“My brain is only a receiver; in the Universe there is a core from which we obtain knowledge, strength, and inspiration. I have not penetrated into the secrets of this core, but I know that it exists.” ~ Nikola Tesla
___
@bridgethoughts
___
@bridgethoughts
❤8👌2👍1
ትዝ አለኝ የጥንቱ...
[ያው እንደነገርኳችሁ የተወለድኩት በቅዳሴና አዛን መሐል ነው... የከተማው ትልቅ ደብርና ታሪካዊው ፈትኸል መስጅድ ጎረቤቶቼ ናቸው... በደብሩ ወገን ያለው ግድም - ገዳም ሰፈር፣ ከመስጅዱ ዙሪያ ያለው መንደር ደግሞ ነፃ ሰፈር ይባሉ ነበር... እርግጥ ዛሬ የሁለቱም ሰፈር ስሞች ለጥሪ ሲውሉ አይሰማም... በኔ ዘመንተኞች ዘንድ ካልሆነ በቀር... ]
ላወራችሁ የፈለግሁት ስለዚህ አይደለም... ከልጅነቴ ትዝታዎች በአንዱ ፈገግ ላስብላችሁ እንጂ...
___
ከዓመታት በፊት የሆነ ነው...
ቀኑ አርብ... የከተማዋ የገበያ ቀን ነው...
እንደተለመደው የደብሩ የማምሻ ጉባኤ እስኪጀመር ድረስ በግዙፍ ስፒከር መዝሙር ተከፍቶ ጥሪው ከየጓዳችን እየደረሰ ነው...
ይህን የማድረግ ተራ የደረሰው አንድ ጓደኛዬ የመዝሙሩን ካሴት ቴፑ ላይ ጥዶ የመቅደሱን በር ቆልፎ ወደ ከተማ ወጥቷል... [ቴፑ ለወቅቱ ዘመናዊ ቴፕ ነው - በራሱ ስለሚገለብጥ በእርሱ ቤት 'እደርሳለሁ' ብሎ ነው የራቀው...]
[ለዛሬ ልጆች ለማስረዳት - ካሴት ሁለት Side ያለው፣ በአንዱ ጎን 30 ደቂቃ፣ ሲገለበጥም ያንኑ ያህል ዜማ ተሸክሞ የሚዞር፣ ብዙ ጊዜ እስከ አስር የሚደርሱ ስራዎች የሚሸከፉበት የክር ጥቅል ነው... 😂😂😂]
ጓደኛዬ ከደብሩ ብዙ ርቋል...
የካሴትን ችግር ታውቃላችሁ መቼም...
ወይ የቴፑ "አልማዝ" ያልቅና ድምጹ ይነፋነፋል...
[አድገን እንደገባን 'አልማዝ' የሚባል ነገር የለም... Read head ነው የሚባለው... መቅጃው Record head፣ መደምሰሻው Erase head እንደሚባለው ማለት ነው...]
ወይ ደግሞ ቴፑ ክሩን ይጎለጉለውና የዜማውን ስልት ወደ ብዙ ድመቶች ጠብና አምባጓሮ ያሳድገዋል...
እርግጥ ያንለት ሁለቱም አልሆነም...
መዝሙሮቹ በየተራ ሲፈሱ ቆዩና ድንገት ምዕመናን ከየቤታቸው ብቻ የሚሰሟት የአንዲት ገናና ከያኒ ድምጽ በስፒከሩ ውስጥ ተንቆረቆረ... አስቱካ ነበረች...
"... ጠይም ዘለግ ያለ - የኮራው ደረቱ..."
ሰው ሁሉ በጥፊ የተመታ ያህል ጆሮው ጭው አለ... በተለይ የገዳም ሰፈር ልጆች ድንጋጤ ቅጥ አልነበረውም... ቤተክርስቲያኗ በጠላት ቁጥጥር ስር የዋለች ያህል ተሰማን... ጎዳናውን በአንድ ጊዜ ሞላነው... [በዚያው ቀን 'መዝሙሩ የማን ነበር?' ብንባል ማስታወስ የሚከብደን ሰዎች በአስቱካ ስርቅርቅ ድምጽ ጆሮአችን የነቃበት ሚስጢር ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ ይሆንብኛል...]
አስቱካ ቀጥላለች...
'እንዴ፣ አይዘጉትም እንዴ?' ሰው ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያን አሻግሮ እያየ ይንቆራጠጣል... አንዳንዱም መላምት ይሰጣል... ያን ሰሞን 'ተሐድሶዎች ከቤ/ን ተባረሩ' የሚለው ዜና አልበረደ ኖሮ 'እነርሱ ናቸው፣ ሊያዋርዱን፣ በጠላት ሊያስቁብን...' ብቻ ብዙ ብዙ ተባለ... [በወቅቱ ሞባይል የለ ምናምን... ለማን ተደውሎ ይነገራል?] ብቻ ድንጋጤዎች አንዳንድ ጫጫታዎችን ዝም ስላሰኙ ሙዚቃው በብዙ ሰዎች የመሰማት ዕድል አገኘ...
አስቱካ ናኘች...
በዚህ መሐል ጓደኛዬ ከሄደበት ተመለሰ... እያለከለከ፣ ላቡን እያዘራ፣ ምላሱ ጉሮሮው ላይ እንዳትወተፍበት እየተጨነቀ ወደ ቤተ/ን ገሰገሰ...
አስቱካ ወደሌላኛው ሙዚቃ ተሻግራለች... [አጠቃላይ ክስተቱ 7 ደቂቃ ቢሆነው ነው... ሆኖም የ 7 ቀን ያህል ረጅም ነበር...]
ጓደኛዬ ደርሶ ዘጋው... እፎይ... [አስቱ በቁጥጥር ስር ዋለች]
[ወዳጄ እንደነገረኝ ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበሩ ሰዎች ቴፑን ለመዝጋት ያላደረጉት አልነበረም... ግን በየት በኩል ይግቡ... 'ባልቦላ' እንዳያጠፉ ለቆጣሪው ጥንቃቄ ሲባል የተሰራው የጣውላ ቀፎ ተቆልፎ በየት ያግኙት?...]
___
ያን ዕለት ጓደኛዬ ብዙ ወቀሳና ትችት ወረደበት... [ቀድሞ ሌላ ሐይማኖት ይከተል ስለነበር 'ድሮስ' ምናምን ያሉትም አልጠፉም...]
የካሴቱ ቅድመ-ታሪክ ሲመረመር - የአስቴር አወቀ ሙዚቃዎች ስብስብ ሸክፎ ኖሯል ለካ... ሆኖም ተደምስሶ መዝሙር ሲቀዳበት ነባሩ ሙዚቃ የነበረው ርዝመት የክሩን ሰፊ ክፍል ይሸፍን ኖሮ ሳይደመሰስ የተረፈው ሙዚቃ ነው አየሩ ላይ የናኘው... [ካሴቱ ከ 20 ደቂቃ በላይ በመዝሙር ቢሸፈንም ቀሪ ቦታውን የያዘው ሙዚቃ አልጠፋም ነበር እንደማለት - መዝሙር ሲቀዳበት ከ Erase head የተረፈ...]
ያንለት ከወትሮው ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ቤተክርስቲያኒቱን አጥለቀለቃት... የብዙዎች የመገኘት ምክንያት ታዲያ የጉዳዩን ሰበብ መስማት ነበር... [ያን ሰሞን የከተማዋ የቡና ተርቲበኞች አቦል ቶናና በረካ የሚወራረደው በወዳጄ "ሥጋ" ነበር...]
____
አንዳንዴ... [የሰው ልጅ]
ተኩላ ማንነቱን ለመሸፈን በለበሰው የበግ ለምድ የከረመ ዓመሉን መደበቅ ሲያቅተው፣ አልያም ቂመኛ ልቡን ለመከለል ከፊቱ የሞላው አስመሳይ ፈገግታ ጨካኝ ማንነቱን መከለስ ሲሳነው ሳይ ይህን ገጠመኝ አስታውሳለሁ...
___
@bridgethoughts
[ያው እንደነገርኳችሁ የተወለድኩት በቅዳሴና አዛን መሐል ነው... የከተማው ትልቅ ደብርና ታሪካዊው ፈትኸል መስጅድ ጎረቤቶቼ ናቸው... በደብሩ ወገን ያለው ግድም - ገዳም ሰፈር፣ ከመስጅዱ ዙሪያ ያለው መንደር ደግሞ ነፃ ሰፈር ይባሉ ነበር... እርግጥ ዛሬ የሁለቱም ሰፈር ስሞች ለጥሪ ሲውሉ አይሰማም... በኔ ዘመንተኞች ዘንድ ካልሆነ በቀር... ]
ላወራችሁ የፈለግሁት ስለዚህ አይደለም... ከልጅነቴ ትዝታዎች በአንዱ ፈገግ ላስብላችሁ እንጂ...
___
ከዓመታት በፊት የሆነ ነው...
ቀኑ አርብ... የከተማዋ የገበያ ቀን ነው...
እንደተለመደው የደብሩ የማምሻ ጉባኤ እስኪጀመር ድረስ በግዙፍ ስፒከር መዝሙር ተከፍቶ ጥሪው ከየጓዳችን እየደረሰ ነው...
ይህን የማድረግ ተራ የደረሰው አንድ ጓደኛዬ የመዝሙሩን ካሴት ቴፑ ላይ ጥዶ የመቅደሱን በር ቆልፎ ወደ ከተማ ወጥቷል... [ቴፑ ለወቅቱ ዘመናዊ ቴፕ ነው - በራሱ ስለሚገለብጥ በእርሱ ቤት 'እደርሳለሁ' ብሎ ነው የራቀው...]
[ለዛሬ ልጆች ለማስረዳት - ካሴት ሁለት Side ያለው፣ በአንዱ ጎን 30 ደቂቃ፣ ሲገለበጥም ያንኑ ያህል ዜማ ተሸክሞ የሚዞር፣ ብዙ ጊዜ እስከ አስር የሚደርሱ ስራዎች የሚሸከፉበት የክር ጥቅል ነው... 😂😂😂]
ጓደኛዬ ከደብሩ ብዙ ርቋል...
የካሴትን ችግር ታውቃላችሁ መቼም...
ወይ የቴፑ "አልማዝ" ያልቅና ድምጹ ይነፋነፋል...
[አድገን እንደገባን 'አልማዝ' የሚባል ነገር የለም... Read head ነው የሚባለው... መቅጃው Record head፣ መደምሰሻው Erase head እንደሚባለው ማለት ነው...]
ወይ ደግሞ ቴፑ ክሩን ይጎለጉለውና የዜማውን ስልት ወደ ብዙ ድመቶች ጠብና አምባጓሮ ያሳድገዋል...
እርግጥ ያንለት ሁለቱም አልሆነም...
መዝሙሮቹ በየተራ ሲፈሱ ቆዩና ድንገት ምዕመናን ከየቤታቸው ብቻ የሚሰሟት የአንዲት ገናና ከያኒ ድምጽ በስፒከሩ ውስጥ ተንቆረቆረ... አስቱካ ነበረች...
"... ጠይም ዘለግ ያለ - የኮራው ደረቱ..."
ሰው ሁሉ በጥፊ የተመታ ያህል ጆሮው ጭው አለ... በተለይ የገዳም ሰፈር ልጆች ድንጋጤ ቅጥ አልነበረውም... ቤተክርስቲያኗ በጠላት ቁጥጥር ስር የዋለች ያህል ተሰማን... ጎዳናውን በአንድ ጊዜ ሞላነው... [በዚያው ቀን 'መዝሙሩ የማን ነበር?' ብንባል ማስታወስ የሚከብደን ሰዎች በአስቱካ ስርቅርቅ ድምጽ ጆሮአችን የነቃበት ሚስጢር ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ ይሆንብኛል...]
አስቱካ ቀጥላለች...
'እንዴ፣ አይዘጉትም እንዴ?' ሰው ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያን አሻግሮ እያየ ይንቆራጠጣል... አንዳንዱም መላምት ይሰጣል... ያን ሰሞን 'ተሐድሶዎች ከቤ/ን ተባረሩ' የሚለው ዜና አልበረደ ኖሮ 'እነርሱ ናቸው፣ ሊያዋርዱን፣ በጠላት ሊያስቁብን...' ብቻ ብዙ ብዙ ተባለ... [በወቅቱ ሞባይል የለ ምናምን... ለማን ተደውሎ ይነገራል?] ብቻ ድንጋጤዎች አንዳንድ ጫጫታዎችን ዝም ስላሰኙ ሙዚቃው በብዙ ሰዎች የመሰማት ዕድል አገኘ...
አስቱካ ናኘች...
በዚህ መሐል ጓደኛዬ ከሄደበት ተመለሰ... እያለከለከ፣ ላቡን እያዘራ፣ ምላሱ ጉሮሮው ላይ እንዳትወተፍበት እየተጨነቀ ወደ ቤተ/ን ገሰገሰ...
አስቱካ ወደሌላኛው ሙዚቃ ተሻግራለች... [አጠቃላይ ክስተቱ 7 ደቂቃ ቢሆነው ነው... ሆኖም የ 7 ቀን ያህል ረጅም ነበር...]
ጓደኛዬ ደርሶ ዘጋው... እፎይ... [አስቱ በቁጥጥር ስር ዋለች]
[ወዳጄ እንደነገረኝ ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበሩ ሰዎች ቴፑን ለመዝጋት ያላደረጉት አልነበረም... ግን በየት በኩል ይግቡ... 'ባልቦላ' እንዳያጠፉ ለቆጣሪው ጥንቃቄ ሲባል የተሰራው የጣውላ ቀፎ ተቆልፎ በየት ያግኙት?...]
___
ያን ዕለት ጓደኛዬ ብዙ ወቀሳና ትችት ወረደበት... [ቀድሞ ሌላ ሐይማኖት ይከተል ስለነበር 'ድሮስ' ምናምን ያሉትም አልጠፉም...]
የካሴቱ ቅድመ-ታሪክ ሲመረመር - የአስቴር አወቀ ሙዚቃዎች ስብስብ ሸክፎ ኖሯል ለካ... ሆኖም ተደምስሶ መዝሙር ሲቀዳበት ነባሩ ሙዚቃ የነበረው ርዝመት የክሩን ሰፊ ክፍል ይሸፍን ኖሮ ሳይደመሰስ የተረፈው ሙዚቃ ነው አየሩ ላይ የናኘው... [ካሴቱ ከ 20 ደቂቃ በላይ በመዝሙር ቢሸፈንም ቀሪ ቦታውን የያዘው ሙዚቃ አልጠፋም ነበር እንደማለት - መዝሙር ሲቀዳበት ከ Erase head የተረፈ...]
ያንለት ከወትሮው ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ቤተክርስቲያኒቱን አጥለቀለቃት... የብዙዎች የመገኘት ምክንያት ታዲያ የጉዳዩን ሰበብ መስማት ነበር... [ያን ሰሞን የከተማዋ የቡና ተርቲበኞች አቦል ቶናና በረካ የሚወራረደው በወዳጄ "ሥጋ" ነበር...]
____
አንዳንዴ... [የሰው ልጅ]
ተኩላ ማንነቱን ለመሸፈን በለበሰው የበግ ለምድ የከረመ ዓመሉን መደበቅ ሲያቅተው፣ አልያም ቂመኛ ልቡን ለመከለል ከፊቱ የሞላው አስመሳይ ፈገግታ ጨካኝ ማንነቱን መከለስ ሲሳነው ሳይ ይህን ገጠመኝ አስታውሳለሁ...
___
@bridgethoughts
❤8🥰3🙏2
.
.
.
የዓለማችን 'ግዙፍ ሚዲያዎች' - የቀን ውሎ 90% ያህሉ - በጦርነት፣ በሽብር፣ በግጭትና በጉስቁልና ዜናዎች ብቻ ይሸፈናል ቢባል ድምዳሜው ግነት ተጭኖታል አያስብልም...
በጎ ነገር ባለበት በጭራሽ ዝር አይሉም - ቢሉም እንኳ ደጉን ለመዘገብ ሊሆን አይችልም... ይልቁን በሰርግህ ዕለት ተገኝተው ያንተ ደስታ ለሌሎች የሃዘን ምክንያት ሊሆን የሚችልበትን መንገድ በዘገባቸው በማንሳት ሊያስገርሙህ ይችላሉ...
ይህ በተዘዋዋሪ የሚፈጥረው ጫናና ውጥረት ቀላል አይደለም...
ዓለሚቱ አንዳችም በጎ ነገር የሌላት መስላ ስትቀርብ ዕለታዊ መስተጋብራችን ድንዛዜ ይዋረሰዋል... ተስፋ መቁረጥና ሕይወትን አጨልሞ የማየት አባዜ ይጫነዋል...
ምዕራባውያን ሚዲያዎች ከበጎ ነገር ይልቅ 'ክፉው' ላይ ብቻ የሚረባረቡበት ምክንያት ምንም ይሁን የሚቃኙበት Editorial policy ግን አስገራሚም አሳዛኝም ነው...
ይህን እውነት ይዘን በልካቸው ስናወራ እንዲህ እንላቸዋለን...
CNN - Continuous Negative News
BBC - Brutal Biased Channel
AFP - All Fear Press
NYT - Not Your Truth
____
@bridgethoughts
.
.
የዓለማችን 'ግዙፍ ሚዲያዎች' - የቀን ውሎ 90% ያህሉ - በጦርነት፣ በሽብር፣ በግጭትና በጉስቁልና ዜናዎች ብቻ ይሸፈናል ቢባል ድምዳሜው ግነት ተጭኖታል አያስብልም...
በጎ ነገር ባለበት በጭራሽ ዝር አይሉም - ቢሉም እንኳ ደጉን ለመዘገብ ሊሆን አይችልም... ይልቁን በሰርግህ ዕለት ተገኝተው ያንተ ደስታ ለሌሎች የሃዘን ምክንያት ሊሆን የሚችልበትን መንገድ በዘገባቸው በማንሳት ሊያስገርሙህ ይችላሉ...
ይህ በተዘዋዋሪ የሚፈጥረው ጫናና ውጥረት ቀላል አይደለም...
ዓለሚቱ አንዳችም በጎ ነገር የሌላት መስላ ስትቀርብ ዕለታዊ መስተጋብራችን ድንዛዜ ይዋረሰዋል... ተስፋ መቁረጥና ሕይወትን አጨልሞ የማየት አባዜ ይጫነዋል...
ምዕራባውያን ሚዲያዎች ከበጎ ነገር ይልቅ 'ክፉው' ላይ ብቻ የሚረባረቡበት ምክንያት ምንም ይሁን የሚቃኙበት Editorial policy ግን አስገራሚም አሳዛኝም ነው...
ይህን እውነት ይዘን በልካቸው ስናወራ እንዲህ እንላቸዋለን...
CNN - Continuous Negative News
BBC - Brutal Biased Channel
AFP - All Fear Press
NYT - Not Your Truth
____
@bridgethoughts
❤11👌2
🔔 Before the Drums Beat Again 🔔
Once upon a time, there was no Ethiopia and Eritrea.
There were only brothers — children of the same highlands,
breathing the same wind that rises from the Red Sea
and settles on the mountains.
The rivers did not know borders.
The mothers spoke the same lullabies.
The sky covered us all — without a passport.
But then came the shadow of lines drawn on the earth —
names that separated hearts, flags that replaced embraces.
And in the name of these lines,
thousands of young men and women offered their blood to the soil.
Still, the soil cried — not for victory,
but for the innocence lost.
Years later, the world rejoiced when the two brothers met again —
smiles, handshakes, hope.
The world said, “At last, the Horn of Africa breathes again.”
You both promised peace,
and the earth, weary from the echo of guns, finally rested.
Our Prime Minister received the world’s peace prize —
but more importantly,
our people received the peace itself.
Seven years passed.
Yet now, we hear the sound of old drums beating again.
Excellencies,
Before those drums awaken the ghosts of yesterday, please —
sit and talk.
Sit not as leaders of separate lands,
but as brothers who share one ancient wound.
History has already buried too many sons.
Must we dig new graves for the same reason?
A sea is not worth a single mother’s tear.
A port is not worth the trembling of a child
who hears warplanes in the sky.
The world does not need another headline of sorrow from the Horn;
it needs the light of wisdom from its cradle.
Yes — Ethiopia needs a gate to the sea.
And yes — Eritrea needs her sovereignty respected.
But more than that, both need each other.
The sea and the highlands are not enemies;
they complete each other —
like breath and heartbeat.
If you two meet,
not to debate, but to listen —
the Red Sea will calm its waves.
Trade will flow, families will unite,
and the wounds of decades will begin to heal.
But if the guns speak again,
no one will win —
except those who sell the bullets.
Please, for the sake of history yet to be written,
for the mothers who have already buried too much,
for the youth who dream of life, not war —
Sit and talk.
Let wisdom be your weapon.
Let love be your strategy.
Let peace be your legacy.
The Horn does not need heroes of war anymore.
It needs fathers of peace.
🕊️ May reason rise above rage,
and may love remember what history forgets.
____
@bridgethoughts
Once upon a time, there was no Ethiopia and Eritrea.
There were only brothers — children of the same highlands,
breathing the same wind that rises from the Red Sea
and settles on the mountains.
The rivers did not know borders.
The mothers spoke the same lullabies.
The sky covered us all — without a passport.
But then came the shadow of lines drawn on the earth —
names that separated hearts, flags that replaced embraces.
And in the name of these lines,
thousands of young men and women offered their blood to the soil.
Still, the soil cried — not for victory,
but for the innocence lost.
Years later, the world rejoiced when the two brothers met again —
smiles, handshakes, hope.
The world said, “At last, the Horn of Africa breathes again.”
You both promised peace,
and the earth, weary from the echo of guns, finally rested.
Our Prime Minister received the world’s peace prize —
but more importantly,
our people received the peace itself.
Seven years passed.
Yet now, we hear the sound of old drums beating again.
Excellencies,
Before those drums awaken the ghosts of yesterday, please —
sit and talk.
Sit not as leaders of separate lands,
but as brothers who share one ancient wound.
History has already buried too many sons.
Must we dig new graves for the same reason?
A sea is not worth a single mother’s tear.
A port is not worth the trembling of a child
who hears warplanes in the sky.
The world does not need another headline of sorrow from the Horn;
it needs the light of wisdom from its cradle.
Yes — Ethiopia needs a gate to the sea.
And yes — Eritrea needs her sovereignty respected.
But more than that, both need each other.
The sea and the highlands are not enemies;
they complete each other —
like breath and heartbeat.
If you two meet,
not to debate, but to listen —
the Red Sea will calm its waves.
Trade will flow, families will unite,
and the wounds of decades will begin to heal.
But if the guns speak again,
no one will win —
except those who sell the bullets.
Please, for the sake of history yet to be written,
for the mothers who have already buried too much,
for the youth who dream of life, not war —
Sit and talk.
Let wisdom be your weapon.
Let love be your strategy.
Let peace be your legacy.
The Horn does not need heroes of war anymore.
It needs fathers of peace.
🕊️ May reason rise above rage,
and may love remember what history forgets.
____
@bridgethoughts
🕊10❤3🙏2
.
.
.
ሁሉንም አታወራም አይደል?... ሁሉን ከሁሉ ጋር አትካፈልም...
አንዳንዴ...
በግል ጉባኤህ፣ በልብ ሽሽግህ፣ በነፍስያህ ለዛ፣ ካዘመመ ጎጆህ ታዛ - ብቻህን ቆዝመህ የምታንሾካሹከው ጉዳይ ይኖርሃል...
ደግሞስ ሰው ሁሉ በየቤቱ በራሱ ድካም እየደቀቀ፣ በግሉ ሃሳብ እያለቀ፣ በዕጣፈንታው ህመም ታስሮ፣ በራስ ፈተና ተቸንክሮ - ጉስቁልቁል እያለ ምን ብለህ የኔን ብቻ ስማ ትለዋለህ?...
ከመከራህ መከራዬ ይልቃል ነው?...
ከስቀትህ ሰቀቀኔ ይብሳል ነው?...
[በደንብ ካሰብከው - የሌሎችን ሕማም ለመታመም አይደለም - የራሱን ቁስል ከፍቶ ለማየትም ልቢቱ የሳሳችበት በየቤቱ ብዙ ነው...]
.
.
.
ይልቅ ምን አለ መሰለህ?...
ሰሚህ በችግርህ ውስጥ ጉድለቱን እያየ ከሰማህ - አደመጠህ አይባልም - ተነፈስክበት እንጂ...
ሰሚህ ስለሰማህ ድብርት ከተጫነው - አደመጠህ አይባልም - ጫንክበት እንጂ...
'ይህችማ ምን አላት? እኔ የደረሰብኝን ብታውቅ...' ብሎ ከመለሰልህ - አደመጠህ አይባልም - ቁስልህን ካደብህ እንጂ...
እና እንዳልኩህ ነው...
አንዳንድ ጊዜ... ለብቻህ የምትሸከመው መስቀል ይኖርሃል!!...
____
@bridgethoughts
.
.
ሁሉንም አታወራም አይደል?... ሁሉን ከሁሉ ጋር አትካፈልም...
አንዳንዴ...
በግል ጉባኤህ፣ በልብ ሽሽግህ፣ በነፍስያህ ለዛ፣ ካዘመመ ጎጆህ ታዛ - ብቻህን ቆዝመህ የምታንሾካሹከው ጉዳይ ይኖርሃል...
ደግሞስ ሰው ሁሉ በየቤቱ በራሱ ድካም እየደቀቀ፣ በግሉ ሃሳብ እያለቀ፣ በዕጣፈንታው ህመም ታስሮ፣ በራስ ፈተና ተቸንክሮ - ጉስቁልቁል እያለ ምን ብለህ የኔን ብቻ ስማ ትለዋለህ?...
ከመከራህ መከራዬ ይልቃል ነው?...
ከስቀትህ ሰቀቀኔ ይብሳል ነው?...
[በደንብ ካሰብከው - የሌሎችን ሕማም ለመታመም አይደለም - የራሱን ቁስል ከፍቶ ለማየትም ልቢቱ የሳሳችበት በየቤቱ ብዙ ነው...]
.
.
.
ይልቅ ምን አለ መሰለህ?...
ሰሚህ በችግርህ ውስጥ ጉድለቱን እያየ ከሰማህ - አደመጠህ አይባልም - ተነፈስክበት እንጂ...
ሰሚህ ስለሰማህ ድብርት ከተጫነው - አደመጠህ አይባልም - ጫንክበት እንጂ...
'ይህችማ ምን አላት? እኔ የደረሰብኝን ብታውቅ...' ብሎ ከመለሰልህ - አደመጠህ አይባልም - ቁስልህን ካደብህ እንጂ...
እና እንዳልኩህ ነው...
አንዳንድ ጊዜ... ለብቻህ የምትሸከመው መስቀል ይኖርሃል!!...
____
@bridgethoughts
❤15❤🔥2🫡2
ሰላም ወዳጆች፤
ድልድይ - ቀለም ላይ አምደኛ ሆና ተከስታለች፤ ይህንን የጥበብ ብፌ ስጋብዛችሁ ደስ እያለኝ ነው...
___
ግቡ፣ Join አድርጉ፣ አዲሱን ቅጽ አንብቡ!!
___
ቀለም መጽሔት🗞️
ቅፅ 1 እትም 5
እያነበባቹህ ለወዳጅዎ ያጋሩ
ለሀሳብ አስተያየት
@KelemMagazine
Telegram 👇❤️
@kelemofficial
ድልድይ - ቀለም ላይ አምደኛ ሆና ተከስታለች፤ ይህንን የጥበብ ብፌ ስጋብዛችሁ ደስ እያለኝ ነው...
___
ግቡ፣ Join አድርጉ፣ አዲሱን ቅጽ አንብቡ!!
___
ቀለም መጽሔት🗞️
ቅፅ 1 እትም 5
እያነበባቹህ ለወዳጅዎ ያጋሩ
ለሀሳብ አስተያየት
@KelemMagazine
Telegram 👇❤️
@kelemofficial
❤3🥰1👏1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.
"ምንአገባኝ?" ብሎ መተው እኮ ይቻላል...
"ማንን ነው የሚያገባው ታዲያ?" ቢሉን መልስ የለንም እንጂ...
__
የገጠመን ፈተና ይህ ነው... ብዙ ሰዎች ብዙ ነገር አያገባቸውም...
ለዚህ ነው - ሃገር የጥቂት ትጉሃን መዋጮ ውጤት ነች ለማለት የምደፍረው... ብዙሃኑ ነገር ዓለሙን እኒሁ ጥቂቶች ላይ ጥሎ 'ጥቅሙን' ብቻ የሚያሳድድ ነው...
__
በተገኘህበት ቦታ - 'መገኘትህን' የሚናገር አንዳች ቁምነገር ካልተውክ መኖርህ ከቁጥርነት አልዘለለም ነበር ማለት ነው...
__
@bridgethoughts
.
.
"ምንአገባኝ?" ብሎ መተው እኮ ይቻላል...
"ማንን ነው የሚያገባው ታዲያ?" ቢሉን መልስ የለንም እንጂ...
__
የገጠመን ፈተና ይህ ነው... ብዙ ሰዎች ብዙ ነገር አያገባቸውም...
ለዚህ ነው - ሃገር የጥቂት ትጉሃን መዋጮ ውጤት ነች ለማለት የምደፍረው... ብዙሃኑ ነገር ዓለሙን እኒሁ ጥቂቶች ላይ ጥሎ 'ጥቅሙን' ብቻ የሚያሳድድ ነው...
__
በተገኘህበት ቦታ - 'መገኘትህን' የሚናገር አንዳች ቁምነገር ካልተውክ መኖርህ ከቁጥርነት አልዘለለም ነበር ማለት ነው...
__
@bridgethoughts
❤13
.
.
.
የኔነሽ፣
የኔነሽ፣
የኔነሽ ይሏታል
እርሷም ደስ ይላታል
የሁሉ መሆን ግን ምን ያደርግላታል?
.
.
.
የሁሉ የሆነ - እንዳይሆን ለማንም
ሁሉ ዘንድ የሞቀ - እንዳይገኝ የትም፤
ጸሐይ ነግራናለች - በዘለለት ልሳን
ሰርክ አዲስ እንግዳ - እኛ እንጂ ያልነቃን፤
በጠዋት ፈገግታ
በእኩለ ቀን ዋዕይ
ከባን ብትውልም፣
ጽልመት ሲገማሸር አታስተማምንም።
___
@bridgethoughts
.
.
የኔነሽ፣
የኔነሽ፣
የኔነሽ ይሏታል
እርሷም ደስ ይላታል
የሁሉ መሆን ግን ምን ያደርግላታል?
.
.
.
የሁሉ የሆነ - እንዳይሆን ለማንም
ሁሉ ዘንድ የሞቀ - እንዳይገኝ የትም፤
ጸሐይ ነግራናለች - በዘለለት ልሳን
ሰርክ አዲስ እንግዳ - እኛ እንጂ ያልነቃን፤
በጠዋት ፈገግታ
በእኩለ ቀን ዋዕይ
ከባን ብትውልም፣
ጽልመት ሲገማሸር አታስተማምንም።
___
@bridgethoughts
❤5👏3
.
.
.
"Let him who is without sin among you be the first to throw a stone at her." ~ Jesus
__
ፍርድ እውቀት አይጠይቅም... ማንም ሰው ላይ መፍረድ ቀላል ነው... የሞራል ጥያቄ ግን አለው... 'አንተ ማን ሆነህ ነው ሌላው ላይ ጣት የምትቀስረው?' የሚያስብል...
የ blame shift ጨዋታ በጣም ያስተዛዝባል... 'ከደሙ ንጹህ ነኝ' ክህደት በጣም ያሳቅቃል... 'የወደቀ እንጨት' ላይ ምሳር መጠቅጠቅ የባለ እጁን ቁሸት አይከልልም... 'እነ እከሌ' የማለት ድፍረት የእኔታን በደል አይፍቅም...
ሁላችንም ቤት ጉዶች አሉ... ወይ እስኪመቸን የምንጠብቅ 'አድፋጮች'፣ አልያም ነጥቀን የምንሰጋ 'ድንጉጦች' ነን... ይህን መካድ አይቻልም...
አዎን...
እስክንያዝ እንጂ ሁላችንም የሰረቅነው አለን... ስላልተመቸን እንጂ ልንዘርፍ የምናደባለት አለን... ይህ የሚዋሽ አይደለም...
በነገራችን ላይ ሌሎች ላይ የምንቀስራት ጣት ስሟ 'ሌባ ጣት' ይባላል...
___
ሃበሻ ጥሩ ብሂል አለችው...
"ስራው ያውጣው" የምትል...
በምሳሌዋ ውስጥ... በግል - ከፍርድ የመቆጠብ ትህትና፣ ለሌሎች - ከተግባር የሚወለድ አርነት፣ ለሁሉም - በጥፋት ልክ የመዳኘት ፍትሕ ተዛንቆ ይታያል...
አዎን... ሁሉም ስራው ያውጣው!!
__
እጆቹን በማንፃት ላይ የተጠመደ ድንጋይ ይወረውር ዘንድ አይቻለውም...
___
@bridgethoughts
.
.
"Let him who is without sin among you be the first to throw a stone at her." ~ Jesus
__
ፍርድ እውቀት አይጠይቅም... ማንም ሰው ላይ መፍረድ ቀላል ነው... የሞራል ጥያቄ ግን አለው... 'አንተ ማን ሆነህ ነው ሌላው ላይ ጣት የምትቀስረው?' የሚያስብል...
የ blame shift ጨዋታ በጣም ያስተዛዝባል... 'ከደሙ ንጹህ ነኝ' ክህደት በጣም ያሳቅቃል... 'የወደቀ እንጨት' ላይ ምሳር መጠቅጠቅ የባለ እጁን ቁሸት አይከልልም... 'እነ እከሌ' የማለት ድፍረት የእኔታን በደል አይፍቅም...
ሁላችንም ቤት ጉዶች አሉ... ወይ እስኪመቸን የምንጠብቅ 'አድፋጮች'፣ አልያም ነጥቀን የምንሰጋ 'ድንጉጦች' ነን... ይህን መካድ አይቻልም...
አዎን...
እስክንያዝ እንጂ ሁላችንም የሰረቅነው አለን... ስላልተመቸን እንጂ ልንዘርፍ የምናደባለት አለን... ይህ የሚዋሽ አይደለም...
በነገራችን ላይ ሌሎች ላይ የምንቀስራት ጣት ስሟ 'ሌባ ጣት' ይባላል...
___
ሃበሻ ጥሩ ብሂል አለችው...
"ስራው ያውጣው" የምትል...
በምሳሌዋ ውስጥ... በግል - ከፍርድ የመቆጠብ ትህትና፣ ለሌሎች - ከተግባር የሚወለድ አርነት፣ ለሁሉም - በጥፋት ልክ የመዳኘት ፍትሕ ተዛንቆ ይታያል...
አዎን... ሁሉም ስራው ያውጣው!!
__
እጆቹን በማንፃት ላይ የተጠመደ ድንጋይ ይወረውር ዘንድ አይቻለውም...
___
@bridgethoughts
❤11👍6
ዶ/ር ጴሌ ዳሮታ ...
---
(ፍልስፍናን ከነነፃነቷ የኖራት፣ በልዩ ትወና የሰበካት አይረሴ ምሁር!)
-
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር የነበረውን የጴሌ ዳሮታን (ዶ/ር) ህልፈት የሰማ ከቀድሞ ተማሪዎቹ አንዱ የሆነው ‹‹አሳፍ ኃይሉ›› በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ስለ ጴሌ (ዶ/ር) ካሰፈረው ረዘም ያለ የታሪክ ማስታወሻ በጥቂቱ ቀንጨብ አድርጌ ወደ እኔው ጥቂት ትዝታ ለማለፍ ወደድኹ፤
የዕውቁን የፍልስፍና መምህራችንን የዶ/ር ጴሌ ዳሮታን ህልፈት ሰማሁ። ከልብ አዝኜያለሁ።
በእርግጥ ፔሌ ቀጥታ የእኔ አስተማሪ ሆኖ ባያውቅም፣ ዝናውን በመስማት ጉዱን ለማየት ከጓደኞቼ ጋር ከአንድም ሁለት ቀን በእርሱ ሌክቸር ክፍለጊዜ ገብቼ ሎጂክን እንደ መደሰቻ ሽቶ ተርከፍክፌ ነው የወጣሁት ብል ማጋነን አይደለም!
ጴሌ በጣም ቀልደኛ ሰው ነበረ። ስሙን በእንግሊዝኛ "Pelle" ብሎ ይፅፍና፣ ዕድሜ ለእንግሊዝኛ "ጴ" የሚል ፊደል ስለሌለው ስሜን ከጴሌ ወደ ፔሌ ቀየረልኝ — በማለት ያሳቀንን አልረሳውም!!
--
የፍልስፍና መምህሩን ጴሌ ዳሮታ (ዶ/ር) በጨረፍታ በእኔው ትውስታ!!
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ፍልስፍናን ነፍስ ከዘሩበት ምሁራን መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው፤ በ1990ዎቹ አዲስ አበባ ተማሪ በነበርንበት ጊዜ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል መከፈቱ ስለነበር ከሌላ የትምህርት ክፍል/ዲፓርትመንት እያስፈቀድን ጴሌ የሚያስተምርበት ክፍል እንማር ነበር፡፡
አንድ ወቅት ላይ ስለ እውነታ /what is Reality? / በሚል አርእስት የግሪክ ፈላስፋዎችና ጥልቅ አሳቢዎች /Philosophers and Great Thinkers የተናገሩት/የጻፉትን ሐሳብ እያስተማረን ሳለ፤ አብዛኛውን ጊዜ እንደሚያደርገው በሌክቸሩ መካከል አንድ ጥያቄ ለእኛ ለተማሪዎች እንዲህ ሲል አነሳ፤
‹‹እውነት ለእናንተ ምንድን ነው? ማነው?››
ተማሪዎች እርስ በርስ እየተያየን ዝምታን አሰፈንን… ‹‹በሉ እንጂ አይዞአችሁ ባትመልሱት አያሰቅላችሁም እኮ!›› ሲል ለማደፋፋር ሞከረ፡፡ ከጥቂት አፍታ በኋላ ከፊት ተቀምጦ የነበረ ተማሪ ፍርሃትና ሥጋት በቀላቀለ ድምፀት፤
‹‹ለእኔ እውነት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!›› ሲል መለሰ፡፡
ጴሌ፡- መላጣውን አሸት አሸት እያደረገ ‹‹አረ ባክህ… ተው እንጂ… ይሄኔ በእርሱ ዘመን ኖረህ ቢሆን ኖሮ ሲወገርና ሲሰቀል አንዱ ድንጋይ አቀባይ አንተ ትሆን ነበር?!›› ሲለው ክፍሉ በሣቅ አውካካ…
ከዚህ በፍርድ ወንበር ፊት ከተቀመጠው ከጲላጦስ፤ ‹‹እውነት ምንድ ነው?›› ጥያቄ ጋር በተያያዘ ጴሌ አንድ በገሃዱ ዓለም የሆነ ይሁን ወይም ራሱ የፈጠረው ይሁን ለጊዜው ትዝ ባይለኝም አንድ ታሪክ እንዲህ ሲል አወጋን፤
በናዚ ዘመን አይሁዶች በያሉበት እየታደኑ በመርዝ ጋዝ ሲያልቁ በነበረበት ክፉ ጊዜ አንዲት አይሁዳዊት እናት እና ልጇ ተደብቀው ይኖሩ ነበር፡፡ ይህቺ አይሁዳዊት እናት ለብቸኛው ልጇ እንዲህ እያለች ትነግረው/ታስተምረው ነበር፤
‹‹ልጄ እውነትን ውደድ፤ ሁሌም እውነት ተናገር!››
ታዲያ አንድ ወቅት ላይ የናዚ አሳሽ ወታደሮች በጥቆማ ወደ ቤታቸው ይመጣሉ፤ ወታደሮቹ በሩን ሲያንኳኩ ልጅ በሩን ይከፍታል፤ ልጁን በጥያቄ ያፋጥጡታል፤ ‹‹እዚህ ቤት ውስጥ አንተ ብቻ ነህ የምትኖረው?››
ልጅ ይመልሳል… ‹‹አይ እናቴም አለች ግን እናቴ በታችኛው ምሥጢራዊ ክፍል ውስጥ ነው ያለችው፤›› በማለት የናዚ ወታደሮችን እናቱ ወዳለችበት ይመራቸዋል፡፡
ወታደሮቹ እናቱን እና ልጁን ይዘዋቸው ሄዱ፤ የእናቲቱና የልጁ ዕጣ ፈንታ እንደ ወገኖቻቸው ሁሉ በመርዝ ጋዝ ጭስ ተቃጥሎ፣ ታፍኖና ተልብልቦ መሞት ሆነ…
ጴሌ፡- ታሪኩን ተርኮ ከጨረሰልን በኋላ የተለመደውን ጥያቄውን አስከተለ፤
‹‹ለመሆኑ ለዚህ የግፍ ሞት ተጠያቂው ማነው… እናት፣ ልጅ ወይስ የናዚ ወታደሮች?! ከመመለሳችሁ በፊት ጥቂት አስቡ ዝም ብላችሁ እንዳመጣላችሁ እንዳትመልሱ… ጎበዝ ‹‹F›› ለማግኘትም እኮ ትንሽ ማሰብ፤ ማሰላሰል ይጠይቃል…›› ዳግመኛ ክፍሉ በሳቅ ማዕበል ተናወጠ…
ጴሌ እንዲህ ዓይነት የፍልስፍና መምህር ነበር… ነፍሱ በጥበብ ፍቅር የነደደች…!!
ጴሌ ዳሮታ (ዶ/ር) ነፍስህ በሰላም ትረፍ!!
---
ጸሐፊ - ተረፈ ወርቁ (ወዳጄ ምስጋናዬ ይድረስህ) 🙏
—-
@bridgethoughts
---
(ፍልስፍናን ከነነፃነቷ የኖራት፣ በልዩ ትወና የሰበካት አይረሴ ምሁር!)
-
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር የነበረውን የጴሌ ዳሮታን (ዶ/ር) ህልፈት የሰማ ከቀድሞ ተማሪዎቹ አንዱ የሆነው ‹‹አሳፍ ኃይሉ›› በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ስለ ጴሌ (ዶ/ር) ካሰፈረው ረዘም ያለ የታሪክ ማስታወሻ በጥቂቱ ቀንጨብ አድርጌ ወደ እኔው ጥቂት ትዝታ ለማለፍ ወደድኹ፤
የዕውቁን የፍልስፍና መምህራችንን የዶ/ር ጴሌ ዳሮታን ህልፈት ሰማሁ። ከልብ አዝኜያለሁ።
በእርግጥ ፔሌ ቀጥታ የእኔ አስተማሪ ሆኖ ባያውቅም፣ ዝናውን በመስማት ጉዱን ለማየት ከጓደኞቼ ጋር ከአንድም ሁለት ቀን በእርሱ ሌክቸር ክፍለጊዜ ገብቼ ሎጂክን እንደ መደሰቻ ሽቶ ተርከፍክፌ ነው የወጣሁት ብል ማጋነን አይደለም!
ጴሌ በጣም ቀልደኛ ሰው ነበረ። ስሙን በእንግሊዝኛ "Pelle" ብሎ ይፅፍና፣ ዕድሜ ለእንግሊዝኛ "ጴ" የሚል ፊደል ስለሌለው ስሜን ከጴሌ ወደ ፔሌ ቀየረልኝ — በማለት ያሳቀንን አልረሳውም!!
--
የፍልስፍና መምህሩን ጴሌ ዳሮታ (ዶ/ር) በጨረፍታ በእኔው ትውስታ!!
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ፍልስፍናን ነፍስ ከዘሩበት ምሁራን መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው፤ በ1990ዎቹ አዲስ አበባ ተማሪ በነበርንበት ጊዜ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል መከፈቱ ስለነበር ከሌላ የትምህርት ክፍል/ዲፓርትመንት እያስፈቀድን ጴሌ የሚያስተምርበት ክፍል እንማር ነበር፡፡
አንድ ወቅት ላይ ስለ እውነታ /what is Reality? / በሚል አርእስት የግሪክ ፈላስፋዎችና ጥልቅ አሳቢዎች /Philosophers and Great Thinkers የተናገሩት/የጻፉትን ሐሳብ እያስተማረን ሳለ፤ አብዛኛውን ጊዜ እንደሚያደርገው በሌክቸሩ መካከል አንድ ጥያቄ ለእኛ ለተማሪዎች እንዲህ ሲል አነሳ፤
‹‹እውነት ለእናንተ ምንድን ነው? ማነው?››
ተማሪዎች እርስ በርስ እየተያየን ዝምታን አሰፈንን… ‹‹በሉ እንጂ አይዞአችሁ ባትመልሱት አያሰቅላችሁም እኮ!›› ሲል ለማደፋፋር ሞከረ፡፡ ከጥቂት አፍታ በኋላ ከፊት ተቀምጦ የነበረ ተማሪ ፍርሃትና ሥጋት በቀላቀለ ድምፀት፤
‹‹ለእኔ እውነት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!›› ሲል መለሰ፡፡
ጴሌ፡- መላጣውን አሸት አሸት እያደረገ ‹‹አረ ባክህ… ተው እንጂ… ይሄኔ በእርሱ ዘመን ኖረህ ቢሆን ኖሮ ሲወገርና ሲሰቀል አንዱ ድንጋይ አቀባይ አንተ ትሆን ነበር?!›› ሲለው ክፍሉ በሣቅ አውካካ…
ከዚህ በፍርድ ወንበር ፊት ከተቀመጠው ከጲላጦስ፤ ‹‹እውነት ምንድ ነው?›› ጥያቄ ጋር በተያያዘ ጴሌ አንድ በገሃዱ ዓለም የሆነ ይሁን ወይም ራሱ የፈጠረው ይሁን ለጊዜው ትዝ ባይለኝም አንድ ታሪክ እንዲህ ሲል አወጋን፤
በናዚ ዘመን አይሁዶች በያሉበት እየታደኑ በመርዝ ጋዝ ሲያልቁ በነበረበት ክፉ ጊዜ አንዲት አይሁዳዊት እናት እና ልጇ ተደብቀው ይኖሩ ነበር፡፡ ይህቺ አይሁዳዊት እናት ለብቸኛው ልጇ እንዲህ እያለች ትነግረው/ታስተምረው ነበር፤
‹‹ልጄ እውነትን ውደድ፤ ሁሌም እውነት ተናገር!››
ታዲያ አንድ ወቅት ላይ የናዚ አሳሽ ወታደሮች በጥቆማ ወደ ቤታቸው ይመጣሉ፤ ወታደሮቹ በሩን ሲያንኳኩ ልጅ በሩን ይከፍታል፤ ልጁን በጥያቄ ያፋጥጡታል፤ ‹‹እዚህ ቤት ውስጥ አንተ ብቻ ነህ የምትኖረው?››
ልጅ ይመልሳል… ‹‹አይ እናቴም አለች ግን እናቴ በታችኛው ምሥጢራዊ ክፍል ውስጥ ነው ያለችው፤›› በማለት የናዚ ወታደሮችን እናቱ ወዳለችበት ይመራቸዋል፡፡
ወታደሮቹ እናቱን እና ልጁን ይዘዋቸው ሄዱ፤ የእናቲቱና የልጁ ዕጣ ፈንታ እንደ ወገኖቻቸው ሁሉ በመርዝ ጋዝ ጭስ ተቃጥሎ፣ ታፍኖና ተልብልቦ መሞት ሆነ…
ጴሌ፡- ታሪኩን ተርኮ ከጨረሰልን በኋላ የተለመደውን ጥያቄውን አስከተለ፤
‹‹ለመሆኑ ለዚህ የግፍ ሞት ተጠያቂው ማነው… እናት፣ ልጅ ወይስ የናዚ ወታደሮች?! ከመመለሳችሁ በፊት ጥቂት አስቡ ዝም ብላችሁ እንዳመጣላችሁ እንዳትመልሱ… ጎበዝ ‹‹F›› ለማግኘትም እኮ ትንሽ ማሰብ፤ ማሰላሰል ይጠይቃል…›› ዳግመኛ ክፍሉ በሳቅ ማዕበል ተናወጠ…
ጴሌ እንዲህ ዓይነት የፍልስፍና መምህር ነበር… ነፍሱ በጥበብ ፍቅር የነደደች…!!
ጴሌ ዳሮታ (ዶ/ር) ነፍስህ በሰላም ትረፍ!!
---
ጸሐፊ - ተረፈ ወርቁ (ወዳጄ ምስጋናዬ ይድረስህ) 🙏
—-
@bridgethoughts
🙏6❤4👍1
The Fallen Lineman
.
.
.
ለእርሱ...
ስሙን ከማወቃችን በፊት፣ ያኔ ድሮ - ራሱን ለመስመር ለሰጠው... ከተሞች ባንቀላፉበት ቀዝቃዛ ለሊት በምድሪቱ ለተመላለሰው... በሚንቀለቀል ነበልባል ሙቀት ከምሰሶ ጋር ለታከከው... ብናኝ ካፈነው ንፋስ ጋር ታግሎ ታወር ለደመረው... ፒንሳ፣ ሽቦ፣ ቀበቶና ስታፌ ታጥቆ ብርሃን ለሚያዋልደው...
ለእርሱ...
በጊዜ ቤት መግባት ለማይሆንለት... ልጆቹን በንቃት ማግኘት ለሚናፍቀው... እንቅልፍ ሲጥላቸው ተኝተው፣ ሲበረቱ ከበር ጠብቀው - አቧራ የጠገበ ጫማውን፣ በላብ የተላቆጠ ልብሱን፣ ድካም ያዛለው ገላውን እያዩ ለሚያዝኑለት...
[ግን ደግሞ ለማያዝኑበት...]
ብርሃን ለናፈቀ ሕዝብ የሚደርስ አባት እንዳላቸው ስለሚያውቁ ለሚኮሩበት... ለእርሱ!!
__
[ከተማው ሲፈካ ሰዎች ይደሰታሉ... ጨለማው ሲገፈፍ እልፎች ይረካሉ...]
የመጨረሻዋን ምሰሶ በዝናብ እየተደበደበ የወጣትን ሰው ግን አያውቁትም...
የመጨረሻዋን ገመድ በሃሩር እየደበነ የሳባትን ሰው ግን አያውቁትም...
ለዚያች ከተማ ድምቀት አካሉን የገበረውን ሰው ግን አያውቁትም...
ለዚያች አምፑል ብርሃን ሕልውናውን ያጣውን ሰው ግን አያውቁትም...
[ቢያውቁትም አበጀህ አይሉትም... ይልቁን ለስድብ፣ ለውርደት፣ ለነቀፋ የሚቀላቸው ሰው ነው...]
__
ሕዝቤ መብራት ሲጠፋ ጠብቆ 'ዓይናችሁ ይጥፋ!' ለማለት ብርቱ ነው...
ግና...
ለጥቂት የሳቱት የታወር ብረት፣ ዝናብ አርሶት ያዳለጠ መሬት፣ የተወረወረ የሽቦ ብጥሳት፣ የተለኮሰ የመስመር እሳት - የስንቱን ሕይወት ቀጥፎ ብርሃኑ እንደተገኘ አያውቅም...
ወፍ ሳይጮህ፣ ፀሐይ ሳትወጣ ከቤቱ የወጣ - ግና በበሮቹ መሃል መመለስ ያልቻለ ባሏን አስባ ሚስት እንዴት እንደምታነባ አያውቅም...
የአባት ኮቴ፣ የጎብኚ ድምጽ፣ የዘመድ ሰላምታ ሲርቅ - ልጆች እንዴት እንደሚሆኑ አይገምትም...
[ሕዝብ አንድ ነገር ብቻ ያውቃል... ከሆዳቸው በላይ ሕልም የሌላቸውን ከንቱዎች፣ ከድሆች አፍ መንጠቅ የማይቆረቁራቸውን ነጣቂዎች፣ ለማገልገል የተሰጣቸውን ዕድል የሚገለገሉበት ነውረኞች...]
_
ይህን የወደቀ ሰውን ጓዳ ግን አያውቁም...
__
[እርግጥ ነው -ይህ ሰው በስጋ አልፏል...]
እያንዳንዲቷ ደማቅ አምፑል ግን ደማቅ ትግሉን ትናገራለች...
[እርግጥ ነው - አንደበቱ በሞት ክንድ ተሸብቧል...]
እያንዳንዷ መስመር ግን የሕይወት መስዋዕትነቱን ትመሰክራለች...
[እርግጥ ነው -ስምና ታሪኩ ተዘንግቷል...]
በእያንዳንዱ ታወር የምትፈሰው ኢነርጂ ግን ቦይ የቀደደላትን እጅ ታስታውሳለች...
__
እርሱ የመስመር ሰራተኛ ብቻ አልነበረም...
የማይታይ የሃገር ዋልታ፣ የሰርክ ድምቀቷ ባለውለታ እንጂ...
እርሱ ቴክኒሺያን ብቻ አልነበረም...
የምድሪቱን ጭለማ በብርሃን ስለት የሚገልጥ መምህር፣ አጥንትና ወዙን ለሃገሩ የሰጠ ወታደርም እንጂ...
__
ዛሬ ይህን ብርቱ ሰው አሰብኩ!!...
[በእርሱም ውስጥ...]
እያንዳንዱን ምሰሶ ያለፍርሃት የሚወጣ፣ እያንዳንዱን ታወር በልበ ሙሉነት የሚረግጥ፣ ከእያንዳንዱ ሽቦ ብርሃን የሚያፈስ ቋሚውን የመስመር ሰው አወደስኩ...
___
ክብር ለወደቀው የመስመር ሰው!!...
የወጣባቸው ምሰሶዎች ዛሬም እንደቆሙ ነው...
የጠገናቸው መስመሮች የብርሃን ጅረት እያፈሰሱ ነው...
በእጁ የዳሰሳቸው አምፑሎች መደብርና መንደሩን እያደመቁ ነው...
እርሱ በአካል ባይኖርም የስራው ፍሬ በዙሪያችን እንደከበበን ይኖራል...
_
ይህ ሰው ዝነኛ አልነበረም - አይታወስም...
ሀብታም አልነበረም - በስሙ ሐውልት የለም...
ሆኖም...
[ሃገሩ በግብሩ ቀና እንድትል የሚያደርግ ያልተዘመረለት ጀግና ነው...]
___
ይህ ድምጽ ለእርሱ ለወደቀው ለመስመር ሰው የቀረበ አኮቴት ነው...
___
[ጓዴ ነፍስህ በሰላም ትረፍ]
___
@bridgethoughts
.
.
.
ለእርሱ...
ስሙን ከማወቃችን በፊት፣ ያኔ ድሮ - ራሱን ለመስመር ለሰጠው... ከተሞች ባንቀላፉበት ቀዝቃዛ ለሊት በምድሪቱ ለተመላለሰው... በሚንቀለቀል ነበልባል ሙቀት ከምሰሶ ጋር ለታከከው... ብናኝ ካፈነው ንፋስ ጋር ታግሎ ታወር ለደመረው... ፒንሳ፣ ሽቦ፣ ቀበቶና ስታፌ ታጥቆ ብርሃን ለሚያዋልደው...
ለእርሱ...
በጊዜ ቤት መግባት ለማይሆንለት... ልጆቹን በንቃት ማግኘት ለሚናፍቀው... እንቅልፍ ሲጥላቸው ተኝተው፣ ሲበረቱ ከበር ጠብቀው - አቧራ የጠገበ ጫማውን፣ በላብ የተላቆጠ ልብሱን፣ ድካም ያዛለው ገላውን እያዩ ለሚያዝኑለት...
[ግን ደግሞ ለማያዝኑበት...]
ብርሃን ለናፈቀ ሕዝብ የሚደርስ አባት እንዳላቸው ስለሚያውቁ ለሚኮሩበት... ለእርሱ!!
__
[ከተማው ሲፈካ ሰዎች ይደሰታሉ... ጨለማው ሲገፈፍ እልፎች ይረካሉ...]
የመጨረሻዋን ምሰሶ በዝናብ እየተደበደበ የወጣትን ሰው ግን አያውቁትም...
የመጨረሻዋን ገመድ በሃሩር እየደበነ የሳባትን ሰው ግን አያውቁትም...
ለዚያች ከተማ ድምቀት አካሉን የገበረውን ሰው ግን አያውቁትም...
ለዚያች አምፑል ብርሃን ሕልውናውን ያጣውን ሰው ግን አያውቁትም...
[ቢያውቁትም አበጀህ አይሉትም... ይልቁን ለስድብ፣ ለውርደት፣ ለነቀፋ የሚቀላቸው ሰው ነው...]
__
ሕዝቤ መብራት ሲጠፋ ጠብቆ 'ዓይናችሁ ይጥፋ!' ለማለት ብርቱ ነው...
ግና...
ለጥቂት የሳቱት የታወር ብረት፣ ዝናብ አርሶት ያዳለጠ መሬት፣ የተወረወረ የሽቦ ብጥሳት፣ የተለኮሰ የመስመር እሳት - የስንቱን ሕይወት ቀጥፎ ብርሃኑ እንደተገኘ አያውቅም...
ወፍ ሳይጮህ፣ ፀሐይ ሳትወጣ ከቤቱ የወጣ - ግና በበሮቹ መሃል መመለስ ያልቻለ ባሏን አስባ ሚስት እንዴት እንደምታነባ አያውቅም...
የአባት ኮቴ፣ የጎብኚ ድምጽ፣ የዘመድ ሰላምታ ሲርቅ - ልጆች እንዴት እንደሚሆኑ አይገምትም...
[ሕዝብ አንድ ነገር ብቻ ያውቃል... ከሆዳቸው በላይ ሕልም የሌላቸውን ከንቱዎች፣ ከድሆች አፍ መንጠቅ የማይቆረቁራቸውን ነጣቂዎች፣ ለማገልገል የተሰጣቸውን ዕድል የሚገለገሉበት ነውረኞች...]
_
ይህን የወደቀ ሰውን ጓዳ ግን አያውቁም...
__
[እርግጥ ነው -ይህ ሰው በስጋ አልፏል...]
እያንዳንዲቷ ደማቅ አምፑል ግን ደማቅ ትግሉን ትናገራለች...
[እርግጥ ነው - አንደበቱ በሞት ክንድ ተሸብቧል...]
እያንዳንዷ መስመር ግን የሕይወት መስዋዕትነቱን ትመሰክራለች...
[እርግጥ ነው -ስምና ታሪኩ ተዘንግቷል...]
በእያንዳንዱ ታወር የምትፈሰው ኢነርጂ ግን ቦይ የቀደደላትን እጅ ታስታውሳለች...
__
እርሱ የመስመር ሰራተኛ ብቻ አልነበረም...
የማይታይ የሃገር ዋልታ፣ የሰርክ ድምቀቷ ባለውለታ እንጂ...
እርሱ ቴክኒሺያን ብቻ አልነበረም...
የምድሪቱን ጭለማ በብርሃን ስለት የሚገልጥ መምህር፣ አጥንትና ወዙን ለሃገሩ የሰጠ ወታደርም እንጂ...
__
ዛሬ ይህን ብርቱ ሰው አሰብኩ!!...
[በእርሱም ውስጥ...]
እያንዳንዱን ምሰሶ ያለፍርሃት የሚወጣ፣ እያንዳንዱን ታወር በልበ ሙሉነት የሚረግጥ፣ ከእያንዳንዱ ሽቦ ብርሃን የሚያፈስ ቋሚውን የመስመር ሰው አወደስኩ...
___
ክብር ለወደቀው የመስመር ሰው!!...
የወጣባቸው ምሰሶዎች ዛሬም እንደቆሙ ነው...
የጠገናቸው መስመሮች የብርሃን ጅረት እያፈሰሱ ነው...
በእጁ የዳሰሳቸው አምፑሎች መደብርና መንደሩን እያደመቁ ነው...
እርሱ በአካል ባይኖርም የስራው ፍሬ በዙሪያችን እንደከበበን ይኖራል...
_
ይህ ሰው ዝነኛ አልነበረም - አይታወስም...
ሀብታም አልነበረም - በስሙ ሐውልት የለም...
ሆኖም...
[ሃገሩ በግብሩ ቀና እንድትል የሚያደርግ ያልተዘመረለት ጀግና ነው...]
___
ይህ ድምጽ ለእርሱ ለወደቀው ለመስመር ሰው የቀረበ አኮቴት ነው...
___
[ጓዴ ነፍስህ በሰላም ትረፍ]
___
@bridgethoughts
❤🔥12👏4
ሰላም ወዳጆች...
___
መጽሔታችን ቀለም በሰዓቷ ከች ብላለች... ቅጽ ፩ ቁጥር ፮ እትምን በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ...
👇
@kelemofficial
ለምታውቋቸው ጋብዟት፤ ለጥበብ አፍቃሪያን ጠቁሟት...
ቻናሉን ተቀላቀሉ!!
ይህን ስለምታደርጉ እናመሰግናለን 🙏
___
መጽሔታችን ቀለም በሰዓቷ ከች ብላለች... ቅጽ ፩ ቁጥር ፮ እትምን በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ...
👇
@kelemofficial
ለምታውቋቸው ጋብዟት፤ ለጥበብ አፍቃሪያን ጠቁሟት...
ቻናሉን ተቀላቀሉ!!
ይህን ስለምታደርጉ እናመሰግናለን 🙏
❤5🔥1