This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
.
.
.
አንተ አለህ ከጎኔ - ዝናብ የታባቱ
ክንድህ ይከልለኝ - ጥላ ምኑ ብርቱ?
ገላዬ ቢርስም - በደመና ፍ*ራሽ
ምድጃ ነው ልቤ - በፍቅርህ ተለኳሽ።
___
@bridgethoughts
.
.
አንተ አለህ ከጎኔ - ዝናብ የታባቱ
ክንድህ ይከልለኝ - ጥላ ምኑ ብርቱ?
ገላዬ ቢርስም - በደመና ፍ*ራሽ
ምድጃ ነው ልቤ - በፍቅርህ ተለኳሽ።
___
@bridgethoughts
❤9🔥2
.
.
.
የምሰራበት ተቋም "በቀጣይ አገልግሎቶቼን የማቀርበው የፋይዳ መታወቂያ ላላቸው ሰራተኞች ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ መታወቂያ እንድታወጡ" የሚለውን ማሳሰቢያ ሰብሰብ ብለን በተቀመጥን ባልደረቦች የእጅ ስልክ ላይ ላከ...
ስልኮቻችን ጢው፣ ጺው፣ ኳኳ፣ ቡምቡም... እያሉ 'እንደየሃገራቸው' ጮሁ...
ይህ እንደሆነ አንደኛው ባልደረባችን 'ቴክስቱን' አንብቦ ሲጨርስ ለሌላኛው "እከሌ ፋይዳ አለህ?" ሲል ጠየቀው...
Oh my day!!
ሃሳቡ እኮ ገብቶኛል... ግን ደነገጥኩ...
ወደ ራሴ ዞሬ እኔዬን ጠየቅሁት... "እውን ፋይዳ አለህ?" ብዬ...
ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ጥያቄ ለመመለስ ሲያምጥ ያላየሁት እኔታዬ ቁዘማ ሲወርሰው ታዘብኩ...
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አላችሁ?...
በቤታችሁ፣
በሰፈራችሁ፣
በማሕበረሰብ፣
በሃገራችሁ፣
በሕይወታችሁ፣
በመኖራችሁ፣
በስራ ቦታችሁ... ፋይዳ አላችሁ?... እውነት ፋይዳችሁ ምንድነው?...
የመኖር ዘፍጥረት፣ የሕላዌ አሃዱ፣ የመውጣት መግባታችን ውበት ፋይዳ ነው... አበርክቶ... ዋጋ... ክብረት... ከተቀበሉት በላይ መስጠት፣ ማኖር፣ መብራት፣ መምራት፣ ወዝ መቀላቀል፣ መፍጋት፣ ምርኩዝ መሆን...
እንጂማ መኖር ምን ትርጉም አለው? - እየፈየዱ ትርጉም ካልሰጡት...
___
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አለሽሽ?...
___
ሁለቱ የምድራችን ታላላቅ ነፍሶች ስለ ፋይዳ ይህን ብለው ነበር...
"Only a life lived for others is a life worthwhile." ~ Albert Eisenstein
"The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others." ~ Mahatma Gandhi
___
@bridgethoughts
.
.
የምሰራበት ተቋም "በቀጣይ አገልግሎቶቼን የማቀርበው የፋይዳ መታወቂያ ላላቸው ሰራተኞች ብቻ ስለሆነ ከወዲሁ መታወቂያ እንድታወጡ" የሚለውን ማሳሰቢያ ሰብሰብ ብለን በተቀመጥን ባልደረቦች የእጅ ስልክ ላይ ላከ...
ስልኮቻችን ጢው፣ ጺው፣ ኳኳ፣ ቡምቡም... እያሉ 'እንደየሃገራቸው' ጮሁ...
ይህ እንደሆነ አንደኛው ባልደረባችን 'ቴክስቱን' አንብቦ ሲጨርስ ለሌላኛው "እከሌ ፋይዳ አለህ?" ሲል ጠየቀው...
Oh my day!!
ሃሳቡ እኮ ገብቶኛል... ግን ደነገጥኩ...
ወደ ራሴ ዞሬ እኔዬን ጠየቅሁት... "እውን ፋይዳ አለህ?" ብዬ...
ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ጥያቄ ለመመለስ ሲያምጥ ያላየሁት እኔታዬ ቁዘማ ሲወርሰው ታዘብኩ...
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አላችሁ?...
በቤታችሁ፣
በሰፈራችሁ፣
በማሕበረሰብ፣
በሃገራችሁ፣
በሕይወታችሁ፣
በመኖራችሁ፣
በስራ ቦታችሁ... ፋይዳ አላችሁ?... እውነት ፋይዳችሁ ምንድነው?...
የመኖር ዘፍጥረት፣ የሕላዌ አሃዱ፣ የመውጣት መግባታችን ውበት ፋይዳ ነው... አበርክቶ... ዋጋ... ክብረት... ከተቀበሉት በላይ መስጠት፣ ማኖር፣ መብራት፣ መምራት፣ ወዝ መቀላቀል፣ መፍጋት፣ ምርኩዝ መሆን...
እንጂማ መኖር ምን ትርጉም አለው? - እየፈየዱ ትርጉም ካልሰጡት...
___
ፋይዳ አለህ?... ፋይዳ አለሽሽ?...
___
ሁለቱ የምድራችን ታላላቅ ነፍሶች ስለ ፋይዳ ይህን ብለው ነበር...
"Only a life lived for others is a life worthwhile." ~ Albert Eisenstein
"The best way to find yourself is to lose yourself in the service of others." ~ Mahatma Gandhi
___
@bridgethoughts
❤15🥰2
.
.
.
ድሃ ቤት ስታድግ 'ሃብታም' የማያውቃቸውን ብዙ ወጎች ትለምዳለህ...
ለምሳሌ...
እናትህ እራትህ ላይ ጨው በዛ አድርጋ የሰጠችህ ዕለት... ምግቡን ቀመስ ታደርግና...
'እማዬ፣ ጨው እኮ በዝቷል...' ስትላት፤
'አውቄያለሁ ዝም ብለህ ብላ... ውሃ እንዲያስጠጣህ ብዬ ነው' ትልሃለች...
___
የሆነ ቀን ደግሞ መባያው ያንስባታል... እንዲርብህ ግን በጭራሽ አትፈልግም ድስቱን ጠራርጋም ቢሆን ታቀርብልህና...
'በል እያጠቀስክ ብላ፣ መበያና ወንድም ማስፈራሪያ ነው' ትልሃለች...
___
ያው ሁሌ አይሳካም አይደል?... ሌላ ጊዜ ደግሞ ቤቱ ብጣሽ እንጀራ ብርቅ ይሆንበታል... ይሄኔ እናትህ...
'ይህችን ቀምሰህ ውሃ ጠጣበት፣ ሆድ እንዳሳዩት ነው' ብላ ለእራት ሽምብራ ቆሎ ትሰጥሃለች...
___
በዓል ደርሶ፣ ጎረቤት የተሰራው ሥጋ ወጥ ሲያስጎመዥህና ምራቅህን እያስዋጠ ሲያስቸግርህ...
'እማዬ፣ እዚህ ቤት ግን ሥጋ ወጥ የሚበላው መች ነው?' ስትላት...
'ያለለት... አለች የያለለት እናት፤ ያለለት ነዋ ልጄ!' ትልሃለች...
ምናልባት በጥያቄህ ገፍተህ ከተጫንካት ደግሞ፣ 'ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም' ብላ ኮስተር ትልብሃለች...
___
እናት ግን ሳታበላህ የማትበላ፣ 'አፈር ልብላ' ሳትልህ የማትውል፣ የሆዷን ጥያቄ በመቀነት ጨቁና የአንተን ሆድ ብቻ ለመሙላት የምትታትር... መሆኗን ልብ በል!!
___
ደግሞ ወዲህ...
ጥሬ ሽሮ ተበጥብጦ፣ ብትን ጨው በውሃ ሟሙቶ፣ ሚጥሚጣ ተጠቅሶ፣ በርበሬ ድልህ ሆኖ፣ ተልባ በውሃ ርሶ፣ ቃሪያ በጨው ተሰንጎ፣ ጎመን ተለብልቦ (ዘይት የጠፋ'ለት)፣ ሽንኩርት በጨው ተጠቅሶ... ወዘተ
በመበያነት የሚታወቁት ድሃ ቤት ብቻ ነው...
___
ሌላም አለ...
"አይቶ አጣ ቤት ጎመን የተቀቀለ ዕለት ሲጨበጨብ ያድራል"
"ሆድን በጎመን ቢደልሉት፣ ጉልበት በዳገት ይለግማል"
"ለአኩራፊ ምሳው እራቱ ነው"
"ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ"
"በሚያዝያ ጎመን የዘራ፣ ክረምቱን ሁሉ በላ"
"አህያ እንደምትታለብ፣ ከላሞች ፊት ትቅለበለብ"
"የችግር ክፉ እህል ማጣት፣ የኃጢዓት ክፉ ነፍስ ማጥፋት"
"ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ፣ ይላል እርኩም"
.
.
.
ዓይነቶቹን ተረት የምትሰማው ከድሃ ብቻ ነው...
___
Damn!!...
ዛሬም እዚያው ነን...
___
አንድ እውነት ግን አለ...
የድሃ ድህነት የሞራል አይደለም!!... ለማግኘት ብሎ ክብሩን አይጥልም!!!... ሆዱን ሊሞላ ሃገር አይሰርቅም!!!... ረሃብ ሊከላ ቃሉን አይበላም!!!...
___
@bridgethoughts
.
.
ድሃ ቤት ስታድግ 'ሃብታም' የማያውቃቸውን ብዙ ወጎች ትለምዳለህ...
ለምሳሌ...
እናትህ እራትህ ላይ ጨው በዛ አድርጋ የሰጠችህ ዕለት... ምግቡን ቀመስ ታደርግና...
'እማዬ፣ ጨው እኮ በዝቷል...' ስትላት፤
'አውቄያለሁ ዝም ብለህ ብላ... ውሃ እንዲያስጠጣህ ብዬ ነው' ትልሃለች...
___
የሆነ ቀን ደግሞ መባያው ያንስባታል... እንዲርብህ ግን በጭራሽ አትፈልግም ድስቱን ጠራርጋም ቢሆን ታቀርብልህና...
'በል እያጠቀስክ ብላ፣ መበያና ወንድም ማስፈራሪያ ነው' ትልሃለች...
___
ያው ሁሌ አይሳካም አይደል?... ሌላ ጊዜ ደግሞ ቤቱ ብጣሽ እንጀራ ብርቅ ይሆንበታል... ይሄኔ እናትህ...
'ይህችን ቀምሰህ ውሃ ጠጣበት፣ ሆድ እንዳሳዩት ነው' ብላ ለእራት ሽምብራ ቆሎ ትሰጥሃለች...
___
በዓል ደርሶ፣ ጎረቤት የተሰራው ሥጋ ወጥ ሲያስጎመዥህና ምራቅህን እያስዋጠ ሲያስቸግርህ...
'እማዬ፣ እዚህ ቤት ግን ሥጋ ወጥ የሚበላው መች ነው?' ስትላት...
'ያለለት... አለች የያለለት እናት፤ ያለለት ነዋ ልጄ!' ትልሃለች...
ምናልባት በጥያቄህ ገፍተህ ከተጫንካት ደግሞ፣ 'ሰው እንደ ቤቱ እንጂ እንደ ጎረቤቱ አይኖርም' ብላ ኮስተር ትልብሃለች...
___
እናት ግን ሳታበላህ የማትበላ፣ 'አፈር ልብላ' ሳትልህ የማትውል፣ የሆዷን ጥያቄ በመቀነት ጨቁና የአንተን ሆድ ብቻ ለመሙላት የምትታትር... መሆኗን ልብ በል!!
___
ደግሞ ወዲህ...
ጥሬ ሽሮ ተበጥብጦ፣ ብትን ጨው በውሃ ሟሙቶ፣ ሚጥሚጣ ተጠቅሶ፣ በርበሬ ድልህ ሆኖ፣ ተልባ በውሃ ርሶ፣ ቃሪያ በጨው ተሰንጎ፣ ጎመን ተለብልቦ (ዘይት የጠፋ'ለት)፣ ሽንኩርት በጨው ተጠቅሶ... ወዘተ
በመበያነት የሚታወቁት ድሃ ቤት ብቻ ነው...
___
ሌላም አለ...
"አይቶ አጣ ቤት ጎመን የተቀቀለ ዕለት ሲጨበጨብ ያድራል"
"ሆድን በጎመን ቢደልሉት፣ ጉልበት በዳገት ይለግማል"
"ለአኩራፊ ምሳው እራቱ ነው"
"ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ"
"በሚያዝያ ጎመን የዘራ፣ ክረምቱን ሁሉ በላ"
"አህያ እንደምትታለብ፣ ከላሞች ፊት ትቅለበለብ"
"የችግር ክፉ እህል ማጣት፣ የኃጢዓት ክፉ ነፍስ ማጥፋት"
"ያፌን እስክውጥ ዕድሜ ይስጠኝ፣ ይላል እርኩም"
.
.
.
ዓይነቶቹን ተረት የምትሰማው ከድሃ ብቻ ነው...
___
Damn!!...
ዛሬም እዚያው ነን...
___
አንድ እውነት ግን አለ...
የድሃ ድህነት የሞራል አይደለም!!... ለማግኘት ብሎ ክብሩን አይጥልም!!!... ሆዱን ሊሞላ ሃገር አይሰርቅም!!!... ረሃብ ሊከላ ቃሉን አይበላም!!!...
___
@bridgethoughts
❤22👍3🥰3🙏1
.
.
.
ለራስህ እውነተኛ ስሜት ታማኝ ሆነህ ትቆያለህ ወይስ ለሌሎች ስሜት ለመመቸት ስትል ሚዛን ትስታለህ?
ዋጋ የምትሰጣቸው ነገሮች ምንነት አጠቃላይ ነገርህን ይወስኑታል... እሴትህ ወይም 'value' የምታደርጋቸው ነገሮች ስላንተ ያለውን አጠቃላይ እውነት ይናገራሉ...
ለሃቅ ዋጋ ትሰጣለህ - እውነተኛ ትሆናለህ... ሃሰት ካልጎረበጠህ በክህደት ትሰለጥናለህ... ገንዘብ ታመልካለህ - ለሃብት ስትል እስከ መግደል ትደርሳለህ... ባለህ ከተብቃቃህ መካፈል ታውቃለህ...
የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
ብዙዎች 'ለወርቅ' ይሰግዳሉ - ጥቂቶች የጸጥታን ውበት ያመልካሉ... እልፎች እውነትን ለጭብጨባና ርካሽ አድናቆት አሳልፈው ይሰጣሉ - ጥቂቶች የሃቂቃቸውን ላምባ ከፍ አድርገው ይጓዛሉ...
እነዚያ 'እኛን ምሰል' ማለት ያዘወትራሉ - ያልመሰለን ማራቅ፣ ያልመሰለን ማድቀቅ ያውቁበታል...
እነዚህ መሆንን ይኖራሉ - መምሰል የነፍስያን ቀለም የሚያጠፋ ጥላት፣ ውስጠትን የሚበላ ሻህላ እንደሆነ ያውቃሉ...
አዎን... መንጋውን ከሚያብር ፍም ይልቅ በሚያረግድ ንፋስ ፊት የሚቆም የኩራዝ ነበልባል የበለጠ የሞራል ብርታት አለው...
እሴተኝነት እስረኝነት አይደለም - ፍሬ እንጂ... አጥልቀህ ስትቀብረው ተልቆ ብቅ ይላል... ሥጋህ እንኳ ቢያልፍ ለስምህ ዘብነት ደን ሆኖ ይበቅላል... ልጆችህ ይኮሩበታል - መንዝረው ይከብሩበታል...
ይህን ያጣህ'ለት ግን ማንም ትሆናለህ... ከቆምክበት ሞገስ አይኖርህም... ባለፍክበት ክብር አይቆይልህም...
እንጂማ...
ሰው ከእሴቱ ውጭ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
.
.
ለራስህ እውነተኛ ስሜት ታማኝ ሆነህ ትቆያለህ ወይስ ለሌሎች ስሜት ለመመቸት ስትል ሚዛን ትስታለህ?
ዋጋ የምትሰጣቸው ነገሮች ምንነት አጠቃላይ ነገርህን ይወስኑታል... እሴትህ ወይም 'value' የምታደርጋቸው ነገሮች ስላንተ ያለውን አጠቃላይ እውነት ይናገራሉ...
ለሃቅ ዋጋ ትሰጣለህ - እውነተኛ ትሆናለህ... ሃሰት ካልጎረበጠህ በክህደት ትሰለጥናለህ... ገንዘብ ታመልካለህ - ለሃብት ስትል እስከ መግደል ትደርሳለህ... ባለህ ከተብቃቃህ መካፈል ታውቃለህ...
የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
ብዙዎች 'ለወርቅ' ይሰግዳሉ - ጥቂቶች የጸጥታን ውበት ያመልካሉ... እልፎች እውነትን ለጭብጨባና ርካሽ አድናቆት አሳልፈው ይሰጣሉ - ጥቂቶች የሃቂቃቸውን ላምባ ከፍ አድርገው ይጓዛሉ...
እነዚያ 'እኛን ምሰል' ማለት ያዘወትራሉ - ያልመሰለን ማራቅ፣ ያልመሰለን ማድቀቅ ያውቁበታል...
እነዚህ መሆንን ይኖራሉ - መምሰል የነፍስያን ቀለም የሚያጠፋ ጥላት፣ ውስጠትን የሚበላ ሻህላ እንደሆነ ያውቃሉ...
አዎን... መንጋውን ከሚያብር ፍም ይልቅ በሚያረግድ ንፋስ ፊት የሚቆም የኩራዝ ነበልባል የበለጠ የሞራል ብርታት አለው...
እሴተኝነት እስረኝነት አይደለም - ፍሬ እንጂ... አጥልቀህ ስትቀብረው ተልቆ ብቅ ይላል... ሥጋህ እንኳ ቢያልፍ ለስምህ ዘብነት ደን ሆኖ ይበቅላል... ልጆችህ ይኮሩበታል - መንዝረው ይከብሩበታል...
ይህን ያጣህ'ለት ግን ማንም ትሆናለህ... ከቆምክበት ሞገስ አይኖርህም... ባለፍክበት ክብር አይቆይልህም...
እንጂማ...
ሰው ከእሴቱ ውጭ ምንድነው?...
___
@bridgethoughts
🥰6❤4
.
.
.
ትናንት ስለመጣሽበት መንገድ አብዝተሽ ከተጨነቅሽ ዛሬን አልደረስሽም፤ ነገም ያንቺ አይደለም ማለት ነው...
የስብዕናሽ ጥራት የሚለካው ትናንት በፈጸምሻቸው ስህተቶች ሳይሆን ዛሬ ላትደግሚያቸው በምትይዥው አቋም ነው...
የእኔ እህት...
ከየት መምጣትሽ አይደለም ችግሩ ወደየት ለመሄድ መወሰንሽ እንጂ...
ወደኋላ የሚያዩ ዓይኖች ወደፊት የሚጓዙበትን መላ ሲቀምሩ - ተማሩ፤ ይበልጥ የሚቆዝሙበትን ትውስታ ሲጭሩ - ተቸነከሩ ይባላል...
መቸንከር ትፈልጊያለሽ?... [I know አትፈልጊም!!...]
የኔ ውድ!!...
ፊትሽን ከትናንት አዙሪ!... ሁላችንም እዚያ ነበርን... ደስ የሚል መልክ የለውም... ቢያንስ ሲሶ፣ እርቦ፣ ሩብ፣ ግማሽ፣ ምናምን ገጽታው ግርጣት አያጣውም...
የሚገርምሽ - ሊፈርዱብሽ፣ ሊያሸማቅቁሽ፣ ሊያሳንሱሽ የሚፈልጉ ሁሉ እዚያው ነበሩ... ማንም ንጹህ የለም!!...
ዛሬ ግን ውብ ነው!!... ከእጅሽ ያለ ዕንቁ - የምርጫ ጎተራ!!
ዳይ!!... ወደፊት ብቻ!!
____
@bridgethoughts
.
.
ትናንት ስለመጣሽበት መንገድ አብዝተሽ ከተጨነቅሽ ዛሬን አልደረስሽም፤ ነገም ያንቺ አይደለም ማለት ነው...
የስብዕናሽ ጥራት የሚለካው ትናንት በፈጸምሻቸው ስህተቶች ሳይሆን ዛሬ ላትደግሚያቸው በምትይዥው አቋም ነው...
የእኔ እህት...
ከየት መምጣትሽ አይደለም ችግሩ ወደየት ለመሄድ መወሰንሽ እንጂ...
ወደኋላ የሚያዩ ዓይኖች ወደፊት የሚጓዙበትን መላ ሲቀምሩ - ተማሩ፤ ይበልጥ የሚቆዝሙበትን ትውስታ ሲጭሩ - ተቸነከሩ ይባላል...
መቸንከር ትፈልጊያለሽ?... [I know አትፈልጊም!!...]
የኔ ውድ!!...
ፊትሽን ከትናንት አዙሪ!... ሁላችንም እዚያ ነበርን... ደስ የሚል መልክ የለውም... ቢያንስ ሲሶ፣ እርቦ፣ ሩብ፣ ግማሽ፣ ምናምን ገጽታው ግርጣት አያጣውም...
የሚገርምሽ - ሊፈርዱብሽ፣ ሊያሸማቅቁሽ፣ ሊያሳንሱሽ የሚፈልጉ ሁሉ እዚያው ነበሩ... ማንም ንጹህ የለም!!...
ዛሬ ግን ውብ ነው!!... ከእጅሽ ያለ ዕንቁ - የምርጫ ጎተራ!!
ዳይ!!... ወደፊት ብቻ!!
____
@bridgethoughts
🙏6❤5🥰4❤🔥1👍1
ማስተንከሪያ
___
📢 Are we evolving or are we just getting better at masking our madness?
[በጥያቄ ነቃሁ... ጠዋቴ ከማወቅ ጉጉቴ ጋር በራች... እንዲሁ ነኝ... አንዳንድ ቀኔን የሚረከቡ ሃሳቦች ማለዳዬ ላይ ይራወጣሉ... ዛሬም የሆነው እንዲሁ ነበር...]
እናም ጠየቅሁ...
'እውን ሰይጣን ይሉት 'አካል' አለ?... ቀንዳም፣ የጨለማ ገዢ፣ አስፈሪ፣ ጨካኝ entity በሕዋችን ላይ ታቅፏል?... ወይስ ላልተቀበልነው ተፈጥሮአችን፣ ለውድመት፣ ለበደል፣ ለግፊያችን - ማምለጫ፣ ማቋረጫ፣ መሿለኪያ የተቀመጠ የስርየት ፍየል ይሆን?... 🤔🤔🤔
___
ማጮለቂያ... 👀
___
ርዕዮት - ፩
የሐይማኖት መጽሐፍት የሰይጣንን ኑባሬ ይቀበላሉ... ለምሳሌ ክርስትና 'የተጣለው መልዓክ፣ መከራ አማጭ፣ ፈታኝ' ብሎ የሚጠራው ሰይጣንን 'ከመለኮት ትዕዛዝ በተቃርኖ የሚጓዝ አማጺ' አድርጎ ያስቀምጠዋል...
በእስልምና 'ኢብሊስ' ተብሎ የሚጠራው ሰይጣን 'ለአዳም ባለመገዛቱ የተባረረ፣ የኩራትና ያለመታዘዝ ምልክት ነው'...
አይሁዶች በዕብራይስጥ 'ሃ-ሴታን' ወይም ከሳሽ ሲሉ የሚጠሩት ሰይጣን 'በፈጣሪ የፍርድ ችሎት ላይ የሚቀመጥና የሰዎችን ታማኝነት የሚፈታተን ነው' ሲሉ ያስተምራሉ...
ርዕዮት - ፪
ነገሩን ምዕራባዊ መሰረት ካላቸው ሐይማኖቶች አስተምህሮ አውጥተን በአሳቢያን እና ማላዮች መነጽር ብንመለከተው ሰይጣን ከአካላዊ ግዝፈት ይልቅ ምልክታዊ ጉላት ያይልበታል...
ሰይጣን የሰው ልጅ ባሕሪያዊ ጽላሎት (Inner shadow) ትዕምርት ሲሆን ያልተፈተነ ፍርሐት፣ ስግብግብነትና ድብቅ ጭካኔያችን ነጸብራቅ ነው...
ከእውነት፣ ከፍቅር እና ከሕላዌ ነቅዕ (Being) የመለያየት ተምሳሌት፤ እንዲሁም ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ለማምለጥ የምንከለልበት ዓይነ-ርግብ (mask) ነው...
Carl Jung ቆንጆ አድርጎ እንዳስቀመጠው...
🔔 "The devil is the personification of the shadow side of human nature." 🔔
ማላዮችም ስለ ሰይጣን አብዝተው ከመናገር ይልቅ ስለ ንቃትና ተገንዝቦት ማውጋትን የሚመርጡት ለዚህ ነው...
ለምሳሌ ሱፊስቶች - “There is no Satan but the ego unobserved.” በማለት ከነዩንግ እሳቤ ጋር ሲዛመዱ ሌሎች ምስራቃዊ መሰረት ያላቸው አስተምህሮዎችም ከዚህ መሰረት ብዙም ያልራቀ ዕይታን ያስተጋባሉ...
___
📌 የሰይጣንን እሳቤ የወለደው ክህደት፣ ድንዛዜ እና ኃላፊነትን ያለመውሰድ ቅዋሜ ነው... ሁሌም ቢሆን አጥፊነታችንን መቀበል ሲቸግረን ሌላ ተወቃሽ እናሻትታለን... የሁኔታው ሰበብና የቅጣቱ ተቀባይ እኛው ራሳችን ብንሆንም እኛን ተገብቶ እንዲጠየቅልን የምንፈልገው የጦስ ዶሮ መፈለጋችን የተለመደ ነው...
📌 ክፋታችንን ውጫዊ ስናደርግ 'ለምንድነው ይህን ያደረግሁት? የትኛው እኔታዬ ነው ይህ እንዲሆን የፈለገው?' ብለን ከመጠየቅ ይልቅ 'እኔ አላደረግሁትም ወይም ሰይጣን አስቶኝ ነው' የማለትን ቀላል መንገድ እንመርጣለን...
___
@bridgethoughts
___
📢 Are we evolving or are we just getting better at masking our madness?
[በጥያቄ ነቃሁ... ጠዋቴ ከማወቅ ጉጉቴ ጋር በራች... እንዲሁ ነኝ... አንዳንድ ቀኔን የሚረከቡ ሃሳቦች ማለዳዬ ላይ ይራወጣሉ... ዛሬም የሆነው እንዲሁ ነበር...]
እናም ጠየቅሁ...
'እውን ሰይጣን ይሉት 'አካል' አለ?... ቀንዳም፣ የጨለማ ገዢ፣ አስፈሪ፣ ጨካኝ entity በሕዋችን ላይ ታቅፏል?... ወይስ ላልተቀበልነው ተፈጥሮአችን፣ ለውድመት፣ ለበደል፣ ለግፊያችን - ማምለጫ፣ ማቋረጫ፣ መሿለኪያ የተቀመጠ የስርየት ፍየል ይሆን?... 🤔🤔🤔
___
ማጮለቂያ... 👀
___
ርዕዮት - ፩
የሐይማኖት መጽሐፍት የሰይጣንን ኑባሬ ይቀበላሉ... ለምሳሌ ክርስትና 'የተጣለው መልዓክ፣ መከራ አማጭ፣ ፈታኝ' ብሎ የሚጠራው ሰይጣንን 'ከመለኮት ትዕዛዝ በተቃርኖ የሚጓዝ አማጺ' አድርጎ ያስቀምጠዋል...
በእስልምና 'ኢብሊስ' ተብሎ የሚጠራው ሰይጣን 'ለአዳም ባለመገዛቱ የተባረረ፣ የኩራትና ያለመታዘዝ ምልክት ነው'...
አይሁዶች በዕብራይስጥ 'ሃ-ሴታን' ወይም ከሳሽ ሲሉ የሚጠሩት ሰይጣን 'በፈጣሪ የፍርድ ችሎት ላይ የሚቀመጥና የሰዎችን ታማኝነት የሚፈታተን ነው' ሲሉ ያስተምራሉ...
ርዕዮት - ፪
ነገሩን ምዕራባዊ መሰረት ካላቸው ሐይማኖቶች አስተምህሮ አውጥተን በአሳቢያን እና ማላዮች መነጽር ብንመለከተው ሰይጣን ከአካላዊ ግዝፈት ይልቅ ምልክታዊ ጉላት ያይልበታል...
ሰይጣን የሰው ልጅ ባሕሪያዊ ጽላሎት (Inner shadow) ትዕምርት ሲሆን ያልተፈተነ ፍርሐት፣ ስግብግብነትና ድብቅ ጭካኔያችን ነጸብራቅ ነው...
ከእውነት፣ ከፍቅር እና ከሕላዌ ነቅዕ (Being) የመለያየት ተምሳሌት፤ እንዲሁም ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ለማምለጥ የምንከለልበት ዓይነ-ርግብ (mask) ነው...
Carl Jung ቆንጆ አድርጎ እንዳስቀመጠው...
🔔 "The devil is the personification of the shadow side of human nature." 🔔
ማላዮችም ስለ ሰይጣን አብዝተው ከመናገር ይልቅ ስለ ንቃትና ተገንዝቦት ማውጋትን የሚመርጡት ለዚህ ነው...
ለምሳሌ ሱፊስቶች - “There is no Satan but the ego unobserved.” በማለት ከነዩንግ እሳቤ ጋር ሲዛመዱ ሌሎች ምስራቃዊ መሰረት ያላቸው አስተምህሮዎችም ከዚህ መሰረት ብዙም ያልራቀ ዕይታን ያስተጋባሉ...
___
📌 የሰይጣንን እሳቤ የወለደው ክህደት፣ ድንዛዜ እና ኃላፊነትን ያለመውሰድ ቅዋሜ ነው... ሁሌም ቢሆን አጥፊነታችንን መቀበል ሲቸግረን ሌላ ተወቃሽ እናሻትታለን... የሁኔታው ሰበብና የቅጣቱ ተቀባይ እኛው ራሳችን ብንሆንም እኛን ተገብቶ እንዲጠየቅልን የምንፈልገው የጦስ ዶሮ መፈለጋችን የተለመደ ነው...
📌 ክፋታችንን ውጫዊ ስናደርግ 'ለምንድነው ይህን ያደረግሁት? የትኛው እኔታዬ ነው ይህ እንዲሆን የፈለገው?' ብለን ከመጠየቅ ይልቅ 'እኔ አላደረግሁትም ወይም ሰይጣን አስቶኝ ነው' የማለትን ቀላል መንገድ እንመርጣለን...
___
@bridgethoughts
❤4👍2🥰2👏1👌1
[የቀጠለ...]
🤔 ማብሰልሰያ - ፩
ሰይጣን አለ ብለን ብናስብና እንደተነገረን ክፋቱን ብንቀበል፣ maximum ሊያደርግብን የሚችለው ነገር ምንድነው?... ስቃይ ማብዛት?፣ መከራ መቆለል?፣ ለሞት መዳረግ? ወይስ ሌላ?... ታዲያ ሰይጣን የሚያደርገው እኛ እስካሁን ያላደረግነው ምን ነገር አለ?...
መንደሮችን አቃጥለናል... ሕፃናትን በቦምብ ደብድበናል... አፍላጋትን መርዘናል... ድንበር ፈጥረን ተቋስለናል... በረሃብ ሰው ፈጅተናል... ፍቅርን ሸቅጠናል... ሃቂቃን አፍነናል... ጨቅላ ሕፃን ደፍረናል... እርጉዝ ሴት በሳንጃ ዘንጥለናል... ሰውን በቁሙ አቃጥለናል... ስጋውን ቀርጥፈን ከርስ ሞልተናል... ከመሰዊያ ላይ አርደናል... በስልጣናችን ባልገናል... ዘርፈናል፣ ቀጥፈናል፣ ሰስነናል - ይህች ምድር በእኛ ምክንያት ያላየችው ምን ቀሪ መከራ አለ?...
[ለኢጎአችን እስከጠቀመ ድረስ ጆሮ አደንዛዡን፣ ዓይን አፍዛዡን ሁሉ አድርገናል - እስካሁን ካደረግነው የሚበልጥ ምንም ሌላ ነገር ወደፊት አናደርግም... ከኛ በላይ የሚያደርግ ሌላ 'ሰይጣንም' የለም]
🌟 "If Satan is the exile of love, then maybe redemption is not believing in God — but becoming someone who does not create hell for another."
እውነት ሰይጣን ካለ ግን በእርግጠኝነት በዚህ ሰዓት ጡረታ ወጥቷል... አልያም መዝገብ ይዞ ክፋታችንን እየከተበ ነው... ወይም ደግሞ ከከፋው ተግባራችን ልምድ እየቀሰመ ይሆናል...
ያን የ Desert father's wisdom ታስታውሱት የለ?...
በአንድ ገዳም ውስጥ፣ አንድ ወጣኒ መነኩሴ እንቁላል ይሰርቅና ተደብቆ ሲጠብስ ይገኛል...
'ምን እያደረግህ ነው?' ያገኙት አባት ይጠይቁታል...
'አይ አባ... ሰይጣን አስቶኝ...' ወጣቱ ይርበተበታል...
ጉዳዩን ከመስኮት በኩል ሆኖ ሲከታተል የነበረው 'ሰይጣን' ታዲያ እንዲህ ሲል ራሱን ነፃ አወጣ...
'አባ ውሸቱን ነው... ይህችን መላ ያለዛሬም አላየሁዋት'...
___
🌟 ጎበዝ ሰዋዊ ጉዳዮቻችን የሚመሩት በግላጭም በስውርም ነው... እኛ - አስበን፣ ወስነን የምንከውነው ብቻ አይደለንም... ከማለዳ ዕድሜያችን ጀምሮ በልቡሰ-ጥላ (subconscious mind) ሲሞላ የኖረው ፕሮግራምም በድብቅ ይመራናል፤ ይቆጣጠረናል...
እርሱ ማንነታችንን ይገነባል... እርሱ ግንኙነታችንን ይመራል...
እዚያ ቅይጥ መልካችን ይከተባል... እዚያ መሻት መጥላታችን ይቀመራል...
ደግነት ክፋታችን፣ ርህራሔ ተንኮላችን፣ ጨዋነት ወራዳነታችን፣ ንቃት ድንዛዜያችን የመንታ አንድ ሆኖ ይላቆጣል...
___
🤔 ማብሰልሰያ - ፪
ንድፈ ሃሳባዊውን መለኪያ ትተን በተግባር ብንፈተሽ 'ሰይጣን' ከሚባለው 'ትርክት' የሚለየን ምንድነው?...
ለምሳሌ - ሰይጣን 'ፈታኝ ነው' እንላለን... እኛም በአባይ ቃል፣ በአታላይ ጥቅም ሌሎችን በማማለል እንፈትናለን...
ሰይጣን 'ከፋፋይ ነው' እንላለን... እኛም 'ልዩነትን' የጥላቻ ምንጭ፣ 'ማንነትን' የጦር መስበቂያ ሰበብ አድርገን የሰውን ልጅ ስንበልት እንኖራለን...
ሰይጣን 'ሐሰተኛ ነው' እንላለን... ነግቶ እስኪመሽ ቅጥፈት፣ መሽቶ እስኪነጋ እብለት አሽሞንሙነን ወገናችንን እንወጋለን...
🦋 ሰይጣን ለመባል ቀንድ አያስፈልገንም - ከቀንድ በላይ የሚወጋ ምላስ አለን... ገሃነመ እሳት አያስፈልገንም - ከጥይት አረር እስከ ከፋው ኒውክለር ሁሉን ታጥቀናል...
___
አንድ ጥንታዊ የሱፊ ወግ ልንገራችሁ...
አንድ ቀን አንድ ደርቪሽ መምህሩን እንዲህ ሲል ጠየቀ...
"መምህር ሆይ፣ ሰይጣንን ማሸነፍ የምችለው እንዴት ነው?"
መምህሩ መለሱ...
"በቅድሚያ የእርሱን ጫማ መዋስ አቁም"
መምህሩ በጫማ ነጽሮት ውስጥ ውስጠ ቅኝታችንን ነው ያጠየቁት... አሳባቢ፣ ጥሩር ቀጥቃጭ፣ ኃላፊነት ካጂ ውስጠ ማንነታችንን...
ያመሰጠሩት ስለ ዓይነ ትልልቅ፣ ባለ ጨልጨሌ፣ ቀንዳም ሰይጣን ሳይሆን - ልናይ ስላልፈቀድነው ማንነታችን ነው...
___
Meister Eckhart እንዲህ ይላል...
“The devil is simply that which pushes you away from your own center.”
🌟 ማዕከል (center) የሰው ልጅ ለሕላዌው ጣዕም የሚፈጥርበት፣ እንዲሁም በመኖር ወጀብ ከመናወጥ የሚድንበት መልህቁ ነው... ፍቅሩ፣ አገልጋይነቱ፣ እሴቱ፣ የሕይወት ፍቺው... ሻገር ብሎ ደግሞ ከነፍስያው፣ ከምንጩ፣ ከምልዓተ ዓለሙ የሚዋደድበት እትብቱ... ከዚህ ማዕከል የሚገፋውን ነገር ነው ማላዩ ኤካርት 'devil' ሲል የጠራው...
___
መውጫ - መወጣጫ
___
🔔 [ሰይጣን ከአካላዊ ማንነት ይልቅ ከፍቅር የመፋታት ምልክት ቢሆንስ?... ምናልባትም የንቃት ስንጥቃት አልያም ከአማናዊው የማንነታችን ምንጭ የመለያያት ጥልቀት ቢሆንስ?...]
እንደ እውነቱ ከሆነ ክፉ አስፈፃሚ አይደለም ያለው - ፈፃሚው ራሱ እንጂ... በሌላ አነጋገር ወይ እኛ ሰይጣን ነን - አልያም ብቅ እልም የምትል ስይጥንና አለችብን...
___
👉 ጨለማን ሁልጊዜ ሻማ በመለኮስ አንፋታውም... አንዳንዴ ጨለማነቱን መቀበልም ይኖርብናል... በተለይ የውስጣችን ኑባሬ ሲሆን በዓይኖቻችን ልናየው መድፈርም ግድ ይሆናል... ልክ ራሳችንን በመስታወት ፊት እያየን እንደምናወራው ሁሉ - "አንተ - እኔን ነህ... ያልተፈቀርከው፣ ያልተጎበኘኸው፣ ያልተደመጥከው እኔ... አሁን አጠገብህ ነኝ፣ እያየሁህ ነው..." ልንለው ይገባል...
___
@bridgethoughts
🤔 ማብሰልሰያ - ፩
ሰይጣን አለ ብለን ብናስብና እንደተነገረን ክፋቱን ብንቀበል፣ maximum ሊያደርግብን የሚችለው ነገር ምንድነው?... ስቃይ ማብዛት?፣ መከራ መቆለል?፣ ለሞት መዳረግ? ወይስ ሌላ?... ታዲያ ሰይጣን የሚያደርገው እኛ እስካሁን ያላደረግነው ምን ነገር አለ?...
መንደሮችን አቃጥለናል... ሕፃናትን በቦምብ ደብድበናል... አፍላጋትን መርዘናል... ድንበር ፈጥረን ተቋስለናል... በረሃብ ሰው ፈጅተናል... ፍቅርን ሸቅጠናል... ሃቂቃን አፍነናል... ጨቅላ ሕፃን ደፍረናል... እርጉዝ ሴት በሳንጃ ዘንጥለናል... ሰውን በቁሙ አቃጥለናል... ስጋውን ቀርጥፈን ከርስ ሞልተናል... ከመሰዊያ ላይ አርደናል... በስልጣናችን ባልገናል... ዘርፈናል፣ ቀጥፈናል፣ ሰስነናል - ይህች ምድር በእኛ ምክንያት ያላየችው ምን ቀሪ መከራ አለ?...
[ለኢጎአችን እስከጠቀመ ድረስ ጆሮ አደንዛዡን፣ ዓይን አፍዛዡን ሁሉ አድርገናል - እስካሁን ካደረግነው የሚበልጥ ምንም ሌላ ነገር ወደፊት አናደርግም... ከኛ በላይ የሚያደርግ ሌላ 'ሰይጣንም' የለም]
🌟 "If Satan is the exile of love, then maybe redemption is not believing in God — but becoming someone who does not create hell for another."
እውነት ሰይጣን ካለ ግን በእርግጠኝነት በዚህ ሰዓት ጡረታ ወጥቷል... አልያም መዝገብ ይዞ ክፋታችንን እየከተበ ነው... ወይም ደግሞ ከከፋው ተግባራችን ልምድ እየቀሰመ ይሆናል...
ያን የ Desert father's wisdom ታስታውሱት የለ?...
በአንድ ገዳም ውስጥ፣ አንድ ወጣኒ መነኩሴ እንቁላል ይሰርቅና ተደብቆ ሲጠብስ ይገኛል...
'ምን እያደረግህ ነው?' ያገኙት አባት ይጠይቁታል...
'አይ አባ... ሰይጣን አስቶኝ...' ወጣቱ ይርበተበታል...
ጉዳዩን ከመስኮት በኩል ሆኖ ሲከታተል የነበረው 'ሰይጣን' ታዲያ እንዲህ ሲል ራሱን ነፃ አወጣ...
'አባ ውሸቱን ነው... ይህችን መላ ያለዛሬም አላየሁዋት'...
___
🌟 ጎበዝ ሰዋዊ ጉዳዮቻችን የሚመሩት በግላጭም በስውርም ነው... እኛ - አስበን፣ ወስነን የምንከውነው ብቻ አይደለንም... ከማለዳ ዕድሜያችን ጀምሮ በልቡሰ-ጥላ (subconscious mind) ሲሞላ የኖረው ፕሮግራምም በድብቅ ይመራናል፤ ይቆጣጠረናል...
እርሱ ማንነታችንን ይገነባል... እርሱ ግንኙነታችንን ይመራል...
እዚያ ቅይጥ መልካችን ይከተባል... እዚያ መሻት መጥላታችን ይቀመራል...
ደግነት ክፋታችን፣ ርህራሔ ተንኮላችን፣ ጨዋነት ወራዳነታችን፣ ንቃት ድንዛዜያችን የመንታ አንድ ሆኖ ይላቆጣል...
___
🤔 ማብሰልሰያ - ፪
ንድፈ ሃሳባዊውን መለኪያ ትተን በተግባር ብንፈተሽ 'ሰይጣን' ከሚባለው 'ትርክት' የሚለየን ምንድነው?...
ለምሳሌ - ሰይጣን 'ፈታኝ ነው' እንላለን... እኛም በአባይ ቃል፣ በአታላይ ጥቅም ሌሎችን በማማለል እንፈትናለን...
ሰይጣን 'ከፋፋይ ነው' እንላለን... እኛም 'ልዩነትን' የጥላቻ ምንጭ፣ 'ማንነትን' የጦር መስበቂያ ሰበብ አድርገን የሰውን ልጅ ስንበልት እንኖራለን...
ሰይጣን 'ሐሰተኛ ነው' እንላለን... ነግቶ እስኪመሽ ቅጥፈት፣ መሽቶ እስኪነጋ እብለት አሽሞንሙነን ወገናችንን እንወጋለን...
🦋 ሰይጣን ለመባል ቀንድ አያስፈልገንም - ከቀንድ በላይ የሚወጋ ምላስ አለን... ገሃነመ እሳት አያስፈልገንም - ከጥይት አረር እስከ ከፋው ኒውክለር ሁሉን ታጥቀናል...
___
አንድ ጥንታዊ የሱፊ ወግ ልንገራችሁ...
አንድ ቀን አንድ ደርቪሽ መምህሩን እንዲህ ሲል ጠየቀ...
"መምህር ሆይ፣ ሰይጣንን ማሸነፍ የምችለው እንዴት ነው?"
መምህሩ መለሱ...
"በቅድሚያ የእርሱን ጫማ መዋስ አቁም"
መምህሩ በጫማ ነጽሮት ውስጥ ውስጠ ቅኝታችንን ነው ያጠየቁት... አሳባቢ፣ ጥሩር ቀጥቃጭ፣ ኃላፊነት ካጂ ውስጠ ማንነታችንን...
ያመሰጠሩት ስለ ዓይነ ትልልቅ፣ ባለ ጨልጨሌ፣ ቀንዳም ሰይጣን ሳይሆን - ልናይ ስላልፈቀድነው ማንነታችን ነው...
___
Meister Eckhart እንዲህ ይላል...
“The devil is simply that which pushes you away from your own center.”
🌟 ማዕከል (center) የሰው ልጅ ለሕላዌው ጣዕም የሚፈጥርበት፣ እንዲሁም በመኖር ወጀብ ከመናወጥ የሚድንበት መልህቁ ነው... ፍቅሩ፣ አገልጋይነቱ፣ እሴቱ፣ የሕይወት ፍቺው... ሻገር ብሎ ደግሞ ከነፍስያው፣ ከምንጩ፣ ከምልዓተ ዓለሙ የሚዋደድበት እትብቱ... ከዚህ ማዕከል የሚገፋውን ነገር ነው ማላዩ ኤካርት 'devil' ሲል የጠራው...
___
መውጫ - መወጣጫ
___
🔔 [ሰይጣን ከአካላዊ ማንነት ይልቅ ከፍቅር የመፋታት ምልክት ቢሆንስ?... ምናልባትም የንቃት ስንጥቃት አልያም ከአማናዊው የማንነታችን ምንጭ የመለያያት ጥልቀት ቢሆንስ?...]
እንደ እውነቱ ከሆነ ክፉ አስፈፃሚ አይደለም ያለው - ፈፃሚው ራሱ እንጂ... በሌላ አነጋገር ወይ እኛ ሰይጣን ነን - አልያም ብቅ እልም የምትል ስይጥንና አለችብን...
___
👉 ጨለማን ሁልጊዜ ሻማ በመለኮስ አንፋታውም... አንዳንዴ ጨለማነቱን መቀበልም ይኖርብናል... በተለይ የውስጣችን ኑባሬ ሲሆን በዓይኖቻችን ልናየው መድፈርም ግድ ይሆናል... ልክ ራሳችንን በመስታወት ፊት እያየን እንደምናወራው ሁሉ - "አንተ - እኔን ነህ... ያልተፈቀርከው፣ ያልተጎበኘኸው፣ ያልተደመጥከው እኔ... አሁን አጠገብህ ነኝ፣ እያየሁህ ነው..." ልንለው ይገባል...
___
@bridgethoughts
❤14👌3🔥2👍1🙏1
.
.
.
ከሩቅ የሚያይህ ሰው፣ 'በኑሮዬ ጎድሏል' ብሎ የሚያስበውን፣ አልያም 'ከእኔ የተሻለ ነው' ብሎ ያመነበትን ነገር አንተ ዘንድ ስላገኘ ሊቀናብህ ይችላል...
በሩቅ 'ምታውቀው ሰው፣ ከቤቴ የለም ያልከው ኖሮት፣ አልያም ከአንተ ይልቅ በዝቶለት ስላየኸው ትቀናበት ይሆናል...
ደግሞ ሁለታችሁ፣ በሩቅ 'ምታዩት ሰው የለንም ባላችሁት ተከቦ፣ ካላችሁ በላይ ደርቦ የሚኖር ሲመስላችሁ ትቀኑበት ይሆናል...
ከሩቅ የሚያያችሁ፣ የቀናችሁበት ሰው ግን እናንተ ዘንድ ባየው ታኮ ጉድለቱን የሚያስብ ነው... የእርሱ ቤት ለሌሎች ሙላት ሆኖ እንደሚያስቀና ግን አንዳች ግንዛቤ የለውም...
አንተ ዘንድ ያለውን በሙላት ተርጎሞ የእጁን የሚያሳንስ ብዙ ተጓዥ አለ...
[ወርቅ አፈር ሆኖብህ መቸገርህን ያላየ]
የሞላለት ያልከው ብዙ እንከኑን 'ሚያስብ የሩቅ ሰው ደግሞ አለ...
[አልማዙን እንደ አመድ ሲቀበል የኖረ]
እኛ ዘንድ ያለው፣ ሁሌም ሌሎች ዘንድ ካለው አንሶ የሚታየን ነገር የኑረት እንቆቅልሽ ነው... አንዳንድ የሙላትና ጉድለት ዕይታዎቻችን 'ሃብት' እና 'ድህነት' ከምንለው ማሕበረሰባዊ መለኪያዎች ሁሉ ይሻገራሉ...
____
ለምሳሌ...
የምትወደው ሚስት አልያም አፍቃሪ ቤተሰብ ያለው የሚመስልህ አንድ ሰው ላይ ትቀና ይሆናል... ይሁንና ሰውየው የብቻነት ጉጉትና የነፃነት ናፍቆት የሚያባክነው ዓይነት ሆኖ ባንተ አኗኗር እየቀና ሊሆን ይችላል...
በመንፈሳዊ እሴቶች ተጊጠህ ስታበቃ ቁሳዊ ሃብት ባለው ሌላኛ ሰው ትቀና ይሆናል... ምናልባት ግን ባለ ቁሱ አንተ ያለህን የአዕምሮ ሰላም በማጣት ስቃይ ውስጥ እየኖረ ይሆናል...
የአካል ጉድለት ስላለብህ ብቻ በሌላው ጥንካሬና ገጽታ ትቀና ይሆናል... ይሁን እንጂ የምትቀናበት ሰው የሚጋደልበትን ስውር ጦርነት አታውቅም... ምናልባትም ሰውየው በአንተ ጽናትና የስሜት መረጋጋት የሚቀና ሊሆን ይችላል...
እይታ ነው ጎዳይ፣ አተያይ ነው ሞዪ...
___
የሰዎች 'ሙላት' የሚታየን በራሳችን 'ጉድለት' በኩል ነው... ሆኖም 'ጉድለት' የአንድ ነገር አለመኖር አይደለም... ሙላት የሚከሰትበት ስፍራ መኖሩን ማሳያ እንጂ...
የጉድለት ስሜት የንጽጽር ህመም ውጤት ነው... አንድ ጊዜ ማነፃፀር ከጀመርክ ሙላትህን ለማሰብ ዕድል አትሰጥም... ይልቁን የሌለህን ከማሰብ ስለምትጀምር ያለህን ለማየት ጊዜ ታጣለህ... ማነፃፀር የማመስገን ተነሳሽነትህን የሚሰልብ ክፉ ባላንጣ ነው...
አስታውስ -
🔔 ሙላትና ጉድለት ሁልጊዜም ተለዋዋጭ ናቸው፤
🔔 የሰዎችን ከመጋረጃ ጀርባ ያለ ትግል ሳታይ ራስህን ከእነርሱ ጋር አታነፃጽር፤
🔔 በዓይን ለማይታየው ሃብትህ ዕውቅና ከመስጠት ጀምር... [አዕምሮህ ሰላም አለው፣ የሰው ፍቅር አለህ፣ ጤነኛ ነህ፣ እጅህ ላይ የበደል ደም የለም፣ አትሰርቅም፣ አትገፋም፣ ዓላማ አለህ...]
___
በዚህ ርዕሰ ላይ Mystics የሚያስተምሩትን ጠቅልለህ ልትረዳ ብትሞክር የምታጠለው እውነት እንዲህ የሚል ነው...
"The cup is full when you recognize its emptiness. And it is empty when you ignore its fullness."
___
በነገራችን ላይ...
🐔 በሕይወትህ የት ስፍራ ነው ጉድለት የሚያቃጭልብህ?
🐔 ሌሎች አንተ ላይ የሚያደንቁት ምናልባት ትኩረት የነፈግኸው ነገርስ የለህም?...
🐔 የሌላኛውን ሰው አኗኗር ያንተን ልምምድ ለመመዘን እየተገለገልክ ይሆን?...
___
ሁላችንም የጉድለትና ሙላት ኮሮጆ ተሸክመን የምንዞር ምንዱባን ነን... ባጣነው ነገር ላይ ስናተኩር ጉድለት ያዛጋብናል... ባለን ስንደሰት ሙላት በምስጋና ይሞላናል...
___
ደቀመዝሙሩ የሱፊውን መምህር ይጠይቃል... "ለምንድነው ሌሎች ሁሉ ነገር ሲኖራቸው እኔ ብቻ ባዶነት የሚሰማኝ?"
መምህሩ አልተገረሙም... ሆኖም ጥያቄውን ከመመለሳቸው በፊት አንድ የሸክላ ማሰሮ ሰጡትና "ከወንዝ ውሃ ሞልተህ አምጣልኝ" አሉት...
ደቀመዝሙሩ እንደታዘዘው አደረገ...
ውሃ የሞላውን ማሰሮ ይዞ ከፊታቸው እንደቆመ መምህሩ ቀስ አድርገው ማሰሮውን ከስሩ ስለበሱት ውሃ መንጠባጠብ ጀመረ...
"አሁንስ ሙሉ ነው ጎደሎ?" ጠየቁት...
"ሙሉ ነው፣ ግን ደግሞ እያንጠባጠበ ነው"...
መምህሩ ፈገግ ብለው...
" እኛም እንዲሁ ነን... የሆነ ቦታ ሙላት ይሰማናል፤ በሌላ ገጽታ ደግሞ ስንጥቃት አለን - በዚያ በኩልም ጉድለት እናያለን... ሰዎችን በሙላታቸው በኩል አትመዝን፤ በየትኛው በኩል ሽንቁር እንዳላቸው አታውቅምና... በስንጥቃትህ አትሳቀቅ፣ የት ላይ መስራት እንዳለብህ አስታዋሽህ ነውና" ሲሉ መለሱለት...
___
ከጉድለትህ ጋር ግብግብ በፈጠርክበት ጊዜ ሳይቀር የሆነ አንድ ሰው የሙላት ተምሳሌት ልትሆን እንደምትችል አስብ... የሆነ ዓይነት ውበት፣ የሃሳብ ጥራት፣ ጥንካሬ እና ሰላም በጸጥታህ ውስጥ እንደተሸጎጠ ተመልከት...
ልብ በል...
ከምታስበው በላይ የተሟላህ፣ ከምታውቀው በላይ ክፍት ነህ... መንታ!! የምታተኩርበት ቦታ ዕይታህን ይወስነዋል...
___
@bridgethoughts
.
.
ከሩቅ የሚያይህ ሰው፣ 'በኑሮዬ ጎድሏል' ብሎ የሚያስበውን፣ አልያም 'ከእኔ የተሻለ ነው' ብሎ ያመነበትን ነገር አንተ ዘንድ ስላገኘ ሊቀናብህ ይችላል...
በሩቅ 'ምታውቀው ሰው፣ ከቤቴ የለም ያልከው ኖሮት፣ አልያም ከአንተ ይልቅ በዝቶለት ስላየኸው ትቀናበት ይሆናል...
ደግሞ ሁለታችሁ፣ በሩቅ 'ምታዩት ሰው የለንም ባላችሁት ተከቦ፣ ካላችሁ በላይ ደርቦ የሚኖር ሲመስላችሁ ትቀኑበት ይሆናል...
ከሩቅ የሚያያችሁ፣ የቀናችሁበት ሰው ግን እናንተ ዘንድ ባየው ታኮ ጉድለቱን የሚያስብ ነው... የእርሱ ቤት ለሌሎች ሙላት ሆኖ እንደሚያስቀና ግን አንዳች ግንዛቤ የለውም...
አንተ ዘንድ ያለውን በሙላት ተርጎሞ የእጁን የሚያሳንስ ብዙ ተጓዥ አለ...
[ወርቅ አፈር ሆኖብህ መቸገርህን ያላየ]
የሞላለት ያልከው ብዙ እንከኑን 'ሚያስብ የሩቅ ሰው ደግሞ አለ...
[አልማዙን እንደ አመድ ሲቀበል የኖረ]
እኛ ዘንድ ያለው፣ ሁሌም ሌሎች ዘንድ ካለው አንሶ የሚታየን ነገር የኑረት እንቆቅልሽ ነው... አንዳንድ የሙላትና ጉድለት ዕይታዎቻችን 'ሃብት' እና 'ድህነት' ከምንለው ማሕበረሰባዊ መለኪያዎች ሁሉ ይሻገራሉ...
____
ለምሳሌ...
የምትወደው ሚስት አልያም አፍቃሪ ቤተሰብ ያለው የሚመስልህ አንድ ሰው ላይ ትቀና ይሆናል... ይሁንና ሰውየው የብቻነት ጉጉትና የነፃነት ናፍቆት የሚያባክነው ዓይነት ሆኖ ባንተ አኗኗር እየቀና ሊሆን ይችላል...
በመንፈሳዊ እሴቶች ተጊጠህ ስታበቃ ቁሳዊ ሃብት ባለው ሌላኛ ሰው ትቀና ይሆናል... ምናልባት ግን ባለ ቁሱ አንተ ያለህን የአዕምሮ ሰላም በማጣት ስቃይ ውስጥ እየኖረ ይሆናል...
የአካል ጉድለት ስላለብህ ብቻ በሌላው ጥንካሬና ገጽታ ትቀና ይሆናል... ይሁን እንጂ የምትቀናበት ሰው የሚጋደልበትን ስውር ጦርነት አታውቅም... ምናልባትም ሰውየው በአንተ ጽናትና የስሜት መረጋጋት የሚቀና ሊሆን ይችላል...
እይታ ነው ጎዳይ፣ አተያይ ነው ሞዪ...
___
የሰዎች 'ሙላት' የሚታየን በራሳችን 'ጉድለት' በኩል ነው... ሆኖም 'ጉድለት' የአንድ ነገር አለመኖር አይደለም... ሙላት የሚከሰትበት ስፍራ መኖሩን ማሳያ እንጂ...
የጉድለት ስሜት የንጽጽር ህመም ውጤት ነው... አንድ ጊዜ ማነፃፀር ከጀመርክ ሙላትህን ለማሰብ ዕድል አትሰጥም... ይልቁን የሌለህን ከማሰብ ስለምትጀምር ያለህን ለማየት ጊዜ ታጣለህ... ማነፃፀር የማመስገን ተነሳሽነትህን የሚሰልብ ክፉ ባላንጣ ነው...
አስታውስ -
🔔 ሙላትና ጉድለት ሁልጊዜም ተለዋዋጭ ናቸው፤
🔔 የሰዎችን ከመጋረጃ ጀርባ ያለ ትግል ሳታይ ራስህን ከእነርሱ ጋር አታነፃጽር፤
🔔 በዓይን ለማይታየው ሃብትህ ዕውቅና ከመስጠት ጀምር... [አዕምሮህ ሰላም አለው፣ የሰው ፍቅር አለህ፣ ጤነኛ ነህ፣ እጅህ ላይ የበደል ደም የለም፣ አትሰርቅም፣ አትገፋም፣ ዓላማ አለህ...]
___
በዚህ ርዕሰ ላይ Mystics የሚያስተምሩትን ጠቅልለህ ልትረዳ ብትሞክር የምታጠለው እውነት እንዲህ የሚል ነው...
"The cup is full when you recognize its emptiness. And it is empty when you ignore its fullness."
___
በነገራችን ላይ...
🐔 በሕይወትህ የት ስፍራ ነው ጉድለት የሚያቃጭልብህ?
🐔 ሌሎች አንተ ላይ የሚያደንቁት ምናልባት ትኩረት የነፈግኸው ነገርስ የለህም?...
🐔 የሌላኛውን ሰው አኗኗር ያንተን ልምምድ ለመመዘን እየተገለገልክ ይሆን?...
___
ሁላችንም የጉድለትና ሙላት ኮሮጆ ተሸክመን የምንዞር ምንዱባን ነን... ባጣነው ነገር ላይ ስናተኩር ጉድለት ያዛጋብናል... ባለን ስንደሰት ሙላት በምስጋና ይሞላናል...
___
ደቀመዝሙሩ የሱፊውን መምህር ይጠይቃል... "ለምንድነው ሌሎች ሁሉ ነገር ሲኖራቸው እኔ ብቻ ባዶነት የሚሰማኝ?"
መምህሩ አልተገረሙም... ሆኖም ጥያቄውን ከመመለሳቸው በፊት አንድ የሸክላ ማሰሮ ሰጡትና "ከወንዝ ውሃ ሞልተህ አምጣልኝ" አሉት...
ደቀመዝሙሩ እንደታዘዘው አደረገ...
ውሃ የሞላውን ማሰሮ ይዞ ከፊታቸው እንደቆመ መምህሩ ቀስ አድርገው ማሰሮውን ከስሩ ስለበሱት ውሃ መንጠባጠብ ጀመረ...
"አሁንስ ሙሉ ነው ጎደሎ?" ጠየቁት...
"ሙሉ ነው፣ ግን ደግሞ እያንጠባጠበ ነው"...
መምህሩ ፈገግ ብለው...
" እኛም እንዲሁ ነን... የሆነ ቦታ ሙላት ይሰማናል፤ በሌላ ገጽታ ደግሞ ስንጥቃት አለን - በዚያ በኩልም ጉድለት እናያለን... ሰዎችን በሙላታቸው በኩል አትመዝን፤ በየትኛው በኩል ሽንቁር እንዳላቸው አታውቅምና... በስንጥቃትህ አትሳቀቅ፣ የት ላይ መስራት እንዳለብህ አስታዋሽህ ነውና" ሲሉ መለሱለት...
___
ከጉድለትህ ጋር ግብግብ በፈጠርክበት ጊዜ ሳይቀር የሆነ አንድ ሰው የሙላት ተምሳሌት ልትሆን እንደምትችል አስብ... የሆነ ዓይነት ውበት፣ የሃሳብ ጥራት፣ ጥንካሬ እና ሰላም በጸጥታህ ውስጥ እንደተሸጎጠ ተመልከት...
ልብ በል...
ከምታስበው በላይ የተሟላህ፣ ከምታውቀው በላይ ክፍት ነህ... መንታ!! የምታተኩርበት ቦታ ዕይታህን ይወስነዋል...
___
@bridgethoughts
❤23🙏3🥰1
.
.
.
... የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
___
@bridgethoughts
.
.
... የሰው ልጅ 'ሰውነት' የተለየው በጥላው ቅርጽ አይደለም... በሚጠራበት ስም፣ በተሸከመው ስመ-ማሕተም፣ በሰበሰበው ሃብት እና ምድራዊ ቁሳቁስ አይደለም... በልቡ መሰዊያ ላይ በሚያቀርባት የዕጣን ሽቱ፣ ዓይን ባላየው ጊዜ በሚንበረከክላት እውነቱ፣ ሁሉ ባወገዘው ጊዜ በሚቆምላት እምነቱ እንጂ...
___
@bridgethoughts
❤23🥰1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
A Beautiful Mind (2001)
Directed by Ron Howard, starring Russell Crowe as John Nash, with Jennifer Connelly in a supporting role.
_
The film is based on the life of the Nobel Prize-winning mathematician John Nash and explores his struggles with schizophrenia and his remarkable contributions to mathematics.
___
@bridgethoughts
Directed by Ron Howard, starring Russell Crowe as John Nash, with Jennifer Connelly in a supporting role.
_
The film is based on the life of the Nobel Prize-winning mathematician John Nash and explores his struggles with schizophrenia and his remarkable contributions to mathematics.
___
@bridgethoughts
🔥5🥰2❤1
.
.
.
'የኔ ሁኚ' የማልልሽ የኔ በመሆን የምታጭው [የሚመስለኝን] ሁሉ ስለማስብ ነው... አብሮነትን የማልጠይቅሽ ማግስት የሚነጥቅሽ [የሚመስለኝን] ሁሉ እያብሰለሰልኩ ነው...
(የሚመስለኝ ያልኩሽ - በእኔ ልብ ውስጥ ያለውን እምነት እንጂ አንቺ ዘንድ ያለውን ጥንካሬ ስለማላውቅ ነው...)
ከልቤ እልፍኝ ያልጋበዝኩሽ ስለማልፈቅድሽ አይደለም... መንገዴን ያላጋራሁሽ ስለማልወድሽ አይደለም... ይልቁን ስለምጠነቀቅልሽ ነው... [የኔ በመሆን የምትከፍይው ዋጋ እንዳይኖር በመስጋት... ወይም በጥሬ ቃል 'ደስታዋን ስለ አብሮነታችን ሰውታ ብታዝንብኝስ?' ብዬ በመፍራት...]
[እንግዳ ነገር ይመስላል አይደል?... 'የነገን እግዜር ያውቃል' በሚል ተስፈኛ ሕዝብ መሐል በቅሎ 'ነገ ብትከፋብኝስ?' ብሎ ማሰብ ይገርማል አይደል?...]
____
[የነግ ፍርሃት እያጠየመብኝ እንጂ እኮ...]
ልብሽ ለኔ ያላትን ቦታ እረዳለሁ - [ልብሽን እንዳልሰብራት ደግሞ እፈራለሁ...]
ስታገኚኝ የፊትሽ ጸዳል ለልቤ እንዲያበራ አውቃለሁ - [የኔ አድርጌሽ ሳቅሽን እንዳልነጥቅሽ እያልኩ ግን እፈራለሁ...]
ጨዋታሽ ደዌ ሲፈውስ፣ ቃላትሽ ለነፍስ ሲደርስ፣ ፈገግታሽ መንፈስ ሲያድስ አውቃለሁ - [አብሮነታችን ስሜትሽን እንዳያጎሸው ግን ሁሌም እሰጋለሁ...]
[ግን ደግሞ ሰው አይደለሁ?...]
ዛሬ የገባኝ ሁሉ ከነፃነትሽ ላለመወለዱ፣ ዛሬ የወደድኩት ሁሉ ነገም ለመራመዱ እርግጠኝነት እንዲከበኝ እሻለሁ...
[እናም በልቤ እጠይቅሻለሁ...]
የመጣሁበት መንገድ አያዝልሽም?... የምደርስበት ነገ አያስከፋሽም?... እርጅናዬ ውስጥ ልትኖሪ ትሺያለሽ?... በጉዞዬ ልታብሪኝ በቂ አቅም አለሽ?... [ይኸውልሽ ማሬ፣ ፊቴ ላይ የማታነቢው ምሬት ከውስጤ ሊኖር ይችላል...]
ውድቀቴ ተስፋ አያስቆርጥሽም?... ድህነቴ አያስፈራሽም?... ቀርነቴስ አያሳቅቅሽም?... [ከዘመነኞችሽ ጋር ያለኝን መልከ ብዙ ልዩነትና ርቀት አውቀዋለሁ...]
ፍቅሬ ይበቃሻል?... ቤቴስ ይስብሻል?...
ህመሜን አትጠየፊውም?... ድካሜንስ አትሰቀቂውም?...
[ይሄ ሁሉ ይቅር...]
ስለ ውሳኔሽ አትጸጸቺም???...
___
ጣፋጯ...
ለነዚህ ጥያቄዎች የአዎንታ ልብ ከሌለሽ 'ና' አትበይኝ... እኔም 'ምጪልኝ' ብዬ አላስጨንቅሽም...
የወደድኩሽ የማትፈልጊውን እንድትኖሪ ከመጨከን ጋር ስላልሆነ ምርጫሽን አከብራለሁ... ግን አትርሺ - ስላላበርን ፍቅሬ ፈጽሞ አይቀየርም...
___
ይህን ግን ለምን ፃፍኩልሽ?...
ራስ ወዳድ እንዳልሆንኩ እንድታውቂ ይሆናል... [ምናልባት ደግሞ ነፃነትሽን ላስታውስሽ ብዬም ይሆናል...]
[አየሽ... ሰው በገዛ ልቡ ውስጥ ስላለች የፍቅር ኩራዝ እንጂ በሌላኛው ሰው ልብ ውስጥ ስለተዘጋጀለት እቶን መውደድ በቀላሉ እርግጠኝነት አይሰማውም... በመኖር ካልፈተነው በቀር...]
ሁሌም ግን እወድሻለሁ 💞
___
@bridgethoughts
.
.
'የኔ ሁኚ' የማልልሽ የኔ በመሆን የምታጭው [የሚመስለኝን] ሁሉ ስለማስብ ነው... አብሮነትን የማልጠይቅሽ ማግስት የሚነጥቅሽ [የሚመስለኝን] ሁሉ እያብሰለሰልኩ ነው...
(የሚመስለኝ ያልኩሽ - በእኔ ልብ ውስጥ ያለውን እምነት እንጂ አንቺ ዘንድ ያለውን ጥንካሬ ስለማላውቅ ነው...)
ከልቤ እልፍኝ ያልጋበዝኩሽ ስለማልፈቅድሽ አይደለም... መንገዴን ያላጋራሁሽ ስለማልወድሽ አይደለም... ይልቁን ስለምጠነቀቅልሽ ነው... [የኔ በመሆን የምትከፍይው ዋጋ እንዳይኖር በመስጋት... ወይም በጥሬ ቃል 'ደስታዋን ስለ አብሮነታችን ሰውታ ብታዝንብኝስ?' ብዬ በመፍራት...]
[እንግዳ ነገር ይመስላል አይደል?... 'የነገን እግዜር ያውቃል' በሚል ተስፈኛ ሕዝብ መሐል በቅሎ 'ነገ ብትከፋብኝስ?' ብሎ ማሰብ ይገርማል አይደል?...]
____
[የነግ ፍርሃት እያጠየመብኝ እንጂ እኮ...]
ልብሽ ለኔ ያላትን ቦታ እረዳለሁ - [ልብሽን እንዳልሰብራት ደግሞ እፈራለሁ...]
ስታገኚኝ የፊትሽ ጸዳል ለልቤ እንዲያበራ አውቃለሁ - [የኔ አድርጌሽ ሳቅሽን እንዳልነጥቅሽ እያልኩ ግን እፈራለሁ...]
ጨዋታሽ ደዌ ሲፈውስ፣ ቃላትሽ ለነፍስ ሲደርስ፣ ፈገግታሽ መንፈስ ሲያድስ አውቃለሁ - [አብሮነታችን ስሜትሽን እንዳያጎሸው ግን ሁሌም እሰጋለሁ...]
[ግን ደግሞ ሰው አይደለሁ?...]
ዛሬ የገባኝ ሁሉ ከነፃነትሽ ላለመወለዱ፣ ዛሬ የወደድኩት ሁሉ ነገም ለመራመዱ እርግጠኝነት እንዲከበኝ እሻለሁ...
[እናም በልቤ እጠይቅሻለሁ...]
የመጣሁበት መንገድ አያዝልሽም?... የምደርስበት ነገ አያስከፋሽም?... እርጅናዬ ውስጥ ልትኖሪ ትሺያለሽ?... በጉዞዬ ልታብሪኝ በቂ አቅም አለሽ?... [ይኸውልሽ ማሬ፣ ፊቴ ላይ የማታነቢው ምሬት ከውስጤ ሊኖር ይችላል...]
ውድቀቴ ተስፋ አያስቆርጥሽም?... ድህነቴ አያስፈራሽም?... ቀርነቴስ አያሳቅቅሽም?... [ከዘመነኞችሽ ጋር ያለኝን መልከ ብዙ ልዩነትና ርቀት አውቀዋለሁ...]
ፍቅሬ ይበቃሻል?... ቤቴስ ይስብሻል?...
ህመሜን አትጠየፊውም?... ድካሜንስ አትሰቀቂውም?...
[ይሄ ሁሉ ይቅር...]
ስለ ውሳኔሽ አትጸጸቺም???...
___
ጣፋጯ...
ለነዚህ ጥያቄዎች የአዎንታ ልብ ከሌለሽ 'ና' አትበይኝ... እኔም 'ምጪልኝ' ብዬ አላስጨንቅሽም...
የወደድኩሽ የማትፈልጊውን እንድትኖሪ ከመጨከን ጋር ስላልሆነ ምርጫሽን አከብራለሁ... ግን አትርሺ - ስላላበርን ፍቅሬ ፈጽሞ አይቀየርም...
___
ይህን ግን ለምን ፃፍኩልሽ?...
ራስ ወዳድ እንዳልሆንኩ እንድታውቂ ይሆናል... [ምናልባት ደግሞ ነፃነትሽን ላስታውስሽ ብዬም ይሆናል...]
[አየሽ... ሰው በገዛ ልቡ ውስጥ ስላለች የፍቅር ኩራዝ እንጂ በሌላኛው ሰው ልብ ውስጥ ስለተዘጋጀለት እቶን መውደድ በቀላሉ እርግጠኝነት አይሰማውም... በመኖር ካልፈተነው በቀር...]
ሁሌም ግን እወድሻለሁ 💞
___
@bridgethoughts
❤26🥰4
.
.
.
ከምከፍተው ሙዚቃ ይልቅ፣ እንዳልረብሽ የማደርገው ጥንቃቄ ከፍ ብሎ ይሰማል... ይገርማል!!
ከምጠቀመው ውሃ በላይ፣ ላለማባከን የማደርገው ጥረት ትኩረት ስቦ ያስከፋል... ምን ይባላል??
ከማበራት አምፑል በላይ፣ የመቆጠብ ልምዴ ጠያቂ ይጎትታል... ያሳቅቃል!!
ገላ ለመታጠብ 'ሻወር ቤት' ብመርጥም፣ ድንገት የገባሁ'ለት - አንኳኪ አላጣም...
በወር የምከፍለው ቁጥሩ ባይናቅም፣ 'የጨምር' ዕድገቱ አንዴም ቆሞ አያቅም...
አታምሽ ያሉኝ ፈሪ በጊዜ ብሰፍርም፣ ቤት መዋል ሲያምረኝ ግን ገላማጭ አላጣም...
.
.
.
ምክንያቱም...
👇
ያለሁት ኪራይ ቤት ነው!!
___
የአንዳንድ አከራዮች የመጀመሪያ ተግባር እንደ ሰው የሚገባህን ክብር መንጠቅ ነው... ይህንንም የሚያደርጉት ተከራይነትህን እንዳትረሳ ነው...
___
በመሰረቱ ሁላችንም ተከራይ ነን... ሰውነታችን ኪራይ ቤት ነው፣ ዓለም ኪራይ ቤት ናት፣ ተፈጥሮም እንደዚያው... አንድም ቋሚ ነገር የለም!!...
በአጭሩ - ትተነው እስከሄድን ድረስ ሁሉም ነገር ኪራይ 'ቤት' ነው...
[ታዲያ ለምንድነው - የኔ የሚባል ሳይኖርህ 'የኔ' የሚለው 'የሌለውን' የምትገፋው?...]
___
@bridgethoughts
.
.
ከምከፍተው ሙዚቃ ይልቅ፣ እንዳልረብሽ የማደርገው ጥንቃቄ ከፍ ብሎ ይሰማል... ይገርማል!!
ከምጠቀመው ውሃ በላይ፣ ላለማባከን የማደርገው ጥረት ትኩረት ስቦ ያስከፋል... ምን ይባላል??
ከማበራት አምፑል በላይ፣ የመቆጠብ ልምዴ ጠያቂ ይጎትታል... ያሳቅቃል!!
ገላ ለመታጠብ 'ሻወር ቤት' ብመርጥም፣ ድንገት የገባሁ'ለት - አንኳኪ አላጣም...
በወር የምከፍለው ቁጥሩ ባይናቅም፣ 'የጨምር' ዕድገቱ አንዴም ቆሞ አያቅም...
አታምሽ ያሉኝ ፈሪ በጊዜ ብሰፍርም፣ ቤት መዋል ሲያምረኝ ግን ገላማጭ አላጣም...
.
.
.
ምክንያቱም...
👇
ያለሁት ኪራይ ቤት ነው!!
___
የአንዳንድ አከራዮች የመጀመሪያ ተግባር እንደ ሰው የሚገባህን ክብር መንጠቅ ነው... ይህንንም የሚያደርጉት ተከራይነትህን እንዳትረሳ ነው...
___
በመሰረቱ ሁላችንም ተከራይ ነን... ሰውነታችን ኪራይ ቤት ነው፣ ዓለም ኪራይ ቤት ናት፣ ተፈጥሮም እንደዚያው... አንድም ቋሚ ነገር የለም!!...
በአጭሩ - ትተነው እስከሄድን ድረስ ሁሉም ነገር ኪራይ 'ቤት' ነው...
[ታዲያ ለምንድነው - የኔ የሚባል ሳይኖርህ 'የኔ' የሚለው 'የሌለውን' የምትገፋው?...]
___
@bridgethoughts
❤16👌3🔥1🤔1