.
.
.
[ግራ እየገባኝ ስሄድ አንድ ነገር እየተማርኩ እንደሆነ አውቃለሁ... ምናልባትም ለመንገዴ አንድ ተጨማሪ የብርሃን አምድ እየተተከለች ይሆናል...]
.
.
.
አንዳንዴ ተራ ብዬ ባቃለልኩት ነገር ውስጥ ተቆጥሮ የማያልቅ መደነቅ ይወርሰኛል... ሌላ ጊዜ ደግሞ ድንቅ ያልኩትን ሳሳድድ ከእጄ ያለውን ውበት አጣና ሃዘን ይከበኛል...
[ወደላይ ብቻ የሚያዩ ከእግሮቻቸው ስር ያለውን የምድር ሃብት አይረዱም... አዘቅዝቀው የሚመለከቱም ከበላያቸው ያለውን ንጽህና አይገነዘቡም...]
___
አንዳንዴ ብዙ አለኝ ያልኩትን ጊዜ በአልባሌ ነገር ሞልቼ አባክነዋለሁ... አጠረኝ ያልኩትን ደግሞ ከበድ ባሉ ስራዎች አጭቄ ሳልጠቀም ፈጀዋለሁ...
በሁለቱ መካከል የሚተርፈኝ አንዳች የለም - ከጭንቀትና እረፍት አልባነት ውጭ...
[ነገ ይሆንልኛል እያሉ የሚጠብቁ ዛሬን አያጣጥሙም... ዛሬ ካልሞላልኝ ብለው ሙጥኝ የሚሉም ከነግ ተስፋ አይገናኙም...]
___
አንዳንድ ቀን በፍቅር እንደተጥለቀለቅሁ ይሰማኛል - ሆኖም ወዲያው በእውር ድንብር አስረክቤው ዝምታ ይውጠኛል... ሌላ ጊዜ ደግሞ ፍቅር አጣሁ ብዬ ፍለጋ እወጣለሁ - ይሁንና ቅንስናሽ ማንነቴን በየቦታው ተቀምጦ ሳገኘው እደነግጣለሁ...
በዚህ ሰበብ የሃሳብ ድካም ያናውዘኛል... ውርሱ ሃዘን የሆነ ዘር በውስጤ ያጎነቁላል...
[መፈቀርን ብቻ የሚሻ መስጠትን ሳይማር ያልፋል... ፍቅር ሲሰጥ ብቻ የኖረም የመቀበል ቆምታን ይተላለፋል...]
___
የሕይወት መትረፍረፍ በተሰማኝ ማግስት ራሴን የሚጠፋ ጥላ ሲያሳድድ አገኘዋለሁ... ኑረት በጉድለት ስሜት ስትከበኝ ደግሞ ጫፍ በሌለው ምኞት ሸክሟን አበዛዋለሁ...
በዚህ ሰበብ ባዶነት ይወርሰኛል... ተስፋቢስነት ይጫነኛል...
[መድረሻውን ብቻ የሚያይ ጉዞውን ይረሳል... መንገዱን ብቻ ሙጥኝ ያለ አድማሱን ይዘነጋል...]
___
ነፃ የሆንኩ ይመስለኛል - ግና ራሴን የማገኘው በምርጫዎች ሰንሰለት ታብቶ ነው... ነፃ እንዳልሆንኩ አስባለሁ - ግና ውስጤ የማየው የግዞት ጫና የማይታከካቸውን ዕልፍ ቦታዎች ነው...
በዚህ ሰበብ ቀልቤን ቅዥት ሞልቶት ያታልለኝና የምር ትግል ውስጥ እገባለሁ...
[ነፃነትን የሚፈሩ የራሳቸው አዕምሮ እስረኛ ከመሆን አይድኑም... ነፃነትን ያለአግባብ የሚጠቀሙ የምኞቶቻቸው ባሪያ ከመሆን አይቀሩም...]
___
እንደነገርኳችሁ ነው...
ግራ እየገባኝ ስሄድ አንድ ነገር እየተማርኩ እንደሆነ አውቃለሁ...
___
@bridgethoughts
.
.
[ግራ እየገባኝ ስሄድ አንድ ነገር እየተማርኩ እንደሆነ አውቃለሁ... ምናልባትም ለመንገዴ አንድ ተጨማሪ የብርሃን አምድ እየተተከለች ይሆናል...]
.
.
.
አንዳንዴ ተራ ብዬ ባቃለልኩት ነገር ውስጥ ተቆጥሮ የማያልቅ መደነቅ ይወርሰኛል... ሌላ ጊዜ ደግሞ ድንቅ ያልኩትን ሳሳድድ ከእጄ ያለውን ውበት አጣና ሃዘን ይከበኛል...
[ወደላይ ብቻ የሚያዩ ከእግሮቻቸው ስር ያለውን የምድር ሃብት አይረዱም... አዘቅዝቀው የሚመለከቱም ከበላያቸው ያለውን ንጽህና አይገነዘቡም...]
___
አንዳንዴ ብዙ አለኝ ያልኩትን ጊዜ በአልባሌ ነገር ሞልቼ አባክነዋለሁ... አጠረኝ ያልኩትን ደግሞ ከበድ ባሉ ስራዎች አጭቄ ሳልጠቀም ፈጀዋለሁ...
በሁለቱ መካከል የሚተርፈኝ አንዳች የለም - ከጭንቀትና እረፍት አልባነት ውጭ...
[ነገ ይሆንልኛል እያሉ የሚጠብቁ ዛሬን አያጣጥሙም... ዛሬ ካልሞላልኝ ብለው ሙጥኝ የሚሉም ከነግ ተስፋ አይገናኙም...]
___
አንዳንድ ቀን በፍቅር እንደተጥለቀለቅሁ ይሰማኛል - ሆኖም ወዲያው በእውር ድንብር አስረክቤው ዝምታ ይውጠኛል... ሌላ ጊዜ ደግሞ ፍቅር አጣሁ ብዬ ፍለጋ እወጣለሁ - ይሁንና ቅንስናሽ ማንነቴን በየቦታው ተቀምጦ ሳገኘው እደነግጣለሁ...
በዚህ ሰበብ የሃሳብ ድካም ያናውዘኛል... ውርሱ ሃዘን የሆነ ዘር በውስጤ ያጎነቁላል...
[መፈቀርን ብቻ የሚሻ መስጠትን ሳይማር ያልፋል... ፍቅር ሲሰጥ ብቻ የኖረም የመቀበል ቆምታን ይተላለፋል...]
___
የሕይወት መትረፍረፍ በተሰማኝ ማግስት ራሴን የሚጠፋ ጥላ ሲያሳድድ አገኘዋለሁ... ኑረት በጉድለት ስሜት ስትከበኝ ደግሞ ጫፍ በሌለው ምኞት ሸክሟን አበዛዋለሁ...
በዚህ ሰበብ ባዶነት ይወርሰኛል... ተስፋቢስነት ይጫነኛል...
[መድረሻውን ብቻ የሚያይ ጉዞውን ይረሳል... መንገዱን ብቻ ሙጥኝ ያለ አድማሱን ይዘነጋል...]
___
ነፃ የሆንኩ ይመስለኛል - ግና ራሴን የማገኘው በምርጫዎች ሰንሰለት ታብቶ ነው... ነፃ እንዳልሆንኩ አስባለሁ - ግና ውስጤ የማየው የግዞት ጫና የማይታከካቸውን ዕልፍ ቦታዎች ነው...
በዚህ ሰበብ ቀልቤን ቅዥት ሞልቶት ያታልለኝና የምር ትግል ውስጥ እገባለሁ...
[ነፃነትን የሚፈሩ የራሳቸው አዕምሮ እስረኛ ከመሆን አይድኑም... ነፃነትን ያለአግባብ የሚጠቀሙ የምኞቶቻቸው ባሪያ ከመሆን አይቀሩም...]
___
እንደነገርኳችሁ ነው...
ግራ እየገባኝ ስሄድ አንድ ነገር እየተማርኩ እንደሆነ አውቃለሁ...
___
@bridgethoughts
❤9🔥5🥰5💊1
.
.
.
የዛሬ ስንት ዓመት በእናትና አባቴ ጠያቂነት ምድሪቱ ከነገረ ስሪቷ የቆነጠረችውን ሥጋ በኪራይ አስረክባኝ በዚህች ውብ ዓለም ውስጥ ተከሰትኩ...
[የኑረት ስሌትህ እየገፋ ሲመጣ አባቶችህ ያስረከቡህን ስንቅ ቅርጥፍ አድርገህ ብትበላም ለልጅህ የምታቆየው ውርስ እጅህ ላይ አለመቅረቱ ስለሚያሳፍርህ ዕድሜህን አትናገርም...]
በኖርኩባቸው ዓመታት ሳቅና ለቅሶዬ ተላቁጧል... ደስታና ሃዘኔ ተጋምዷል... አክብሮት ንቀቴ ተሳስሯል... ፍቅር ጥላቻዬ ተቀይጧል... ማግኘት ማጣቴም ተዛንቋል...
እጅግ የረዘሙ ለሊቶች በጎጆ ጓዳዬ አቀርዝዘው ያውቃሉ... እጅግ አስደሳች ወቅቶችም በኑሮ ደጄ ተመላልሰው አልፈዋል... እጅግ የከፉ ሰዎች ሆዴን አሻክረው ያውቃሉ... እጅግ ልዩ ሰዎች ልቤን በሃሴት ሞልተዋል...
[የብዙ ሰዎች መዋጮ ነኝ...]
ቆጥሬ የማልጨርሳቸው ሰዎች ቃላት የማይገዳደሩትን ውለታ እየዋሉልኝ ነው እዚህ የደረስኩት... ማወቅ ሳይገዳቸው እጅ የዘረጉልኝ፣ ስስት ሳይፈትናቸው በር የከፈቱልኝ፣ ምላሽ ሳይጠብቁ እልፍ የለገሱኝ - ብዙ ናቸው... ['የኔ የምለው አንዳች የለኝም' የምለው ለዚህ ነው]...
[መልካምነቴን እንጃ - እንጂ እኔም ብሆን ለሃዘናቸው ሰበብ፣ ለእንባቸው ምክንያት የሆንኳቸው አይጠፉም...]
ከደረሰብኝ ያልተናገርኩት ይንዛዛል... [ካልተናገርኩት የዘነጋሁት ይበዛል፣ ከተረፈው ውስጥ 'ይቅር' ያሟሟው ይገዝፋል]...
ያም ሆኖ...
እንቆቆ የጋቱኝ ማርነቴን አላጠፉትም... አይዞህ ያላሉኝ ብርታቴን አልነኩትም...
የገፉኝ ከገደል ወለል አልጣሉኝም፣ ወለል የጣሉኝ መውጫዬን መዝጋት አልቻሉም፣ ለመዝጋት ቋጥኝ ያኖሩ መብረሪያ ክንፌን አላዩም...
ሳይረዱኝ ለቀሩ ሰዎች ራሴን ላብራራ መድከሜ ያናድደኛል... ሳልረዳቸው ቀርቼ ያዘኑብኝን ሳስብ ይጸጽተኛል... [መተው ባይኖር - ከስረን ነበር]
የለመንኳቸው ሰዎች የተለማመጥኳቸው እንደመስላቸው ሲገባኝ ብስጭቴ ብቅ ትላለች... [ለመኖር ብዬ ግን አልተናነስም - ለመኗኗር ካልሆነ በቀር]...
ግማሽ መንገድ ሊመጡ ሲገባቸው አልፌ የጠበኩዋቸው ሰዎች ግዴታዬ እንደሆነ ማሰባቸው ከገባኝ ድጋሚ አላገኛቸውም... በፍቅር ካደረጉት ግን እንደ ውለታ አልቆጥረውም...
ዝምታዬን ከሞኝነት፣ አንገት መድፋቴን ከሃፍረት ሲቆጥሩ በልቤ የናቅሁዋቸው አይጠፉም... ብልጣብልጥ መስዬ ከመንገዳቸው ግን አልወደቅሁም...
የአንዳንድ ሰዎች ክፋት አይሎ 'እንኳን አውላላ ላይ ጣሉኝ' አስብሎኝ ያውቃል... ምክንያቱም አማራጭ እንድፈልግ፣ አዲስ ሰው እንዳውቅ አድርጎኛልና...
___
የሆነስ ሆነና...
[ከመኖር ምን ተማርኩ?...]
☘ መተው! [እርግፍ አድርጎ መተው!]
☘ የኖረ ሁሉ ይሞታል! [ከውቅያኖሱ ላይ ወደላይ የወጣች የውሃ ጠብታ መልሳ ወደ ውቅያኖሱ ትቀላቀላለች]
☘ ይህም ያልፋል! [መፈራረቅ የገጽታ ደንቡ ነው]
___
እንኳንም ተወለድኩ...
[ዛሬ የወጣችውን ፀሐይ ማን በእኔ አንፃር ያያት ነበር?...]
____
@bridgethoughts
.
.
የዛሬ ስንት ዓመት በእናትና አባቴ ጠያቂነት ምድሪቱ ከነገረ ስሪቷ የቆነጠረችውን ሥጋ በኪራይ አስረክባኝ በዚህች ውብ ዓለም ውስጥ ተከሰትኩ...
[የኑረት ስሌትህ እየገፋ ሲመጣ አባቶችህ ያስረከቡህን ስንቅ ቅርጥፍ አድርገህ ብትበላም ለልጅህ የምታቆየው ውርስ እጅህ ላይ አለመቅረቱ ስለሚያሳፍርህ ዕድሜህን አትናገርም...]
በኖርኩባቸው ዓመታት ሳቅና ለቅሶዬ ተላቁጧል... ደስታና ሃዘኔ ተጋምዷል... አክብሮት ንቀቴ ተሳስሯል... ፍቅር ጥላቻዬ ተቀይጧል... ማግኘት ማጣቴም ተዛንቋል...
እጅግ የረዘሙ ለሊቶች በጎጆ ጓዳዬ አቀርዝዘው ያውቃሉ... እጅግ አስደሳች ወቅቶችም በኑሮ ደጄ ተመላልሰው አልፈዋል... እጅግ የከፉ ሰዎች ሆዴን አሻክረው ያውቃሉ... እጅግ ልዩ ሰዎች ልቤን በሃሴት ሞልተዋል...
[የብዙ ሰዎች መዋጮ ነኝ...]
ቆጥሬ የማልጨርሳቸው ሰዎች ቃላት የማይገዳደሩትን ውለታ እየዋሉልኝ ነው እዚህ የደረስኩት... ማወቅ ሳይገዳቸው እጅ የዘረጉልኝ፣ ስስት ሳይፈትናቸው በር የከፈቱልኝ፣ ምላሽ ሳይጠብቁ እልፍ የለገሱኝ - ብዙ ናቸው... ['የኔ የምለው አንዳች የለኝም' የምለው ለዚህ ነው]...
[መልካምነቴን እንጃ - እንጂ እኔም ብሆን ለሃዘናቸው ሰበብ፣ ለእንባቸው ምክንያት የሆንኳቸው አይጠፉም...]
ከደረሰብኝ ያልተናገርኩት ይንዛዛል... [ካልተናገርኩት የዘነጋሁት ይበዛል፣ ከተረፈው ውስጥ 'ይቅር' ያሟሟው ይገዝፋል]...
ያም ሆኖ...
እንቆቆ የጋቱኝ ማርነቴን አላጠፉትም... አይዞህ ያላሉኝ ብርታቴን አልነኩትም...
የገፉኝ ከገደል ወለል አልጣሉኝም፣ ወለል የጣሉኝ መውጫዬን መዝጋት አልቻሉም፣ ለመዝጋት ቋጥኝ ያኖሩ መብረሪያ ክንፌን አላዩም...
ሳይረዱኝ ለቀሩ ሰዎች ራሴን ላብራራ መድከሜ ያናድደኛል... ሳልረዳቸው ቀርቼ ያዘኑብኝን ሳስብ ይጸጽተኛል... [መተው ባይኖር - ከስረን ነበር]
የለመንኳቸው ሰዎች የተለማመጥኳቸው እንደመስላቸው ሲገባኝ ብስጭቴ ብቅ ትላለች... [ለመኖር ብዬ ግን አልተናነስም - ለመኗኗር ካልሆነ በቀር]...
ግማሽ መንገድ ሊመጡ ሲገባቸው አልፌ የጠበኩዋቸው ሰዎች ግዴታዬ እንደሆነ ማሰባቸው ከገባኝ ድጋሚ አላገኛቸውም... በፍቅር ካደረጉት ግን እንደ ውለታ አልቆጥረውም...
ዝምታዬን ከሞኝነት፣ አንገት መድፋቴን ከሃፍረት ሲቆጥሩ በልቤ የናቅሁዋቸው አይጠፉም... ብልጣብልጥ መስዬ ከመንገዳቸው ግን አልወደቅሁም...
የአንዳንድ ሰዎች ክፋት አይሎ 'እንኳን አውላላ ላይ ጣሉኝ' አስብሎኝ ያውቃል... ምክንያቱም አማራጭ እንድፈልግ፣ አዲስ ሰው እንዳውቅ አድርጎኛልና...
___
የሆነስ ሆነና...
[ከመኖር ምን ተማርኩ?...]
☘ መተው! [እርግፍ አድርጎ መተው!]
☘ የኖረ ሁሉ ይሞታል! [ከውቅያኖሱ ላይ ወደላይ የወጣች የውሃ ጠብታ መልሳ ወደ ውቅያኖሱ ትቀላቀላለች]
☘ ይህም ያልፋል! [መፈራረቅ የገጽታ ደንቡ ነው]
___
እንኳንም ተወለድኩ...
[ዛሬ የወጣችውን ፀሐይ ማን በእኔ አንፃር ያያት ነበር?...]
____
@bridgethoughts
❤19🥰7
ያገኙሽ ሁሉ በአንቺ ምክንያት የውበት መለኪያ ሚዛናቸው ተደነቃቀፈ... ትናንት 'የውበት ጥግ' ካሏት ጋር ሲያነፃጽሩሽ አልደራረስ አልሽና - አልቀው ሰቀሉሽ...
በእውነት ከዚህ ከፍታ ላይ ሌላ ሴት አይደለም አንቺ ራስሽም መድረስሽን እጠራጠራለሁ...
ውበትሽ ምን እንደሆን ታውቂያለሽ?...
መረዳትሽ!!
___
@bridgethoughts
በእውነት ከዚህ ከፍታ ላይ ሌላ ሴት አይደለም አንቺ ራስሽም መድረስሽን እጠራጠራለሁ...
ውበትሽ ምን እንደሆን ታውቂያለሽ?...
መረዳትሽ!!
___
@bridgethoughts
❤9🥰6
.
.
.
ዘወትር እሁድ ምሽት ከሩቅ የሚሰማኝ አንድ ሙዚቃ አለ... የሚስረቀረቅ፣ የሚስለመለም፣ የሚያባባ ዓይነት...
ግጥም የለውም... ዘፋኝ የለውም... የመሳሪያ ብቻ ሙዚቃ ነው... የጊታር፣ የክራር፣ የዋሽንት፣ የሳክስ፣ የቫዮሊን... [ቆይ ተውት - የመሳሪያውን ስም አላወቅሁትም...]
ስሰማው እንባዬ ይመጣል... ባር ባር ይለኛል... ጭብጥ እላለሁ... ድምጹ የሩቅ ነው... አንዳንዴ ወደ ደጅ ወጥቼ የድምጹን አቅጣጫ አስሳለሁ... ግራና ቀኝ ከጎረቤት - አይደለም... ሽቅብ ሰማይ ቁልቁል መሬት - አይደለም... ምንጩ የት ነው?...
ዛሬም እንዲሁ ሆነ...
አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ እየሰማሁት ቁልቁል እንባዬ ወረደ... እንደተለመደው ወጥቼ ከበሬ ቆምኩ... ጆሮዬን አዟዙሬ ቀሰርኩ... ምንጩን አላወቅሁትም... ከግቢ ወጥቼ ዞርዞር አልኩ... ስልኬን አውጥቼ Shazam ላደርግ ሞከርኩ... ሞባይሌ ድምጹ አልተሰማትም... [ሙዚቃውን ላገኝ አልቻልኩም] አለችኝ...
ወደ ቤቴ ገባሁ...
የዚህ ሙዚቃ ምንጭ የት ነው?... ማድመጤን ቀጠልኩ... ዜማው አልተለወጠም... ውበቱ ግን አይሰለችም... ጣዕሙ ሁሌም አዲስ ነው...
ግራ ሲገባኝ ጆሮዬን ደፈንኩ... ግጥም አድርጌ በትራስ አፈንኩት... የሙዚቃው ጥራት ጨመረ... ጆሮዬን ከግንዱ ጋር ጨቆንኩ... ድምጹ ጭራሽ እየጎላ መጣ...
በዚህ መሃል አንድ ድምጽ በሙዚቃው ስልት ውስጥ ሆኖ በለሆሳስ አናገረኝ...
ድምጹን አውቀዋለሁ... ያንተ ያለህ!... የራሴ ድምጽ ነው...
አንድ ቃል ብቻ ነው ደጋግሞ የሚነገረኝ...
'ትተኸኛል'...
'ትተኸኛል'...
'ትተኸኛል'...
እንደ ሰማሁት ሲያውቅ እየሳሳ ሄደ... እየራቀ... እየራቀ...
____
✨ ለራሳችሁ ጊዜ ከሰጣችሁ ስንት ጊዜ ሆነ?... ከራሳችሁ ጋር ቁጭ ካላችሁ ስንት ጊዜ አለፈ?... በወግ ካወጋችሁ፣ ከተደማመጣችሁ፣ ሰከን ብላችሁ ከመከራችሁ - ምን ያህል ዓመት ሆነ?... ✨
____
“Nowhere you can go is more peaceful—more free of interruptions—than your own soul.” ~ Marcus Aurelius
___
@bridgethoughts
.
.
ዘወትር እሁድ ምሽት ከሩቅ የሚሰማኝ አንድ ሙዚቃ አለ... የሚስረቀረቅ፣ የሚስለመለም፣ የሚያባባ ዓይነት...
ግጥም የለውም... ዘፋኝ የለውም... የመሳሪያ ብቻ ሙዚቃ ነው... የጊታር፣ የክራር፣ የዋሽንት፣ የሳክስ፣ የቫዮሊን... [ቆይ ተውት - የመሳሪያውን ስም አላወቅሁትም...]
ስሰማው እንባዬ ይመጣል... ባር ባር ይለኛል... ጭብጥ እላለሁ... ድምጹ የሩቅ ነው... አንዳንዴ ወደ ደጅ ወጥቼ የድምጹን አቅጣጫ አስሳለሁ... ግራና ቀኝ ከጎረቤት - አይደለም... ሽቅብ ሰማይ ቁልቁል መሬት - አይደለም... ምንጩ የት ነው?...
ዛሬም እንዲሁ ሆነ...
አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ እየሰማሁት ቁልቁል እንባዬ ወረደ... እንደተለመደው ወጥቼ ከበሬ ቆምኩ... ጆሮዬን አዟዙሬ ቀሰርኩ... ምንጩን አላወቅሁትም... ከግቢ ወጥቼ ዞርዞር አልኩ... ስልኬን አውጥቼ Shazam ላደርግ ሞከርኩ... ሞባይሌ ድምጹ አልተሰማትም... [ሙዚቃውን ላገኝ አልቻልኩም] አለችኝ...
ወደ ቤቴ ገባሁ...
የዚህ ሙዚቃ ምንጭ የት ነው?... ማድመጤን ቀጠልኩ... ዜማው አልተለወጠም... ውበቱ ግን አይሰለችም... ጣዕሙ ሁሌም አዲስ ነው...
ግራ ሲገባኝ ጆሮዬን ደፈንኩ... ግጥም አድርጌ በትራስ አፈንኩት... የሙዚቃው ጥራት ጨመረ... ጆሮዬን ከግንዱ ጋር ጨቆንኩ... ድምጹ ጭራሽ እየጎላ መጣ...
በዚህ መሃል አንድ ድምጽ በሙዚቃው ስልት ውስጥ ሆኖ በለሆሳስ አናገረኝ...
ድምጹን አውቀዋለሁ... ያንተ ያለህ!... የራሴ ድምጽ ነው...
አንድ ቃል ብቻ ነው ደጋግሞ የሚነገረኝ...
'ትተኸኛል'...
'ትተኸኛል'...
'ትተኸኛል'...
እንደ ሰማሁት ሲያውቅ እየሳሳ ሄደ... እየራቀ... እየራቀ...
____
✨ ለራሳችሁ ጊዜ ከሰጣችሁ ስንት ጊዜ ሆነ?... ከራሳችሁ ጋር ቁጭ ካላችሁ ስንት ጊዜ አለፈ?... በወግ ካወጋችሁ፣ ከተደማመጣችሁ፣ ሰከን ብላችሁ ከመከራችሁ - ምን ያህል ዓመት ሆነ?... ✨
____
“Nowhere you can go is more peaceful—more free of interruptions—than your own soul.” ~ Marcus Aurelius
___
@bridgethoughts
🥰8🔥4❤2🙏2
🌿
🌿
🌿
ፍቅሬን እንዴት ማሳየት እንዳለብኝ ተለማምጄ ሳልጨርስ ሄደች...
በልቤ ውስጥ ያለው ነበልባል በቃል ተሰርቶ ወደጆሮዋ ሊፈስ ይቃትት ነበር... የመውደዴ ብርታት በቃል አክናፍ በርሮ እዝነ ልቡናዋን ሊያንኳኳ ይጓጓ ነበር... ጎርፍ የመውረጃ ፈለጉን እንደሚያስስ... ሕፃን የእናቱን ጡት ፍለጋ በጨለማ እንደሚዳብስ...
በውስጤ የታመቁት ቃላት ከውክብክቡ ዓለም አይደሉምና በተራ ድምጽ አይወከሉም - በጸጥታ ይነግሳሉ እንጂ... መሻቴ ከአፍዓ ገጽዋ አልተቀዱምና ለሙገሳ የተሰሩ ፊደላት አልሰጠሁዋትም - በጥልቅ ዝምታዬ ውስጥ የሚጓደዱትን እንጂ...
[በቅጽበታት መሃል እንደሚገኝ ትንፋሽ... ነፍሶች እንደሚያወጉበት ድምጽ የሌለው ፈሳሽ...]
አዎን - እኔ ይህን ጸጥታ ወደ ቋንቋ መለወጥ ገና አልተማርኩም ነበር... እርሷም እንዲህ ዓይነት ቋንቋ ሰምታ አታውቅም ነበር...
ሄደች...
እውነቱን ከመግለጼ በፊት ተጨለጠች...
[ፍቅር]
የምሰጣት - የኔ 'ምለው፣ የምትነፍገኝ - የእርሷ የሆነው እንዳልሆነ ሳልነግራት በነነች...
የዘላለማዊው ኃይል መስታወት፣ በሁለንታ ላይ የሚፈስ የኃይል ዥረት መሆኑን ሳላስታውሳት ዱካዋን አጠፋች... ዳናዋን ሰወረች...
ሄደች... የአካል ኑረቷን ከለለች...
[አዎን ሄዳለች - ግን ደግሞ አልሄደችም...]
መቅረቷ በሌላ ቅርጽ መኖር ሆኖ ቀጥሏል... አካሏን እንጂ በኔ ዓለም ውስጥ ያነቃችውን ፍቅር በቀላሉ ማጥፋት ስላልተቻላት በመንፈስ ነብራለች...
🌿
ፍቅሯ ወደ ኁልቆ አልባው ዓለም ሲያሻግረኝ ከፈራሽ ገላዋ ብፋታም በእርስዋ ሰበብ የተሰጠኝ ማሕተም የሃገሩን ኬላ ሁሉ የሚያሻግር አርነት ሰጥቶኛል...
[በእውኑ የተወኝ ምኗ ነው?...]
___
@bridgethoughts
🌿
🌿
ፍቅሬን እንዴት ማሳየት እንዳለብኝ ተለማምጄ ሳልጨርስ ሄደች...
በልቤ ውስጥ ያለው ነበልባል በቃል ተሰርቶ ወደጆሮዋ ሊፈስ ይቃትት ነበር... የመውደዴ ብርታት በቃል አክናፍ በርሮ እዝነ ልቡናዋን ሊያንኳኳ ይጓጓ ነበር... ጎርፍ የመውረጃ ፈለጉን እንደሚያስስ... ሕፃን የእናቱን ጡት ፍለጋ በጨለማ እንደሚዳብስ...
በውስጤ የታመቁት ቃላት ከውክብክቡ ዓለም አይደሉምና በተራ ድምጽ አይወከሉም - በጸጥታ ይነግሳሉ እንጂ... መሻቴ ከአፍዓ ገጽዋ አልተቀዱምና ለሙገሳ የተሰሩ ፊደላት አልሰጠሁዋትም - በጥልቅ ዝምታዬ ውስጥ የሚጓደዱትን እንጂ...
[በቅጽበታት መሃል እንደሚገኝ ትንፋሽ... ነፍሶች እንደሚያወጉበት ድምጽ የሌለው ፈሳሽ...]
አዎን - እኔ ይህን ጸጥታ ወደ ቋንቋ መለወጥ ገና አልተማርኩም ነበር... እርሷም እንዲህ ዓይነት ቋንቋ ሰምታ አታውቅም ነበር...
ሄደች...
እውነቱን ከመግለጼ በፊት ተጨለጠች...
[ፍቅር]
የምሰጣት - የኔ 'ምለው፣ የምትነፍገኝ - የእርሷ የሆነው እንዳልሆነ ሳልነግራት በነነች...
የዘላለማዊው ኃይል መስታወት፣ በሁለንታ ላይ የሚፈስ የኃይል ዥረት መሆኑን ሳላስታውሳት ዱካዋን አጠፋች... ዳናዋን ሰወረች...
ሄደች... የአካል ኑረቷን ከለለች...
[አዎን ሄዳለች - ግን ደግሞ አልሄደችም...]
መቅረቷ በሌላ ቅርጽ መኖር ሆኖ ቀጥሏል... አካሏን እንጂ በኔ ዓለም ውስጥ ያነቃችውን ፍቅር በቀላሉ ማጥፋት ስላልተቻላት በመንፈስ ነብራለች...
🌿
ፍቅሯ ወደ ኁልቆ አልባው ዓለም ሲያሻግረኝ ከፈራሽ ገላዋ ብፋታም በእርስዋ ሰበብ የተሰጠኝ ማሕተም የሃገሩን ኬላ ሁሉ የሚያሻግር አርነት ሰጥቶኛል...
[በእውኑ የተወኝ ምኗ ነው?...]
___
@bridgethoughts
🥰5❤3❤🔥2
የቁጣ ግራ ቀኝ...
.
.
.
[፩]
___
ሰዎች በቁጡነት ይወቅሱሃል እንጂ ያስቆጣህን ሰው ነውር፣ አልያም ለኮስ ያደረገህን ውስጠ ነገር ልብ ብለው አይመረምሩም... በሌላ አገላለጽ ያስቆጡሃል እንጂ ያስቆጣህን ጸባይ ጥመት በአንተ ቦታ ቆመው አይመዝኑም...
በምን ተቆጣህ?... No one cares [እርሱ ያንተ ጉዳይ ብቻ ነው]... ሌላው ይህን ለመጠየቅ ጊዜ አያጠፋም... ለራሱ ሲሆን ትንሽ ነገር የሚበቃው ሁሉ አንተ ላይ ሲደርስ አንዳች አይሰማውም...
ብዙ ሰዎች በእነርሱ ሰበብ ባይሆንም እንኳ ተናደህ ሲያገኙህ ሊረዱህ ከመሞከር ይልቅ ምቾታቸውን እንደነሳህ ሊያስቡ ይችላሉ... ወይ ደግሞ እነርሱ ቢሆኑ ፈጽሞ የማያደርጉትን ነገር በምክር መልክ ሊለግሱህ ይሞክራሉ...
ንዴት፣ ብስጭት፣ ቁጣ ወዘተ - ጥሩ ነገር እንዳልሆኑ እኮ ታውቃለህ... ስሜትን መግዛት መሰረታዊ የኑሮ መርህ እንደሆነም አይጠፋህም... ግን ደግሞ ስሜት አለህ... ሰውም ነህ... ነገሮች ከገደባቸው ሲሻገሩ ምላሽ መስጠት መጀመርህ ተጠባቂ ነው...
[ብስለት ማለት ለነገሮች ስሜት ማጣት ማለት አይደለም - ሚዛን መጠበቅ እንጂ...ብልህነት ይህን ስሜት መቆጣጠር እንጂ ዜሮ ማድረግ አይደለም... ምላሹን መመጠን እንጂ እንዳልተሰማው መሆን አይደለም... 'ምንም አይሰማኝም' ምናምን የሚል ደረቅ ስታገኝ ታዝበህ እለፈው...]
አንዳንዱ ገፍቶ፣ ገፋፍቶ፣ ገፍትሮ ከብስጭት ጫፍ ያደርስህና React ማድረግ ስትጀምር በተራው መናደድ ይጀምራል... እንዴ 'ቅቤ እየቀባህ' ነበር እንዴ የመሰለው?...
ለመከፋትህ፣ ለብስጭትህ፣ ለንዴትህ ነዳጅ ሲጨምር መቆየቱን ሳይሆን በነዳጁ ብዛት መቀጣጠል መጀመርህን ነው ሰው የሚያስተውለው... ነገሩ የሆነበትን ምክንያት ሳይሆን የሆነውን ክስተት ብቻ ነው የሚመለከተው... ይህ ዓይነት ሰው ለፍርድ ቅርብ ነው... የደረሰበት ላይ ሆኖ ውሳኔ ይሰጣል... ከመነሻው ደርሶ አይመረምርም... ከመድረሻው ዘልቆም አያመሳክርም... ጭራሽ ሰው መሆንህን ይረሳዋል... ስሜትም ያለህ አይመስለው...
በእርሱ ቤት ሲቀዳልህ የቆየው ነዳጅ ተራ ውሃ ነበር... 'ደግሞ ይሄ ምን ያናድዳል?' ይልሃል... [አይገርምም?... እዚህ ጥግ ድረስ ለሌሎች ስሜት እናጣለን]... 'አካበድከው' ይልሃል... 'Emotional intelligence ላይ መስራት አለብህ' ምናምን የሚልም አይጠፋም... በሌላ ቀን ያንተን ቁራጭ በማትደርስ እንከን ሲብከነከን ብታገኘው ታዲያ አይግረምህ...
[እኛ ከሌሎች ስንክሳር በላይ የራሳችን ስንጥር ዘልቆ የሚሰማን ግለኞች ነን]
መረሳት የሌለበት...
ሁላችንም ቅኝታችን ለየቅል ነው... ተመሳሳይ ነገሮች እኩል ስሜት አይሰጡንም... አንድ ዓይነት ነገሮች እኩል አይነዝሩንም... ለብግነትህ ምክንያት የሆነ ነገር ለእኔ ቁብ ላይሰጠኝ ይችላል... እኔን ያስደነገጠ ጉዳይ አንዳች ስሜት አይፈጥርብህ ይሆናል... [በዚህ ረገድ ልዩ ልዩ ነን]
___
[፪]
___
ቁጣህን በማሰሮ ውስጥ እንደሚንተከተክ ወተት ብታፍነው ጊዜው እየገፋ ሲመጣ መገንፈሉ አይቀርም... ስለዚህም መተንፈስ አለበት... የታፈነ፣ የታመቀ፣ የተወጠረ ነገር በራሱም ሆነ በሌላው ላይ ጉዳት ከማምጣት አይመለስም...
"ድስት ቢገነፍል የሚያቆሽሸው ራሱን ነው" ቢባልም ፍንጥርጣሪው ልብስ አያበላሽም ማለት አይቻልም...
እርግጥ ነው - ቁጣ የማይፈለግ ስሜት ነው... ከዚያ በላይ ግን ቁጣን አምቆ መቆየት እጅግ አደገኛ ነገር ነው... Buddha እንዳለው:
“Holding on to anger is like grasping a hot coal with the intent of throwing it at someone else; you are the one who gets burned.”
ለዚህም ሲባል ቁጣን በልኩ ማስተናገድ፣ ከልብ ማዳመጥ፣ ምንጩን መመርመር፣ ቆስቋሽ ሰበቡን መለየት፣ ከምንም በላይ ደግሞ [በራስ ላይ መንቃት] እጅግ ጠቃሚ ይሆናል...
በመሰረቱ ስሜቶቻችን ጠላቶቻችን አይደሉም - ምልክቶች እንጂ... አንዳንዴ ቁጣ የጥልቁ እኛነታችን ባሕሪያዊ ጥላ ሊሆን ይችላል... በስውሩ የአዕምሮአችን ክፍል ውስጥ ያለውን ጠቋሚ መስታወት... በዚህ አውድ መምህር ሲሆን በቅጡ ለማያነበው ደግሞ የአዕምሮ ገዢ ሆኖ እውነታን ይከልላል - ያስክዳልም...
እናም ስሜቶቻችንን በማፈን ጠቢብ አንሆንም... በአንክሮ በማዳመጥ እንማርባቸዋለን እንጂ...
_
እናም እንዲህ እንላለን...
ለሌሎች ብሽቀት ምክንያት አለመሆን ደግ ነገር ነው... ሲናደዱ ለመረዳት መሞከር ደግሞ ሩሕሩሕነት ነው... ስሜት አለማመቅ ጠቃሚ ነገር ነው... በስሜት መስታወት ውስጥ ውስጠትን ማየት ደግሞ ዘላቂ መላ...
___
እነሆ ነገራችንን በሚዛን የሚጠቀልልልን የጠቢብ ቃል...
___
“Anybody can become angry — that is easy. But to be angry with the right person, to the right degree, at the right time, for the right purpose, and in the right way—that is not within everybody's power and is not easy.” – Aristotle
___
@bridgethoughts
.
.
.
[፩]
___
ሰዎች በቁጡነት ይወቅሱሃል እንጂ ያስቆጣህን ሰው ነውር፣ አልያም ለኮስ ያደረገህን ውስጠ ነገር ልብ ብለው አይመረምሩም... በሌላ አገላለጽ ያስቆጡሃል እንጂ ያስቆጣህን ጸባይ ጥመት በአንተ ቦታ ቆመው አይመዝኑም...
በምን ተቆጣህ?... No one cares [እርሱ ያንተ ጉዳይ ብቻ ነው]... ሌላው ይህን ለመጠየቅ ጊዜ አያጠፋም... ለራሱ ሲሆን ትንሽ ነገር የሚበቃው ሁሉ አንተ ላይ ሲደርስ አንዳች አይሰማውም...
ብዙ ሰዎች በእነርሱ ሰበብ ባይሆንም እንኳ ተናደህ ሲያገኙህ ሊረዱህ ከመሞከር ይልቅ ምቾታቸውን እንደነሳህ ሊያስቡ ይችላሉ... ወይ ደግሞ እነርሱ ቢሆኑ ፈጽሞ የማያደርጉትን ነገር በምክር መልክ ሊለግሱህ ይሞክራሉ...
ንዴት፣ ብስጭት፣ ቁጣ ወዘተ - ጥሩ ነገር እንዳልሆኑ እኮ ታውቃለህ... ስሜትን መግዛት መሰረታዊ የኑሮ መርህ እንደሆነም አይጠፋህም... ግን ደግሞ ስሜት አለህ... ሰውም ነህ... ነገሮች ከገደባቸው ሲሻገሩ ምላሽ መስጠት መጀመርህ ተጠባቂ ነው...
[ብስለት ማለት ለነገሮች ስሜት ማጣት ማለት አይደለም - ሚዛን መጠበቅ እንጂ...ብልህነት ይህን ስሜት መቆጣጠር እንጂ ዜሮ ማድረግ አይደለም... ምላሹን መመጠን እንጂ እንዳልተሰማው መሆን አይደለም... 'ምንም አይሰማኝም' ምናምን የሚል ደረቅ ስታገኝ ታዝበህ እለፈው...]
አንዳንዱ ገፍቶ፣ ገፋፍቶ፣ ገፍትሮ ከብስጭት ጫፍ ያደርስህና React ማድረግ ስትጀምር በተራው መናደድ ይጀምራል... እንዴ 'ቅቤ እየቀባህ' ነበር እንዴ የመሰለው?...
ለመከፋትህ፣ ለብስጭትህ፣ ለንዴትህ ነዳጅ ሲጨምር መቆየቱን ሳይሆን በነዳጁ ብዛት መቀጣጠል መጀመርህን ነው ሰው የሚያስተውለው... ነገሩ የሆነበትን ምክንያት ሳይሆን የሆነውን ክስተት ብቻ ነው የሚመለከተው... ይህ ዓይነት ሰው ለፍርድ ቅርብ ነው... የደረሰበት ላይ ሆኖ ውሳኔ ይሰጣል... ከመነሻው ደርሶ አይመረምርም... ከመድረሻው ዘልቆም አያመሳክርም... ጭራሽ ሰው መሆንህን ይረሳዋል... ስሜትም ያለህ አይመስለው...
በእርሱ ቤት ሲቀዳልህ የቆየው ነዳጅ ተራ ውሃ ነበር... 'ደግሞ ይሄ ምን ያናድዳል?' ይልሃል... [አይገርምም?... እዚህ ጥግ ድረስ ለሌሎች ስሜት እናጣለን]... 'አካበድከው' ይልሃል... 'Emotional intelligence ላይ መስራት አለብህ' ምናምን የሚልም አይጠፋም... በሌላ ቀን ያንተን ቁራጭ በማትደርስ እንከን ሲብከነከን ብታገኘው ታዲያ አይግረምህ...
[እኛ ከሌሎች ስንክሳር በላይ የራሳችን ስንጥር ዘልቆ የሚሰማን ግለኞች ነን]
መረሳት የሌለበት...
ሁላችንም ቅኝታችን ለየቅል ነው... ተመሳሳይ ነገሮች እኩል ስሜት አይሰጡንም... አንድ ዓይነት ነገሮች እኩል አይነዝሩንም... ለብግነትህ ምክንያት የሆነ ነገር ለእኔ ቁብ ላይሰጠኝ ይችላል... እኔን ያስደነገጠ ጉዳይ አንዳች ስሜት አይፈጥርብህ ይሆናል... [በዚህ ረገድ ልዩ ልዩ ነን]
___
[፪]
___
ቁጣህን በማሰሮ ውስጥ እንደሚንተከተክ ወተት ብታፍነው ጊዜው እየገፋ ሲመጣ መገንፈሉ አይቀርም... ስለዚህም መተንፈስ አለበት... የታፈነ፣ የታመቀ፣ የተወጠረ ነገር በራሱም ሆነ በሌላው ላይ ጉዳት ከማምጣት አይመለስም...
"ድስት ቢገነፍል የሚያቆሽሸው ራሱን ነው" ቢባልም ፍንጥርጣሪው ልብስ አያበላሽም ማለት አይቻልም...
እርግጥ ነው - ቁጣ የማይፈለግ ስሜት ነው... ከዚያ በላይ ግን ቁጣን አምቆ መቆየት እጅግ አደገኛ ነገር ነው... Buddha እንዳለው:
“Holding on to anger is like grasping a hot coal with the intent of throwing it at someone else; you are the one who gets burned.”
ለዚህም ሲባል ቁጣን በልኩ ማስተናገድ፣ ከልብ ማዳመጥ፣ ምንጩን መመርመር፣ ቆስቋሽ ሰበቡን መለየት፣ ከምንም በላይ ደግሞ [በራስ ላይ መንቃት] እጅግ ጠቃሚ ይሆናል...
በመሰረቱ ስሜቶቻችን ጠላቶቻችን አይደሉም - ምልክቶች እንጂ... አንዳንዴ ቁጣ የጥልቁ እኛነታችን ባሕሪያዊ ጥላ ሊሆን ይችላል... በስውሩ የአዕምሮአችን ክፍል ውስጥ ያለውን ጠቋሚ መስታወት... በዚህ አውድ መምህር ሲሆን በቅጡ ለማያነበው ደግሞ የአዕምሮ ገዢ ሆኖ እውነታን ይከልላል - ያስክዳልም...
እናም ስሜቶቻችንን በማፈን ጠቢብ አንሆንም... በአንክሮ በማዳመጥ እንማርባቸዋለን እንጂ...
_
እናም እንዲህ እንላለን...
ለሌሎች ብሽቀት ምክንያት አለመሆን ደግ ነገር ነው... ሲናደዱ ለመረዳት መሞከር ደግሞ ሩሕሩሕነት ነው... ስሜት አለማመቅ ጠቃሚ ነገር ነው... በስሜት መስታወት ውስጥ ውስጠትን ማየት ደግሞ ዘላቂ መላ...
___
እነሆ ነገራችንን በሚዛን የሚጠቀልልልን የጠቢብ ቃል...
___
“Anybody can become angry — that is easy. But to be angry with the right person, to the right degree, at the right time, for the right purpose, and in the right way—that is not within everybody's power and is not easy.” – Aristotle
___
@bridgethoughts
❤8🥰2🙏2💯1💊1
.
.
.
እነርሱ - በቅኝ ግዛት ቀንበር ስር ቆይተው የባርነት አባዜ ባይተዋቸው ወራሪዎቻቸው የፀነሱት 'ስምምነት' ጸንቶ ይግዛን ይሉናል...
እኛ - በአባቶቻችን የደም ዋጋ በነፃ ሃገር ተወልደን ጌትነት ስለተቀዳጀን በራሳችን ጉዳይ ላይ ለመወሰን እኛ እንበቃለን እንላለን...
The difference is visible!!
ኢትዮጵያ...
[አባይ ወንዟና የታሪክ ጓዟ ጎስቋላ ያደረጓት ሃገር ነች...]
ዛሬ በአባይ ወንዟ ላይ ሰልጥናለች - ነገ በታሪክ ሰበብ የተጣባትን ቀውስ ትፈታለች...
.
.
.
አዎን...
📯 የሚጀምር ትውልድ አባል መሆን ደስ ይላል!
📯 ሂደት የሚመራ ትውልድ አካል መሆን ደስ ይላል!
📯 የሚጨርስ ትውልድ አባል መሆን ደስ ይላል!
___
@bridgethoughts
.
.
እነርሱ - በቅኝ ግዛት ቀንበር ስር ቆይተው የባርነት አባዜ ባይተዋቸው ወራሪዎቻቸው የፀነሱት 'ስምምነት' ጸንቶ ይግዛን ይሉናል...
እኛ - በአባቶቻችን የደም ዋጋ በነፃ ሃገር ተወልደን ጌትነት ስለተቀዳጀን በራሳችን ጉዳይ ላይ ለመወሰን እኛ እንበቃለን እንላለን...
The difference is visible!!
ኢትዮጵያ...
[አባይ ወንዟና የታሪክ ጓዟ ጎስቋላ ያደረጓት ሃገር ነች...]
ዛሬ በአባይ ወንዟ ላይ ሰልጥናለች - ነገ በታሪክ ሰበብ የተጣባትን ቀውስ ትፈታለች...
.
.
.
አዎን...
📯 የሚጀምር ትውልድ አባል መሆን ደስ ይላል!
📯 ሂደት የሚመራ ትውልድ አካል መሆን ደስ ይላል!
📯 የሚጨርስ ትውልድ አባል መሆን ደስ ይላል!
___
@bridgethoughts
❤12🔥3🙏1💯1
✨Dildiy's New Year Reflection✨
As the old year dissolves into silence, may we step into the new one not as travelers bound by calendars, but as seekers of the infinite—sparks in the great mystery of existence.
This year, let us see beyond the veils of yesterday and tomorrow, awakening to the sacred rhythm of Now.
May our laughter become cosmic music, our tears cleanse illusions, and our love expand like starlight across the sky of being.
Together, let us walk as companions of the unseen, remembering that every breath is a doorway, every meeting a mirror, and every step a return home—to the timeless truth within.
For us, a New Year is not the measure of time, but the unfolding of consciousness.
___
@bridgethoughts
As the old year dissolves into silence, may we step into the new one not as travelers bound by calendars, but as seekers of the infinite—sparks in the great mystery of existence.
This year, let us see beyond the veils of yesterday and tomorrow, awakening to the sacred rhythm of Now.
May our laughter become cosmic music, our tears cleanse illusions, and our love expand like starlight across the sky of being.
Together, let us walk as companions of the unseen, remembering that every breath is a doorway, every meeting a mirror, and every step a return home—to the timeless truth within.
For us, a New Year is not the measure of time, but the unfolding of consciousness.
___
@bridgethoughts
🥰7❤4👍2🔥2👌2
✨አልከራማ - ባለቤት አልባው ጎጆ ✨
.
.
.
በቤንሻንጉል ኮረብቶች፣ በበርታዎች መንደር ውስጥ - የየትኛውንም ትውልድ አንደበት ትንግርት የሚያስብል ተግባር ይከወናል... በጸጥታ፣ በስውር፣ በድብቅ...
ነገሩ ምን መሰላችሁ?...
በርታዎች በነፋሻማዎቹ መመላለሻዎች ዳርቻ፣ ከተጓዥ መተላለፊያ መንገዶች ግራና ቀኝ ትናንሽ ቤቶችን ይገነባሉ... ለመኖሪያ አይደለም፣ ለንግድም አይደለም፣ ለመንገደኛ እንጂ...
ተሾመ ገ/ሥላሴ 'የባሕር ጠብታ' በተሰኘ የግጥም መድብሉ መግቢያ ላይ [በርታዎች በዚያች ቤት ውስጥ] "... ምግብ፣ ውሃ፣ የመስገጃ ምንጣፍ፣ ቡናና ከሰል ያስቀምጣሉ... ቤቱ የማንም አይደለም... የእንግዳ ቤት ነው... የራበው መንገደኛ [ምግብ] በልቶ፣ [ውሃ ጠጥቶ]፣ አርፎ ይወጣበታል... ማንንም ማመስገን አይጠበቅበትም..." በማለት በሁለት መስመር ብርታት የባሕሩን ግማድ ያሳየናል...
የቤቱ ስም 'አልከራማ' ይባላል... እናንተ 'የአብርሐም ቤት' ልትሉት ትችላላችሁ... የልግስና ታዛ፣ የደግነት አምድ ቢባልም ትርጉሙ ያው ነው... ትልቁ ቁምነገር ግን በቤቱ ውስጥ የምናገኘው ምግብና መጠጥ አይደለም - ከዚያ ጀርባ ያለው የመንፈስ ንጽሕና እንጂ... ባለቤት አልባ ቤት፣ ቀኙ 'ሚሰጠውን ግራው የማያይበት ልባም፣ ምስጋና ሽቶ ከታዛው ያልተቀመጠ ለጋሽ፣ በጸጥታ - በዝምታ - በአርምሞ የሚቸር ስጦታ... በክብረት - በከፍታ - በምልዓት የሚመለስ ውለታ...
[አዎን - ዛሬም ድረስ መንገድ መንገደኝነቱን አልተወም... ተጓዥም ደረስኩ ብሎ መጓጓዝ አልቀረም...]
አልከራማ ከቤትነት የምትሻገር ከፍታ ናት... የጥልቅ ፍልስፍና ሰንዱቅ፣ የልግስና ምጡቅ፣ የሰብዓዊነት ረቂቅ ናት... አማናዊው ስጦታ በእውቅና የማይመተር፣ በውለታ የማይታሰር፣ መቀበል ሳይጠብቁ መቸር መሆኑንም ታስተምረናለች...
🔥 መስጠት ግን ሰጪ ሆኖ አለመገኘት - መሄድ...
🔥 መድከም ግን ድካምን አለማወጅ - ራስ መካድ...
🔥 ማስቀመጥ ግን ጠባቂ አለመፈለግ - ማመን...
[ይገርማል!!...]
እንኳን ማዕድ አኑረህበት የእከሌ የማትለው ባዶ ቤት በግላጭ መገኘቱ፣ ማሕበረሰቡ ይሆነኝ ብሎ አልከራማን መገንባቱ - ብቻውን ድንቅ ነገር ነው...
አዋጅ ሳይነገር ምንም በማይደረግባት ሃገር ውስጥ ድምጹን ሳያሰማ ሹልክ ብሎ ገብቶ - ለሆድ የበሰለውን፣ ለጥም የሚያረካውን የሚያስቀምጥ ንጹህ ልብ መገኘቱም አስገራሚ ነገር ነው...
[እስኪ አስበው...]
🌼 ከተሜ እኮ ለለቅሶ ቤት እንኳ እራት የሚወስደው የዕድር ሰብሳቢዋ ስታዘው ነው... እነርሱን ማን አስገደዳቸው?...
🌼 እዚህ ሃገር በራስ ድልም ሆነ በሌላው ድካም ስሜ ካልገነነ ባይ ብዙ ነው... መደበቅን ለእነርሱ ማን ነገራቸው?...
🌼 በተስኪያን ተገኝቶ 'ምጽዋቴ በድምጽ ማጉያ አልተነገረም' ብሎ የሚከፋው፣ በደመወዝ እየሰራ ውለታ የዋለ የሚመስለው፣ ያበደረህን መልሰህ እንኳ አኮቴት የሚጠብቀው፣ ወዘተ - እጅግ ብዙ ነው... ውለታ ሳይጠብቁ ቅንነት መዋልን ማን አስተማራቸው?...
[ልብ አድርግ...]
የለመነንን አይተን ያለንን መስጠትና ለማያውቁት ሰው በማይታወቁበት ሁኔታ ደግ መሆን የተለያዩ ነገሮች ናቸው... በሌህበት ድርጊትህ ብቻ ሲገኝ 'ጠላቴ' የምትለውን ሰው ሳይቀር ሊጠቅም ይችላል... ቤትህ መጥቶ የለመነህ ግን በአኳኋኑ ብቻ እጅህን ሊያሰበሰብ ይችላል...
[አልከራማ... የደግነት ማማ!!]
ይህ ዓይነቱ ልምምድ በሱፊዎች መንደር የተለመደ ነው... እነርሱ ጋ መንገደኞች ስውር አገልጋይ አላቸው... በበረሃ እዚህና እዚያ በተሰሩ ታዛዎች፣ በከተሞች ውብ ተደርገው በተሰሩ ማረፊያዎች ይስተናገዳሉ... ማዕድና ቀዝቃዛ ውሃም ያገኛሉ... [አይከፍሉም - ሻጭ ከባንኮኒው የለም... ስም አይጠየቁም - ተቆጣጣሪው ከበር አልቆመም...] ለእነርሱ የማያውቁትን እንግዳ ማስተናገድ መለኮትን በሰው አምሳል ማገልገል ነው...
አዎን - ታላቁ ስጦታ ምላሽ የማይጠብቁበት ነው... ይህ ችሮታ ተናጥሎን አያውቅም - ተጓዥ እና ለጋሽ፣ መንገድና ታዛ፣ [ማዕድ ያኖሩ ልቦች፣ የተቀበሉም እጆች] - በአንድ ነጠላ ክር ይዳወራሉ... በፍቅር!!...
[ፍቅርን ከመስጠት በላይ ዕዳ አይኑርባችሁ!!...]
___
ወጋችንን ከሱፊዎች መንደር በተዋስናት ውብ መስመር እንቋጭ:
“The water does not drink itself, the tree does not eat its own fruit, the sun does not shine for itself. To live is to give.”
___
@bridgethoughts
.
.
.
በቤንሻንጉል ኮረብቶች፣ በበርታዎች መንደር ውስጥ - የየትኛውንም ትውልድ አንደበት ትንግርት የሚያስብል ተግባር ይከወናል... በጸጥታ፣ በስውር፣ በድብቅ...
ነገሩ ምን መሰላችሁ?...
በርታዎች በነፋሻማዎቹ መመላለሻዎች ዳርቻ፣ ከተጓዥ መተላለፊያ መንገዶች ግራና ቀኝ ትናንሽ ቤቶችን ይገነባሉ... ለመኖሪያ አይደለም፣ ለንግድም አይደለም፣ ለመንገደኛ እንጂ...
ተሾመ ገ/ሥላሴ 'የባሕር ጠብታ' በተሰኘ የግጥም መድብሉ መግቢያ ላይ [በርታዎች በዚያች ቤት ውስጥ] "... ምግብ፣ ውሃ፣ የመስገጃ ምንጣፍ፣ ቡናና ከሰል ያስቀምጣሉ... ቤቱ የማንም አይደለም... የእንግዳ ቤት ነው... የራበው መንገደኛ [ምግብ] በልቶ፣ [ውሃ ጠጥቶ]፣ አርፎ ይወጣበታል... ማንንም ማመስገን አይጠበቅበትም..." በማለት በሁለት መስመር ብርታት የባሕሩን ግማድ ያሳየናል...
የቤቱ ስም 'አልከራማ' ይባላል... እናንተ 'የአብርሐም ቤት' ልትሉት ትችላላችሁ... የልግስና ታዛ፣ የደግነት አምድ ቢባልም ትርጉሙ ያው ነው... ትልቁ ቁምነገር ግን በቤቱ ውስጥ የምናገኘው ምግብና መጠጥ አይደለም - ከዚያ ጀርባ ያለው የመንፈስ ንጽሕና እንጂ... ባለቤት አልባ ቤት፣ ቀኙ 'ሚሰጠውን ግራው የማያይበት ልባም፣ ምስጋና ሽቶ ከታዛው ያልተቀመጠ ለጋሽ፣ በጸጥታ - በዝምታ - በአርምሞ የሚቸር ስጦታ... በክብረት - በከፍታ - በምልዓት የሚመለስ ውለታ...
[አዎን - ዛሬም ድረስ መንገድ መንገደኝነቱን አልተወም... ተጓዥም ደረስኩ ብሎ መጓጓዝ አልቀረም...]
አልከራማ ከቤትነት የምትሻገር ከፍታ ናት... የጥልቅ ፍልስፍና ሰንዱቅ፣ የልግስና ምጡቅ፣ የሰብዓዊነት ረቂቅ ናት... አማናዊው ስጦታ በእውቅና የማይመተር፣ በውለታ የማይታሰር፣ መቀበል ሳይጠብቁ መቸር መሆኑንም ታስተምረናለች...
🔥 መስጠት ግን ሰጪ ሆኖ አለመገኘት - መሄድ...
🔥 መድከም ግን ድካምን አለማወጅ - ራስ መካድ...
🔥 ማስቀመጥ ግን ጠባቂ አለመፈለግ - ማመን...
[ይገርማል!!...]
እንኳን ማዕድ አኑረህበት የእከሌ የማትለው ባዶ ቤት በግላጭ መገኘቱ፣ ማሕበረሰቡ ይሆነኝ ብሎ አልከራማን መገንባቱ - ብቻውን ድንቅ ነገር ነው...
አዋጅ ሳይነገር ምንም በማይደረግባት ሃገር ውስጥ ድምጹን ሳያሰማ ሹልክ ብሎ ገብቶ - ለሆድ የበሰለውን፣ ለጥም የሚያረካውን የሚያስቀምጥ ንጹህ ልብ መገኘቱም አስገራሚ ነገር ነው...
[እስኪ አስበው...]
🌼 ከተሜ እኮ ለለቅሶ ቤት እንኳ እራት የሚወስደው የዕድር ሰብሳቢዋ ስታዘው ነው... እነርሱን ማን አስገደዳቸው?...
🌼 እዚህ ሃገር በራስ ድልም ሆነ በሌላው ድካም ስሜ ካልገነነ ባይ ብዙ ነው... መደበቅን ለእነርሱ ማን ነገራቸው?...
🌼 በተስኪያን ተገኝቶ 'ምጽዋቴ በድምጽ ማጉያ አልተነገረም' ብሎ የሚከፋው፣ በደመወዝ እየሰራ ውለታ የዋለ የሚመስለው፣ ያበደረህን መልሰህ እንኳ አኮቴት የሚጠብቀው፣ ወዘተ - እጅግ ብዙ ነው... ውለታ ሳይጠብቁ ቅንነት መዋልን ማን አስተማራቸው?...
[ልብ አድርግ...]
የለመነንን አይተን ያለንን መስጠትና ለማያውቁት ሰው በማይታወቁበት ሁኔታ ደግ መሆን የተለያዩ ነገሮች ናቸው... በሌህበት ድርጊትህ ብቻ ሲገኝ 'ጠላቴ' የምትለውን ሰው ሳይቀር ሊጠቅም ይችላል... ቤትህ መጥቶ የለመነህ ግን በአኳኋኑ ብቻ እጅህን ሊያሰበሰብ ይችላል...
[አልከራማ... የደግነት ማማ!!]
ይህ ዓይነቱ ልምምድ በሱፊዎች መንደር የተለመደ ነው... እነርሱ ጋ መንገደኞች ስውር አገልጋይ አላቸው... በበረሃ እዚህና እዚያ በተሰሩ ታዛዎች፣ በከተሞች ውብ ተደርገው በተሰሩ ማረፊያዎች ይስተናገዳሉ... ማዕድና ቀዝቃዛ ውሃም ያገኛሉ... [አይከፍሉም - ሻጭ ከባንኮኒው የለም... ስም አይጠየቁም - ተቆጣጣሪው ከበር አልቆመም...] ለእነርሱ የማያውቁትን እንግዳ ማስተናገድ መለኮትን በሰው አምሳል ማገልገል ነው...
አዎን - ታላቁ ስጦታ ምላሽ የማይጠብቁበት ነው... ይህ ችሮታ ተናጥሎን አያውቅም - ተጓዥ እና ለጋሽ፣ መንገድና ታዛ፣ [ማዕድ ያኖሩ ልቦች፣ የተቀበሉም እጆች] - በአንድ ነጠላ ክር ይዳወራሉ... በፍቅር!!...
[ፍቅርን ከመስጠት በላይ ዕዳ አይኑርባችሁ!!...]
___
ወጋችንን ከሱፊዎች መንደር በተዋስናት ውብ መስመር እንቋጭ:
“The water does not drink itself, the tree does not eat its own fruit, the sun does not shine for itself. To live is to give.”
___
@bridgethoughts
❤7👍4❤🔥1🔥1🥰1💯1
ሰላም ወዳጆች
--
ከዚህ ቀደም መንደራችን ውስጥ የሚገኙ ሦስት ምርጥ Digital magazines አስተዋውቄያችሁ እንደነበር አትዘነጉም… ዛሬ ውብ የስነጽሑፍ ስራዎች የሚስተናገዱበት ሌላ መጽሔት ላስተዋውቃችሁ ነው…
ቀለም ይባላል…
በስነጽሑፍ፣ በፍልስፍና፣ በግለ-ታሪክና በወጎች ያጌጠ መጽሔት ነው…
እስኪ ጎራ ብላችሁ፣ አዲሱን ቅጽ 1 እትም 3 መጽሔትና ሌሎች ቁምነገሮችን ከቀደሙ ህትመቶቻቸው ጋር ተቋደሱ…
https://t.me/kelemofficial
--
ከዚህ ቀደም መንደራችን ውስጥ የሚገኙ ሦስት ምርጥ Digital magazines አስተዋውቄያችሁ እንደነበር አትዘነጉም… ዛሬ ውብ የስነጽሑፍ ስራዎች የሚስተናገዱበት ሌላ መጽሔት ላስተዋውቃችሁ ነው…
ቀለም ይባላል…
በስነጽሑፍ፣ በፍልስፍና፣ በግለ-ታሪክና በወጎች ያጌጠ መጽሔት ነው…
እስኪ ጎራ ብላችሁ፣ አዲሱን ቅጽ 1 እትም 3 መጽሔትና ሌሎች ቁምነገሮችን ከቀደሙ ህትመቶቻቸው ጋር ተቋደሱ…
https://t.me/kelemofficial
❤4🙏2👌1
.
.
.
በዓለም ታሪክ አንድም ሃገር ጦርነትን አሸንፎ አያውቅም!... አንድም ሃገር!!...
የመስተጋብራችን ታሪክ በተሸከፈባቸው ባለፉት ብዙ ሺህ ዓመታት በምድራችን ላይ ብዙ የጦር አውድማዎች ተፈጥረዋል... የሰው ልጅ ሳይሰለች ጦር ተሳብቋል፣ ሳያሰልስ ተሞሻልቋል፣ ያለፋታ በባሩድ ጢስ ታጥኗል፣ በጥይት ጫፍ ህልም ቀጥፏል...
[ጦርነትን ግን አሸንፎ አያውቅም...]
ከባሕላዊ እስከ ዘመናዊ፣ ከእግረኛ እስከ አየር በራሪ፣ ከሃገር ድንበር እስከ ባሕር ተሻጋሪ፣ ከፊት ውጊያ እስከ ስውር ግፊያ - ተራቀቅሁ ባለባቸው መሳሪያዎች ሁሉ - የሰው ልጅ እስኪበቃው በራሱ ላይ ዘምቷል...
[ግን ጦርነትን አሸንፎ አያውቅም...]
የዓለሚቱ ጭካኔ ቅጥ አጥቷል... ጭቆናና የበላይነት የምድርን መልክ አጥፍቶታል... መግፋት፣ መንቀል፣ መግደል ተራ ጉዳዮች እየሆኑ ነው... በእያንዳንዱ ሰከንድና ደቂቃ ነፍሶች ይረግፋሉ... በእያንዳንዱ የዓለም ዳርቻ ሰቆቃ ይንበለበላል...
“In modern war, you will die like a dog for no good reason.” – Ernest Hemingway
አንዱ ሌላኛውን በብርቱ ያስጨንቃል... በመሪ እብሪት ታዝሎ እንባ ደም ያፈሳል... ግጭት ከመቀስቀስ እስከ መንግስት ማፍረስ፣ በቦንብ ከማውደም እስከ መሪ መሾም፣ ዜጋን ከገዛ ሃገሩ ከማባረር ሌላ ሃገር እስከ ማስፈር - የማንሰማው ጉድ የለም... ገራሚው ግን ይህን ሁሉ ሃይ የሚል አለመኖሩ ነው... ዜጎችን ከእብሪተኞች ጡጫና ከእብዶች እርግጫ የሚከልል የዓለም ስርዓት የለም... የሃገራትም ሆነ የዜጎቻቸው ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በመሳሪያ አምራቾች ምርጫ ነው...
ጥቂት የገንዘብ ብቻ ሃብት ያላቸው ሰዎች ኪስ እንዲሞላ በየቀኑ የጥይት ናዳ፣ የከተሞች ጎድጓዳ፣ የንጹሃን ዕዳ የማይተዋቸው ሃገራት ይኖሩናል... ከስልጣናቸው መክረም ውጭ አንዳች የሚሻገር ህልም በሌላቸው አምባገነን መሪዎች ቅዠት - እንቦቃቅላ ሕፃናት በጥይት ይረግፋሉ፣ ተስፋ ያላቸው ወጣቶች ይማገዳሉ፣ አዛውንቶች በየጎጆው ይደፋሉ...
[ያም ሆኖ ዛሬም ድረስ ጦርነትን አሸንፎ የሚያውቅ የለም...]
አፍሪካ በራሷ ልጆች አንገት ላይ ካራ ትሰካለች... በድሃ አደግ ሕዝቦቿ ላይ የደም አበላ ታወርዳለች... ከሰሜን ከፍታ እስከ ደቡብ ዝቅታ፣ ከምስራቅ ጫፍ እስከ ምዕራብ አጽናፍ - ሰላም ጸንቶ አያውቅም... ፍቅር አይሰነብትም...
የተፈጥሮ ሃብቷን ለመቀራመት ባላቸው ጉጉት ታውረው ልጆቿን በእልፍ ጎራ ከፍለው ያተጋትጓታል... ለዚህኛውም ለዚያኛውም ልጇ መሳሪያ ያቀርቡላታል... ለዚህኛውም ለዚያኛውም አካሏ አማካሪ ይሆኗታል... እርሷ እንቅልፍ ላይ ናት... ሴራ አታስተውልም፣ ስራይ አትገነዘብም... ዜጓቿ ሰርቶ መኖር፣ ገብቶ መውጣት፣ ተምሮ መለወጥ ሲያምራቸው ይቀራል እንጂ ጥቂቶች ኪሳቸው እስከሞላ፣ ሆዳቸው እስከቀላ ድረስ ግድ አይሰጣትም...
[ዛሬም ድረስ አፍሪካ የውስጧን ጦርነት አሸንፋ አታውቅም...]
በየመዳረሻው የሰው ልጅ በረሃብ ያሸልባል፣ በጠኔ ይረግፋል፣ በጥም ይጠወልጋል...
ግጭት የማያውቀው፣ የጦርነት አለንጋ የማይገርፈው፣ የጥይት አረር የማያስደነብረው አንድም የዓለም ጥግ የለም... ጦርነትና ግጭት የሰው ልጅ ቋሚ ልማድ ሆኗል...
ዜጎች በገዛ ቤታቸው በሰላም አይተኙም... በገዛ ምድራቸው ተረጋግተው አይኖሩም... በዕጣ ፈንታቸው ላይ አይወስኑም... የኔ የሚሉት አንድም ዋስትና የላቸውም... ነቃይና ተካያቸው ጉልበተኛው ነው...
“If we have no peace, it is because we have forgotten that we belong to each other.” – Mother Teresa
ሃገር በሌላ ሃገር ላይ እጅ ታነሳለች፣ መንግስት በዜጎቹ ላይ በእብሪት ይኮፈሳል፣ ክፉው ከወገኑ መከራ 'ሲሳይ' ያፍሳል...
በጣም የሚያስደነግጠኝ ብዙ ደካሞች በጥቂት ጉልቤዎች ስር መጨፍለቃችን አይደለም... ጭፍለቃውን justify የሚያደርግ አመለካከት ማዳበራችን እንጂ...
አዎን ጦርነትን የተለማመደ ትውልድ እየፈጠርን ነው... ከሌሎች እንባ የሚመነጭን ጥቅም፣ ከደማቸው የተላቆጠን ሃብት - 'አርበኝነት'፣ 'ብሔራዊ ጥቅም'፣ 'የሃገር ፍቅር' ፍቅር እያለ የሚያንቆለጳጵስ ድንዛዜ ውስጥ እየገባን ነው... ጦርነትን ምክንያታዊ ለማድረግ የምንሄድበት ርቀት ደግሞ ከጦርነቱ በላይ ያስፈራል...
“There is no flag large enough to cover the shame of killing innocent people.” – Howard Zinn
በዚህ የዓለም ስሪት ውስጥ ነገ የሚባለው ተስፋ ሁሌም የማይዳሰስ ነው... ሟችና በማንኛዋም ሰከንድ ውስጥ ተሰናባች መሆንህ የተፈጥሮ ድንጋጌ ቢሆንም ነቃይህ ከተፈጥሮ ቅኝት ውጭ የሚጓዘው እብሪተኛ መሆኑን ማሰብ ያደክማል...
___
የድልድይ አቋም...
.
.
.
ሃገር - ተፈጥሮ ከለገሳት፣ ድካሟም ከቸራት ሁሉ እንዳትበላ የሚያደርጋትን ማንኛውንም ኃይል መቃወም ጤነኛ ተግባር ነው... እያንዳንዱን ችግር ጦር መዞ፣ ሳንጃ ደቅኖ መጋተር ግን ብልህነት አይሆንም...
ዛሬ በጦር አስገብረህ የምታገኘው ነገር ለነገው ትውልድ የሌላ ዙር ጦርነት ሰበብ እስከሆነ ድረስ ጦርነቱን አላሸነፍከውም... የዛሬ ኃይልህ ለነገ ሰላም ዋስትና ካልሰጠ ያንተን ስግብግብነት እንጂ ለልጅህ ያለህን አሳቢነት አያመለክትም...
“Wars are poor chisels for carving out peaceful tomorrows.” – Martin Luther King Jr.
'ለልጄ የበቀል አዙሪት አላስቀምጥም' ያሉ ዛሬን ያስገብራሉ፣ ነገንም ያሸንፋሉ...
ያልተሄደበትን መንገድ ደፍረው መሻታቸውን የሚፈጽሙ ሃገርን ይወዳሉ፣ ለትውልድ ይጨነቃሉ...
'ልጆቼ ላይ ዕዳ ጭኜ አልሄድም' ያሉ በአስተዋይ ውሳኔያቸው ብርታት በትውልዶች ይዘከራሉ...
አዎን...
ጦርነትን ያሸነፉት ጦርነትን ያስቀሩት ናቸው...
___
@bridgethoughts
.
.
በዓለም ታሪክ አንድም ሃገር ጦርነትን አሸንፎ አያውቅም!... አንድም ሃገር!!...
የመስተጋብራችን ታሪክ በተሸከፈባቸው ባለፉት ብዙ ሺህ ዓመታት በምድራችን ላይ ብዙ የጦር አውድማዎች ተፈጥረዋል... የሰው ልጅ ሳይሰለች ጦር ተሳብቋል፣ ሳያሰልስ ተሞሻልቋል፣ ያለፋታ በባሩድ ጢስ ታጥኗል፣ በጥይት ጫፍ ህልም ቀጥፏል...
[ጦርነትን ግን አሸንፎ አያውቅም...]
ከባሕላዊ እስከ ዘመናዊ፣ ከእግረኛ እስከ አየር በራሪ፣ ከሃገር ድንበር እስከ ባሕር ተሻጋሪ፣ ከፊት ውጊያ እስከ ስውር ግፊያ - ተራቀቅሁ ባለባቸው መሳሪያዎች ሁሉ - የሰው ልጅ እስኪበቃው በራሱ ላይ ዘምቷል...
[ግን ጦርነትን አሸንፎ አያውቅም...]
የዓለሚቱ ጭካኔ ቅጥ አጥቷል... ጭቆናና የበላይነት የምድርን መልክ አጥፍቶታል... መግፋት፣ መንቀል፣ መግደል ተራ ጉዳዮች እየሆኑ ነው... በእያንዳንዱ ሰከንድና ደቂቃ ነፍሶች ይረግፋሉ... በእያንዳንዱ የዓለም ዳርቻ ሰቆቃ ይንበለበላል...
“In modern war, you will die like a dog for no good reason.” – Ernest Hemingway
አንዱ ሌላኛውን በብርቱ ያስጨንቃል... በመሪ እብሪት ታዝሎ እንባ ደም ያፈሳል... ግጭት ከመቀስቀስ እስከ መንግስት ማፍረስ፣ በቦንብ ከማውደም እስከ መሪ መሾም፣ ዜጋን ከገዛ ሃገሩ ከማባረር ሌላ ሃገር እስከ ማስፈር - የማንሰማው ጉድ የለም... ገራሚው ግን ይህን ሁሉ ሃይ የሚል አለመኖሩ ነው... ዜጎችን ከእብሪተኞች ጡጫና ከእብዶች እርግጫ የሚከልል የዓለም ስርዓት የለም... የሃገራትም ሆነ የዜጎቻቸው ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በመሳሪያ አምራቾች ምርጫ ነው...
ጥቂት የገንዘብ ብቻ ሃብት ያላቸው ሰዎች ኪስ እንዲሞላ በየቀኑ የጥይት ናዳ፣ የከተሞች ጎድጓዳ፣ የንጹሃን ዕዳ የማይተዋቸው ሃገራት ይኖሩናል... ከስልጣናቸው መክረም ውጭ አንዳች የሚሻገር ህልም በሌላቸው አምባገነን መሪዎች ቅዠት - እንቦቃቅላ ሕፃናት በጥይት ይረግፋሉ፣ ተስፋ ያላቸው ወጣቶች ይማገዳሉ፣ አዛውንቶች በየጎጆው ይደፋሉ...
[ያም ሆኖ ዛሬም ድረስ ጦርነትን አሸንፎ የሚያውቅ የለም...]
አፍሪካ በራሷ ልጆች አንገት ላይ ካራ ትሰካለች... በድሃ አደግ ሕዝቦቿ ላይ የደም አበላ ታወርዳለች... ከሰሜን ከፍታ እስከ ደቡብ ዝቅታ፣ ከምስራቅ ጫፍ እስከ ምዕራብ አጽናፍ - ሰላም ጸንቶ አያውቅም... ፍቅር አይሰነብትም...
የተፈጥሮ ሃብቷን ለመቀራመት ባላቸው ጉጉት ታውረው ልጆቿን በእልፍ ጎራ ከፍለው ያተጋትጓታል... ለዚህኛውም ለዚያኛውም ልጇ መሳሪያ ያቀርቡላታል... ለዚህኛውም ለዚያኛውም አካሏ አማካሪ ይሆኗታል... እርሷ እንቅልፍ ላይ ናት... ሴራ አታስተውልም፣ ስራይ አትገነዘብም... ዜጓቿ ሰርቶ መኖር፣ ገብቶ መውጣት፣ ተምሮ መለወጥ ሲያምራቸው ይቀራል እንጂ ጥቂቶች ኪሳቸው እስከሞላ፣ ሆዳቸው እስከቀላ ድረስ ግድ አይሰጣትም...
[ዛሬም ድረስ አፍሪካ የውስጧን ጦርነት አሸንፋ አታውቅም...]
በየመዳረሻው የሰው ልጅ በረሃብ ያሸልባል፣ በጠኔ ይረግፋል፣ በጥም ይጠወልጋል...
ግጭት የማያውቀው፣ የጦርነት አለንጋ የማይገርፈው፣ የጥይት አረር የማያስደነብረው አንድም የዓለም ጥግ የለም... ጦርነትና ግጭት የሰው ልጅ ቋሚ ልማድ ሆኗል...
ዜጎች በገዛ ቤታቸው በሰላም አይተኙም... በገዛ ምድራቸው ተረጋግተው አይኖሩም... በዕጣ ፈንታቸው ላይ አይወስኑም... የኔ የሚሉት አንድም ዋስትና የላቸውም... ነቃይና ተካያቸው ጉልበተኛው ነው...
“If we have no peace, it is because we have forgotten that we belong to each other.” – Mother Teresa
ሃገር በሌላ ሃገር ላይ እጅ ታነሳለች፣ መንግስት በዜጎቹ ላይ በእብሪት ይኮፈሳል፣ ክፉው ከወገኑ መከራ 'ሲሳይ' ያፍሳል...
በጣም የሚያስደነግጠኝ ብዙ ደካሞች በጥቂት ጉልቤዎች ስር መጨፍለቃችን አይደለም... ጭፍለቃውን justify የሚያደርግ አመለካከት ማዳበራችን እንጂ...
አዎን ጦርነትን የተለማመደ ትውልድ እየፈጠርን ነው... ከሌሎች እንባ የሚመነጭን ጥቅም፣ ከደማቸው የተላቆጠን ሃብት - 'አርበኝነት'፣ 'ብሔራዊ ጥቅም'፣ 'የሃገር ፍቅር' ፍቅር እያለ የሚያንቆለጳጵስ ድንዛዜ ውስጥ እየገባን ነው... ጦርነትን ምክንያታዊ ለማድረግ የምንሄድበት ርቀት ደግሞ ከጦርነቱ በላይ ያስፈራል...
“There is no flag large enough to cover the shame of killing innocent people.” – Howard Zinn
በዚህ የዓለም ስሪት ውስጥ ነገ የሚባለው ተስፋ ሁሌም የማይዳሰስ ነው... ሟችና በማንኛዋም ሰከንድ ውስጥ ተሰናባች መሆንህ የተፈጥሮ ድንጋጌ ቢሆንም ነቃይህ ከተፈጥሮ ቅኝት ውጭ የሚጓዘው እብሪተኛ መሆኑን ማሰብ ያደክማል...
___
የድልድይ አቋም...
.
.
.
ሃገር - ተፈጥሮ ከለገሳት፣ ድካሟም ከቸራት ሁሉ እንዳትበላ የሚያደርጋትን ማንኛውንም ኃይል መቃወም ጤነኛ ተግባር ነው... እያንዳንዱን ችግር ጦር መዞ፣ ሳንጃ ደቅኖ መጋተር ግን ብልህነት አይሆንም...
ዛሬ በጦር አስገብረህ የምታገኘው ነገር ለነገው ትውልድ የሌላ ዙር ጦርነት ሰበብ እስከሆነ ድረስ ጦርነቱን አላሸነፍከውም... የዛሬ ኃይልህ ለነገ ሰላም ዋስትና ካልሰጠ ያንተን ስግብግብነት እንጂ ለልጅህ ያለህን አሳቢነት አያመለክትም...
“Wars are poor chisels for carving out peaceful tomorrows.” – Martin Luther King Jr.
'ለልጄ የበቀል አዙሪት አላስቀምጥም' ያሉ ዛሬን ያስገብራሉ፣ ነገንም ያሸንፋሉ...
ያልተሄደበትን መንገድ ደፍረው መሻታቸውን የሚፈጽሙ ሃገርን ይወዳሉ፣ ለትውልድ ይጨነቃሉ...
'ልጆቼ ላይ ዕዳ ጭኜ አልሄድም' ያሉ በአስተዋይ ውሳኔያቸው ብርታት በትውልዶች ይዘከራሉ...
አዎን...
ጦርነትን ያሸነፉት ጦርነትን ያስቀሩት ናቸው...
___
@bridgethoughts
❤13🔥1🙏1👌1💯1
አንቺ የሌለሽበት
Demis Seifu
❤5❤🔥1🔥1💘1
.
.
.
አንብቤው እንዳልገባኝ መስመር - ፊትሽን ደጋግሜ እንዳየው የሚጎትተኝ መግነጢስ ምን ይሆን?...
የእናቱን ጡት 'ጠገብኩ' ብሎ እንደማይተው ሕፃን... ቆሎ 'በቃኝ' ብሎ እጁን ወደ ሌማት መዘርጋት እንደማይሰለች ሰው...
በስንኞች መሃል ሲመላለስ በድግግሞሹ ልክ አዲስ የምስጢር ቋት እንደሚከፍት ጠቢብ... ከተራ መስመሮች መሃል የጠለቀ ሃሳብ፣ የረቀቀ ውበት፣ ያረመመ ቅኔ እንደሚፈለቅቅ ትጉህ አንባቢ - ፎቶሽ ሰርክ አዲስ የሚሆንብኝስ ለምንድነው?...
ዕጹብ ነው... ድንቅ ነው...
በዝምታ፣ በጸጥታ፣ በእርጋታ ውስጥ ሆኖ ቅኔውን ያራቅቃል... በኃይል፣ በግርማ፣ በመርዕድ ዘዬ ሰምና ወርቁን ያፈልቃል...
[ደጋግሜ ባየሁት ቁጥር...]
አዲስ ውበት፣ አዲስ ጸዳል፣ አዲስ ሞገስ፣ አዲስ ስለት እያቀበለ ልቤን ይቦረቡራታል...
ቁራኛዬ...
ምን ይሉት መግነጢስ ነው ከፎቶሽ ስር እያጣደፈ፣ እያክለፈለፈ፣ እየሳበ የሚወስደኝ?...
Desktop እና Laptop ላይ Screensaver... ስልኬ ላይ Lock screen እና Home screen Wallpaper... Wallet ላይ፣ Album ውስጥ፣ ጠረጴዛዬ ላይ... [አልበዛም?...]
አንቺዬ... የእስከዛሬው ኩራቴ 'ከቡና ውጪ ሱስ አያውቀኝም' ነበር... ውሸቴን ይቅር በይው - ከፎቶሽ ጋር ሱስ ይዞኛል...
የምር ግን...
በአካል ጥላሽ ብርታት ልቤ ቀልቡን ካጣ - ከፊትሽ ስቆም አጥንቶቼ ላለመቅለጣቸው ዋስትናዬ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
.
.
አንብቤው እንዳልገባኝ መስመር - ፊትሽን ደጋግሜ እንዳየው የሚጎትተኝ መግነጢስ ምን ይሆን?...
የእናቱን ጡት 'ጠገብኩ' ብሎ እንደማይተው ሕፃን... ቆሎ 'በቃኝ' ብሎ እጁን ወደ ሌማት መዘርጋት እንደማይሰለች ሰው...
በስንኞች መሃል ሲመላለስ በድግግሞሹ ልክ አዲስ የምስጢር ቋት እንደሚከፍት ጠቢብ... ከተራ መስመሮች መሃል የጠለቀ ሃሳብ፣ የረቀቀ ውበት፣ ያረመመ ቅኔ እንደሚፈለቅቅ ትጉህ አንባቢ - ፎቶሽ ሰርክ አዲስ የሚሆንብኝስ ለምንድነው?...
ዕጹብ ነው... ድንቅ ነው...
በዝምታ፣ በጸጥታ፣ በእርጋታ ውስጥ ሆኖ ቅኔውን ያራቅቃል... በኃይል፣ በግርማ፣ በመርዕድ ዘዬ ሰምና ወርቁን ያፈልቃል...
[ደጋግሜ ባየሁት ቁጥር...]
አዲስ ውበት፣ አዲስ ጸዳል፣ አዲስ ሞገስ፣ አዲስ ስለት እያቀበለ ልቤን ይቦረቡራታል...
ቁራኛዬ...
ምን ይሉት መግነጢስ ነው ከፎቶሽ ስር እያጣደፈ፣ እያክለፈለፈ፣ እየሳበ የሚወስደኝ?...
Desktop እና Laptop ላይ Screensaver... ስልኬ ላይ Lock screen እና Home screen Wallpaper... Wallet ላይ፣ Album ውስጥ፣ ጠረጴዛዬ ላይ... [አልበዛም?...]
አንቺዬ... የእስከዛሬው ኩራቴ 'ከቡና ውጪ ሱስ አያውቀኝም' ነበር... ውሸቴን ይቅር በይው - ከፎቶሽ ጋር ሱስ ይዞኛል...
የምር ግን...
በአካል ጥላሽ ብርታት ልቤ ቀልቡን ካጣ - ከፊትሽ ስቆም አጥንቶቼ ላለመቅለጣቸው ዋስትናዬ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
❤6👍2🥰2❤🔥1💘1