Dildiy - (ድልድይ)
1.38K subscribers
401 photos
85 videos
1 file
116 links
Dildiy - Whispers of the soul, echoes of the universe. 

A space where mysticism meets quantum wonder, where love, presence, and oneness awaken us. 

Thoughts, poems, and reflections for the seekers of light and the questioners of truth.

Bridge.
Download Telegram
ማስተንከሪያ
___

📢 Are we evolving or are we just getting better at masking our madness?

[በጥያቄ ነቃሁ... ጠዋቴ ከማወቅ ጉጉቴ ጋር በራች... እንዲሁ ነኝ... አንዳንድ ቀኔን የሚረከቡ ሃሳቦች ማለዳዬ ላይ ይራወጣሉ... ዛሬም የሆነው እንዲሁ ነበር...]


እናም ጠየቅሁ...


'እውን ሰይጣን ይሉት 'አካል' አለ?... ቀንዳም፣ የጨለማ ገዢ፣ አስፈሪ፣ ጨካኝ entity በሕዋችን ላይ ታቅፏል?... ወይስ ላልተቀበልነው ተፈጥሮአችን፣ ለውድመት፣ ለበደል፣ ለግፊያችን - ማምለጫ፣ ማቋረጫ፣ መሿለኪያ የተቀመጠ የስርየት ፍየል ይሆን?... 🤔🤔🤔

___

ማጮለቂያ... 👀
___

ርዕዮት - ፩


የሐይማኖት መጽሐፍት የሰይጣንን ኑባሬ ይቀበላሉ... ለምሳሌ ክርስትና 'የተጣለው መልዓክ፣ መከራ አማጭ፣ ፈታኝ' ብሎ የሚጠራው ሰይጣንን 'ከመለኮት ትዕዛዝ በተቃርኖ የሚጓዝ አማጺ' አድርጎ ያስቀምጠዋል...


በእስልምና 'ኢብሊስ' ተብሎ የሚጠራው ሰይጣን 'ለአዳም ባለመገዛቱ የተባረረ፣ የኩራትና ያለመታዘዝ ምልክት ነው'...


አይሁዶች በዕብራይስጥ 'ሃ-ሴታን' ወይም ከሳሽ ሲሉ የሚጠሩት ሰይጣን 'በፈጣሪ የፍርድ ችሎት ላይ የሚቀመጥና የሰዎችን ታማኝነት የሚፈታተን ነው' ሲሉ ያስተምራሉ...


ርዕዮት - ፪


ነገሩን ምዕራባዊ መሰረት ካላቸው ሐይማኖቶች አስተምህሮ አውጥተን በአሳቢያን እና ማላዮች መነጽር ብንመለከተው ሰይጣን ከአካላዊ ግዝፈት ይልቅ ምልክታዊ ጉላት ያይልበታል...


ሰይጣን የሰው ልጅ ባሕሪያዊ ጽላሎት (Inner shadow) ትዕምርት ሲሆን ያልተፈተነ ፍርሐት፣ ስግብግብነትና ድብቅ ጭካኔያችን ነጸብራቅ ነው...


ከእውነት፣ ከፍቅር እና ከሕላዌ ነቅዕ (Being) የመለያየት ተምሳሌት፤ እንዲሁም ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ለማምለጥ የምንከለልበት ዓይነ-ርግብ (mask) ነው...


Carl Jung ቆንጆ አድርጎ እንዳስቀመጠው... 


🔔 "The devil is the personification of the shadow side of human nature." 🔔


ማላዮችም ስለ ሰይጣን አብዝተው ከመናገር ይልቅ ስለ ንቃትና ተገንዝቦት ማውጋትን የሚመርጡት ለዚህ ነው...


ለምሳሌ ሱፊስቶች - “There is no Satan but the ego unobserved.” በማለት ከነዩንግ እሳቤ ጋር ሲዛመዱ ሌሎች ምስራቃዊ መሰረት ያላቸው አስተምህሮዎችም ከዚህ መሰረት ብዙም ያልራቀ ዕይታን ያስተጋባሉ...

___

📌 የሰይጣንን እሳቤ የወለደው ክህደት፣ ድንዛዜ እና ኃላፊነትን ያለመውሰድ ቅዋሜ ነው... ሁሌም ቢሆን አጥፊነታችንን መቀበል ሲቸግረን ሌላ ተወቃሽ እናሻትታለን... የሁኔታው ሰበብና የቅጣቱ ተቀባይ እኛው ራሳችን ብንሆንም እኛን ተገብቶ እንዲጠየቅልን የምንፈልገው የጦስ ዶሮ መፈለጋችን የተለመደ ነው...


📌 ክፋታችንን ውጫዊ ስናደርግ 'ለምንድነው ይህን ያደረግሁት? የትኛው እኔታዬ ነው ይህ እንዲሆን የፈለገው?' ብለን ከመጠየቅ ይልቅ 'እኔ አላደረግሁትም ወይም ሰይጣን አስቶኝ ነው' የማለትን ቀላል መንገድ እንመርጣለን...

___

@bridgethoughts
4👍2🥰2👏1👌1
[የቀጠለ...]

🤔 ማብሰልሰያ - ፩


ሰይጣን አለ ብለን ብናስብና እንደተነገረን ክፋቱን ብንቀበል፣ maximum ሊያደርግብን የሚችለው ነገር ምንድነው?... ስቃይ ማብዛት?፣ መከራ መቆለል?፣ ለሞት መዳረግ? ወይስ ሌላ?... ታዲያ ሰይጣን የሚያደርገው እኛ እስካሁን ያላደረግነው ምን ነገር አለ?...


መንደሮችን አቃጥለናል... ሕፃናትን በቦምብ ደብድበናል... አፍላጋትን መርዘናል... ድንበር ፈጥረን ተቋስለናል... በረሃብ ሰው ፈጅተናል... ፍቅርን ሸቅጠናል... ሃቂቃን አፍነናል... ጨቅላ ሕፃን ደፍረናል... እርጉዝ ሴት በሳንጃ ዘንጥለናል... ሰውን በቁሙ አቃጥለናል... ስጋውን ቀርጥፈን ከርስ ሞልተናል... ከመሰዊያ ላይ አርደናል... በስልጣናችን ባልገናል... ዘርፈናል፣ ቀጥፈናል፣ ሰስነናል - ይህች ምድር በእኛ ምክንያት ያላየችው ምን ቀሪ መከራ አለ?...


[ለኢጎአችን እስከጠቀመ ድረስ ጆሮ አደንዛዡን፣ ዓይን አፍዛዡን ሁሉ አድርገናል - እስካሁን ካደረግነው የሚበልጥ ምንም ሌላ ነገር ወደፊት አናደርግም... ከኛ በላይ የሚያደርግ ሌላ 'ሰይጣንም' የለም]


🌟 "If Satan is the exile of love, then maybe redemption is not believing in God — but becoming someone who does not create hell for another."


እውነት ሰይጣን ካለ ግን በእርግጠኝነት በዚህ ሰዓት ጡረታ ወጥቷል... አልያም መዝገብ ይዞ ክፋታችንን እየከተበ ነው... ወይም ደግሞ ከከፋው ተግባራችን ልምድ እየቀሰመ ይሆናል...


ያን የ Desert father's wisdom ታስታውሱት የለ?...


በአንድ ገዳም ውስጥ፣ አንድ ወጣኒ መነኩሴ እንቁላል ይሰርቅና ተደብቆ ሲጠብስ ይገኛል... 


'ምን እያደረግህ ነው?' ያገኙት አባት ይጠይቁታል...

'አይ አባ... ሰይጣን አስቶኝ...' ወጣቱ ይርበተበታል...

ጉዳዩን ከመስኮት በኩል ሆኖ ሲከታተል የነበረው 'ሰይጣን' ታዲያ እንዲህ ሲል ራሱን ነፃ አወጣ...

'አባ ውሸቱን ነው... ይህችን መላ ያለዛሬም አላየሁዋት'...

___

🌟 ጎበዝ ሰዋዊ ጉዳዮቻችን የሚመሩት በግላጭም በስውርም ነው... እኛ - አስበን፣ ወስነን የምንከውነው ብቻ አይደለንም... ከማለዳ ዕድሜያችን ጀምሮ በልቡሰ-ጥላ (subconscious mind) ሲሞላ የኖረው ፕሮግራምም በድብቅ ይመራናል፤ ይቆጣጠረናል...


እርሱ ማንነታችንን ይገነባል... እርሱ ግንኙነታችንን ይመራል...


እዚያ ቅይጥ መልካችን ይከተባል... እዚያ መሻት መጥላታችን ይቀመራል... 


ደግነት ክፋታችን፣ ርህራሔ ተንኮላችን፣ ጨዋነት ወራዳነታችን፣ ንቃት ድንዛዜያችን የመንታ አንድ ሆኖ ይላቆጣል...

___

🤔 ማብሰልሰያ - ፪


ንድፈ ሃሳባዊውን መለኪያ ትተን በተግባር ብንፈተሽ 'ሰይጣን' ከሚባለው 'ትርክት' የሚለየን ምንድነው?...


ለምሳሌ - ሰይጣን 'ፈታኝ ነው' እንላለን... እኛም በአባይ ቃል፣ በአታላይ ጥቅም ሌሎችን በማማለል እንፈትናለን...


ሰይጣን 'ከፋፋይ ነው' እንላለን... እኛም 'ልዩነትን' የጥላቻ ምንጭ፣ 'ማንነትን' የጦር መስበቂያ ሰበብ አድርገን የሰውን ልጅ ስንበልት እንኖራለን...


ሰይጣን 'ሐሰተኛ ነው' እንላለን... ነግቶ እስኪመሽ ቅጥፈት፣ መሽቶ እስኪነጋ እብለት አሽሞንሙነን ወገናችንን እንወጋለን...


🦋 ሰይጣን ለመባል ቀንድ አያስፈልገንም - ከቀንድ በላይ የሚወጋ ምላስ አለን... ገሃነመ እሳት አያስፈልገንም - ከጥይት አረር እስከ ከፋው ኒውክለር ሁሉን ታጥቀናል...

___

አንድ ጥንታዊ የሱፊ ወግ ልንገራችሁ...

አንድ ቀን አንድ ደርቪሽ መምህሩን እንዲህ ሲል ጠየቀ...

"መምህር ሆይ፣ ሰይጣንን ማሸነፍ የምችለው እንዴት ነው?"

መምህሩ መለሱ...

"በቅድሚያ የእርሱን ጫማ መዋስ አቁም"


መምህሩ በጫማ ነጽሮት ውስጥ ውስጠ ቅኝታችንን ነው ያጠየቁት... አሳባቢ፣ ጥሩር ቀጥቃጭ፣ ኃላፊነት ካጂ ውስጠ ማንነታችንን...

ያመሰጠሩት ስለ ዓይነ ትልልቅ፣ ባለ ጨልጨሌ፣ ቀንዳም ሰይጣን ሳይሆን - ልናይ ስላልፈቀድነው ማንነታችን ነው...

___

Meister Eckhart እንዲህ ይላል...

“The devil is simply that which pushes you away from your own center.”


🌟 ማዕከል (center) የሰው ልጅ ለሕላዌው ጣዕም የሚፈጥርበት፣ እንዲሁም በመኖር ወጀብ ከመናወጥ የሚድንበት መልህቁ ነው... ፍቅሩ፣ አገልጋይነቱ፣ እሴቱ፣ የሕይወት ፍቺው... ሻገር ብሎ ደግሞ ከነፍስያው፣ ከምንጩ፣ ከምልዓተ ዓለሙ የሚዋደድበት እትብቱ... ከዚህ ማዕከል የሚገፋውን ነገር ነው ማላዩ ኤካርት 'devil' ሲል የጠራው...

___

መውጫ - መወጣጫ

___

🔔 [ሰይጣን ከአካላዊ ማንነት ይልቅ ከፍቅር የመፋታት ምልክት ቢሆንስ?... ምናልባትም የንቃት ስንጥቃት አልያም ከአማናዊው የማንነታችን ምንጭ የመለያያት ጥልቀት ቢሆንስ?...]

እንደ እውነቱ ከሆነ ክፉ አስፈፃሚ አይደለም ያለው - ፈፃሚው ራሱ እንጂ... በሌላ አነጋገር ወይ እኛ ሰይጣን ነን - አልያም ብቅ እልም የምትል ስይጥንና አለችብን...

___

👉 ጨለማን ሁልጊዜ ሻማ በመለኮስ አንፋታውም... አንዳንዴ ጨለማነቱን መቀበልም ይኖርብናል... በተለይ የውስጣችን ኑባሬ ሲሆን በዓይኖቻችን ልናየው መድፈርም ግድ ይሆናል... ልክ ራሳችንን በመስታወት ፊት እያየን እንደምናወራው ሁሉ - "አንተ - እኔን ነህ... ያልተፈቀርከው፣ ያልተጎበኘኸው፣ ያልተደመጥከው እኔ... አሁን አጠገብህ ነኝ፣ እያየሁህ ነው..." ልንለው ይገባል...

___

@bridgethoughts
14👌3🔥2👍1🙏1
.
.
.

እንዳልነበርክ ለመሆን ሰከንዶች እንኳ ረጅም ናቸው... አትታበይ!!

___

@bridgethoughts
19💊3👍2🙏1
.
.
.

ከሩቅ የሚያይህ ሰው፣ 'በኑሮዬ ጎድሏል' ብሎ የሚያስበውን፣ አልያም 'ከእኔ የተሻለ ነው' ብሎ ያመነበትን ነገር አንተ ዘንድ ስላገኘ ሊቀናብህ ይችላል...


በሩቅ 'ምታውቀው ሰው፣ ከቤቴ የለም ያልከው ኖሮት፣ አልያም ከአንተ ይልቅ በዝቶለት ስላየኸው ትቀናበት ይሆናል...


ደግሞ ሁለታችሁ፣ በሩቅ 'ምታዩት ሰው የለንም ባላችሁት ተከቦ፣ ካላችሁ በላይ ደርቦ የሚኖር ሲመስላችሁ ትቀኑበት ይሆናል...


ከሩቅ የሚያያችሁ፣ የቀናችሁበት ሰው ግን እናንተ ዘንድ ባየው ታኮ ጉድለቱን የሚያስብ ነው... የእርሱ ቤት ለሌሎች ሙላት ሆኖ እንደሚያስቀና ግን አንዳች ግንዛቤ የለውም...


አንተ ዘንድ ያለውን በሙላት ተርጎሞ የእጁን የሚያሳንስ ብዙ ተጓዥ አለ... 

[ወርቅ አፈር ሆኖብህ መቸገርህን ያላየ]


የሞላለት ያልከው ብዙ እንከኑን 'ሚያስብ የሩቅ ሰው ደግሞ አለ...

[አልማዙን እንደ አመድ ሲቀበል የኖረ]


እኛ ዘንድ ያለው፣ ሁሌም ሌሎች ዘንድ ካለው አንሶ የሚታየን ነገር የኑረት እንቆቅልሽ ነው... አንዳንድ የሙላትና ጉድለት ዕይታዎቻችን 'ሃብት' እና 'ድህነት' ከምንለው ማሕበረሰባዊ መለኪያዎች ሁሉ ይሻገራሉ...

____

ለምሳሌ...

የምትወደው ሚስት አልያም አፍቃሪ ቤተሰብ ያለው የሚመስልህ አንድ ሰው ላይ ትቀና ይሆናል... ይሁንና ሰውየው የብቻነት ጉጉትና የነፃነት ናፍቆት የሚያባክነው ዓይነት ሆኖ ባንተ አኗኗር እየቀና ሊሆን ይችላል...


በመንፈሳዊ እሴቶች ተጊጠህ ስታበቃ ቁሳዊ ሃብት ባለው ሌላኛ ሰው ትቀና ይሆናል... ምናልባት ግን ባለ ቁሱ አንተ ያለህን የአዕምሮ ሰላም በማጣት ስቃይ ውስጥ እየኖረ ይሆናል...


የአካል ጉድለት ስላለብህ ብቻ በሌላው ጥንካሬና ገጽታ ትቀና ይሆናል... ይሁን እንጂ የምትቀናበት ሰው የሚጋደልበትን ስውር ጦርነት አታውቅም... ምናልባትም ሰውየው በአንተ ጽናትና የስሜት መረጋጋት የሚቀና ሊሆን ይችላል...


እይታ ነው ጎዳይ፣ አተያይ ነው ሞዪ...

___

የሰዎች 'ሙላት' የሚታየን በራሳችን 'ጉድለት' በኩል ነው... ሆኖም 'ጉድለት' የአንድ ነገር አለመኖር አይደለም... ሙላት የሚከሰትበት ስፍራ መኖሩን ማሳያ እንጂ... 


የጉድለት ስሜት የንጽጽር ህመም ውጤት ነው... አንድ ጊዜ ማነፃፀር ከጀመርክ ሙላትህን ለማሰብ ዕድል አትሰጥም... ይልቁን የሌለህን ከማሰብ ስለምትጀምር ያለህን ለማየት ጊዜ ታጣለህ... ማነፃፀር የማመስገን ተነሳሽነትህን የሚሰልብ ክፉ ባላንጣ ነው... 


አስታውስ - 


🔔 ሙላትና ጉድለት ሁልጊዜም ተለዋዋጭ ናቸው፤

🔔 የሰዎችን ከመጋረጃ ጀርባ ያለ ትግል ሳታይ ራስህን ከእነርሱ ጋር አታነፃጽር፤

🔔 በዓይን ለማይታየው ሃብትህ ዕውቅና ከመስጠት ጀምር... [አዕምሮህ ሰላም አለው፣ የሰው ፍቅር አለህ፣ ጤነኛ ነህ፣ እጅህ ላይ የበደል ደም የለም፣ አትሰርቅም፣ አትገፋም፣ ዓላማ አለህ...]

___

በዚህ ርዕሰ ላይ Mystics የሚያስተምሩትን ጠቅልለህ ልትረዳ ብትሞክር የምታጠለው እውነት እንዲህ የሚል ነው...

"The cup is full when you recognize its emptiness. And it is empty when you ignore its fullness."

___

በነገራችን ላይ...


🐔 በሕይወትህ የት ስፍራ ነው ጉድለት የሚያቃጭልብህ? 

🐔 ሌሎች አንተ ላይ የሚያደንቁት ምናልባት ትኩረት የነፈግኸው ነገርስ የለህም?...

🐔 የሌላኛውን ሰው አኗኗር ያንተን ልምምድ ለመመዘን እየተገለገልክ ይሆን?...

___


ሁላችንም የጉድለትና ሙላት ኮሮጆ ተሸክመን የምንዞር ምንዱባን ነን... ባጣነው ነገር ላይ ስናተኩር ጉድለት ያዛጋብናል... ባለን ስንደሰት ሙላት በምስጋና ይሞላናል...

___

ደቀመዝሙሩ የሱፊውን መምህር ይጠይቃል... "ለምንድነው ሌሎች ሁሉ ነገር ሲኖራቸው እኔ ብቻ ባዶነት የሚሰማኝ?"

መምህሩ አልተገረሙም... ሆኖም ጥያቄውን ከመመለሳቸው በፊት አንድ የሸክላ ማሰሮ ሰጡትና "ከወንዝ ውሃ ሞልተህ አምጣልኝ" አሉት... 

ደቀመዝሙሩ እንደታዘዘው አደረገ... 

ውሃ የሞላውን ማሰሮ ይዞ ከፊታቸው እንደቆመ መምህሩ ቀስ አድርገው ማሰሮውን ከስሩ ስለበሱት ውሃ መንጠባጠብ ጀመረ...

"አሁንስ ሙሉ ነው ጎደሎ?" ጠየቁት...

"ሙሉ ነው፣ ግን ደግሞ እያንጠባጠበ ነው"...

መምህሩ ፈገግ ብለው...

" እኛም እንዲሁ ነን... የሆነ ቦታ ሙላት ይሰማናል፤ በሌላ ገጽታ ደግሞ ስንጥቃት አለን - በዚያ በኩልም ጉድለት እናያለን... ሰዎችን በሙላታቸው በኩል አትመዝን፤ በየትኛው በኩል ሽንቁር እንዳላቸው አታውቅምና... በስንጥቃትህ አትሳቀቅ፣ የት ላይ መስራት እንዳለብህ አስታዋሽህ ነውና" ሲሉ መለሱለት...

___


ከጉድለትህ ጋር ግብግብ በፈጠርክበት ጊዜ ሳይቀር የሆነ አንድ ሰው የሙላት ተምሳሌት ልትሆን እንደምትችል አስብ... የሆነ ዓይነት ውበት፣ የሃሳብ ጥራት፣ ጥንካሬ እና ሰላም በጸጥታህ ውስጥ እንደተሸጎጠ ተመልከት...

ልብ በል... 

ከምታስበው በላይ የተሟላህ፣ ከምታውቀው በላይ ክፍት ነህ... መንታ!! የምታተኩርበት ቦታ ዕይታህን ይወስነዋል...

___

@bridgethoughts
23🙏3🥰1
.
.
.

... የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ... 

___

@bridgethoughts
23🥰1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
A Beautiful Mind (2001)

Directed by Ron Howard, starring Russell Crowe as John Nash, with Jennifer Connelly in a supporting role.

_

The film is based on the life of the Nobel Prize-winning mathematician John Nash and explores his struggles with schizophrenia and his remarkable contributions to mathematics.

___

@bridgethoughts
🔥5🥰21
.
.
.

'የኔ ሁኚ' የማልልሽ የኔ በመሆን የምታጭው [የሚመስለኝን] ሁሉ ስለማስብ ነው... አብሮነትን የማልጠይቅሽ ማግስት የሚነጥቅሽ [የሚመስለኝን] ሁሉ እያብሰለሰልኩ ነው...


(የሚመስለኝ ያልኩሽ - በእኔ ልብ ውስጥ ያለውን እምነት እንጂ አንቺ ዘንድ ያለውን ጥንካሬ ስለማላውቅ ነው...)


ከልቤ እልፍኝ ያልጋበዝኩሽ ስለማልፈቅድሽ አይደለም... መንገዴን ያላጋራሁሽ ስለማልወድሽ አይደለም... ይልቁን ስለምጠነቀቅልሽ ነው... [የኔ በመሆን የምትከፍይው ዋጋ እንዳይኖር በመስጋት... ወይም በጥሬ ቃል 'ደስታዋን ስለ አብሮነታችን ሰውታ ብታዝንብኝስ?' ብዬ በመፍራት...]


[እንግዳ ነገር ይመስላል አይደል?... 'የነገን እግዜር ያውቃል' በሚል ተስፈኛ ሕዝብ መሐል በቅሎ 'ነገ ብትከፋብኝስ?' ብሎ ማሰብ ይገርማል አይደል?...]

____


[የነግ ፍርሃት እያጠየመብኝ እንጂ እኮ...]


ልብሽ ለኔ ያላትን ቦታ እረዳለሁ - [ልብሽን እንዳልሰብራት ደግሞ እፈራለሁ...]


ስታገኚኝ የፊትሽ ጸዳል ለልቤ እንዲያበራ አውቃለሁ - [የኔ አድርጌሽ ሳቅሽን እንዳልነጥቅሽ እያልኩ ግን እፈራለሁ...]


ጨዋታሽ ደዌ ሲፈውስ፣ ቃላትሽ ለነፍስ ሲደርስ፣ ፈገግታሽ መንፈስ ሲያድስ አውቃለሁ - [አብሮነታችን ስሜትሽን እንዳያጎሸው ግን ሁሌም እሰጋለሁ...]


[ግን ደግሞ ሰው አይደለሁ?...]


ዛሬ የገባኝ ሁሉ ከነፃነትሽ ላለመወለዱ፣ ዛሬ የወደድኩት ሁሉ ነገም ለመራመዱ እርግጠኝነት እንዲከበኝ እሻለሁ...



[እናም በልቤ እጠይቅሻለሁ...]



የመጣሁበት መንገድ አያዝልሽም?... የምደርስበት ነገ አያስከፋሽም?... እርጅናዬ ውስጥ ልትኖሪ ትሺያለሽ?... በጉዞዬ ልታብሪኝ በቂ አቅም አለሽ?... [ይኸውልሽ ማሬ፣ ፊቴ ላይ የማታነቢው ምሬት ከውስጤ ሊኖር ይችላል...]


ውድቀቴ ተስፋ አያስቆርጥሽም?... ድህነቴ አያስፈራሽም?... ቀርነቴስ አያሳቅቅሽም?... [ከዘመነኞችሽ ጋር ያለኝን መልከ ብዙ ልዩነትና ርቀት አውቀዋለሁ...]


ፍቅሬ ይበቃሻል?... ቤቴስ ይስብሻል?...

ህመሜን አትጠየፊውም?... ድካሜንስ አትሰቀቂውም?...

[ይሄ ሁሉ ይቅር...] 

ስለ ውሳኔሽ አትጸጸቺም???...

___

ጣፋጯ...

ለነዚህ ጥያቄዎች የአዎንታ ልብ ከሌለሽ 'ና' አትበይኝ... እኔም 'ምጪልኝ' ብዬ አላስጨንቅሽም...


የወደድኩሽ የማትፈልጊውን እንድትኖሪ ከመጨከን ጋር ስላልሆነ ምርጫሽን አከብራለሁ... ግን አትርሺ - ስላላበርን ፍቅሬ ፈጽሞ አይቀየርም... 


___

ይህን ግን ለምን ፃፍኩልሽ?...


ራስ ወዳድ እንዳልሆንኩ እንድታውቂ ይሆናል... [ምናልባት ደግሞ ነፃነትሽን ላስታውስሽ ብዬም ይሆናል...]


[አየሽ... ሰው በገዛ ልቡ ውስጥ ስላለች የፍቅር ኩራዝ እንጂ በሌላኛው ሰው ልብ ውስጥ ስለተዘጋጀለት እቶን መውደድ በቀላሉ እርግጠኝነት አይሰማውም... በመኖር ካልፈተነው በቀር...]


ሁሌም ግን እወድሻለሁ 💞

___

@bridgethoughts
26🥰4
.
.
.


ከምከፍተው ሙዚቃ ይልቅ፣ እንዳልረብሽ የማደርገው ጥንቃቄ ከፍ ብሎ ይሰማል... ይገርማል!!


ከምጠቀመው ውሃ በላይ፣ ላለማባከን የማደርገው ጥረት ትኩረት ስቦ ያስከፋል... ምን ይባላል??


ከማበራት አምፑል በላይ፣ የመቆጠብ ልምዴ ጠያቂ ይጎትታል... ያሳቅቃል!!


ገላ ለመታጠብ 'ሻወር ቤት' ብመርጥም፣ ድንገት የገባሁ'ለት -  አንኳኪ አላጣም...


በወር የምከፍለው ቁጥሩ ባይናቅም፣ 'የጨምር' ዕድገቱ አንዴም ቆሞ አያቅም... 


አታምሽ ያሉኝ ፈሪ በጊዜ ብሰፍርም፣ ቤት መዋል ሲያምረኝ ግን ገላማጭ አላጣም...

.
.
.

ምክንያቱም...

👇

ያለሁት ኪራይ ቤት ነው!!

___

የአንዳንድ አከራዮች የመጀመሪያ ተግባር እንደ ሰው የሚገባህን ክብር መንጠቅ ነው... ይህንንም የሚያደርጉት ተከራይነትህን እንዳትረሳ ነው...


___


በመሰረቱ ሁላችንም ተከራይ ነን... ሰውነታችን ኪራይ ቤት ነው፣ ዓለም ኪራይ ቤት ናት፣ ተፈጥሮም እንደዚያው... አንድም ቋሚ ነገር የለም!!... 


በአጭሩ - ትተነው እስከሄድን ድረስ ሁሉም ነገር ኪራይ 'ቤት' ነው... 


[ታዲያ ለምንድነው - የኔ የሚባል ሳይኖርህ 'የኔ' የሚለው 'የሌለውን' የምትገፋው?...]

___


@bridgethoughts
16👌3🔥1🤔1
.
.
.

ውዴ
_

ሞትሽ በልቤ ውስጥ ያለውን መውደድ አልገደለውም፤ 
መለየትሽ ከነፍሴ የታተመውን ፍቅር አልፋቀውም፤ 
_

አብረሽኝ ባትሆኚ አብሮኝ የሚኖረውን አክብሮት የሚነጥቀኝ የለም፤
በስጋ ባናብርም በመንፈስ የምንቆራኝበትን እውነት አልተሰረቅንም፤ 
_

በአካል ባናወራም በቀልባችን የምንግባባበትን አቅም ሜዳ አልጣልኩም፤ 
በድምጽ ባልሰማሽም ከዕዝነ-ልቡናዬ ታትሞ በየመዓልቱ የሚያዜም ቀናነትሽን ዝም አላስባልኩም፤
_

ዕጣሽ ዕጣዬ ሆኖ እስክንመሳሳል የአካል ንጥለትሽን ጉዳት በመንፈስ ተቋልፎሽ ውበት እያደስኩ እኖራለሁ።
_

የኔ ውድ 🌺

____

@bridgethoughts
7🥰2
.
.
.

___

ከፍ ባልን ቁጥር... 'ከስር የሚገፉን አልያም ከላይ የሚስቡን ስላሉ ነው' ብለን አስበን እናውቃለን?

'ከትናንት የተሻለ ዕይታ የኖረን - በተሸካሚዎቻችን ትከሻ ስለተንጠላጠልን እንጂ በራሳችን ጉልበት ስለቆምን አልነበረም' ብለን እናውቃለን?

ከእጅ ያለው - የኖረን፣ የደረስንበት - የተገባን፣ ጉድፍ ይሁን እልፍ -  የከበበን፣ ደቆም ይሁን ልቆ - ያደመቀን... ሌሎች ስለነበሩ ነው ብለንስ እናውቃለን?
__

የእውነት ይህ ጉድለታችን ነው!!...

__

ስንቴ... 

           የተራዱንን እጆች ገፋን?

ስንቴስ...

           ከፍ ያደረጉንን ትከሻዎች ረገጥን?

ምን ያህል ጊዜ...

           ያጎሉንን ሃሳብ ባለቤቶች አደበዘዝን?

ለስንተኛ ጊዜስ...

           ተሻግረን ስናበቃ ያሻገረንን ድልድይ ሰበርን?

___

"Someone is sitting in the shade today because someone planted a tree a long time ago" ~ Warren Buffet

___

@bridgethoughts
👏5❤‍🔥4👌1
.
.
.

"Mankind must put an end to war before war puts an end to mankind." ~ John F. Kennedy

___

የሰው ልጅ የውድቀቱ ጥግ፣ የድንዛዜው ቁንጮ፣ የኋላቀርነቱ መስታወት...


ጦርነት!!!


"I know not with what weapons World War III will be fought, but World War IV will be fought with sticks and stones." ~ Albert Einstein


ሰልጥነን እንደ ሰየጠን፣ ዘምነን እንደ ጎመዘዝን የሚናገርብን እውነት... 

በቁስ ተጊጠን በመንፈስ እንደነጠፍን የሚያሳብቅ ገጽታ....

በሳይንስ ተራቀን በሞራል እንደቀነጨርን መስካሪ ሃቂቃ...


ጦርነት!!...


የሰው ልጅ የትኛውንም ዓይነት አመክንዮ ቢደረድር፣ የትኛውንም ዓይነት ሰበብ ቢያግተለትል ልክ የማይሆንበት ተግባሩ የጦርነት ግብሩ ነው...


ድህነት ጦርነት አይቀሰቅስም - የሌጣ አዕምሮ ግልፍተኝነት ግን ጠብ ጭሮ ሌማት ያራቁታል...


'የድንበር መገፋት' ጦር አያሳብቅም - የብልሃት አልባ ችኩል ግብር ግን የእግር መቆሚያ ይነጥቃል...


የሃሳብ ልዩነት ሳንጃ አያማዝዝም - የአምባገነን ግትር አቋም ግን የቂም እርሾ ይወልዳል...


ኢጎህን መግደል አቅቶህ ሰው መግደል የቀለለህ ዕለት ያኔ አንተ ቀለሃል!... 


እናም - እነሆ ቃል...


ማኔ - ቴቄል - ፋሬስ!!

__

"The greatest victory is that which requires no battle." ~ Sun Tzu 'The Art of War'

__


'የዘመነ' የጦር መሳሪያ መስራትህ ዘመናዊ አያደርግህም - ከንቱነትህን ያሳብቅ እንደሁ እንጂ...



ራስን የማሸነፊያ ብስለት ስለሌለህ ሌሎችን የምታጠቃበት ሰይፍ መሳልህ ጠቢብ አያደርግህም - ጦረኛ እንጂ...



በጠብመንጃህ ነድተህ የፈጠርከውን ጠብ ቢሸሽ ፈሪ አይባልም - ስሜት ከሚነዳው ጋር የማይታገል ብልህ እንጂ...



ፍርሃትህን የምትገራበት መላ ስለሌለህ ሌሎችን በፍርሃት ውስጥ የሚከት ጠብመንጃ ታከማቻለህ...



በራስህ ዓለም የሁልጊዜ ባለስልጣን የመሆን ክህሎት ሲያጥጥህ - ተሰባሪ ወንበር ለማስጠበቅ ለጋ ሕልም ትሰብራለህ...

____

No More War!!

I do not like war—  
I know what it makes us:  
Children lost to the storm,  
Mothers weeping in vain.  

Houses turned to ash,  
Hope a fleeting spark,  
Future crushed to dust,  
Revenge left in the dark.  

Power feeds the flame,  
Lives cut short, unnamed—  
This is my plea, my cry,  
No more war—we don’t deserve to die.  

(Humble words from one who sees,  
A world aching for peace.)

____

@bridgethoughts
👍65🙏2🕊2👏1
ዝንብን ያቆሸሻት ተፈጥሮዋ አይደለም፣ ውሎዋ እንጂ።

____

@bridgethoughts
👍105👌5
ግትርነት የሚያውቁትን መላ ላለመተግበር፣ የማያውቁትን ብልሃት ላለመጠየቅ የሚያዝ አቋም ነው።

____

@bridgethoughts
10👍4👌2
ልብ ያላሉ ልቦች


የትናንቱ አዳም...

ከጥልቅ ሰመመኑ - ከእንቅልፉ ቢነቃ
ስጦታ ጠበቀው - ከነፍሱ ጠበቃ፤

የዕድሜ ልክ እውነቱ - ተከፍላ ካ’ጥንቱ
ከጎኑ አገኛት - ስጋ ደም አምሳሉ፤


                                          
እናም ያኔ...


የታደለች ሔዋን - ዓይን አዋጅ ሳይገላት
ዕድለኛው አዳም - መስፈርት ሳይበዛበት
ያለ አማራጭ ... መጥተው
እርሷ - ለእርስ ... ኖረው
አለፉ ተባዝተው!


                                          
ይብላኝ ለዛሬ አዳም - ይብላኝ ለሔዋኑ
ከዕልፍ እንስቶች መሃል - ለጠፋች መጠኑ
እኒህ ሁሉ ተባዕት - ዓይኖቿን ላልሞሉ


                                          
እርሱ...

ዓይኑ ውበት ሲያሳድድ
ፈራሽ ገላ ማርኮት፣

                                          
እርሷ...

ልቧ ‘ብር...’ ስትል
ንዋይ ቀልቧን ነስቷት፤

 
ይኸው አሉ ዛሬም - የኔ ’ሚሉት አጥተው
ልብን ከልብ ውስጥ - አላሳድር ብለው፡፡

 
____


[ይህች ግጥም ከተጫረች ትንሽ ቆየች፤ ሰሞኑን ብዙ እየተነገረለት ያለውን 'Materialists' የተሰኘ ፊልም ሳይ ድንገት ትዝ ብላኝ ተጋራሁዋችሁ... በዚህ አጋጣሚ ፊልሙን እንድታዩት እመክራችኋለሁ...]

____

@bridgethoughts
8👌4🙏1
.
.
.

ከቅኔ ወርቁን ላዋልድ - የሰሙን ሽፋን ጠርጌ
የዘመን ስልቱን ላወጋ - ከ[አ]ደባባይ ሸሽጌ፤

.

ለእኔዬ እኔው ልናገር - እኔዬን እኔው [ላ]ርቀው
ከወዳጅ አልፎ ሂያጅ ሃሜት - ቢያተርፈኝ ላስጠነቅቀው፤

.


'ካለቃ ምንዝር ግርግር - ከአስመሳይ ሌጣ ፈገግታ
ከተንኮል ከክፋት ግብሩ - ከሰው ልጅ የአፍ ወለምታ

መዳኛ - ላወጋው መላ
ልሰጠው - ጋሻ ከለላ

ላርቀው - ከነገር ጠለል
ላመጥቀው - በጠቢብ ብሂል

እኔዬን - እኔው ላድነው
ከቦታው - ድንገት ብነቅለው

.
.
.

እኔዬን ከኔ አጣሁት - ለኔዬ ማን ይናገረው?

___

@bridgethoughts
3👍2🥰2
.
.
.

ባለፍሽበት መንገድ የረጨሽው ሽቱ ቅንጣቱ አልሳሳም - በሄድሽበት ስሄድ 'ውድህ በዚህ አለች' የሚል ጣፋጭ ጠረን ደርሶ ያጅበኛል...


የፃፍሽልኝ ደብዳቤ ሃሳብ ዛሬም አልደበዘዘም - አጠገቤ እንዳለሽ ሁሉ በፍቅር ቃና ያወጋኛል... 


የሰማናቸው ዜማዎች ለዛ በየማለዳው አዲስ ነው... ከርመው ልክ እንደ ወይን ሁሌም ይጥሙኛል... 


የሳቅሽ ገደል ማሚቶ በሕዋው ላይ እንደታዘለ ንፋስ ነው - በሄድኩበት ሁሉ ሲስረቀረቅ ይሰማኛል...


ዓይኖችሽን የተዋሱ ከዋክብት በየመዳረሻዬ ያበራሉ - በሌለሽበት ጎዳና ምሽቴን ይጋሩኛል...


ያኔ የተቀመጥሽበት ሶፋ ቅድም እንደተውሽው ሁሉ ሙቀቱ ይሰማኛል... 


የግቢያችን ውሻ ስትመጪ እንዳየ ጭራውን ይቆላል...


የማዕድቤቱ ሽታ እንዳበሰልሽ ሁሉ መዓዛው ያውዳል... 


ከመስታወቱ ውስጥ ፊትሽን አያለሁ - ፊቴን ብቻ ማየት ድሮ አቁሜያለሁ...


ለስላሳ ኮቴሽን ዛሬም እሰማለሁ - ድምጹን ተከትዬ ዞር ብዬ አያለሁ...


ሻይ ያልቀዳሁበት ብርጭቆሽ ይሞቃል - በእንፋሎቱ መሃል ከንፈርሽ ይሳላል...


በጉዞዬ መሃል ጥላሽ ይታየኛል - ሳይቀድም ሳይከተል መንገድ ያጋፋኛል...


የምትወጂው መጽሐፍ ከፊቴ ይታየኛል - እያነበብሽው ነው? በዓይኖችሽ ሲገለጥ ድምጹ ይሰማኛል...


ከመተኛሽ በኩል ትራሱ ጎድጉዷል - ዓይኔ ባያይሽም ተኝተሽበታል...


____


እንደ ሰው ኖረሽ ብታልፊም ዳሩ ፍጥረትሽ የመልዓክ ነው - ሳትታይ መድመቅ፣ አለሽ ሲሉ መርቀቅ ተሰጥቶሻልና...

____

ዓይኑ ሌላ አያይም ለሚሉኝ መልሴ አንቺ ነሽ...


ባትኖሪም - አለሽ!!

____

@bridgethoughts
11🥰2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.



ገጣሚ - ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን



አንባቢ - ገጣሚ ነብይ መኮንን



ርዕስ - እንኳን ለዓመት ጉድ አበቃን!

___

@bridgethoughts
🔥63