባ ውሻ ባጠገቡ ካለፍህ ሽምቅቅ ብሎ ገለል ይላል፤ ይመግቡኛል ብሎ ሳይሆን ይደበድቡኛል ብሎ እንደሚያስብ ግልጥ ነው ፤ በከተማችን የዕለት ዱላውን ሳይቀበል የሚውል ውሻ የለም፤ ድሮ ሰዎች የጎዳና ውሻ የሚደበድቡት “ሊጣችንን ደፋብን፣ ከቅርጫው መደብ ላይ አንድ ጎድን መነተፈብን” በሚል ሰበብ ነበር፤ አሁን አሁን ያለ ሰበብ ውሻና ድመት የሚነርት ነዋሪ ጥቂት አይደለም፤ ለመዝናናት ወይም የቆረፈደ ክንዱን ለማፍታት ውሻ የሚደበድብ አለ፤ ረሀቡን በአንቅልፍ ለማሳለፍ የተኛውን ውሻ ከመንገድ አፈንግጦ በወጣ ኮብል ድንጋይ የሚወግር አይጠፋም፤

በቀደም አንዱ ከሱቅ በር ላይ ተጎልቶ የሚቅም ጎረምሳ ባንድ ምስኪን ውሻ ላይ ድንጋይ ወረወረበት፤ ውሻው ከድንጋዩ ለማምለጥ ደመነፍሱን አስፋልት ለማቋረጥ ሲሞክር ከላይ የመጣ ታክሲ በጎማው እግሩን ዳጠው! ውሻው እያነከሰ ያለቀሰው ለቅሶ!...

ካዲስአባ እምብርት እየራቅን ስንሄድ እቃ የሚያጉዋጉዙ ጋሪዎችን እናገኛለን፤ አንድ የጠወለገ ፈረስ ትልልቅ ጎማ ያለው ጋሪ ለመጎተት የሞት የሽረቱን ሲፍጨረጨር ታያለሽ፤ በጋሪው መዓት የስሚንቶ ከረጢት ተከምሯል፤ ከስሚንቶው በተረፈው ቦታ ቡልኬት ተገጥግጦበታል፤ በዚያ ላይ ጋሪ ነጂው እንደ ፈርኦን ተኮፍሶ ፈረሱን በጅራፍ ይጠብሰዋል፤

በእንስሳት መገልገል አንድ ነገር ነው፤ በአንስሳት አለምክንያት መጨከን ሌላ ነገር ነው፤ የከተማው አስተዳደር የጋማ ፈረሶችን ያላግባብ የሚጨኑ፥ በግልጋሎታቸው ሳይሆን በስቃያቸው የሚደሰቱ ሰዎችን መቅጣት አለበት፤

ለመኖር እንስሳትን መግደል አለብን፤ ይህ የህይወት አንድ አሳዛኝ ግን አይቀሬ ገጽታ ነው፤ ከዚያ ባሻገር ለእንስሳት ርህራሄ የማሳየት ዝንባሌም አናጣም፤ የኢትዮጵያ ባህል ባንድ ገጹ ለእንስሳት መራራትን ያስተምራል፤ ድንግል ማርያም የተጠማ ውሻ እንዳጠጣች ሲነገረን አድገናል፤ ያገራችን የባላባት ወግ ስለ ዝሆን ገዳዮች ጀብድ ባድናቆት የሚተርከውን ያህል ስለ “ቆቅ ማሪ አቦየ”ም ይተርካል፤

እኒህ አቦየ የዳግማይ ምኒልክ አያት የንጉስ ሳህለስላሴ አማች ነበሩ፤ ባንድ ወቅት አንድ ባላገር ቆቅ አጥምዶ እጅመንሻ አመጣላቸው፤ ለባላገሩ የሚገባውን ከሰጡት በሁዋላ ወደ መኝታ ቤታቸው መስኮት ተራመዱ፤ ማጀት ውስጥ ገረዶቻቸው ቢላዋ እየሳሉ ነው፤ አቦየ ቆቂቱን መስኮት ላይ አስቀመጡና “ደህና ሰንብቺ” አሉዋት፤ ወደ መጣችበት በረረች፤

ያገሩ ሰው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አቦየን “ ቆቅ ማሪ አቦየ” ብሎ ባድናቆት ይጠራቸው ጀመር!

አለምክንያት በእንስሳት ላይ የመጨከንን ልማድ አስወግደን የመንፈስ ስልጣኔ ያለን ህዝቦች መሆናችንን እናሳይ!

--
@bridgethoughts
13👍2🥰1